cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

አንተነህ በላይ_Anteneh Belay

በመረጃ የበለፀጉ ዜጎችን እናፈራለን! https://t.me/antenehbelay

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
414
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-630 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ታምዕር ነዉ ‼ ዳሩ ዉስጡን ለቄስ ነው 🤔 የትግራይ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ በልዩ ዝግጅት 12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና ያስፈተኗቸው ተማሪዎች 69.96% እንዳሳለፉ አጋርተዋል፡፡ ተማሪዎቹ ባለፉት 3 ዓመታት ካሳለፉት ጊዜያት አንጻር እንኳን ለዚህ አበቃችሁ የሚያሰኝ ነው፡፡ ሆኖም ግን በሀገር አቅፍ ደረጃ 12ኛ ክፍል መልቀቅያ ፈተና 3% አመጣን ተብለን በተነገረን ማግስት፤ ለሶስት ዓመታት አብዛኛውን ጊዚያቸውን ከቀያቸው ከትምህርት ቤታቸው ተፈናቅለው ወይም ወደውም ሆነ ተገደው መሳርያ አንግተው ሲፋለሙ የነበሩ ወጣቶችን፤ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ አዘጋጅታና ፈተና አስቀምጣ 70% ተማሪ ማሳለፍ የምንችልበት ሁኔታ ከተአምር በላይ ነው፡፡ ፕሮፌሰር ብርሀኑ ቀመሩን እንዴት አድርገው ያስረዱን ይሆን....እንድምታው ትምህርት መማር ፋይዳ የለውም ከሆነ ይንገሩን ..........ትውልድን ማምከን
نمایش همه...
#የዩኒቨርስቲ ምደባ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሄራዊ ፈተና ወስደው ያለፉ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ምደባ አሰራርን አስመልክቶ የተሰጠ ማብራሪያ የተማሪ ምደባ መስፈርቶች፡- 1. 1000 ለሚሆኑ ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች፡- የምደባ ስርዓቱ በተፈጥሮም ሆነ በማህበራዊ ሳይንስ መስኮች 1000 ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎችን በመጀመሪያ የዩኒቨርስቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫቸው ምደባ የሚካሄድ ይሆናል። 2. ውጤት፡- የምደባ ስርዓቱ እያንዳንዱ ተማሪ ያስመዘገበውን አጠቃላይ ውጤት በምደባ ስርዓት ሂደት ውስጥ መለያ አድርጎ ይጠቀማል፡፡የተሻለ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ሌሎች ተፈጻሚ የሚሆኑ ህግና ደንቦችን ባልጣሰ መልኩ ምርጫቸውን በመጠበቅ ረገድ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል፡፡ 3. የዩኒቨርሲቲ ምርጫ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የቅበላ አቅም ታሳቢ ያደረገ ነው፡፡ ተማሪዎች 46 ዩኒቨርሲቲዎች ለምርጫ ቀርበውላቸዋል፡፡ መረጃው የተሰበሰበው https://portal.etherenet.edu.et ላይ ነው፡፡ 4. በተማሪዎች የተመረጡ ተቋማት ያላቸው የትምህርት ፕሮግራሞች ፡- የምደባ ስርዓቱ በተማሪዎች የተመረጡ የትምህርት ፕሮግራሞች እና የተመረጡት ዩኒቨርሲቲዎች ያላቸውን የትምህርት ፕሮግራም መሰረት ያደረገ እንዲሆን ተደርጓል፡፡ 5. ጾታ ፡- በተቋማት የጾታ ተዋጽኦን ለመጠበቅ በሚኖረው የምደባ ስርዓት የጾታ ተዋጽኦና ሚዛን እንዲጠበቅ ተደርጓል፣ 6. የትምህርት ቤት ተዋጽኦ ፡- የምደባ ስርዓቱ ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች የሚመደቡ ተማሪዎችን ተዋጽኦ በጠበቀ መልኩ እንዲሆን ያግዛል፡፡ይህም ከአንድ ት/ቤት የወጡ ተማሪዎች በአንድ ዩኒቨርሲቲ ወይም ፕሮግራም ውስጥ እንዳይታጨቁ ይደርጋል፡፡ 7. የውጤት ተዋጽኦ ፡-የምደባ ስርዓቱ ተማሪዎች ያስመዘገቡትን ውጤት ታሳቢ ያረገ ሲሆን ይህም ተመሳሳይ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች አንድ ላይ እንዳይመደቡ በማድረግ የተለያየ ችሎታና ተሰጥኦ ያላቸው ተማሪዎችን ቀላቅሎ ለማስተማር ያግዛል፡፡ 8. ወሊድን በተመለከተ፡- የምደባ ስርዓቱ እንደ ወሊድ ያሉ ልዩ ሁኔታዎችን ያማከለ ነው፡፡ በመሆኑም በመሰል ሁኔታ ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ለመቀጠል የሚቸገሩ ከሆነ ትክክለኛ ለውጥና ድጋፍ የሚደረግ ይሆናል፡፡ መረጃዎቹ የተሰበሰቡት https//student.ethernet.edu.et ላይ ነው፡፡ •አስፈላጊ ማስረጃዎች: - ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የህጻናት የክትባት ካርድ 9. ትክክለኛ የሕክምና ቦርድ ማስረጃዎች፡- በምደባ ወቅት የጤና ችግር ኖሮባቸው ትክክለኛ የሕክምና ማስረጃ ላላቸው ተማሪዎች ምደባው በተለየ መልኩ ሊታይ ይችላል፡፡ • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና ከህዝብ ጤና ተቋማት የህክምና ምስክር ወረቀት በሶስት ዶክተሮች እና በህክምና ዳይሬክተሩ የጸደቀ። • የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው። 10. ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች (identical twins) ፡- በተማሪዎቹ መካከል ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትዮች ካሉ የምደባ ስርዓቱ ከፍተኛ ነጥብ ያገኘው/ችው ተማሪ ከተመደበበት/ችበት የትምህርት ተቋም ቀሪው መንትያ ደግሞ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በቀጥታ ይመድባል። የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et ላይ ነው። • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡- ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የልደት የምስክር ወረቀት፣ 11. የአካል ጉዳት ያለባቸው ተማሪዎች:- የምደባ ሲስተሙ የአካል ችግር ላለባቸው ተማሪዎች እኩል እድሎችን የሚሰጥ ሲሆን ልዩ ፍላጎቶቻቸውን እና ለምደባ መስፈርቶቻቸውን ግምትውስጥ በማስገባት የሚሰራ ይሆናል። የዚህ አይነት መረጃ የተሰበሰበው https://student.ethernet.edu.et በመጠቀም ነው። • አስፈላጊ ማስረጃዎች፡ ከትምህርት ቤታቸው የድጋፍ ደብዳቤ እና የአካል ችግር ያለበትን የሰውነት ክፍል የሚያሳይ ፎቶግራፍ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣ ማሳሰቢያ፣ ሀሰተኛ የህክምና ማስረጃ የሚያቀርብ ተማሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከምደባ ውጭ የሚሆን መሆኑን እንገልጻለን፡፡ የኢፌዲሪ ትምህርት ሚኒስቴር!
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
‹‹ ማንም ሀገር ላይ ወረራ አንፈፅምም ›› - የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐብይ አህመድ ዜና | ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዥ ዐብይ አህመድ ‹‹ ኢትዮጵያ ማንም ሀገር ላይ ወረራ አትፈፅምም ›› ሲሉ ተናገሩ፡፡ የጦር ሀይሎች ጠቅላይ አዛዡ ይህን የተናገሩት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ በተከበረው 116ኛው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ቀን ላይ ተገኝተው ባሰተላለፉት መልዕክት ነው፡፡ 17 ደቂቃ ገደማ የወሰደው የዐብይ ንግግር ስለኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ታሪካዊ ዳራ ሰፊ ጊዜ ወስደው አብራርተዋል፡፡ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ታሪኩን ፈትሾ፣ የተፈጠረበትንና ሀገርን የሚያፀናበትን ዕለት በዚህ መንገድ ማክበር ሲችል እንዲያስታውሳቸው የምፈልገው ጥቂት ሃሳቦች እንዳሏቸወ የተናገሩት ዐብይ ቀዳሚው ጉዳይ ‹‹ ኢትዮጵያ በማንም ሀይል ተሸንፋ አታውቅም፣ አሁንም አትሸነፍም ›› የሚለው ነው፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሁለተኛ እንዲታወስልኝ እፈልጋለሁ ያሉት ‹‹ ኢትዮጵያ ማንንም ሀገር ወርራ አታውቅም፤ አሁንም ማንንም ሀገር አትወርም ›› ያሉበት መልዕክትን ነው፡፡ ኢትዮጵያ የመከላከል እንጂ የማጥቃትና የመውረር ታሪክ እንደሌላት ያስታወሱት ዐብይ ለኢትዮጵያ ሕዝብና መከላከያ ሠራዊት ላረጋግጥላችሁ የምፈልገው ‹‹ ኢትዮጵያ በሀይልና በወረራ ማሳካት የምትፈልገው አንዳች ነገር የለም › ሲሉ ተናግረዋል፡፡
نمایش همه...
ህዝብ አልቦ መንግሥት አባገነንነትን ይወልዳል:: መንግስት አልቦ ህዝብ ደግሞ ስርዓት አልበኝነትን ይፈጥራል:: የህዝብ አልቦ መንግሥት ምርኩዝ ወታደር ነው:: የህዝባዊ መንግሥት ምርኩዝ ደግሞ ህዝብ ነው:: ወታደር ምርኩዝ የሆነው መንግሥት ሃገርን ያወድማል:: እድሜውም አጭር ነው:: ህዝብ ምርኩዝ የሆነው ግን ሃገርን ያለማል:: ስልጣኑም ቋሚ ነው:: ኢትዮጵያ በህዝብ አልቦ መንግሥትና በመንግሥት አልቦ ህዝብ ( ወይም በአምባገነንነትና ስርዓት አልበኝነት) መካከል ትገኛለች:: ) የትኛው አሸንፎ ይወጣል የሚለውን ጊዜ ይመልሰዋል:: ህዝብ ካስማው የሆነለት መንግሥት እስካልተወለደ ድረስ የኢትዮጵያ ፍዳ ይቀጥላል::
نمایش همه...
ከ810ሺህ በላይ ተማሪዎች ወድቀዋል! በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን ከወሰዱ 845 ሺህ ገደማ ተማሪዎች መካከል፤ ወደ ዩኒቨርስቲ መግቢያ የማለፊያ ነጥብ ያመጡት ተፈታኞች ብዛት 27,267 ተማሪዎች አሊያም 3.2 በመቶዎቹ ብቻ መሆናቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ዘንድሮ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ 16,451 የማታ ተማሪዎች መካከል፤ ከ50 በመቶ በላይ ውጤት ያመጡት 12ቱ ብቻ መሆናቸውን ሚኒስቴሩ ገልጿል። እነዚህን አሃዞች ዛሬ ሰኞ መስከረም 28፤ 2016 በሰጡት መግለጫ ይፋ ያደረጉት፤ የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ናቸው። ፕሮፌሰር ብርሃኑ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ባለፈው ዓመት ከነበረው ጋር ሲነጻጸር “በጣም ከፍተኛ የሚባል መሰረታዊ ለውጥ የለም” ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል። የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል፤ 1,328ቱ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል። አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ማሳለፋቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 94.5 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ማሳለፋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። ለትኩስ መረጃዎችን የቴሌግራም ገፃችንን ይመልከቱ!👇 https://t.me/Gionamhara
نمایش همه...
ግዮን-አማራ

