fa
Feedback
Amhara forensic media

Amhara forensic media

رفتن به کانال در Telegram

ሰብስክራይብ subscribe አማራ ፎረንሲክ ሚዲያ ለእውነታዎች፣ ለእውነት እና ለፍትህ የቆመ https://www.youtube.com/@Amharaforensicmedia

نمایش بیشتر
1 349
مشترکین
+124 ساعت
-17 روز
-6730 روز
آرشیو پست ها
photo content

ህወሃት የራሱን ስትራቴጅካዊ ስሌት ይዞ አማራን አልወጋም፥ ኤርትራ ላይም አልዘምትም ሲል ቀመሩ ተዛባ። የአማራው የህልውና ትግልም በመካከል በፍጥነት ሌላ ደረጃ ላይ ደረሰ።ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ በአንድ እጁ እየተዋጋ በሌላኛው እጁ የራሱን ትግሉን የሚመራ ተቋም ፈጠረ።ይህ ሲሆን የጨዋታው መልክ ሙሉ በሙሉ ተቀየረ ማለት ነው። አብይ ግን እድሎች ከተገኙ አሁንም እዛው ጨዋታ ውስጥ መሆኑን እና ተስፋ አለመቁረጡን የሚያሳየው በተለይ ባለፉት ሶስት ወራት ውስጥ አማራውን ለመነጠል የሚያደርገው ሩጫ ነው። በዚህ መሃል አንዳንድ አውቀው የተኙ ወይንም በአሞሌ ጨው ራሳቸውን የሸጡ የኛን ወገኖች ሳይ "ሌላው ሁሉ ይቅር ይህ ሁሉ ሩጫና ግርግር አማራን ብቻውን አቁሞ ለማጥፋት በመመኜት የሚደረግ መሆኑን እንዴት ማወቅ ተሳናቸው ?" እላለሁ።ለዚህ እፍኝ እድሜስ ስንት አመት አሞሌ ይላሳል? በእኔ እምነት፦ የፕሪቶሪያ አፈራራሚዎች ዋና ግብ ፀረ-አማራ ብለው ያሰቧቸውን ሃይሎች አስተባብሮ እየተነሳ ያለው አዲሱ የአማራ አቢዮት መንፈስ ላይ ማዝመት ነበር።ለጊዜው አልተሳካም። እነዚህ ሃይሎች የአማራ ልዩ ሃይል እንዲፈርስ ለአብይ ቀጭን ትእዛዝ ሰጠዋል።ልዩ ሃይሉ ፈረሰ። ያም ሆኖ ያሰቡት ሳይሳካ እንዴውም የፈረሰው ልዩ ሃይል ለትግሉ ልዩ ግብአት ሆነ። ትንሽ ገፋ እና ደፈር አድርጌ ከደመደምሁ... የፕሪቶሪያው ስምምነት በራሱ "የአማራ ትንሳኤ" ፍርሃትና ድንጋጤ ውጤት ነው።አማራው ባይነሳ ኖሮ የፕሪቶሪያ ስምምነትም አይፈጠርም ነበር።ለዚህ ነው አንዳንድ ወገኖች የአማራው የህልውና ትግል የዘመናት ፍጅትና መጎሳቆል ውጤት መሆኑን ረስተው በፕሪቶሪያው ስምምነት ምክንያት የተፈጠረ ኩርፊያ የወለደው ሊያስመስሉት ሲሞክሩ ሲታይ አስቂኝና አስተዛዛቢ የሚሆነው።ፕሪቶሪያ የአማራን ትግል አልወለደም፥ የአማራ መነሳት ፕሪቶሪያን ወለደ እንጅ። ቆላም ነፈሰ ደጋ ጨዋታውን በደንብ ተጫውተናል። ።ስርአቱንም እንደተደገመበት ሰይጣን አፍዝዘን አስቀምጠነዋል። እጣፋንታውንም በምንወስደው ቀጣይ ሙሉ ለሙሉ ገፍቶ የመጣል እርምጃ ላይ እንዲወሰን አድርገነዋል። የዚህ ትብብር ስኬትና ውድቀት ግን የሚቀጥሉት ብዙ መቶ አመታት የእርስበርስ እልቂት ወይም ሰላምና ልማት ማለት ነው። በዚህ አጋጣሚ፦ ባለሃብት ነን የምትሉና ይህን ትግል ለማፍረስ በድለላ የተሰማራችሁ ወገኖች ተው።!---ከፀሃይ በታች የምትሰሩት እያንዳንዱ ስራ ይታወቃል።እንኳን ከህዝብ ከጎረቤት ተጣልቶ መኖር ይቸግራልና አስቡበት።አርፋችሁ ስራችሁን ስሩ። በዚሁ የፖለቲካ ድለላ ውስጥ የተሰማራችሁ አንዳንድ የሃይማኖት አባት ነን የምትሉ የየቤተ እምነቱ ሰዎችም ከዚህ ድርጊታችሁ ተቆጠቡ።ሌላው ቢቀር ቤተ እምነታችሁን ለሚያፈርስ ሃይል አካፋ አቀባይ አትሁኑ።ለምድርም ለሰማይም የማይሆን ነገር አትስሩ። በ80 አመታችሁ የሰላሳ አመት ጆሮ ጠቢን አትፍሩ።በውድቀታችሁ የጣላችሁትን ዘመንና ህዝብ ልናቃና ስንደክም ደንቃራ አትሁኑ።ትንሽ እንኳን እፈሩ። ለውዱ የአማራ ህዝብ! የአለምን መከራ ተሸክመሃል፥ እንድታልቅ ፍጅት ታውጆብሃል።ከዘመናት ሞት-ቀመስ እንቅልፍ በኋላ ተነስተሃል። ጠላትህ አቁስለህ የምትተወው አውሬ አይደለምና ሳትቀብረው እንዳትቀመጥ።ጠላት አንድነትህን በወንዝ ለመክፈል፥ በጎጥ ለመተልተል፥እየሰራ በመሆኑ በደምህ የገነባኸውን ቤት የሙጥኝ በል። እንደወትሮው ሁሉ በተለይ ደግሞ ከቅርብ ግዜ ወዲህ አብይ የሃይማኖት ግጭት ለመፍጠር እየሰራ በመሆኑ መዋደድህ የበለጠ መጠንከር ይኖርበታል። በየቀኑ የሚከፈለውን ዋጋ ባውቅም በነፃ ነፃ አይወጣምና አይዞህ በርታ! ለመላው የኢትዮጲያ ህዝብ‼️ ይህ እብድ ሰውዬና ቡድኑ በስልጣን ላይ እስካሉ ድረስ የማይጎሳቆል፥ የማይራብ፥ የማይታረዝና ህልውናው አደጋ ውስጥ የማይገባ ኢትዮጲያዊ አይኖርም። በኢትዮጲያ ምድር ላይ ቆሞ መራመድ እስከቻለ ድረስ መሬቱንም ህዝቡንም በግራም ሳይቀር እየለካ ከመሸጥና ከማጥፋት አይመለስም። ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይነሳ። ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ‼️ ዛሬ ከአብይ ጎን ቁሞ የሚገኝ ብሄራዊ ጥቅም ነገ ከቀጠናው የሚመነጭ ትልቅ ብሄራዊ ኪሳራን ያመጣባችኋልና ከእውነት፥ ከፍትህና ከነፃነት ሃይሎች ጎን ቁሙ። በተለይ አንዳድ ሃገራት አብይን መደገፍ አቁሙ።አብይ አማራን ሲፈጅ፥ የትግራይን፥ የኦሮሞን፥ የጋምቤላን፥ የሲዳማን፥ የጉምዝን፥ የቤኒሻንጉልን፥ የአፋርን፥ የሶማሊን፥ የጉራጌን በአጠቃላይ የሃገሪቱ ህዝብ ላይ እሳት ለኩሶ እያቃጠለ ቆሞ መመልከት ነገ አለም ቢጮህ የማይፈታው ቀጠናዊና አለም አቀፋዊ ምስቅልቅል ይፈጥራልና አስቡበት።ፍትህና ነፃነት ደንበር የላቸውም። እንደ ፀሃይ ለሁሉም መሆን አለባቸው። ለሚሊሻ፥መደበኛና አድማ ብተና ፖሊስ አባላት።---በራሳችሁ ፀብ ውስጥ የጠላት ዱላም ገላጋይም መሆን ታሪክ የማይረሳው ክህደት ነው። ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።ያለበለዚያ እጣ ፋንታችሁ አንደኛው ተራራ ስር ወይ አንዱ ጎዳና ላይ ደመ-ከልብ መሆን ነው።አሁንም ቢረፍድም አልመሸምና ወደ ወገኖቻችሁ ኑ።በኛ በኩል እንደ ወንድምና እንደ አባት እንቀበላችኋለን። ድል ለአማራ ህዝብ! ክፋት ለማንም፥ በጎነት ለሁሉም አዲስ ትውልድ፥ አዲስ አስተሳሰብ አዲስ ተስፋ! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! በጣም አመሰግናለሁ!!

