cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

⟣฿Ⱡ₳₵₭ ⱠØVɆⱤƧ╣😘😘😘😘

ᣜɴᴇᴡ ᴘɪᴄᴛᴜʀᴇꜱ ᴡɪʟʟ ᴘᴏꜱᴛ ʜᴇʀᴇᣲ ᣜQᴜᴏᴛᴇꜱ ᴀɴᴅ ᴍᴇᴍᴇꜱ ᴀʟꜱᴏ ꜰɪɴᴅ ʜᴇʀᴇᣲ ᣘᴀʙꜱᴏᴜʟᴇᴛʟʏ ᴇᴠᴇʀʏ ᴛʜɪɴɢ ʏᴏᴜ ᴡᴀɴᴛ ɪᴛ ɪꜱ ʜᴇʀᴇ ᳕☻⭛ ꜰᴏʀ ᴀɴʏ ᴄᴏᴍᴍᴇɴᴛ @shainyy5 @DELETED_ACC_OUNT

نمایش بیشتر
أثيوبيا10 414امهری8 624دسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
189
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የጠቢቡ ሰሎሞን ፍርድ ሦስት ነጋዴዎች ድንገት አንድ ቀን በንጉሥ ሰሎሞን የዘውድ ችሎት ተገኙ፡፡ ሦስቱም ለብዙ ዘመን አብረው ለመነገድ ተማምለው፣ ግመል ጭነው፣ ገንዘብ ቋጥረው፣ ስንቅ አንጠልጥለው፣ ሀገር ጥለው የሄዱ ናቸው፡፡ ‹ንጉሥ ሆይ› አለ አንዱ በዙፋኑ ፊት እጅ ነሥቶ፡፡ ‹እኛ አብረን ለመነገድ ተስማምተን መንገድ የጀመርን ጓደኛሞች ነን› አለ፡፡ ሁለተኛውም ነጋዴ ተቀብሎ ‹ቃላችንንም አክብረን ለንግድ ሩቅ ሀገር ስንጓዝ ድንገት የሰንበት በዓል ደረሰብን› ሲል ቀጠለ፡፡ ሦስተኛውም ነጋዴ ‹ሰንበትን አክብረን ለመዋል ስለፈለግንም ድንኳን ከተከልንበት ቦታ ራቅ አድርገን ጉድጓድ ቆፍረን ገንዘባችንን በከረጢት ቀበርነው፡፡ ከመካከላችን ማናችንም ገንዘቡን ተደብቀን ላንወስድ መሐላ ፈጽመን ነበር፡፡ በማግሥቱ ግን ወደ ጉደጓዱ ሄደን ስንቆፍረው ገንዘባችንን አጣነው› አለና አስረዳ፡፡ የመጀመሪያው ነጋዴም አንገቱን ከነቀነቀ በኋላ ‹ንጉሥ ሆይ ጉድጓዱን ስንቆፍርም ሆነ ገንዘቡን ስንደብቅ ሌላ ሰው ያየን የለም፡፡ ከሰረቅነው እኛው ነን፡፡ ነገር ግን ማናችን እንደሰረቅን ልንተማመን አልቻልንም› አለ፡፡ ንጉሥ ሰሎሞን በልቡ ‹መስረቅ የቻለ ሰው መዋሸትና መሐላን ማፍረስ አያቅተውም› ብሎ አሰበና ነገሩን ቀለል አድርጎ ‹ነገ ተመልሳችሁ ስትመጡ ማን እንደሰቀረው እነግራችኋለሁ› ሲል አሰናበታቸው፡፡ በማግሥቱ ሦስቱ ጓደኛሞች መጡ፡፡ ችሎቱም ተጀመረ፡፡ ንጉሥ ሰሎሞን ‹የእናንተን ጉዳይ ከመመልከቴ በፊት ሦስታችሁም ጠቢባን መሆናችሁን ማወቅ እፈልጋለሁ፡፡ በመሆኑም በሚከተለው ታሪክ ላይ ያላችሁን አስተያየት እንድትሰጡ እፈልጋለሁ፡፡ ነገሩ እንዲህ ነው፡- አንዲት ሴትና አንድ ወንድ ከልጅነታቸው ጀምሮ አብረው