cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

CNN መረጃ

ምን ጊዜም ኢትዮጵያ

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
199
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-430 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#ፑቲን አሜሪካ ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤቷ በኩል በሰጠችው መግለጫ ፤ የሩስያ ምርጫን " ኢ-ዲሞክራሲያዊ ነው " ስትል አጣጥላለች። በከፍተኛ ልዩነት አሸንፈዋል የተባሉትን ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንንም " እንኳን ደስ አልዎት " አንላቸውም ብላለች። ሩስያን እስከ 2030 ለመምራት በበላይነት ፕሬዜዳንታዊ ምርጫውን ያሸነፉት ቭላድሚር ፑቲ ትላንት ድላቸውን አስመልክቶ በሰጡት መግለጫ የአሜሪካን ዴሞክራሲ ወርፈዋል። ምን አሉ ? ቭላድሚፕ ፑቲን ፦ " ያካሄድነው ምርጫ ከአሜሪካ በላይ ተዓማኒ እና ግልጽ የሆነ ዓላማ ያለው ነው። በአሜሪካ በፖስታ አማካይነት ድምጽ እንደሚሰጡት አይደለም። እዛ (አሜሪካ) ድምጽ በ10 ዶላር መግዛት ይቻላል። የምርጫ ስርዓታቸው ኢ-ዴሞክራሲያዊ ነው። ዓለም ሁሉ እዚያ እየሆነ ባለው ነገር ይስቃል (በአሜሪካ ዴሞክራሲ) " ብለዋል። ፕሬዚዳንት ፑቲን ፕሬዜዳንታዊ ምርጫውን በከፍተኛ ብልጫ ማሸነፋቸው ተከትሎ ፦ - ቻይና - ህንድ - ኢራን - ሰሜን ኮሪያ - ቬንዙዌላ #የደስታ መልዕክት ሲያስተላልፉ እነ አሜሪካ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ ዩክሬን፣ ዩናይትድ ኪንግደም እና ሌሎች አጋሮቻቸው ምርጫውን ኢ-ዴሞክራሲያዊ ሲሉ እያጣጣሉት ይገኛሉ። ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
በቤልግሮድ የአየር ላይ ጥቃት መድረሱን ተከትሎ ትምህርት ቤቶችና ሱቆች እንዲዘጉ ተደረገ፡፡ ባለስልጣናት ዩክሬንን ተጠያቂ ባደረጉበት የሩሲያዋ ቤልግሮድ ከተማ ጥቃት ሞስኮ በከተማዋ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችና ሱቆች እንዲዘጉ አድርጋለች ተብሏል፡፡ የከተማዋ ገዥ ቭያችስላቭ ግላድኮቭ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እየተካሄደ በነበረበት ወቅት በደረሰ የቦምብ ጥቃት ሁለት ሰዎች ሙተዋል ማለታቸው ተነግሯል። "የአየር መከላከያ ሲስተም ስምንት የዩክሬን ሚሳዔሎችን መትተው ጥለዋል" ብለዋል ግላድኮቭ፡፡ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ዩክሬን ሩሲያ ያካሄደችውን ምርጫ ለማስተጓጎል ያደረገችው ሙከራ ነው ሲሉ ኪቭን ለድርጊቱ ኪቭን ተጠያቂ አድርገዋል፡፡ የቤልግሮድ ገዥ ቭያችስላቭ ግላድኮቭ ሩሲያና ዩክሬንን በምታዋስነው በዚች ከተማ ሰኞና ማክሰኞ ትምህርት ቤቶች ዝግ እንደሚሆኑና ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት እንደማይሄዱ መናገራቸውን የዘገበው BBC ነው፡፡ ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
