cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Amhara today

ፈጣን ሚዛናዊ መረጃዎችን ይከታተሉ

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
9 250
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

"…ለማንኛውም ይሄ የምታዩት የስንዴ ልመና አቁማ ስንዴ መሸጥ ኤክስፖርት ማድረግም በጀመረችዋ የዘመነ ብልጽግናዋ ኢትዮጵያ በኦሮሚያ ወለጋ እና በዐማራ ክልል በሰሜን ጎንደር ውስጥ የሚታይ አሰቃቂ የራብ አደጋ ነው። "…ዘንድሮ 7 ሚልዮን ህጻናት ወደ ትምህርት ቤት አልሄዱም። በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ትምህርት ቤቶች ወድመዋል። የኦሮሞ ብልፅግና ለድጋሚ ጦርነት ጡንቻ ማሟቁን ተያይዞታል። ደጋፊዎቹም አንበሳ በለው፣ ወደፊት እያሉት ነው። ትግሬም እርሙን ካወጣ በኋላ በሰለስቱ ቀይ ባሕር፣ ወደብ ወደብ ብሎ ሊሞት ነው። ኦሮሞም ያለ "ገላነ ዲማ" ሌላ ወሬ ትቷል። እነ ደሳለኝ መሃል ሜዳ የከሰረው ፓስተር እንኳ የሱፐር ቻትና የሱፐር ስቲከር ለጋሾቹ ኤርትራውያንን ከአሁኑ ይሞልጫቸው ይዟል። ትግሬንም በኤርትራ መሰደብ ጮቤ ያስረግጥ ጀምሯል። "…የተለቪዥኗ ኢትዮጵያ ማርና ወተት የምታፈስ ከንዓን ናት፣ ገሃዷ የእውን ዓለሟ ኢትዮጵያ ግን ራብ፣ ጠኔ፣ ጦርነት፣ ወረርሽ፣ ወባና ኮሌራ ሕዝቧን እንዲህ እንደምታዩት እየረፈረፈ የደቀቀች ሆናለች። ጨቅላ መሪዋ ደግሞ ሁሉን ትቶ በካምቦሎጆ ከጎረምሶች ጋር ቅሪላ ሲገፋ ይውላል። "…ኧረወዲያልኝ በሉ ደኅና እደሩልኝ።ዘመዴ
نمایش همه...
👍 23👎 4 2👏 1
#በ15 ቀን እንዲጠናቀቅ አብይ አህመድ ለጀነራሎቹ መመሪያ ያወረደበት 3ኛ ዙሪያ የአማራ ክልል ወረራ በተቃራኒው ከፍተኛ ኪሳራና ሽንፈት ገጥሞታል። በጎጃም፣ ባህር ዳር ዙሪያ፣ በአዴት በሰላካ፣ ቋሪት፣ዳንግላ፣ እንጅባራ፣ ደጋ ዳሞት የአብይ ስራዊት ከፍተና ኪሳራ በላፉት ቀናት ደርሶበታል፡፡ጎንደር 3 ክፍለ ጦር የአብይ አህመድ ስራዊት በመአከላዊ ጎንደር ተንዶ ፣ እየተበታተነ ነው። ወደ ደብረ ታቦር እየሸሸ ነው። ስትራቴጂካዊ የሆነችው እብናት በፋኖ ህዝባዊ ሃይል ቁጥጥር ስር ገብቶአል፣። የአብይ አህመድ ስራዊት በከፍተኛ ቁጥር ስርአቱን እየከዳ፣ እየጠፋ እየሸሸ ነው። ከፍተኛ ቁጥር ያለው ስራዊት አጁን ለፋኖ ህዝባዊ ሃይሎች እጅ እየሰጡ ነው። የኦሆድድ ብልጽግና ሎሌ በመሆን አማራን ህዝብ በመጨፍጨፍ ተባባሪ የሆኑ የአማራ ብልጽግና ፣ የሚሊሺያ መዋቅር ላይ የሚወሰደው እርምጃ ቀጥሎአል። አብዛኛው የአማራ ሚሊሺያ ፋኖን እየተቀላቀሉ፣ አገዛዙን አየጣሉ ወደ የመንደራቸው ጥለው እየሄዱ ነው።
نمایش همه...