√እንዴት ሰነበታችሁ!? እንኳን ለዚህ ቀን አበቃችሁ‼️እንኳን ደስ አላችሁ! ከፊታችሁ በመቆሜ ታላቅ ክብር ይሰማኛል‼️። ታሪክ የራሱ ነፍስና የራሱ ረቂቅ የስሌት ቀመር አለው። ከነመፈጠራቸው የማይተዋወቁ ሁለት ሰዎችን በራሱ ልብ መርምሮ፥ በራሱ ቀመር አንጥሮ ከየጥጉ ጎትቶ አምጥቶ ለአንድ ወርቃማ አላማ ሲል ያገናኛቸዋል። እናም ለብዙሃኑ እውነትና ነፃነት እንደጧፍ ያበሩ ዘንድ በፍቅር ያሰልፋቸዋል። ይበራሉ።በድቅድቅ ጨለማ መሃል የተስፋ ብርሃን የነፃነት ወጋገን ይሆናሉ።ይህ አስበው የማይዘልቁት የታሪክ ጥልቅ ምስጢር ነው።ታሪክ እኔንና እናተንም በዚህ ዘመን በዚሁ ስሌት ለአንድ ወርቃማ የትውልድ ፕሮጀክት አገናኝቶናል።ዛሬ እየታገልን ነው፥ነገ እናሸንፋለን።የአማራን ቀን እናመጣለን። በድጋሜ እንኳን ደስ ያላችሁ‼️ ህልውናችን እስካልተረጋገጠ ድረስ የዛሬ አምሳ አመት በዚህ ቦታ ላይ ሌላ አማራ ቆሞ፥ ሁልጊዜም ስለመሰልጠንና ስለመዘጋጀት አስፈላጊነት ሊናገር ይችላል።መደራጀታችን፥ መሰልጠናችን፥ መታጠቃችንና ለህልውናችን መታገላችን የሚቆመው ህልውናችን የተረጋገጠ እለት ብቻ ነው።ይህ የዛሬው የእናንተ ምርቃት የአማራ ህዝብ ትግልና የሃገሪቱ እጣፋንታ ተገፍቶ አንድ ጫፍ ላይ የቆመበት ምእራፍ ላይ የሚደረግ ነው። ስራ የሚጠይቅ የድል ታዛ ላይ የቆመ እጅግ አጓጊ ምእራፍ ነው ። ውድ ጓዶቼ በዚህ አጋጣሚ አደራ ልላችሁ የምፈልገው ብዙ ጉዳይ አለ፦ ዛሬ ለመመረቅ ላለፉት በርካታ ወራት ብዙ ወጣችኋል፥ብዙ ወርዳችኋል፥ ብዙ ላብ አፍሳችኋል። በአካልና በመንፈስ ጠንክራችኋል፥ የትግላችን ሀሁ እና ግብ ተገንዝባችኋል።በዚህ ሙሉ ቁመናችሁ መከላከያ የሚባል የአብይ አህመድ ታጣቂ ጋር ፊት ለፊት ትገጥማላችሁ። ትግል ግን ሌላም መልክ አለው። ከራስ ጋር የሚደረግ ትግልና አብሮ ሲኖር ከጓድ ጋር የሚደረግ ትግል እጅግ ከባድና ፈታኞቹ የትግል መልኮች እንደሆኑ ልትገነዘቡ ይገባል። ወደ አብይ አህመድ መተኮስና አብይን ማሸነፍ ቀላል ነው፥ ከባዱ ወደ ራስና ጓደኛ ድክመቶች ማነጣጠር ነው። አብይ በታንክና በድሮን ያልቻለውን ጦርነት በገንዘብ፥ በሽማግሌና በወሬ ሊያሸንፍ እየሞከረ ነው።አንዳንዴ ከሽህ የአብይ ታንከኛ አንድ ወሬኛ ትግላችን ላይ ጉዳት ሊያደርስ ይችላልና ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል።እንግሊዞች "ስራ ለፈቱ እጆች ሰይጣን ስራ ይፈጥርላቸዋል" ይላሉ።ብዙ ጊዜ የወሬና ሃሜት ምንጩ መቦዘን ስለሆነ እያንዳንዱን ደቂቃ ስለትግላችን በመድከምና በማሰብ እናሳልፍ። ታጋይ ወንድሞቼ ❗ ይህ በእናንተ ላብ፥በወንሞቻችሁ ደም እና በህዝባችን ሲቃ የተገዛ ትግል ነው። የአቢዮቱ ዘበኞች እናንተ ናችሁ።ስለዚህ ከፋፋይ፥ ለግልና ለቡድን ፍላጎት ብቻ የሚሰሩ መንፈሰ ደካሞች ቢገጥሟችሁ ናቋቸው፥ ታገሏቸው።ይህ ትግል የህልውና አደጋ ለገጠመው የአማራ ህዝብ የህልውና ጉዳይ ነው። የሚሳሱለት አይኖች፥ ሌት ተቀን የሚጠብቁት እጆች ይፈልጋል።እና አደራ!! ክፋትን፥ ምቀኝነትን፥ ቅናትንና ተንኮልን ተፀየፉ። ማንም የግለሰብም ይሁን የቡድን ጠላት አማራ ላይ ይነሳ መግጠምና መጣል እንችላለን። እነዚህ የመፈስ ደዌዎች ከተጠናዎቱን ግን ከጠላት ቀድመው እኛኑ ይጥሉናል።ፖለቲካችን ችላ ያለው ፥ያልተሄደበት መንገድ ቅንነት ነው።አለም ደጋግሞ የሚወድቀውም በዚህ ምክንያት ነው። በተንኮልና በክፋት በቦካ ፖለቲካ አለም የራሱን እጅ እየበላ ለጊዜው ይረካ ይሆናል እንጅ የትም አይደርስም። ይህ የመሳሪያም የቅንነትም አቢዮት ነውና ክፋትንና ተንኮልን ራቁ።የወንድምን ስኬት ውደዱ።ለሌሎች መኖርን ልመዱ።ራስ ወዳድ እንዳትሆኑ። ህዝባችን እያለቀ ራስ ወዳድ እንደመሆን ትልቅ ወንጀል የለም።