በባህር ዳር ከተማ ውሰጥ በጥቁር ገበያ ቤንዚል በሊትር እሰከ ከ300 እየተሸጠ መሆኑ ተሰማ። የነዳጅ የዋጋ ንረቱ የተፈጠረው በተወሰኑ ሰግብግብ ነጋዴዎች አማካኝነት ነው ተብሏል። በባህርዳር የነዳጅ እጥረት በመፈጠሩ ከከተማዋ ነዋሪዎች ባሻገር ከሌላ ቦታ የመጡ ተገልጋዮችና አርሶአደሮች ጀሪካን ይዘው እየተንከራተቱ ይገኛሉ። በከተማዋ የነዳጅ እጥረት ሆን ብለው እንዲፈጠር በማድረግ ችግሩን የሚያባብሱት ደግሞ የተወሰኑ ባለ ማደያዎች ናቸው ተብሏል። እነዚህን ዘግተው የጠፉና በጥቁር ገበያ ነዳጅ ሚሸጡትን ማደያዎች ስም ዝረዝር በቅርቡ ይፋ እንደምናደርግ በቅርቡ እናሳውቃለን። በባህር ዳር በቂ ማደያዎች ቢኖሩም የነዳጅ ዲፖ እንከፍታለን በሚል ከአምስት ዓመታት በፊት ከመንግስት ቦታ ተቀብለው የጠፉ እንዳሉ ለማወቅ ችለናል፡፡ መሬት አጥረውና ባዶ ታንከር አስቀምጠው በፕሮጄክቱ ስም ከባንክ ተበድረው የተጠፉ እንዳሉም ይነገራል። በከተማው የነዳጅ እጥረት ቢኖሩም በተሰጣቸው ኮታ በአግባቡ የሚያከፋፍሉ በጣት የሚቆጠሩ ባለ ማደያዎች እንዳሉ ግን ነዋሪዎች ገለፀዋል:: Via፡ Ethiopian Business ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
የሐማስ ሦስተኛ ከፍተኛ አመራር ማርዋን ኢሳ በእስራኤል የአየር ድብደባ ሕይታቸው አልፏል ተባለ፡፡ የእስራኤል የደህንነት ባለስልጣናት እንደገለጹት ከሆነ፣ የሐማስ ሦስተኛው ዋና አመራር የነበሩት ማርዋን ኢሳ መሞታቸውን አረጋግጠናል ብለዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ቢኒያሚን ኔታንያሁ የጸጥታ ባለሥልጣናቱ ሪፖርት “ለእስራኤል ታላቅ ስኬት ነው” ሲሉ አድንቀው “ሁሉም ይሞታሉ፣ ሁሉንም እናዳርሳቸዋለን” ሲሉ ዝተዋል፡፡ All Israel News እንደዘገበው ከሆነ፣ እስራኤል የፀጥታ ካቢኔ መግለጫ የሰጡ ባለስልጣናት የኢሳ ሞት በእስራዔል ጦር የተሳካ ኦፕሬሽን መጠናቀቁን ተናግረዋል ብሏል። ሃማስ የኢሳን ሞት ትክክል ይሁን ወይንም ውሸት እስካሁን ድረስ ማረጋገጫ አልሰጠም ተብሏል፡፡ ኢሳ የሞታቸው ዜና በእስራዔል የደህንነት ባለስልጣናት ከተነገረ ጊዜ ጀምሮ በህዝብ ታይተው አያውቁም ነው የተባለው፡፡ ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
”በጋዛ ከሁለት ዓመታት በታች የሆኑ ህጻናት ከሦስቱ መካከል አንዱ በከፋ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት የተጎዳ ነው” - ተ.መ.ድ በሰሜን ጋዛ ውስጥ በአሁኑ ጊዜ ከሁለት ዓመታት በታች ከሆኑ ህጻናት መካከል ከሦስቱ አንዱ በከፍተኛ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እና ረሃብ ውስጥ እንደሚገኝ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታውቋል፡፡ የተባበሩት መንግስታት የፍልስጤም ስደተኞች የእርዳታ እና ስራዎች ኤጀንሲ በማህበራዊ ድረ-ገጽ ላይ "የህፃናት የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በፍጥነት እየተስፋፋ እና በጋዛ ታይቶ የማይታወቅ ደረጃ ላይ ደርሷል" ብሏል። እስራኤል በጋዛ የአየር እና የምድር ዘመቻ ከጀመረች በኋላ 2.3 ሚሊዮን ሕዝቧ ተፈናቅሎ ለከፍተኛ ሰብአዊ ቀውስ የተጋለጠ ሲሆን፣ አብዛኛው ክፍሏ ደግሞ ፈራርሷል ሲል Gulf Today ዘግቧል። በቅርቡ የአየር እና የባህር ርዳታ ወደ ጋዛ ማድረስ የተጀመረ ቢሆንም ነገርግን የእርዳታ አቅርቦቱን በየብስ ማምጣት የተሻለ ነበር ተብሏል፡፡ ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
