Merham Hadith
رفتن به کانال در Telegram
1.በል:-እርሡ፡አላህ፡አንድ፡ነው፡2.አላህ፡(የሁሉ)፡መጠጊያ፡ነው፡፡3.አልወለደም፣አልተወለደምም፡፡4.ለርሡም፡አንድም፡ብጤ፡የለውም፡፡ ሱረቱል፡- ኢኽላስ ለማንኛውም ሀሣብና አስተያየት እንዲሁም ለCross or @Merham_bot ሼር በማድረግ ተባበሩን @hadit_h
نمایش بیشتر9 350
مشترکین
-1724 ساعت
-1057 روز
-36630 روز
آرشیو پست ها
9 345
✨"ኢስላም ሰዎችን በጥላቻ መጋፈጥ ሳይሆን፣ በጥፋታቸው ላይ እያዘኑ በፍቅርና በጥበብ ወደ ቀጥተኛው መንገድ መጥራት ነው።"
ሸይኽ አሊ አል-ጂፍሪ✨
.
.
Share @hadit_h
9 345
✨"ኢስላም ሰዎችን በጥላቻ መጋፈጥ ሳይሆን፣ በጥፋታቸው ላይ እያዘኑ በፍቅርና በጥበብ ወደ ቀጥተኛው መንገድ መጥራት ነው።"
ሸይኽ አሊ አል-ጂፍሪ✨
.
.
Share @hadit_h
9 345
ማስረዳት ደክሞን ነው _ በዝቶ ቢያሰለቸን
እራስን እንዳጥፊ _ ቆጥሮ ዝም ያስባለን
የማንናገረው _ ከአፍ ቃል አውጥተን
በፍፁም አደለም
እውነት ስለሌለን _ ወይ ደግሞ ተረተን
አውቆ እንዳላወቀ
ነገር ስናሳልፍ _ ፀብ እንዳይጠነክር
መውደድ ብለን እንጂ _ ልናከርም ፍቅር
ሞኝ ስለሆንን _ ወይ ደግሞ ተታለን
ከቶውን አይደለም _ ከክብራችን ቀለን
እንደ ከዚህ ቀደም
የማንሟገተው _ ብለን ለምን እንዴት
ታክቶን አዝሎን ነው _ ተመሳሳይ ንዴት
ያቅታል አንዳዴ _ አቅም ይሟጠጣል
ያኔ ፀጥ ማለት _ ውስጥህ ግድ ይመርጣል
9 345
አላህ የራሱ ምክንያት እንደሚኖረው
በማመን ውስጥ ትልቅ ተወኩል አለ።
እንዴት እና መቼ እንደሆነ ባናውቅም ሁሉም ነገር ለኸይር ነው❤️🩹
9 345
ሰርቶ ገንዘብን ማጠራቀም፣ ሰርቶ ማገኘት ፣የወንድ ስራ ብቻ አይደለም የሴትም ነዉ ።ሁሌ የሰዉ እጅ መመለከት የለብሽም። ሸሪአዉ ባስቀመጠልሽ መልኩ ጠንካራ ሁኚ።
🤍
9 345
በዙሪያህ ያሉ ሰዎች ሁሉ ካደነቁህ እና ማንም የሚጠላህ ከሌለ፣ አንድ በጣም አደገኛ ስህተት እየሰራህ ነው። እውነተኛ ማንነትህን አጥተኸዋል!"