ከፍ ባላችሁ ቁጥር የበለጠ ትሁት ሁኑ። ይህን የምላችሁ የአለም ፖለቲካ እንዴት እንደሚሰራና እንደሚሰራ የማላውቅ ቂል ሆኜ አይደለም፥ ይልቁንም በመደበኛ ፖለቲካው ውስጥ ያለው መደበኛ የቅጥፈት መንገድ ውጤቱ ውድቀት እንደሆነ የአለም ተሞክሮ በተለይ ደግሞ የራሳችን ልምድ ስለሚነግረኝ እንጅ። ይህ ትግል የህዝብ ትግል ነው። ይህ ትግል ለአማራ ህዝብ የሚደረግ ትግል ነው። መነሻችንም መድረሻችንም ህዝባችን ነው። ምድራዊዩ እግዜራችን ህዝብ ነው። ይህን እግዜር አይኑን መጠንቆል ያስቀስፋል። በስህተት እንኳን ህዝብን የሚያስቀይም ነገር አንዳትሰሩ። ክልክል ነው። ህዝብ እንኳን መብቱን ሰብል የለበሰ የእርሻ መሬቱን ስትረግጥበት፥ የቤት አጥሩን ስትደገፍበት አይወድም። ህዝብ "ፈጣሪያችን" ነውና እንቅስቃሲያችን ያያል፥ እስትንፋሳችን ይለካል።ጥንቃቄ እናድርግ። የአማራ ህዝብ የራሱ የሆነ ንፁህ ተቋም እንዲኖረው ብዙ ቀደምቶች ብዙ ደክመዋል።ታስረዋል፥ አካላቸውም ቅስማቸውም ተሰብሯል፥ህይወታቸውንም ሰጠዋል። በቀጠለ ጥረትና ብዙ ድካም በዚህ በኛ ዘመን ተሳክቷል። የአማራ ህዝብ የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄን ፈጥሯል።ይህ ተቋም መድህናችን ሆኖ ወደምንፈልገው ግብ ያደርሰን ዘንድ በየዘርፉ የተሳሉ ፖሊሲዎች አሉት።የተቋማችን የመጀሪያውና ቋሚው ፖሊሲያችን ራስን መቻል ነው። ሁሉን አቀፍ ራስ በቅነትን በየቀኑ ማሳደግ ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ድርጅታዊ ውስጣዊ አንድነታችን እናጠናክራለን። ራሱን ያልቻለ አንገት የሚያቅፈው የለውም።ስለዚህ የእዞች ውስጣዊ አንድነት፥ የድርጅታችን አፋብን ጠንካራ ውስጣዊ አንድነት እጅግ አስፈላጊ ነው።የህዝባችን አንድነት የመተንፈስ ያክል ፍፁም አስፈላጊ ነው።የተበተነ ህዝብ ነጥሎ የሚበላውን ጠላት ከየአቅጣጫው ይጋብዛልና። ሁለተኛውና ተያያዥ ፖሊሲያችን ከራስ መቻል ላይ የመነጨ ከሌሎች ጋር የሚደረግ የተመረጠ በጎ ትብብር ነው። የተሰላና የተጠና ትብብር ሁልጊዜ አስፈላጊ ነው። ጥቅምህን በሚስጢር ኪስህ ይዘህ ፥ የሌላን ወገን ጥቅም ሳትነካ፥ የራስህን ሳታስነካ መተባበር ሁሌም ልክ ነው። ስለዚህ በአጭርም በረጅምም እንተባበራለን።የቀጠናው ሃይሎችም ጋር ቀጠናዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ከጥቅማችን አኳያ እናብራለን። ፋኖ ልብ አለውም አላለውም የግዙፉና የውስብስቡ የምስራቅ አፍሪካ መልክአፖለቲካ አካል ሆኗል። ወይ ዋኝቶ ይወጣል ያለበለዚያ ግብግቡ በሚያስነሳው ማእበል ውስጥ ይሰጥማል።ግዙፉ ቁመናችን በስሌትና በጥበብ ታግዞ፥ የምላጭ ጠርዝ ላይ የመቆም ያክል ተጠንቅቆ ሌሎችን ሳይደፍቅ አሸናፊ ይሆናል። ከዚህ አኳያ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚስተዋለው ግርግር አማራን ብቻውን ለማቆም ነው።‼️ በእርግጥ ማንም ሃይል መተማመኛው የራሱ አቅም ነው።የማይሸሽ፥ የማይለወጥና የማይነቅዝ የራስ አስተማማኝ አቅም ነው።ይህም ሆኖ አማራ በአለም ፊት ቆሞ ብቻውን ገለባብጦ ተራራውን ሜዳ ፥ሜዳውን ተራራ እንዳላደረገ ሁሉ የአማራ ትግል "ተነጥሎ" የቆመ እለት ይከስማል የተባለ ይመስል ይህ ሁሉ ግርግር ፋኖን ብቻውን ለማቆም ነው። ከሶስት አመታት በፊት ሁሉም የጨዋታው ተሰላፊ የየራሱን ስሌት ይዞ በፕሪቶሪያ መድረክ ቢጫዎትም "በስምምነቱ" ውስጥ የነበረው የብዙዎች ተሰላፊዎች "ድብቅ" የጋራ ግብ ግን መቀጣጠል ጀምሮ የነበረውን የአማራ የአቢዮት እሳት በጋራ የማጥፋት እቅድ ነበር ብዬ አምናለሁ ። በዚህ " አደገኛውን ሰደድ የማጥፋት ተልእኮ" ውስጥ ህወሃትና ብልፅግና በደስታ አብረው እንደሚሰለፉ የፕሮቶሪያ ስምምነት "ሽማግሌዎቹም" እርግጠኞች ነበሩ ማለት ይቻላል። ምናልባት የትግራይ ሃይሎች ታሪካዊ ውሳኔ ወስነው ራሳቸውን ግሉል አድርገው ማቆማቸው እስኪታወቅ ድረስ በቀላሉ አማራን ጨፍልቀው ወደ ኤርትራ መሻገርና የየራሳቸውን ግብ ማሳካት እንደሚችሉ እርግጠኞች ነበሩ።ባልጠበቁት ሁኔታ