" ገንዘቡን ተመላሽ ባደረጉ ተማሪዎች ላይ ባንኩ ምንም አይነት ክስ አይመሰርትም " - ንግድ ባንክ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከቀናት በፊት ባንኩ ላይ አጋጥሞ ስለነበረው ችግር መግለጫ የሰጡት የባንኩ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ፣ አርብ ለሊት ባንኩ አጋጥሞት በነበረው ችግር የደንበኞች የግል አካውንት ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት እንደሌለ ገልጸዋል። ባንኩ የውስጥ አሰራሩን ለማዘመን (የሲስተም ማሻሻያ) ሲያደርግ በነበረው እንቅስቃሴ ምክንያት በተፈጠረ ስህተት የአርብ መጋቢት 6 ለሊቱ ክስተት መፈጠሩን እና ጉዳዩ ከሳይበር ጥቃት ጋር የሚያያዝ እንዳልሆነ ተናግረዋል። " በተፈጠረ ስህተት ምክንያት ጤናማ ያልሆነ የገንዘብ እንቅስቃሴ ነበር " ያሉት አቤ ሳኖ፣ አርብ ለሊት ብቻ ከ490 ሺህ በላይ የገንዘብ ልውውጥ እንደነበር ገልጸው፣ ይህ የገንዘብ ልውውጥ ጤናማ የሆነውንም እንደሚጨምር ጠቁመዋል፡፡ " ገንዘብ በተለያየ መንገድ ጤናማ ባልሆነ መልኩ ከባንኩ በማውጣት ላይ በዋናነት የተሳተፉት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው " ሲሉ ገልጸዋል። የድርጊቱ ተሳታፊ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በባንኩ በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ እነደሆነና ገንዘቡን ተመላሽ ባደረጉ ተማሪዎች ላይ ባንኩ ምንም አይነት ክስ እንደማይመሰርት አሳውቀዋል። አሁንም ያልመለሱ ስም ዝርዝራቸው የወጣ ተማሪዎች የወሰዱትን ገንዘብ እንዲመልሱ አስበው፣ ከዚህ ባለፈ ወደ ሌሎች ባንኮች የተደረጉ እና ጤናማ የማይመስሉ የገንዘብ ዝውውሮች ታግደው እንደሚገኙ አስረድተዋል። የደንበኞች የግል አካውንት ላይ የደረሰ ምንም አይነት ጉዳት ባለመኖሩ የባንኩ ደንበኞች ምንም አይነት ስጋት እንዳይገባቸው ማለታቸውን የብሔራዊ ቴሌቪዥን ዘግቧል። ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
ፈተናውን ያላለፉ ሠራተኞች ሁለት ደረጃ ዝቅ ብለው መመደባቸው ተገለጸ። በአዲስ አበባ በ16 ተቋማት ላይ የተካሄደው የሠራተኞች ምዘናና ምደባ የሪፎርም ሥራ ተጠናቆ ወደ ትግበራ ምዕራፍ መግባቱን የከተማዋ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ኃብት ልማት ቢሮ ገልጿል። የቢሮው ኃላፊ ጣሰው ገብሬ (ዶ/ር)፤ በከተማዋ የሚሰጠውን አገልግሎት ለማሻሻል በተያዘው በጀት ዓመት በ16 ተቋማት ሪፎርም መደረጉን ጠቁመዋል። ሪፎርሙን ተከትሎ የአሠራር ሥርዓት ማሻሻያ ከማዕከል እስከ ወረዳ አደረጃጀት መሠራቱን ገልዋል። በቴክኖሎጂ የሚደገፍ አገልግሎት የመለየት ሥራ መሠራቱን አንስተው፤ የሠራተኛ ብቃት ምዘና መደረጉንም አስረድተዋል። የብቃት ምዘናውን ከ19 ሺህ በላይ የሆኑ ሠራተኞች መውሰዳቸውን ጠቅሰዋል። ከተፈታኞቹ መካከል 33.3 በመቶ አመራሮች እንዲሁም 50.6 በመቶው ሠራተኞች ማለፋቸውን ተናግረዋል። ምዘናውን ያለፉ 99 በመቶ ኃላፊዎች እንዲሁም 88 በመቶ የቡድን መሪና ሠራተኞች መመደባቸውን አስረድተዋል። ፈተናውን ያላለፉትም በድልድል ደንቡ መሠረት ሁለት ደረጃ ዝቅ ብለው መመደባቸውን ገልጸዋል። ምዘናውን ተከትሎ ከ17 ሺህ በላይ ሠራተኞች በሁለት ዙር የአቅም ግንባታ ሥልጠና መውሰዳቸውንም ተናግረዋል። ሪፎርሙ የዝግጅት ምዕራፍ ተጠናቆ ከዛሬ ጀምሮ ወደ ትግበራ መገባቱን ነው ቢሮ ኃላፊው የገለጹት። Source፡ Ethiopian ncws agency ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