👍 16
መረጃ አዴት! በጎጃም ምድር ላይ በኦሮሙማዉ አግዛዝ ልዩ ትዕዛዝ አማራ ህዝብ ላይ ጭፍጨፋ እየተደረገ ይገኛል። ከሰሞኑ በፋኖ ኃይለኛ ብትር ያረፈበት አገዛዙ ከሳምንት በላይ ከባድ ያላቋረጠ ውጊያ አዴት ከተማና ዙሪያዉ ላይ እያደረገ ሰንብቷል። በዚህም በርካታ የጠላት ወገን የተመታና ከባድ ኪሳራ የደረሰበት ቢሆንም ከቆፈረዉ ምሽግ ሳይወጣ በፈርሐት ሳምንት ቆይቶ በርካታ ኃይል ወደ ከተማው በሞጣ በኩል ፣በባህርዳር በኩል ያስገባ ሲሆን ይህ የጎጃም ህዝብ እየጨፈጨፈ ያለዉ ኃያል በርካታ ጭካኔዎችን ፈፅሟል። ሴቶችን ከመድፈር አልፎ ገሏል፣ ወጣቶችን በአደባባይ ረሽኗል። ከተለያዩ የአገዛዙ ተላላኪዎ ጋር በመሆን ፋኖን አግዛችሁዋል በማለት ንፁሐንን በማያዉቁት እንዲገደሉ ሁነዋል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የአብነት ተማሪዎች ላይ የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ተፈፅሟል። "ለፋኖ እናንተ ናችሁ ጥይት የማያስመታ መዳኒት የሰጣችሁዋቸዉ " በሚል በኦሮሞ አዛዥ ጀነራሮች አዴት የፉስለታ ቤተክርስቲያን የቅኔ ተማሪዎችን  25 በላይ ለምረቃት የደረሱ የቅኔ ተማሪዎች መንገድ ላይ ወጠዉ ተደርድረዉ ተረሽነዋል።  በተጨማሪም አዴት መድሐኒያለም ካቴድራል  ቤተክርስቲያን ውስጥ በመግባት ሁለት ንፁሐን ጠበልተኞችን ረሽነዉ ገለዉ። ህዝቡን ቤተክርስቲያን ውስጥ ለአንድ ቀን ተዘግቶ እንዲያድር ሁኑዋል። በርካቶች ከባድ ድብደባና የአካል መጉደል ደርሶባቸዋል። ቤት ለቤት መሳሪያ አምጡ ተብለው በርካታ ንፁሐን ተደገለዋል: ሴቶች ተደፍረዋል :በይሁዳ መንገዱ የተረሸነዉ ቤት ይቁጠረው መቅበረ እንኳን አልተቻለም።  እንዲሁም መረጃ TV እያያችሁ ነው በሚል በርካታ ሰዎች ቴሌቢዥን ተሰባብሯል። ዲሽ ተነቅሉዋል የተገደሉም በርካቶች ናቸዉ። ፋኖ ያለበትን ጠቁሙ ፣ፋኖን እረድታችሁዋል በሚል በወያላነት የሚያገለግሉ ንፁሐንን የቀን ሰራተኞችን በአደባባይ ገለዋል። "የቋሪት እና የአዴት ፋኖ የሚገለን እናንተ እያገዛችሁ ነዉ በሚል ሁሉን ሰውን እናጠፋለን እያሉም"  በግልፅ እየዛቱ ይገኛሉ። ከ70- 80 % በላይ የሚሆነው የአብይ አህመድ ጦር "ደብረማዊ መውጫ አቡነሐራ አካባቢ ከባድ ምሽግ ቆፉሮ ይገኛል፣ አዴት መግቢያ " ከብት እርባታዉ አካባቢ በርካታ የጠላት ሐይል ከባድ ተተኳሽ መሳሪያዎች ሳይቀር  ወደ ከተማዉ ደቅኖ ካምፕ ውስጥ ንፁሐንን እየገደለና እና ከተማዉን እያሸበረ  ይገኛል።   ስምሪት የሚሰጣቸው ወታደሮች ሁለት ኦሮሞ አንድ "አማርኛ ተናጋሪ"  አንድ ከባድ መሳሪያ ተተኳሽ ይዘዉ :የኦሮሞ ተወላጆች ምንም ሳያናግሩ ንፁሐኑን ቤት ለቤት እየገደሉ ነዉ። በተያያዘ ዜና ዛሬ አዴት የስልክ እና የመብራት ከስምንት ቀናት በኋላ የተወሰኑ ቦታዎች ተለቋል።  ዘንዘልማና ሌሎች የጎጃም አካባቢዎች  አሁንም ከባድ ውጊያ እየተካሄደ እንደሆነ ከቦታው መረጃዎች እየመጡ ነዉ።