እየተማሩና እየተጫወቱ አደጉ፡፡ ወደፊት ትልቅ ሰው ሲሆኑ ተጋብተው አብረው ለመኖር ቃል ተግባቡ፡፡ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የኑሮ መሥመር አለያያቸውና በተለያዩ ቦታዎች መኖርና መሥራት ጀመሩ፡፡ በዚህ መካከልም ሴቷ ቃል ኪዳንዋን ረሳችውና ሌላ ባል አገባች፡፡ ጋብቻው በተፈጸመበት ቀን ማታ የገባቺው ቃል ኪዳን ትዝ አላት፡፡ ደነገጠች፡፡ ነገሩን ለባልዋ ነገረቺው፡፡ ባልዋም ለቃል ኪዳን ትልቅ ቦታ የነበረው ሰው ነበርና ‹በይ ተነሺ ቃል የገባሺለትን ሰው እንፈልገው፤ ስናገኘውም ቃል ኪዳኑን ማፍረሳችንን ነግረነው፣ የገንዘብ ካሣም ከፍለነው ይቅርታ ያድርግልን፡፡ ያለበለዚያ ትዳራችን ይበላሻል› አላት፡፡ ሁለቱ አዲስ ተጋቢዎች ልጁ ይገኝበታል ወደሚባለው ቦታ ሩቅ መንገድ ተጉዘው አገኙት፡፡ የሆኑትንም ነገር ሁሉ ገለጡለት፡፡ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው፣ ገንዘቡን እንዲቀበላቸው ለመኑት፡፡ ልጁ ቀና ሰው ስለነበር ይቅርታ አደረገላቸው፡፡ ‹ያልሠራሁበትን ገንዘብ አልቀበልም› ብሎ ገንዘቡን ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆነም፡፡ እነርሱም አመስግነውት ተመለሱ፡፡ ሲመለሱ በመንገድ ላይ አንድ ዘራፊ አጋጠማቸውና የያዙትን ገንዘብ ነጠቃቸው፡፡ ልጂቱም ገንዘቡ በምን ምክንያት እንደተያዘ ታሪኩን እያለቀሰች ለዘራፊው ነገረቺውና እንዲመልስላቸው ለመነቺው፡፡ ዘራፊውም በታሪኩ ተደንቆ የወሰደውን ገንዘብ መለሰላቸው፡፡ ንጉሥ ሰሎሞን ይህን ታሪክ ከተረከ በኋላ ‹ከባልየው፣ ከሚስቱ፣ ከቀድሞ ወዳጇና ከዘራፊው የትኛው ሰው የበለጠ ምስጋና ይገባዋል ብላችሁ ታስባላችሁ?› ሲል ጠየቃቸው፡፡ የመጀመሪያው ነጋዴም ‹ለእኔ የበለጠ ምስጋና የሚገባት ሴቲቱ ናት፡፡ ቃል ኪዳንዋን አስታውሳ ይቅርታ ለመጠየቅ መነሣቷ ያስመሰግናታል› ሲል ሐሳቡን ሰጠ፡፡ ሁለተኛው ነጋዴም ‹ለእኔ ግን የበለጠ ምስጋና የሚገባው ባልዋ ነው፡፡ ምክንያቱም ሚስቱ ቃል ኪዳንዋን ማፍረሷን ስትነግረው ቃልዋን ተቀብሎ፣ ቤት ንብረቱን ትቶ፣ ገንዘቡን ይዞ ወደ እጮኛዋ ዘንድ መሄዱና ይቅርታ መጠየቁ ያስመሰግነዋል› ሲል አስተያየቱን ሰጠ፡፡ ሦስተኛውም ነጋዴ ‹ባልና ሚስቱ ያደረጉት ነገር የሚገርምና የሚያስመሰግን ነው፤ ነገር ግን የቀድሞ እጮኛዋ ሞኝ ሰው ነው፤ ገንዘቡን መቀበል ነበረበት› ሲል ሐሳቡን