ሰበር ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ጀብደኛው 102ኛ ኮር የቀድሞው ዞብል አምባ ክፍለጦር የአሁኑ 12ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃና 3 ሻለቃ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት ፈፀሙ። የ102ኛ ኮር የጥንካሬ ምልክት የሆነው የ12ኛ ክፍለጦር ሰኔ 18/2018ዓ/ም በተለያየ አቅጣጫ የመጣውን የአገዛዙ ሰራዊት ቀለበት ውስጥ በማስገባት ደመሰሰ። የጨፍጫፊውና የአምባገነኑ ስርዓት ያለ የሌለ ሀይሉን በመያዝ ውጊያ የከፈተባቸው ቀጠናዎች በዞብልና በራማ በኩል በተለምዶ ፅሀይ መግቢያ ድረስ አሰላለፍ በማድረግ እንቅስቃሴ ያደረገ ቢሆንም የ12ኛ ክፍለጦር አናብስቶች በመልሶ ማጥቃትና መከላከል በሁሉም ግንባር ጥቃት በመፈፀማቸው በሽንፈት ተመልሷል። የ12ኛ ክፍለጦር 1ኛና 3ኛ ሻለቃ ረመጦች ከቀዩ ጋሪያ ቡኩ እስከ ጎቡ ጋሪያ በመዘርጋት በወሰዱት እርምጃ የጠላትን ሀይል ቀለበት ውስጥ በመግባቱ ከስናይፐርና መትረየስ አልሞ ተኳሾች የተረፈው ሙትና ቁስለኛውን ሳያነሳ ወደ መንደፈራ ቀበሌ እየፈረጠጠ ተመልሷል። ጠላት በዚህ አውደ ውጊያ የራሱን የሻለቃና የሻምበል አመራሮችን አስከሬን ሳያነሳ በመሸሹ ምን ያክል ጨካኝና ክብር የለሽ መሆኑን በገሀድ ያሳየበት ተራ የወንበደ ቡድን መሆኑን አሳይቷል። በተጨማሪ የቀድሞው ታጠቅ ክፍለጦር የአሁኑ 65ኛ ክፍለጦር የጠላትን የሀይል ሚዛን በማዛባት ሞርተር 82 በመጠቀምና ሻለቃዎችን ከኮባ ወደ ጎለሻና ዳልቻ በማስጠጋት ጠላት ባልጠበቀውና ባላሰበው ሁኔታ በመብረቃዊ ጥቃት በመመታቱ ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። የወገን 65ኛ ክፍለጦር ረመጦች ጠላትን አንዳንቀሳቀስ በማድረግ ከሀብሎ መንደር እስከ ጎቡ ጋሪያ በመዘርጋት ዋጋ አስከፍለውታል። በተመሳሳይ ሁኔታ የ102ኛ ኮር ቃኝ በዋልካ መንደር በኩል በመግባት አሰፍስፎ የመጣውን ጠላት አከርካሪ የሰበሩ ሲሆን እንድሁም የ101ኛ ኮር የ11ኛ ክፍለጦር 1ኛ ሻለቃ አናብስቶች ወንድሞቻቸውን በማገዝ በአርበኛ ጌታየ ከበደ እየተመሩ ወደ ጮቢ በርና ከላይ የተጠቀሰውን ቦታ በመሸፈን ታሪካቸውን በቀይ ቀለም ፅፈዋል። ጠላት 3 መድፍና አንድ ዙ=23 እንድሁም አንድ 120 ሞርተር በማሰለፍ ሆርማትና መንደፈራ ከባድ መሳሪያ በማስወንጨፍ ሙሉ አቅሙን የተጠቀመ ቢሆንም የ102ኛ ኮር ክንደ ብርቱዎቹን መቋቋም ባለመቻሉ ካለበት ቦታ እንዳይንቀሳቀስ በማድረግና የገባውን ሀይል አንዳይወጣ አድርገውታል። በመሆኑም የጠላት ግትልትል ሰራዊት በሁሉም አቅጣጫ ወደ ኋላ በመመለስ ወታደራዊ መረጃና ኦፒ የሌለው የብልፅግና መራሹ አምባገነኑ ስርዓት በግምትና በቸልተኝነት የከባድ መሳሪያ ድብደባ በማድረግ በአማራ ህዝብ ላይ በአድስ ቅኝና በጃሮታ ቀበሌዎች ላይ ግብሩ የሆነውን ጦርነቱ የማይመለከታቸውን 4 ሲቪል አርሶ አደሮች ህይወት ቀጥፏል። ከሞቱት ሲቪሎች መካከል የ80 አመቱ ሽማግሌ የ04 ጃሮታ ቀበሌ አቶ ጉብሳ ገብረ ሂይወትና ዘሀራ ኡመር የ8ዓመት ህፃን እንድሁም የ05 አድስ ቅኝ ቀበሌ አቶ ሙሀመድ ኩቢ 50 ዓመትና አለምነሽ እያሴ የ43 ዓመት እድሜ ያላቸው ንፁሀን ይገኙበታል። የአንድ ቤተሰብ አባል የአቶጉብሳ ገብረ ሂይወት ልጅ ድርብ ጉብሳ፣ ሙሉ ቢሰጠኝ እንድሁም የአቶ ሙሀመድ ኩቢ ባለቤትና ልጆች በሙሉ ከፍተኛ ቁስለኛ በመሆን በሞትና በህይወት መካከል ይገኛሉ። ጀብደኛው የ102ኛ ኮር በአርበኛ ጌታቸው መልኩና በአርበኛ ዘውዱ ዳርጌ ወታደራዊ አዛዥነት እንድሁም በአርበኛ በላይ መንግስቱና በአርበኛ ሻምበል ሞላ ማሩ ዘመቻ መሪነት እየተመራ ዛሬም በከፍታ ማማ ላይ እየበረረ ይገኛል። በመጨረሻም በዛሬው እለት በ12ኛ ክፍለጦር በዚህ አውደ ውጊያ የተገኙ የጥላት ንብረትና ኪሳራ በዝርዝር እንደሚከተለው እንገልፃለን 1ኛ. Ak ክላሽን ኮፍ መሳሪያ-----28 2ኛ. የክላሽ ጥይት ተተኳሽ-----670 3ኛ.የመትረየስ ጥይት ተተኳሽ-- 1834 4ኛ.የብሬን ሸንሸል-------------------6 5ኛ.የድሽቃ ጥይት ተተኳሽ---------434 5ኛ. አይኮም /icom ----------------1 6ኛ. ወታደራዊ ሻንጣ---------------38 7ኛ. ሬን ኮት/የዝናብ ልብስ---------42 8ኛ.ወታደራዊ የውሀ ኮዳ-----------32 9ኛ. F1 ቦንብ------------------ ---18 10ኛ.የተደመሰሰ የጠላት ሰራዊት--89 11ኛ.የተማረከ የጠላት ቁስለኛ ሰራዊት----60 መሆኑን እንገልፃለን። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 19/2018 ዓ.ም