نمایش همه...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
አብይ ወደ ውጭ ሀገር የሚሄደው ብድር ለማሰረዝ እና ብድር ለመጠየቅ ብቻ ነው፣ ብድር ሲጠይቅ ደሞ ካርታና ፕላን ኦርጂናሉን አሲዝ ይባላል፣ ሰውየው ስልጣኑ ይጠበቅ እንጂ ኢትዮጵያ ፍዳዋን ብትበላ ጉዳዩ ስላልሆነ ማስያዢያ ብለው የጠየቁትን ነገር ሁላ እያስያዘ ይበደራል፣ ወገን ሀገር እኮ የለንም፣ ባለቤትነቷ እኮ የሌሎች ሀገራት ሁናል። በሰው ቤት ነው የምንኖረው ማለት ይቻላል፣ ቴሌን ተበድሮበታል፣ አየር መንገዱን አብዛኛውን ድርሻውን ተበድሮበታል፣ ደረቅ ወደቦችና በርካታ የልማት የእርሻ ቦታዎች በብድር ስም በሌሎች ሀገራት ባለቤትነት ወድቀዋል። የህዳሴ ግድቡ 72 ቢሊየን ሜትር ኪዮብ ውሃ ሊሞላ ሲገባው ፣ 42 ቢሊየን ሜ/ኪዩብ ውሃ ሞልቶ ጨርሰናል ብሏል፣ ከግብፅ 2 ቢሊየን ዶላር ተቀብሏል የሚል መረጃ አለ። ሰውየው ስልጣን ከያዘ የተበደረው ብር ወያኔ በአስርተ አመታት ከተበደረው ብር ይበልጣል፣ እኛን ተበድሮ በገዛው ድሮንና መሳሪያ ይገድላል ፣ ሀገሪቱን በቁሟ ይሸጣል፣ አሁንም ይህንኑ ራስ ወዳድነቱን አጠናክሮ ቀጥሏል። ፋሽስት አብይ አህመድ አሊ! Amhara Today
نمایش همه...
👍 3👎 2
ደምቢያ ወረዳ ሙሉ በሙሉ ከብልጽግና መዋቅር ጸድታለች! ሰሞኑን አይንባና ምስራቅ ደምቢያ ላይ ህዝብ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱ ተነግሯል፡፡ ትናንትና አይንባ ላይ የሆነው ግርምትን የሚጭር ነው፡፡ አድማ ብተናና ሚሊሻ ካምፕ ነበረው፡፡ ፋኖ ከየት መጣ ከየት ሳይባል ከበባ ይፈጽምባቸዋል፡፡ የወረዳው አድማ ብተናና ሚሊሻ ሃላፊ ወርቅነህ ውጊያው ላይ አልፏል፡፡ በርካታ አድማ ብተናናና ሚሊሻ እንዲሁ አልፈዋል፡፡ የተቀሩትን ፋኖ ማርኮ የአጼ ቴዎድሮስ ምሽግ ላይ አድርሶ ህዝቡን ሰብስቦ አመራር ሰጥቷል፡፡ ህዝቡም እነዚህ ወንድሞቻችን ናቸው አትግደሏቸው አለ። ፋኖዎችም ብንገድላቸውማ ቀድሞ እንጨርሳቸው ነበር እኮ፡፡ ግን ከዚህ ቀደም እየደወልን ብንነግራቸው እምቢ ያሉ ከሀዲዎች ስለሆኑ ለተወሰነ ጊዜ ጭነት የምንጭናቸው ነን ብለው ወስደዋቸዋል፡፡ አድማ ብተናዎች ለጭነት የተፈለጉበት ምክንያት ለሸክም የሚያታክት ትጥቅ ስለተማረከ እና ፋኖ ይሄንን ለማጓጓዝ የአቅም ውስንነት ስላጋጠመው ነው፡፡ አሁን ላይ የጁላ ሰራዊት ወደካምፕቹ ሄዷል፡፡ ህዝቡ ግን በራሱ አስተዳደር እየተዳደረ ነው፡፡ የቀድሞ አስተዳዳሪዎችም ከህዝቡ ጋር ተስማምተው ስራቸውን እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ የብልጽግና መዋቅር ከእንግዲህ ደምቢያ ላይ የድሮ ተረት ነው፡፡ መረጃው የምስጋናው አንዷለም ነው!
نمایش همه...