ለገሰ፡፡ ንጉሥ ሰሎሞንም ሐሳባቸውን ከሰማ በኋላ ሦስተኛውን ነጋዴ ‹ገንዘቡን የሰረቅከው አንተ ነህ› አለው፡፡ ሰውዬውም ደነገጠና ወደ ንጉሡ ተመለከተ፡፡ ንጉሥ ሰሎሞንም ‹ያልደከመበትን ገንዘብ የሚመኝ አእምሮ ባይኖርህ ኖሮ ያንን ልጅ ሞኝ አትለውም ነበር፡፡ አስተሳሰቡ ከሌለ ድርጊቱ አይመጣም፡፡ አንተ ውስጥ ተጣምሞ የበቀለ ነገር አለ፡፡ ሁለቱ ጓደኞችህ ታማኝነትን ዋጋ ሰጥተውታል፤ አንተ ግን ለታማኝነት ዋጋ አልሰጠኸውም፡፡ ስለዚህ ካንተ በቀር ይህን ሊያደርግ የሚችል ሰው የለም፡፡ የአንተን አእምሮ ሳየው የተሠራበትን ነገር አየሁት፡፡ አእምሮ ሲሰጠን ተሠርቶ አልተሰጠንም፡፡ እንዲሠራ ተሰጠን እንጂ፡፡ ሰው በርስቱ ላይ እንዴት ያለ ቤት እንደሚሠራ መወሰንና ቤቱን መገንባት የእርሱ ድርሻ ነው፡፡ የሚጠቀመው ዕቃ የሚገነባበትም መንገድ የቤቱን ጥንካሬ ይወስነዋል፡፡ አእምሮም እንዲሁ ነው፡፡ በሕግ፣ በምግባር፣ በትምህርት፣ በጥበብ፣ የተገነባ አእምሮ ያንተን ዓይነት አስተሳሰብ አይኖረውም፡፡ አሁን የሰጠኽው ሐሳብ ያሳለፍከውን ሕይወት፣ የተዘራብህን ዘርና የተሠራህበትን ነገር አሳይቶኛል፡፡ ወላጆችህን አየኋቸው፤ ጓደኞችህን አየኋቸው፣ መምህሮችህን አየኋቸው፡፡ እነዚህ ሁሉም ወይም ከእነዚህ አንዱ የዘራብህ ዘር ትክክል አይደለም፡፡ ምናልባትም ይህ ዘር ባንተ ላይ መዘራቱን አታውቀው ይሆናል፡፡ ግን ተዘርቶብሃል፡፡ ‹አንድ ታሪክ ልንገራችሁ› አላቸው ጠቢቡ ሰሎሞን፡፡ እንዲቀመጡ ተፈቀደላቸው፡፡ ሁሉም ሌባውን ያወቀበት መንገድ አስደንቋቸዋል፡፡ ምንጣፍ ላይ ቁጭ አሉ፡፡ አንድ ቀን አንድ ልጅ እኔ ዘንድ ለፍርድ ቀረበ፡፡ የመጣው አባቱን ገድሎ ነው፡፡ ታዳሚዎች ሁሉም ‹አባቱን የገደለ ፈጽሞ ይሙት ይላልና ይገደል› ብለው ወሰኑበት፡፡ እኔ ግን ይህንን ነገር ያደረገበትን ምክንያት ለመረዳት ስለፈለግኩ ጠየቅኩት፡፡ ነገሩም እንዲህ ነበር፡፡ አንድ አባት ልጁን ሁል ጊዜ አንድ ነገር ያስተምረዋል፡፡ ጓደኞቼ መቱኝ ሲለው ‹በላቸው› ይለዋል፡፡ ፍየሉ ወጋኝ ሲለው ‹በለው› ይለዋል፡፡ ዕንቅፋት መታኝ ሲለው ‹በለው› ይለዋል፡፡ የአባቱ መፍትሔ ሁልጊዜ ‹በለው› ብቻ ነበር፡፡ ልጁ በዚህ ትምህርት ነበር ያደገው፡፡ አደገ፡፡ ጎለመሰ፡፡ ፈረጠመ፡፡ ያገኘውን ሁሉ እየደበደበ፡፡ አንድ ቀን የአባቱን በጎች ወስዶ አባቱ ሳይፈቅድለት ሸጠና መጣ፡፡ አባቱ ለምን እንደሸጠ ሲጠይቀው ‹ገንዘብ ያስፈልገኛል› አለው፡፡ አባቱ ተናደደና በበጎች መጠበቂያ ጅራፍ መታው፡፡ ያን ጊዜ ልጁ ድንጋይ አንሥቶ እንደ ቃየል አባቱን አናቱን መትቶ ገደለው፡፡ ልጁን ለምን አባቱን እንደገደለ ስጠይቀው ‹አባቴ ያስቸገረኝን ሰው ሁሉ እንድመታ አስተምሮኛል፡፡ አባቴም ስላስቸገረኝ መታሁት፡፡ ለመሆኑ ከመምታት በቀር ምን ማድረግ እችል ነበር?