በፍልስፍና እና ስነ-ልቦና "The Desire to Please" (ሰዎችን ደስ የማሰኘት አባዜ) ይባላል። ሁሉም ሰው እንዲወድህ ስትሞክር የራስህ አቋም፣ የራስህ መስመር እና የራስህ ልዩ ማንነት አይኖርህም። ለሁሉም ሰው የሚመች ሰው ለመሆን ስትል ‘አይሆንም’ ማለት ታቆማለህ።
ልክ ውሃ እንደመሆን ማለት ነው። ውሃ ቀለምም ጣዕምም የለውም፤ በገባበት እቃ ቅርፅ ይይዛል። አንተ ግን ሰው እንጂ ውሃ አይደለህም። ጠንካራ አቋም ሲኖርህ የሚወዱህም፣ የሚጠሉህም በግልጽ ይለያሉ።"
የሰዎችን ትችት ላለመስማት ብለህ ማንነትህን ደብቀህ ታውቃለህ? ኮሜንት ላይ ተወያዩበት።"
9 345
✍️
አንድ በደዊ ለሐጅ ስነስርዓት ታደመ። ሆኖም ግን በዓረፋ ተራራ ላይ ምን ብሎ ዱዓ ማድረግ እንዳለበት ግራ ገባው።
በመጨረሻም “አሏህ ሆይ! ዓረፋን ከፈጠርካት ዕለት ጀምሮ፣ ዱዓ አድራጊዎች በዚህች ስፍራ ላይ ከለመኑህ መልካም ነገር ሁሉ እኔም እንድትለግሰኝ እማጸንሃለሁ።” በማለት ተማፀነ።
ይህንን የሰሙ ሁሉ አለቀሱ። እርሱንም፦ “የፀሎትን ጥግ አድርሰሃል (ሁሉንም በአንድ አጠቃለኸዋል)” አሉት።
حجّ أعرابي فلم يدرِ ما ذا يقول في عرفة، فقال: "اللهم إني أسألك من خير ما سألك السائلون في عرفة منذ خلقتها"، فبكى من سمعه. وقيل له: "قد أبلغت الدعاء".
9 345
Repost from ʙʀɪɢʜᴛ ᴍᴜꜱʟɪᴍ🇵🇸
🛑 የአረፋ ቀን ፆም!
ነቢዩ (ﷺ) ስለ አረፋ ቀን ፆም ተጠይቀው እንዲህ ብለዋል፦
“ያለፈውንና የመጪውን አመት ወንጀል ያስምራል።”
📚 ሙስሊም ዘግበውታል: 1162
🛑 የአረፋ ቀን ፆም የሚፆመው ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18 ነው።
⚫️ ቀዳ ያለበትም ሰው ቢሆን የዐረፋን ቀን ጾም መጾም ይችላል።
⚫️ ማንኛውም ከነጋ በኋላ ምግብና መጠጥ ያልቀመሰ ሰው ከነጋ በኋላም ቢሆን ነይቶ ጾም መጀመር ይችላል። ነገር ግን ምንዳው የሚጀምረው ከነየተበት ሰዓት ጀምሮ ነው።
⚫️ ከ9ኛው ቀን በፊት ምንም ላልጾመ ሰውም ቢሆን 9ኛው ቀን ብቻ መፆም ይቻላል/ችግር የለውም።
⚫️በዐረፋ (9ኛው ቀን) ላይ ይበልጥ የሚወደዱ 3 ዒባዳዎች፣
1/ ቀኑን መጾም
2/ ዚክር ማብዛት በተለይም ተክቢር
3/ ዱዓእ ማብዛት
9 345
"የኔ ልባም ሴት፣ 👸🏼❤️
ልባም መሆን ማለት ዝምተኛ መሆን ማለት አይደለም፤ ልባምነት ማለት መቼ መናገርና መቼ ዝም ማለት እንዳለብሽ ማወቅ ነው።
የኔ ልባም ሴት፣ አንቺ በዙሪያሽ ላሉት ሰዎች ብርሃን፣ ለቤተሰብሽ መከታ፣ ለራስሽ ደግሞ ኩራት ነሽ።
ብዙ ፈተናዎች ሊገጥሙሽ ይችላሉ፣ አለም ተስፋ እንድትቆርጪ ሊገፋፋሽ ይችላል። ነገር ግን አንቺ ውስጥ ያለው ያ የማይበገር የልባምነት መንፈስ "ገና ነኝ!" ይልሻል። እራስሽን ውደጂ፣ እውቀትሽን አሳድጊ፣ እናም በምትሄጂበት መንገድ ሁሉ በልበ ሙሉነት ተራመጂ።
አንቺ የጥበብ ምንጭ፣ የጽናት ተምሳሌት ነሽ።
ዛሬ የምታደርጊው ጥቃቅን በጎ ነገር ነገ ትልቅ ታሪክ ሆኖ ይነበባል። በርቺ፣ የኔ ልባም ሴት!