👍 2 1
ደራ ዙሪያ የጁ ቀበሌ ሙሉ በሙሉ ወድማለች ይሄ ከህልውና ትግል በላይ መሆኑን አውቃችሁ ሁላችሁም ተነሱ ..‼️‼️ አማራውን በተቀናጀ ሁኔታ ጨፍጭፎ ፣ አፈናቀሎ ከተቻለም አገር አልባ የማድረጉ የጠባብ ፅንፈኛ ኦሮሙማ ስብስብ ሴጣናዊ ምኞትን ለማስፈፀም የስራ ክፍፍል አድርገው ወደ ስምሪት ገብተው በተቀናጀ እና በተናበበ ሁኔታ እያደርሱ ሲገኙ ለዚህም አላማ ጦርነቱን አገራዊ ቅርፅ አለብሰው በፓላማ አሳውጀው የከተማውን በኦህዴድ መከላከያ ሲከውኑ ሌላውን የገጠራማ ቦታዎችን በዳቦ ሰው ኦነግ ሸኔ በተባለ ለይስሙላ አሸባሪ በተባለው እርኩሰት ሰራዊት እያስፈፀመ ይገኛል። በትላንትናው እለት 06/03/ 2016 ዓ.ም በደራ ዙሪያ የጀማ ወንዝን ሳትሻገር የጁ በምትባል መንደር የኦነግ ሼኔ ፅናፈኛ አሸባሪ ቡድን ከለለቱ 6 ሰአት ባልተጠበቀበት ሁኔታ እንደ ምንጃር አውራ ጐዳና ላይ እንዳደረጉት በኦሮሚያ ልዩ ሀይል እና መከላከያ አመራርነት ከባድ መሳሪያን ታጥቀው ጭምር የኦነግ ሸኔን ሀይል ሽፋን በመስጠት ምንም ያልታጠቀ ነዋሪ ባለበት ህዝብ አማን ብሎ በተኛበት ሁኔታ መንደሯን ሙሉ በሙሉ ገብተው በእሳት ሲያወድሙ አድዋል፡ ። ነዋሪዎቹ ባልተዘጋጁበት ሁኔታ በደረሰባቸው ጭካኔያዊ እልቂት እራሳቸውን ማስመለጥ ያልቻሉ አቅመ ደካሞች እና ህፃናት መካከል ቁጥሩ በውል ያልታወቁ ሊጨኖር የሚችል  ከ5አዛውነቶች እና ከ7 የሚበልጡ ህፃናት አብረው ቤት ውስጥ በተቸበት ሲቃጠሉ አብዛኛው በድንግዝግዝ ለሊት ተበትነው ወደ ጫካ ሊያመለጡ ችለዋል። በውድመቱ ባጠቃላይ ከ 1000 በላይ አባወራ ባጠቃላይ በግሞት ከ 7- 10 ሺ ነዋሪዎች ቤት ንብረታቸው ወድሞ ቀዬያቸውን ጥለው ሊሰደዱ ችለዋል። በዚ ወቅት በእርኩስቱ ፋሽስት ሀይል ከፍተኛ ውድመት እና እልቂት እየደረሰባቸው ያለው የማህበረሰብ ክፍል ዉስጥ አብዛኛው አማን ብለዉ የተቀመጡ የማይታገሉ ከጦርነቱ ጋር ምንም አይነት ግንኙነት የሌላቸውን ንፁሐን በመምረጥ ነው። በአብዛኛ የሚታገለው ላይ ይህ ነው የሚባል ጉዳት ሲደርስ አይስተዋልም ምክንያቱም ጎመን ሰራዊቱ ደፍሮ ወደ ታጠቁ ሀይሎች ፊት ሲሄድ አይስተዋልም በሄድም ሙት እና ቁስለኛ እንደሚሆን ጠንቅቆ ይረዳል በአንፃሩ ወደትግል ባልገቡ አገር ለማን ባሉ ንፁሐን ላይ በመንግስት ድሮውን ሲመቱ በገጠር ቀበሌ ያሉት በፅንፈኛው የኦነግ ሽሜ ሰራዊት ስለባ ይሆናሉ። ለዚህም ምንጃር አውራ ጎዳና ምስክር ናት። በምንጃር አውራጎዳና ህዝብ በጦርነቱ ያልነበረ ፍፁም ሰላማዊ ከተማ ነበረች። ሆኖም ልፍስፍሱ ሰራዊት ወንዶች ያሉበት ቦታ ሄዶ መዋጋት የማይሆንለት በመሆኑ ጥቃቶችን የሚያደርሰው በንፁሃን ላይ ብቻ ነው። በመሆኑም አሁን የገጠመን ነገር ቢኖር ትግሉ ከህልውና ትግልም በላይ መሆኑን ነው ይህን አውቆ ከጫፍ ጫፍ አንድላይ በጋራ ተነስቶ ጠላትን ለመጨረሻ ጊዜ መንቀል ምርጫ የሌለው ግዴታ ሆኗል :: አለበለዚያ እኛ ጋራ ሰላም ነው በሚል መዘናጋት ማታ በመኝታ ወቅት ሁላችንንም የየጁ እና አውራ ጎዳና እጣ እንደሚደርሰን ጠንቅቆ መገንዘብ ያስፈልጋል። ለመሆኑም አንተም አንቺም ሁላችንም ዛሬውኑ በንቅናቄ ተነስቶ እራስን እና ቤተሰብን ለማዳን ወታገል ያስፈል ። አሁን የየጁ ህዝብ የሞተው ሞቶ የተረፈው ህፃን አዛውነት ሳይቀር ያመለጠው አምልጦ በየጫካው ተበትነው ይገኛሉ :: በመሆኑም ነገ በኔ ብሎ ሁሉም ዛሬውኑ ይክተት ይነሳ ይዘጋጅ ይህን ኦሮሙማ የእርኩሰት ሰራዊት በጋራ ሊፋለም ቆርጦ ሊነሳ ይገባል።
نمایش همه...