› ሲል ጠየቀኝ፡፡ ይህ ልጅ ሌላ ነገር አልተማረምና ያደረገው የተማረውን ነው፡፡ ሰው የትምህርቱ ውጤት ነውና› አለው፡፡ ሰውዬውም በነገሩ ተገርሞ ገንዘቡን መለሰ ይለናል ሚድራሽ የተባለው የአይሁድ የትውፊት መጽሐፍ፡፡ ይህንን ታሪክ ሳነብ ዛሬ በልጆቻችን ኅሊና እየገነባን ያለነው የዘረኛነትና የጠባብነት፣ የጽንፈኛነትና የአምባገነንነት ጡብ ይታወሰኛል፡፡ እያንዳንዳችን ለሌላው ብለን የምናስታጥቃቸው ነገር አፈሙዙ ወደራሳችን ሊዞረን እንደሚችል ያሰብንበት አልመሰለኝም፡፡ የተጣመመ ሐሳብ እያሰጠን፣ የተጣመመ ትውልድ አፍርተን የተስተካከለች ሀገር አንደመመኘታችን ያለ ሞኝነት ከወዴት ይገኛል? https://t.me/HiMSELEM
نمایش همه...
⟣฿Ⱡ₳₵₭ ⱠØVɆⱤƧ╣😘😘😘😘

ᣜɴᴇᴡ ᴘɪᴄᴛᴜʀᴇꜱ ᴡɪʟʟ ᴘᴏꜱᴛ ʜᴇʀᴇᣲ ᣜQᴜᴏᴛᴇꜱ ᴀɴᴅ ᴍᴇᴍᴇꜱ ᴀʟꜱᴏ ꜰɪɴᴅ ʜᴇʀᴇᣲ ᣘᴀʙꜱᴏᴜʟᴇᴛʟʏ ᴇᴠᴇʀʏ ᴛʜɪɴɢ ʏᴏᴜ ᴡᴀɴᴛ ɪᴛ ɪꜱ ʜᴇʀᴇ ᳕☻⭛ ꜰᴏʀ ᴀɴʏ ᴄᴏᴍᴍᴇɴᴛ @shainyy5 @DELETED_ACC_OUNT

https://t.me/HiMSELEM​#ፈጣሪ_አህያን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው…. አህያ ትሆናለህ፡፡ ሸክሞችን በጀርባህ በመሸከም ፀሐይ ወጥታ እስክትጠልቅ ድረስ ያለመታከት ትሰራለህ። የምትመገበው ደግሞ ሳር ነው፡፡ ምንም አይነት ኢንቴለክት(የማሰብ፣የማመ ዛዘን ችሎታ) የለህም፡፡ እናም 50 ዓመት ትኖራለህ፡፡ አህያው እንዲህ ሲል መለሰ… አህያ እሆናለሁ ችግር የለውም ነገር ግን 50 ዓመት በጣም ብዙ ነውና ሃያውን ብቻ ስጠኝ፡፡ እግዚያብሔርም የፍላጎቱን ሰጠው፡፡ #ፈጣሪ_ውሻን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው…. የሰውን ልጅ ቤት ትጠብቃለህ፡፡ የሰው ልጅም እውነተኛ ጓደኛ ትሆናለህ፡፡ ከጌታህ የሚጣልልህን ፍርፋሪ ትመገባለህ፡፡ እናም 30 ዓመት በሕይዎት ትኖራለህ፡፡ ውሻም ትባላለህ፡፡ ውሻው ሲመልስ… ጌታየ 30 ዓመት እጅግ ብዙ ነው አስራ አምስቱ ዓመት ይበቃኛል አለ፡፡ ፈጣሪም