በስመአብ ወወልድ ወመን ፈስ ቅዱስ አሀዱ አምላክ አሜን::
የባሻኔ ቅድስት አርሴማ እና ቅዱስ ጊዮርጊስ አንድነት ገዳም ታሪክ
-ገዳሙ ከአ.አ 88ኪ.ሜ በስተደቡብ በቡታጅራ መስመር ጢያ ተክል ሲደርሱ ወደ አማውቴ በሚወስድው መንገድ 7 ኪ.ሜ ገባ ብሎ ይገኛል::የገዳሙ ታሪክ የሚጀምረው ቦታው በጣም ጥቅጥቅ ያለ ጫካ እንደነበርና በውስጡም ጅብና አስፈሪ የዱር አራዊት ስለሚኖሩበት ለዘመናት ማንም ድፍሮ የሚገባ አልነበረም ከብቶችም ቢሆኑ ይጠፉ እንደ ነብር የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::በቦታው ዋሻ እንደነበርና ሞጄ የተባሉ የመንደሩ አባ ወራ በሬዎቹን ጠምዶ ለማረስ ሲወጣ መብረቅ ከሰማይ ወርዶ አሁን ፀበሉ በፈለቀበት ቦታ ላይ እንደወደቀና ሳያርስ ፈርቶ እንደተመለሰ ተናግሯል ቦታው ላይ የነበሩትን ዕፅዋቶች የአከባቢው ማህበረሰብ ለመቁረጥ ቢሞክሩም እንዳቃታቸውና እስከዛሬ ድረስ ስድስት ጊዜ ተሸጦ አልቆረጥ ያለ የወይራ ዛፍ ለ እማኝነት በገዳሙ ውስጥ ይገኛል የወይራ ዛፉም ብዙ ተአምር እየሰራ ነው:: ገዳሙ ካለብት በስተ ሰሜን አቅጣጫ በ አጼ ሚንሊክ ዘመነ መንግስት ከውጪ ያመጡት ባርዛፍ እንደ ሽቦ በእሳት ሲቀጣጠል በተደጋጋሚ ይታያቸው እንደነበርና ብዙ ጊዜም በእሳት ሲቀጣጠል በተደጋጋሚ ይታያቸው እንደነበርና ብዙ ጊዜም አከባቢው ላይ እሳት የተነሳ እየመሰላቸው ለማጥፋት ሲመጡ ምንም እንደ ማያገኙ በቅርብ የሚገኙ ነዋሪዎች ይናገራሉ::
ሁሉም በጊዜው ይሆናልና ሰማዕት ቅድስት አርሴማ በራዕይ ተገልጻ ከ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ፀበል ቦታ የሚያገለግሉ ልጆቿን በመንፈስ ቅዱስ እየመራች 32 አዋቂዎችና 2 ህፃናት ሰኔ 11 2014 ዓ.ም የተባለው ቦታ ላይ 2- 14 ቀን ሱባዔ ከቆዩ በዋላ ምህመናን በተገኙበት የፈለቀው ፀበል በአባቶች ተባርኮ የተለያዩ ታምህራትን እያደረገ ይገኛል::በፀበሉም ማየት የተሳናቸው አይናቸው በርቷል ለምፃም ነፅቷል ሁለት ህፃናት ሞተው ተነስተዋል ከተነሱት ህፃናት መካከልም የአንዱ ህፃን አባት በገዳሙ ውስጥ እያገለገሉ ይገኛሉ::የፃድቃኔ ማርያም ስውሯ ፅላት የዘረዓ ያእቆቧ እመቤት ገዳሙ ላይ እፁብ ድንቅ የሆነ ተዓምር እየሰራች ህዝበ ክርስትያኑንና ገዳሙን በቀን 3 ጊዜ ከልጇ ጋራ በወርቅ መስቀሏ እንደምትባርክ ቃልኪዳን ገብታለች::ስሟንም ጠርቶ የተማፀነውን