● ማስታወቂያ ለማሰራት እና ለማናቸውም ጥቆማዎች ካልዎት👇 ❝ @Haimonn @Haimonn ❞ ላይ ያድርሱን! 🟡የዩቱዩብ አድራሻችን:-

https://www.youtube.com/channel/UC-Er22UDSHJTvloM4UeyyVA

ግማሽ ያህሉ ትምህርት ቤቶች ምንም ተማሪ አላሳለፉም❗❗ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ካስፈተኑ 3,106 ትምህርት ቤቶች መካከል 42.8 በመቶ የሚሆኑት አንድም ተማሪ አለማሳለፋቸውን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ በሰጡት መግለጫ ይፋ አድርገዋል። አምስት ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ ማሳለፋቸውንም ሚኒስትሩ አስታውቀዋል። ሌሎች አምስት ትምህርት ቤቶች ደግሞ ለፈተና ካስቀመጧቸው ተማሪዎች ውስጥ 94.5 በመቶ በላይ የሚሆኑትን ማሳለፋቸውንም ጨምረው ገልጸዋል። 👉ከ50 በመቶ በታች ላመጡ ተማሪዎች የሪሚዲል ፕሮግራም ይኖራል ብለዋል።
نمایش همه...
ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በመግለጫቸው " 5 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል፡፡ " ብለዋል። ሌሎች 5 ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉ ገልጸዋል። ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦ 1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረማርቆስ) 2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት 3. ባህርዳር ስቴም ትምህርት ቤት 4. ሀይራንዚ አዳሪ ትምህርት ቤት (ስልጤ ዞን) 5. ሊች ጎጎ አዳሪ ትምህርት ቤት (ሀድያ) 6. ኦዳ አዳሪ ትምህርት ቤት (አዳማ) 7. ኮተቤ ሼርድ ካምፓስ 8. የኔታ አካዳሚ 9. ወላይታሊቃ አዳሪ ትምህርት ቤት 10. ቅዱስ ዮሴፍ ትምህርት ቤት
نمایش همه...
በስራኤልና ፍልስጤም ጦርነት የአለም ሚዲያዎች ወደ "breaking news" ዙረዋል እኛ ግን ለአፍታም "ከአማራ "ላይ አይናችን አንነቅልም።
نمایش همه...
ሀማስ ዛሬ በድንገት በከፈተው ጥቃት በርካታ እስራኤላዊያን ለሞት እና ለጉዳት ተዳርጓል። ከጥቃቱ በኋላ ጠቅላይ ሚንስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ እስራኤል በጦርነት ላይ ነች። የመጀመሪያ አላማችን ወደ ግዛታችን ሰርገው የገቡትን የጠላት ሃይሎች ማፅዳት እና ጥቃት ለደረሰባቸው ማህበረሰቦች ሰላም መመለስ ነው ብለዋል። ማንም በስህተት ይህን ጦርነት እንዳይቀላቀል ሌሎች ግንባሮችን ማጠናከር አለብን ሲሉ ኔታንያሁ ከጥቃቱ በኋላ ትዕዛዝ አስተላልፏል።
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.