"ሲሲ አስርበኸናል" - በኑሮ ውድነት ተማረው ሰልፍ የወጡ ግብጻውያን! ግብጻውያን በሀገራቸው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣውን የኑሮ ውድነትን በመቃወም መፍትሄ እንድበጅለት ለመጠየቅ ሰልፍ ወጥተዋል፡፡ የተቃውሞ ሰልፉ ከጁምዓ ሶላት በኋላ የተጀመረ ሲሆን፣ ተቃዋሚዎች “"ሲሲ አስርበኸናል" የሚሉ ፀረ-መንግስት መፈክሮችን ይዘው ነበር ተብሏል። "አስመርሮናል" ያሉትን የኑሮ ውድነት በመቃወም በሰልፉ ከተሳተፉት ውስጥ በጸጥታ ኃይሎች በቁጥጥር ስር የዋሉ መኖራቸው ተነግሯል፡፡ ተቃውሞው የተነሳው የፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ ኤል ሲሲ መንግሥት ከቀን ወደ ቀን እያሻቀበ የመጣውን የዋጋ ግሽበት ለመቀልበስ እየታገልኩ ነው በሚልበት ወቅት እንደሆነ The New Arab ዘግቧል፡፡ የግብፅ የሰብአዊ መብቶች ጥምረት (ENHR) እንዳስታወቀው ከሆነ፣ በሀገሪቱ ያለውን የዋጋ ንረት እና የኑሮ ውድነትን ተቃውመው ሰልፍ የወጡ ተቃዋሚዎች በግብፅ የጸጥታ ኃይሎች መታሰራቸውን ገልጿል። ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ምንም ምርት እየሰጠ አለመሆኑ ተገለጸ። ፋብሪካው በአገሪቱ የሚስተዋለውን የስኳር ምርት አቅርቦት ችግር ይቀርፋል ተብሎ ቢገነባም በዚህ ዓመት ምንም ምርት እንዳልሰጠ ተገልጿል፡ የጣና በለስ ስኳር ፋብሪካ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አበበ ይሁኔ ገለጹት በተባለው መሠረት፤ ፋብሪካው አዲስ የተቋቋመና ሙሉ አቅሙን በመጠቀም ምርት እና ምርታማነትን ለመጨመር ወደ ሥራ የገባ ቢሆንም እያጋጠሙ ባሉ ችግሮች ምክንያት ስኳር እያመረተ አይደለም፡፡ ከእነዚህም ችግሮች በዋነኝነት ኤሌክትሪክ ኃይል ያገኝበት የነበረው የጎንዝላ ሀይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ከአንድ ዓመት ተኩል በላይ መበላሸት ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ችግር መከሰቱ እና የማሽን አቅርቦት ችግሮች መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡ በዚህ ዓመትም በ6 ሺህ 33 ሄክታር መሬት ላይ የሸንኮራ አገዳ በማምረት 183 ሺህ ኩንታል የስኳር ምርት ለማግኘት የታቀደ ቢሆንም ባጋጠሙ ተግዳሮቶች ምክንያት እስካሁን ምንም ምርት አለማምረቱን ኢፕድ ዘግባሏ። ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...
ታይሰን ምግቦች በኒውዮርክ ከተማ ሕገወጥ ስደተኞችን ለመቅጠር አቅጃለሁ አለ። ታይሰን ምግቦች ስደተኞችን በመጠለያ ጣቢያ ላይ ትኩረት በማድረግ በትብብር የሚሰራ ድርጅት ነው። በአሁኑ ወቅት በ120 ሺሕ የሥራ ቦታዎቹ ላይ ወደ 42 ሺሕ የሚጠጉ ሕገወጥ ስደተኞችን ቀጥሮ ይገኛል። የታይሰን ምግቦች ስራ አስፈፃሚ ጋሬት ዶላር፣ "የምናገኝ ከሆነ ሌሎች 42 ሺዎችን መቅጠር እንወዳለን" ሲሉ ለBloomberg ተናግረዋል። ድርጅቱ ለስደተኛ ሠራተኞቹ በሥራ ቦታ ላይ የህፃናት ማቆያ፣ ትራንስፖርትና አማራጭ የእንግሊዝኛ ትምህርት አቅርቧል። በ2023, ለ1,317 ሠራተኞች የአሜሪካ ዜግነትን እንድያገኙ ክፍያ ፈጽሞላቸዋል። ለፈጣን መረጃ:-👉
نمایش همه...