የፍላጎቱን ሰጠው… #ፈጣሪ_ዝንጀሮን_ፈጠረና_እንዲህ_አለው…. ዝንጀሮ ትሆናለህ፡፡ በዛፎች ቅርንጫፍ ወዲያና ወዲህ እየተንጠላጠልክ ትርኢት ትሰራለህ፡፡ በድርጊትህም አስገራሚ ትሆናለህ እናም 20 ዓመት ትኖራለህ፡፡ ዝንጀሮው ሲመልስ… ሃያ ዓመት መኖር በጣም ብዙ ነውና አስሩ ብቻ ይበቃኛል አለ፡፡ ፈጣሪም የሚኞቱን ሰጠው፡፡ #በመጨረሻም_ፈጣሪ_ሰውን_ፈጠረና|እንዲህ አለው…. የሰው ልጅ ትባላለህ፡፡ በምድር ላይ ካሉት ፍጡራን አመዛዛኝ፣ አሳቢና ምክኒያታዊ ፍጡር አንተ ብቻ ነህ፡፡ በሌሎች ፍጡራን ላይ ለመንገስም የማሰብ ችሎታህን ትጠቀማለህ፡፡ በሌሎች ፍጡራን ላይ ነግሰህም 20 ዓመትን ትኖራለህ አለው። የሰው ልጅ የተሰተውን የማሰብ ችሎታው ተጠቅሞ ሲመልስ… ጌታየ እሽ! የሰው ልጅ እሆናለሁ፡፡ ነገር ግን ሃያ ዓመት መኖር እጅግ ሲበዛ ትንሽ ነው፡፡ ስለሆነም ሠላሳ ዓመት አህያው የተቃወመውን፣ አሥራ አምሥት ዓመት ውሻው አልፈልገውም ያለውን እናም ደግሞ አስሩን ዓመት ዝንጀሮው የማይፈልገውን ስጠኝ ሲል ጥያቄውን አቀረበ (ከራሱ ጋር የሌሎችን ደማምሮ 75 ዓመት አደረሰው)፡፡ ፈጣሪም የፍላጎቱን ሰጠው… #እናም የሰው ልጅ ሕይዎት ከዛን ጊዜ ጀምሮ 20ውን ዓመት እንደ ሰው ይኖራል (ሳያገባ ትዳር ሳይመሰርት ለአንድ ሆዱ ሲኖር ማለት ነው)፡፡ ከዛ በኋላ አግብቶ ትዳር ሲመሰርትና የቤተሰብ ኃላፊ ሲሆን 30ውን ዓመት ልክ እንደ አህያው የአህያውን ሚና ወስዶ ይኖራል፡፡ የቤተሰብ ኃላፊነቱን ይሸከማል፤ የአባወራነቱን ኃላፊነት ለመወጣትም ቀን ከሌት ያለመታከት ይሰራል፡፡ ቀጥሎም ልጆቹ እያደጉ ሲሄዱ 15ቱን ዓመት ልክ እንደውሻው አይነት ኑሮን ይመራል፡፡ ቤቱን ይጠብቃል ይንከባከባል፣ ከልጆቹ ተርፎ የሚሰጠውንም ይበላል፡፡ አርጅቶ እየሸመገለ በሄደ ጊዜም ጡረታ ይወጣና 10ሩን ዓመት እንደ ዝንጀሮው አኗኗር ዘይቤ ይኖራል፡፡ ልጆቹን አጎራብቶ ከአንደኛው ቤት ወደ ሌላኛው ቤት በመዘዋወር የልጅ ልጆቹን በማጫወት፣በማዝናናት ያለፉ ዘመናትን ታሪክ በማውራት ያሳልፋል፡፡ #ሕይዎት_ማለት_ይች_ናት!
نمایش همه...
⟣฿Ⱡ₳₵₭ ⱠØVɆⱤƧ╣

ᣜɴᴇᴡ ᴘɪᴄᴛᴜʀᴇꜱ ᴡɪʟʟ ᴘᴏꜱᴛ ʜᴇʀᴇᣲ ᣜQᴜᴏᴛᴇꜱ ᴀɴᴅ ᴍᴇᴍᴇꜱ ᴀʟꜱᴏ ꜰɪɴᴅ ʜᴇʀᴇᣲ ᣘᴀʙꜱᴏᴜʟᴇᴛʟʏ ᴇᴠᴇʀʏ ᴛʜɪɴɢ ʏᴏᴜ ᴡᴀɴᴛ ɪᴛ ɪꜱ ʜᴇʀᴇ ᳕☻⭛ ꜰᴏʀ ᴀɴʏ ᴄᴏᴍᴍᴇɴᴛ @shainyy5 @DELETED_ACC_OUNT

hi
نمایش همه...