photo content
+3

በራያ ቆቦ ቀጠና በ102ኛ ኮር በተሰነዘረ ጥቃት የአገዛዙ ሰራዊት ተመታ፤ ቃሊም፣ ቡሆሮ እና ሳንቃ ከተማ በፋኖ ቁጥጥር ሥር ዋሉ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር በሚንቀሳቀሰው የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ እና የ11ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አሃዶች በጥምረት በወሰዱት የተቀናጀ መብረቃዊ ወታደራዊ እርምጃ፣ ያለ የሌለ ኃይሉን አሰባስቦ ጥቃት ለመሰንዘር በሞከረው የአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ ሽንፈት ማድረሳቸው ታወቀ። ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም በተለያዩ አቅጣጫዎች ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ አድርጎ የነበረው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ጦር፣ በፋኖ አናብስቶች ብርቱ የመክቶ ማጥቃት እርምጃ ሙሉ በሙሉ ድባቅ ተመትቶ ወደ መጣበት እንዲመለስ ተደርጓል። የጨፍጫፊውና የአምባገነኑ ሥርዓት ጦር መነሻውን ጎብየ ከተማ በማድረግ በቡሆሮ፣ ቃሊም፣ ቀይ አፈር፣ አሰገዳና ወደ ጭራሮ አምባ መስመሮች ሰፊ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ለማድረግ የሞከረ ቢሆንም፣ በሁሉም ግንባሮች በተደረገው የተቀናጀና የተመጣጠነ አውደ ውጊያ የጠላት ኃይል መፈናፈኛ አጥቷል። ከአናብስቶቹ አፈሙዝ የተረፈውና ክፉኛ የተመታው የአገዛዙ ጦር የቆሰሉ ጓዶቹን እንኳ ሳያነሳ እግሬ አውጭኝ በማለት በየገደሉ እየተንከባለለ ወደ ወልዲያ እና ጎብየ ከተሞች በትናተን ለመፈርጠጥ ተገዷል። በቡሆሮና ቃሊም ግንባሮች በነበረው በዚሁ ከፍተኛ አውደ ውጊያ፣ የ49ኛ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ጀግኖች ከ11ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ ኃይሎች ጋር በመሰለፍ ጠላትን ሙትና ቁስለኛ በማድረግ በቀይ ቀለም አዲስ ታሪክ መጻፋቸውን የኮሩ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ አረጋግጧል። በዚህ ወሳኝ ውጊያ ማግሥት የ102ኛ ኮር መዋቅሮች ቃሊም፣ ቡሆሮ እና ሳንቃ ከተማን ጨምሮ ሰፊ ቀጠናዎችን ሙሉ በሙሉ በተደራጀ ሁኔታ በቁጥጥራቸው ሥር ማዋላቸው የተሰማ ሲሆን፣ ይህም ለአገዛዙ ወታደሮች መፈናፈኛ በማሳጣት የአማራ ሕዝብ ጥያቄ ፍጹም የፖለቲካ ጥያቄ መሆኑን ለብልጽግና ምስለኔዎች ትልቅ ትምህርት የሰጠ ክስተት እንደነበር የአካባቢው የአይን እማኞች በሰጡት ምስክርነት ገልጸዋል። የዕዙ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባወጣው ይፋዊ መረጃ መሠረት፣ መዳረሻው ድልና ነጻነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን በመግለጽ፣ "ሕልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" በሚለው መርህ መሠረት ትግሉ በድል አድራጊነት ወደፊት እንደሚገሰግስ በድጋሚ አረጋግጧል።