ሁሉ በገሀድ፣በህልምና በራዕይ ተገልፃ ጤና ያጣውን ድኖ ተፈውሶ የህይወት እንቆቅልሹ ተፈቶለት፣ያዘነው ተደስቶ እንዲሄድ ታደርጋለች በገዳሙ ለተለያዩ አገልግሎቶች የተሰሩ አዳራሾች አሉ::ከ እነዚህም መካከል፦ፀሎት ቤት፣ሱባዔቤት/የወንድ እና የሴት/አርምሞ ክፍል እንዲሁም ለመሳለም የሚመጡ ምህመናን የሚስተናገዱብት፣በሱባዔ ተወስነው ያሉትና የገዳሙ አገልጋዮች በህብረት የሚፀልዩብት አዳራሽ ይገኛል::ይህም ቤተ ማርያም በመባል ይጠራል በዚህ አዳራሽ ውስጥም በጅሩ አርሴማ ቤ/ክ የመጣ የዘንባባ ድንጋይ አለ የዘንባባ ድንጋዩም እጅግ ብዙ ተአምራትን እያደረገ ሲሆን ለአብነትም ያህል 1.ህሙማንን ይፈውሳሉ
2.መካኖች ልጅ ያገኛሉ
3.የተውሳሰበ ችግራቸው ይፈታላችዋል
ለቅድስት አርሴማ ለገዳሙ የተሰጠ ቃል ኪዳን ብጥቂቱ
-ቦታውን የረገጠ ሁሉ 64 ትውልድ እምርለታለው
-ንስሀ ገብቶ የመጣ እና በገዳሜ የአርምሞ ክፍል ውስጥ
ሆኖ የተማፀነኝ እስከ 600 ጥያቄ ድረስ እመልስለታለው
-በገዳሜ ውስጥ የሚገኘውን ዘቢብ ለ 3 ቀናት በባዶ
አፋቸው 7 ፍሬ ቢበሉ ከተለያዩይ የሆድ በሽታዎች ፣ከጨጓራ
በሽታ፣ ከማህፀን በሽታ እፈውሳቸዋለው፣በመተት ወይም በአስማት የተሰራን በሆድ ውስጥ ያደገ አውሬና ማንኛውም አይነት ትላትል አስወግድላችዋለው::
-አንድ ሰላም እለኪ እና አንድ አባታችን ሆይ ፀልየው የባሻኔዋ ቅድስት አርሴማ ሆይ ድረሺልኝ ብለው በስለት ቢያሳስቡኝ ፈጣን ምላሽ እሰጣቸዋለው ምላሹን ከ 2 ሰአት በዋላ ይጠብቁ እመልስላቸዋለው::
የፃድቃኔ ማርያም ስውሯ ፅላት ኢትዮጽያን ትባርክልን::
የሰማእቷ ቅድስት አርሴማ እና የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ
እረዴትና በረከታቸው ይደርብን::
ወደ እዚህች ወደተቀደሰች ቦታ ለመሄድና
የቃል ኪዳኗን በረከት ለመካፈል ማህበራችን ማህበረ ንሴብኦ ደርሶ መልስ
ጉዞ አዘጋጅቷል: :
የጉዞ ቦታ፦ባሻኔ ቅ/አርሴማ
መነሻ ቀን፦ታህ ሳስ 9/04/2015/
መነሻ ሰዓት፦12:00
መመለሻ ቀን፦ታህሳስ 9/04/2015/
የጉዞ ዋጋ፦450
መስተንግዶን ጨምሮ
ለበለጠ መረጃ ፦0924 89 60 47 የሱነ
+251902347665 ሀይለ
-ሲመጡ ክርስትያናዊ አለባበስ ለብሰው ይምጡ
-ሰዓት ይከበር አርፍዶ ለመጣ ማህበሩ ተጠያቂ አይሆንም
-ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ፈጥነው ይመዝገቡ::