9 345
It wasn't a loss, it was an upgrade in awareness.
ሰዎች 'ድክመት' ነው የሚሉሽን ነገር አንቺ 'ልዩ ብቃትሽ' መሆኑን እወቂው።
ብዙ ማሰብሽ ጥልቀትሽ ነው፤
ሁሉንም ማስተዋልሽ ንቃትሽ ነው፤ ነገሮችን ማገናኘትሽ ደግሞ ጥበብሽ ነው። 💡✨
አእምሮሽ የሚነግርሽን ምልክት አትናቂው!! እሱ የማያዩትን የማየት ጥበብ አለው።
🦅🌸
9 345
ግድየለም ኡዝር መሰጣጠቱም አብሮ እንዳቆየን እንመን። የግንኙነቶች የረጅም ጊዜ መቆየት በሰዎች ፍፁም መሆን ብቻ የመጣ ሳይሆን እያዩ ባላየ፣እየሰሙ ባልሰማ በሚሉ ጉዳዮች ውስጥ ታልፎ ነው። ዛሬ በፍቅር ቃል የቆሙ ግንኙነቶች ሁሉ መስመራቸው በፍቅር ብቻ አልሰመረም። ቆይታቸው በመፈላለግ ብቻ አልዘለቀም። ይልቅ ክሬዲት መሰጣጠት ሰፊውን ቦታ ይይዛል። መተላለፍም ቢሆን የዛ አንድ አካል ነው።
አንዳንዴም ወዶ በመተው እና ፈልጎ በመለያየት ውስጥ ሁልጊዜ ጥላቻ የለም። አብሮ በመሆን ብቻ ሳይሆን ፈቅዶ በመለያየትም ውስጥ ፍቅር ሊንፀባረቅ ይችላል። ማንኛውም ነገር ያለቦታው ከተገኘ መነሳቱ አይቀሬ ነው። የትኛውም ጉዳይ የቀድር እጅ ከሌለበት አለመሆኑ የግድ ነው። ያን ልብ ብሎ ያለምንም ትግል መፍትሄ መፈለግና የመፍትሄ አካል መሆን አስተዋይነት ነው። አይመስላችሁም?
(አብድልቃድር ኑር)
9 345
ከስልካችሁ ላይ የመጨረሻውን የላካችሁትን ኢሞጂ ኮመንት ላይ አስቀምጡ። (የኔ፡ 😂)"
"አንድ ቀን ሙሉ ስልክ ባይኖር ምን ታደርጋላችሁ? እኔማ መተኛት ነው!"
"በጣም የምትወዱት ምግብ ምንድነው? (ለኔ ኢንዶሚ ነው!)
9 345
ሀቂቃ መለያየት አይደለም ማሰብ ለሚችል የሰው ልጅ ኸልቅ ማሰብ ለማይችል እንስሳም ልብ ሰባሪ ክስተት ነው። አዎን ተለያይተናል። ልክ ነው ተራርቀናል። በሰአቱ አዝነናል እንዲሁም ደክሞናል። በዛ ሰአት ከጎናችን ማን እንደነበር ግን በሚገባ አይተናል። የሄዱት ሲሄዱ ትርፍ የሆኑንን ሰዎች ለይተናል። ምንም ቢፈጠር አብረውን የቀሩ ትክክለኛ ማንነቶችን አይተናል። አልሀምዱሊላህ ነው እናንተዬ አንዳንድ መለያየቶች ለአቅል ቢከብዱም ፍሬውን ከገለባ ልቅም አድርገው ያሳያሉ። በጨለማ ውስጥ ብርሀን ሆኖ የሚቀረው ማን እንደሆነ በሚገባ ያሳያሉ። ይሁን ለኸይር ነው በሉ። አብሽሩ🤍
(አብድልቃድር ኑር)