በወረኢሉ ወረዳ በ104ኛ ኮር እና 25ኛ ክፍለ ጦር በተጣለ ስልታዊ ደፈጣ አንድ የሻለቃ መሪን ጨምሮ ከአሥር በላይ የአገዛዙ ወታደሮች ተደመሰሱ! በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሥር በሚንቀሳቀሰው የ104ኛ ኮር ቃኝ እና የ25ኛ ክፍለ ጦር አንደኛ ሻለቃ ጥምረት፣ በወረኢሉ ወረዳ በጠላት ኃይል ላይ በወሰዱት የተቀናጀ መብረቃዊ ጥቃት ከፍተኛ ወታደራዊ ድል መቀዳጀታቸውን ዕዙ አስታወቀ። አገዛዙ ጥምር ጦር እያለ በሚጠራውና የአማራን ሕዝብ ለመጨፍጨፍ ስም በተሰጠው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ሰራዊት ላይ፣ የፋኖ አናብስቶች ስልታዊ ደፈጣ በመጣልና ስበው ወደ መግደያ ቀጠና በማስገባት የማያዳግም እርምጃ ወስደውባቸዋል። ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በወረኢሉ ወረዳ በወይብላ ማርያምና በቁልቢ ቦታዎች በተካሄደው በዚህ መብረቃዊ ኦፕሬሽን፣ መቶ አለቃ ፋንታው የተባለ የአገዛዙ የሻለቃ መሪን ጨምሮ ከአሥር በላይ የሰራዊት አባላት ሙሉ በሙሉ መደምሰሳቸው ተረጋግጧል። በዚህ ብርቱ ጥቃት ሳቢያ ከፍተኛ መደናገጥ የገጠመው የአገዛዙ ጦር፣ በርካታ የቆሰሉ ወታደሮቹን ተሸክሞ ወደ መጣበት አካባቢ በትናተን ለመፈርጠጥ መገደዱ ታውቋል። የ104ኛ ኮር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ባስተላለፈው ይፋዊ መግለጫ መሠረት፣ መዳረሻው ፍጹም ድልና ነጻነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አረጋግጧል። ሕዝባዊው ኃይል "ሕልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" በሚለው ጽኑ መርህ መሠረት፣ የአማራን ሕዝብ መብትና ደኅንነት ለማስከበር የጀመረውን ታሪካዊ ተጋድሎ አጠናክሮ ወደፊት እንደሚገሰግስም ዕዙ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

photo content

​#ጀመዶ_ማርያም_ገዳም! ​ጀመዶ ማርያም ገዳም በወሎ (በሰሜን ወሎ) ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ ርዝመቱ 15 ሜትር፣ ወርዱ 7 ሜትር፣ እንዲሁም አማካይ ከፍታው (ቁመቱ) 20 ሜትር በሚሆን ታላቅ ዋሻ ውስ
+2
​#ጀመዶ_ማርያም_ገዳም! ​ጀመዶ ማርያም ገዳም በወሎ (በሰሜን ወሎ) ውስጥ የሚገኝ ሲሆን፤ ርዝመቱ 15 ሜትር፣ ወርዱ 7 ሜትር፣ እንዲሁም አማካይ ከፍታው (ቁመቱ) 20 ሜትር በሚሆን ታላቅ ዋሻ ውስጥ በልዩ የሕንጻ ግንባታ ጥበብ የታነጸና በቅዱሳን ሥዕላት አሸብርቆ የሚገኝ ድንቅ ገዳም ነው። ​ይህ የዋሻ ገዳም ከወልዲያ ከተማ 70 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከምትገኘው የዋጃ ከተማ ተገንጥሎ፣ አስቸጋሪ የእግር መንገድ በሚጠይቀው በግዳን ወረዳ ውስጥ ይገኛል። እንደ ሃይማኖት አባቶች አባባልና ታሪክ ከሆነ ገዳሙ ከተመሠረተ 1,000 ዓመታትን አስቆጥሯል። ​የጀመዶ ገዳምን ካሸበረቁት ጥንታውያን ሥዕላት መካከል የገዳሟ ልዩ የክብር ምንጭ የሆነችውና በወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ እንደተሳለች የሚነገርላት፣ “ምስለ ፍቁር ወልዳ” (የተወደደ ልጇን የታቀፈች) በሚል መጠሪያ የምትታወቀው የቅድስት ድንግል ማርያም ሥዕል ናት። ​ጥቅምት 4 እና ግንቦት 1 ቀን በሚውሉት የገዳሟ ዓመታዊ የንግሥ ክብረ በዓላት ላይ ይህች የ“ምስለ ፍቁር ወልዳ” ሥዕል በመጋረጃ ተሸፍና፣ በሦስት ቀሳውስት በጥንቃቄ ተይዛና በዝማሬ ታጅባ ወደ ውጭ ትወጣለች። ለመቆሚያ በተዘጋጀው የሰጋጃ ምንጣፍ ላይ ስትደርስም መሸፈኛው ተገልጦ ሥዕሏ ለምዕመናን እንዲታይ ይደረጋል። በዚያን ጊዜም ምዕመናኑ ለሥዕለ “ምስለ ፍቁር ወልዳ” ያላቸውን ከፍተኛ ሃይማኖታዊ ክብር በደመቀ እልልታና በስግደት ይገልጻሉ።

የምኒልክ ዕዝን ከባድ ምት መቋቋም ያቃተው የብልፅግና አገዛዝ ሰራዊት በየቀኑ እየፈረሰ ፋኖን እየተቀላቀለ ይገኛል! ሰኔ 11/2018 ዓ.ም ብልፅግና ሥልጣኑን ይጠብቅለት ዘንድ የተመካበት ሠራዊት በመፍረስ አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክ/ጦር አትሮንስ ሬጅመንትን መዳረሻቸው አድርገዋል። የአማራ ህዝብን ለመከራና ሰቆቃ ለመዳረግ በዕብሪትና በማን አለብኝነት አማራን አንገት ለማስደፋት እና ለመጨፍጨፍ ወደ ጦርነት የገባው የኦህዴድ/ብልፅግና ቅጥረኛና ወንጀለኛ ቡድን በግድ ያግበሰበሰው ሠራዊት መኮብለልና መበተን የመጨረሻ አማራጭ የሌለው አማራጩ ሆኖ ቀጥሏል። የጦር ጠበብቶች ስብስብ የሆነውን ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር የተቀላቀሉ የአገዛዙ ሰራዊቶች፦ ✅ 50 አለቃ ሰማው አማረ......11ኛ ዕዝ 205ኛ ኮር 83ኛ ክ/ጦር ሻንበል መሪ ስናይፐር በመያዝ የተቀላቀለ ✅10 አለቃ ዳዊት ዳኛቸው............ከ19ኛ ክ/ጦር ✅መሠረታዊ ወታደር አማኑኤል አዲሴ.......ከ19ኛ ክ/ጦር ✅መሠረታዊ ወታደር ጥላሁን አማረ...........ከ19ኛ ክ/ጦር ወደ 105ኛ ኮር ገቢ የሆነ የጠላት መሳሪያ፦ ➥1 ጥቁር ስናይፐር ከነ ሙሉ ትጥቁ ➥3 ጥቁር ክላሽ ➥600 የክላሽ ተተኳሽ ➥9 የክላሽ ካዝና ➥2 የእጅ ቦንብ ➥ 3 የወገብ ትጥቅ 50 አለቃ ሰማው አማረ ስለ አገዛዙ ሀሳቡን ሲያስረዳ " የህዝብ ልጆች እንዳልሆን ሁሉ በህዝብ እንድንጠላ አድርጎናል። በሀገር መከላከያ ሠራዊት  የንፁሃን ቤት ሆን ተብሎ በከባድ መሳሪያ ተቃጥሏል፤ ሀብትና ንብረት ወድሟል።ከሚሰራው ግፍ አኳያ የተቋሙ አባል መሆንና መባል እጅግ በጣም አሳፋሪ ነው። መለያውን ለብሸ መታየት ያሳቅቀኛል። ሁሉም ተዋጊ ኃይል መውጣት ይፈልጋል፤ ጊዜና ምቹ ሁኔታ ብቻ ነው የሚጠብቀው። ሁሉም አባል በጥርጣሬ ነው የሚታየው፤በተለይ አማርኛ ተናጋሪ የሆነ ወታደር መታሰር መፈታት የዕለት ተዕለት እጣ ፋንታችን ነበር"ብሏል። መከላከያ አባላቱ ፋኖን ሲቀላቀሉ የ105ኛ ኮር ም/ዘመቻ ኃላፊው አርበኛ ጎሹ ታረቀና የአትሮንስ ሻለቃ አመራሮችና አባላት ደማቅ አቀባበል ያደረጉላቸው ሲሆን በተደረገላቸው አቀባበልም ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ47ኛ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃውን አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 11/2018ዓ.ም

