1 199مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+77 روز
+2530 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
መልካም ዜና!
በትንቢተ ኤርሚያስ ክላስተር ትምህርት ቤቶች መካከል በተደረገው የፈጠራ ስራዎች ውደድር አካዳሚያችን ፓሽን #1ኛ በመሆን አጠናቅቋል!!!
እንኳን ደስ አለን!!!
🏆🏆🏆🏆🏆
👏 5
ለመላው የፓሽን አካዳሚ ሙስሊም ወንድምና እህቶቻችን እንኳን አደረሳችሁ ዒድ ሙባረክ።
❤ 18👍 6🔥 2
የተማሪዎች ጥናታዊ ጽሁፎች በፓሽን አካዳሚ ቀረቡ!!
ዛሬ መጋቢት 20/2016 በየማነ ብርሃን ክላስተር ማዕከል ስር የሚገኘዉ የፓሽን አካዳሚ 2ኛደ/ት/ቤት ተማሪዎች የተመረጡ የጥናትና ምርምር ፅሁፋቸዉን አቀረቡ።
የት/ቤቱ ርዕሰ-መምህር አቶ ያሬድ መኮንን በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ እንደተናገሩት በ2ኛ ደረጃ ርከን የሚማሩ ተማሪዎች በፕሮጀክት የማስተማር ዘዴ መማር የሚገባቸው መሆኑን አስታውሰው ፓሽን አካዳሚ ከሚገለጽባቸው ስኬታማ ተሞክሮዎች አንዱ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ባለፉት 2 ሩብ ዓመታት በተለያዩ የትምህርት መስኮች በአካዳሚው ከተሰሩ በርካታ የተማሪዎች ጥናታዊ ጽሁፎች መካከል የተመረጡ 5 ስራዎች የሚቀርቡበትና ውይይት የሚካሄድበት መድረክ መመቻቸቱን አስታውቀው ይህም ተማሪዎች በዩኒቨርሲቲ ለሚጠብቃቸው የጥናትና ምርምር ስራ የማዘጋጀት አንዱ ተግባር መሆኑን በመጥቀስ ተማሪዎች በአጥጋቢ ሁኔታ ጽሁፋቸውን እንደሚያብራሩና ለሚቀርቡላቸው ጥያቄዎች አጥጋቢ ምላሽ በመስጠት እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
በመድረኩ ላይ ከ10ኛ ክፍል 3 ተማሪዎች ፣ ከ11ኛ ክፍል 2 ተማሪዎች በአማርኛ፣ በጂኦግራፊ፣ በፊዚክስና በኢኮኖሚክስ ትምህርቶቻቸው በተሰጧቸው ርዕሶች ላይ ያዘጋጇቸውን ጽሁፎች ለታዳሚ አቅርበዋል፡፡
በፕሮግራሙ ላይ 3 የክላስተር ማዕከሉ ሱፐርቫይዘሮች የተገኙ ሲሆን ሙያዊ ምክራቸዉንም ለግሰዋል። በተለይም አስተባባሪዉ አቶ ምንይችል አዱኛ የዚህ መሰል ፕሮግራም ለተማሪዎች ያለዉን ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ በመዘርዘር አቅራቢ ተማሪዎችን አበረታተዋል።
👍 14❤ 2👏 2🔥 1