photo content
+4

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ  የ106ኛ ኮር 31ኛ ክፍለ ጦር በከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን እጅን በአፍ የሚያስጥል ጀብድ ተፈፅሟል!! ሰኔ 4/2018 ዓ/ም በቀትር ጠራራ  የ31ኛ ክፍለ ጦር አባል የሆነው ፋኖ ገንዘብ አስፌ በፀሀይ መውጫ ከተማ ሰርጎ በመግባት የብርሀኑ ጁላ የመከላከያ ሰራዊት አመራርን ሲደመስስ፤ አንድ ሻምበል መሪ ማርኳል። በዚህ የከተማ ኦፕሬሽን    *02 ጥቁር ክላሽ    *01 የጦር ሜዳ ሬድዮ    *01 መጠባበቂያ የሪድዮ ባትሪ እና    *01 የመከላከያ አባል ተማርኳል። ከአካባቢው በተጣራ መረጃ የተደመሰሰው የመከላከያ አመራር ከፍተኛ የብርሀኑ ጁላ ማዕረግተኛ መሆኑ የተረጋገጠ ሲሆን በቀሪ የጁላ የጦር አመራሮች ላይ ከፍተኛ ፍርሀትና ስጋት ተፈጥሮ ጠለላቸው ጋር ሳይቀር ጥል እየፈጠሩ መሆኑ ታውቋል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ አመራራቸው የተደመሰሰባቸው የመከላከያ ሰራዊቶች ከፍተኛ ተቃውሞ በማንሳት "ከአማራ ክልል አስወጡን" ከህዝብ ጋር አጋጥማችሁ ህዝቡ እንዲጨርሰን አታድርጉን፣ መቼ ነው ጠረፍ ሂደን ለሀገራችን የምንሞተው? ለፖለቲካ መሞትም ሆነ መቁሰል አምስት አመት ውስጥ ሰልችቶናል በማለት ከፍተኛ ተቃውሞ ፈጥረዋል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ  የ106ኛ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 05/2018 ዓ/ም https://t.me/fanoairforcemedia https://t.me/fanoairforcemedia

ዋግኸምራ ምድር ሐሙሲት ግምባር 303ኛ ኮር 14ኛ ክፍለጦር በጠላት ላይ ታላቅ ድል ተቀዳጁ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ኮር 14ኛ ክፍለጦር አካል የሆነችው ሁለተኛ ማንኩሽ ሻለቃ በዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን መቀመጫ ሰቆጣ ከተማ በስተደቡብ ምስራቅ 35 ኪሎ ሜትር ርቀት ከምትገኘው ሰቆጣ ዙሪያ ወረዳ ሐሙሲት ከተማ ላይ በመግባት ታላቅ ጀብዱ ፈፅመዋል። ሰኔ 05 ቀን 2018 ዓ/ም ከንጋቱ 10:00 ሰዓት እስከ ረፋዱ 4:00 ሰዓት በተደረገ የደፈጣና ሽምቅ ውጊያ ዙሪያውን ከበባ በማድረግና በማፈን እንዲሁም መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም በአገዛዙ ሚሊሻ አባላትና ራሳቸውን ስምረት ብለው በሚጠሩ በጌታቸው ረዳ የሚመሩ ኃይሎች ላይ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ኪሳራ በማድረስ በጠላት ላይ ድል ተጎናፅፈዋል። ራሱን ስምረት ብሎ የሚጠራው ኃይልም ሞርታር-82 ወደ ሐሙሲት ከተማ ሁለት ጊዜ በማስወንጨፍ ንፁሃንን የጨፈጨፈ ሲሆን በተወረወረው ቅምቡላ ስድስት ንፁሃን ውድ ህይወታቸውን ሲያጡ ከአስራ አምስት በላይ ንፁሃን ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው እና ወደ ሰቆጣ ሆስፒታል ሪፈር እንደተባሉ የአይን እማኞች መረጃውን አድርሰዋል። በተደረገው አውደ ውጊያ 15 ተደምስሶ፣ ሰድስት ሲቆስል፣ ሁለት ሚሊሻ ተማርኳል ፤ እንዲሁም ሁለት ጂምስሪ(GM-3)፣ አንድ ኤምፎርቲ(M-40) እና ዘጠኝ ክላሽንኮፍ በመማረክ ወደ ክፍለ ጦሩ ካዝና ገቢ መደረጉን የ14ኛ ክፍለ ጦር ቃል አቀባይ አርበኛ ሐብቱ ማሞ (ራስታው) አስታውቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ አርበኛ ቢሆነኝ ቢያበይን መረጃውን አድርሷል! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሰኔ 05/2018 ዓ.ም

በምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 23ኛ ክፍለ ጦር አምባሰል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ! መነሻዉን ከኩታበር ወደ ተለያዬንና ዚሃ እንዲሁም ከደላንታ በተሬ አድርጎ ወደ ዚሃ  በምድር ሞርተር ፣ዙ23 እና መድፍ ሲጠቀም በሰማይ በሁለት ድሮን ታግዞ  ፋኖን አጠፋለሁ በሚል የተለምዶ ቅዠቱ የመጣ ቢሆንም ጀግኖቹ ምንም ነገር ሳይበግራቸዉ እንደቃሪያ ሲያራግፉት ዉለዋል። ዉጊያዉም  ከንጋቱ 11:00 እስከ 6:00 የተደረገ ሲሆን በዚህ እልህ አስጨራሽ ውጊያ የ104ኛ ኮር 23ኛ ክ/ጦር ተናዳፊወች  ዚሃ የገባውን ሃይል ሙሉ ለሙሉ የደመሰሱት ሲሆን በዚህ የተበሳጨዉ  አገዛዝ በዘፈቀደ ሶስት ጊዜ ድሮን በመጣል ከጦርነቱ ተሳታፊ ያልሆኑ ንፁሀንን የጥቃቱ ሰለባ አድርጓል። አሁን ላይ በድሮን ሽፋን በመስጠት ሬሳና ቁስለኛ እያነሳ ሲሆን ከግሸን በአባላ ለመቁረጥ ቢቀሳቀስም በንስሮቹ በደፈጣ ተመቶ ሙትና ቁስለኛውን ይዞ ወደ መጣበት ተመልሷል። ©በአፋብን ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል!

https://youtu.be/hXVhxD82Ocw ቤተሰብ ይሁኑ subscribe

"በ1965 አፄ ኃይለሥላሴ ወሎን ጎበኙ አሉ። በቀጣይ ዓመት ከሥልጣን ተባረሩ። በ1980ዎች መጀመሪያ ደግሞ መንግሥቱ ኃይለማርያም ወሎን ጎበኘና በ83 ላይ ወደ ዚምባብዌ ተሸኘ አሉ። በ2002 ላይ አቶ መለስ ዜናዊ ወሎን ጎበኙና እግረ መንገዳቸውን በነካ እጃቸው በ2004 ላይ ሰማይ ቤትን ጎበኙ አሉ። በ2009 ላይ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ወሎን ጎበኙና በ2010 ላይ በገዛ ፈቃዳቸው ሥልጣን ለቀቁ አሉ። አብይ አህመድ ወሎን እየጎበኘ ነው ተረኛ ነው

ከአፋብን ምኒልክ ዕዝ የተሰጠ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ! በአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየፈፀመ ያለው የብልፅግና አገዛዝ ነውሩን ለመሸፈንና በዋናነት የአዲስ አበባን ዲሞግራፊ ለመቀየር እየተጠቀመበት ያለውን የኮሪደር ልማት ሌሎች አካባቢዎችም ላይ ለማስመሰል እየሰራ ያለ መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን በዚህም ኮሪደር ልማት ለመመረቅ በሚል አብይ አህመድ ወይም ምክትሉ ተመስገን ጥሩነህ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም ወልድያ ከተማ እንደሚመጡ ለማረጋገጥ ችለናል! በዚሁ በዕለተ ማክሰኞ ሰኔ 02/2018 ዓ.ም ወልድያ ከተማ ሊካሄድ ለታሰበው አማራ ላይ እየተፈፀመ ያለውን "ዘር ማጥፋት" ትኩረት መንፈጊያ የብልፅግና ዝግጅት ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የሃገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ግለሰቦችና እንዲሁም አንዳንድ ቲክታከሮች ልትገኙ ጥሪ እንደተደረገላችሁ መርሃ ግብሩን የሰሜን ወሎ ዞን እና የወልድያ ከተማ አስተዳደር የውስጥ አርበኞች አድርሰውን ለማወቅ ችለናል! በመሆኑም የአማራ ህዝብ ላይ ዘር ማጥፋት እየተፈፀመ ባለበት በዚህ ጊዜ እንዲሁም ሰሞኑን ኦሮሚያ የአርሲ ኦርቶዶክሳዊያን በግፍ በታረዱበትና በተጨፈጨፉበት አሁንም ታቦት ተሸክመው ስደት ላይ ባሉበት ነባራዊ ሁኔታ የሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት እና የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተ-ክህነት የኃይማኖት አባቶች ምዕመናንን ገዳይ አሰማርቶ እያስጨፈጨፈ እና እየጨፈጨፈ ያለዉ የአገዛዙ ድግስ ላይ ባለመገኘት አባታዊ ግዴታችሁን  እንድትወጡ ስንል ጥብቅ መልዕክት እናስተላልፋለን። ከዚህ ውጭ ግን አለማዊ ህይወት ላይ ያሉ አርቲስቶች ሳይቀሩ አርሲ ላይ በግፍ ለታረዱና ለተጨፈጨፉ ወገኖቻቸው ቅድሚያ በመስጠት የአዲስ አበባው የብልፅግና የሙዚቃ ድግስ ላይ ባልተገኙበት ሁኔታ መሃል ወልድያ ከተማ በህዝባችሁ መካከል ሆናችሁ ይህንን የማታደርጉና ቀላል የሚባለውን መስዋዕትነት የማትከፍሉ ከሆነ የኃይማኖት ልጆቻችሁን በግፍ እያረዱና እየጨፈጨፉ ካሉት የብልፅግና ሹማምንቶች ለይተን እንደማናያችሁ ልናሳውቃችሁ እንወዳለን። በመጨረሻም ከላይ በዝርዝር ለተገለፃችሁ አካላቶች እንዲሁም ለወልድያ ከተማ እና አካባቢው ማህበረሰባችን በዕለተ ማክሰኞ በገበያ ቀናችሁ የሚወጣውንም ህዝብ ለድግሳቸው ለመጠቀም ሲባል ገዳያችን ብልፅግና ባዘጋጀው "የሃገሩ ሰላም ነው እና ልማት ነው!" የሚል ህዝብ ማታለያና ማጭበርበሪያ ዝግጅት ላይ እንዳትገኙ ስንል መልክታችንን እያስተላለፍን ይህንን ተላልፎ በተገኘ ማንኛውም አካል ላይ ግን  ገዳይ እና አስገዳይ ከሆነው አገዛዝ ለይተን እንደማናየዉ እና በተናጠልም ይሁን በቡድን ለምንወስደው እርምጃ ሃላፊነት የማንወስድ መሆኑን ከወዲሁ ጥብቅ መልክታችንን እናስተላልፋለን! ህልውንችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ግንቦት 30/2018ዓ.ም