👍 7 1
መረጃ ሸበል በረንታ! የብርሃኑ ጁላ ጦር በመንገድ መሪ ባንዳዎች እየተመራ ከብቸና ወደ ሸበል በረንታ በመግባት ንፁሃንን ለመጨፍጨፍ እንቅስቃሴ ጀምሯል። ለዚህ ጭፍጨፋ ይመቸው ዘንድ የስልክ አገልግሎት አቋርጧል። የሸበልበረንታ ተርብ ክንድህን አቅምሰህ መልሰው!
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
ከወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን የተሰጠ መግለጫ! “የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአብክመ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አስተዳደር ውስጥ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ለተከታታይ ሁለት ዓመታት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ዲስትሪክቱን ጎንደር በማድረግ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት የተዘረጋው ሲስተም ወደ ተሟላ ስራ እንዲገባ በዞናችን የሚገኙ ማእከላት በምንጠይቅበት ሰዓት ሲስተሙን ሊያጓትቱ የሚችሉና በህዝብ ዘንድ ቅሬታን የሚያስነሱ ማለትም በአራቱም የአገልግሎት ማእከላት /ዳንሻ፣ ባህከር ፣ አድረመጥና ሁመራ / የሚገኙ ሞያተኞችን ደሞዝ ወደ ሽሬ ዲስትሪክት የማዛወር ፍላጎት እንዳለ ተረድተናል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል በቀደመው ይቀጥል በሚል አገልግሎቱን ወደ ትግራይ ለማሻገር መሞከር የአገልግሎት አሰጣጡን ከማወሳሰቡም በላይ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ የሚፈጥር መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ከጎንደር ዲስትሪክት የተዘረጋውን ሲስተም በተሟላ መልኩ በማስጀመር እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት የበለጠ እንዲሳለጥ እንጠይቃለን!” አቶ አሸተ ደምለው ተድላ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ
نمایش همه...
👍 4
እነዚህ መረጃዎች ከውስጥ የተላኩ ናቸው! በቆቦ፣ አዩብ፣ ተኩለሽ፣ ደበረ ሰላም አቦ ድረስ ፣ላሊበላ፣ ብልብላ፣ ወገል ጤና ፣ ፀሀይ መውጫ እንዲሁም በሽዋ ደብረ ሲና፣ ሰላ ድንጋይ ድረስ በሚቀጥሉት  ቀናት አገዛዙ በእግረኛ ወይንም በከባድ መሳሪያ ወይንም በድሮን እንደሚያጠቃ ከውስጥ መረጃ ደርሶናል።  ስለዚህ በዚህ አካበቢ የምተገኙ ፋኖዎች እራሳችሁን ለመከላከል አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደረጉ እናሳስባለን። በቅርቡ በላሊበላ እና አካባቢው  በብልብላ እና አካባቢው በኮንቦልቻ እና አካባቢው ሰርባ እና አካባቢው ማማ ገዳም እና አካባቢው አብረሃ ጅራ ከተማው እና አካባቢው ደብተራ ጉጥ እና ከባቢው ኩራባስ ጣቁሳ እና አካበበቢው ወገል ጤና አካባቢው እናዋሪ እና ሊሙ አካባቢው በቅርቡ በከባድ መሳሪያ ወይንም በእግረኛ ወይንም በድሮን ስለሚጠቃ እራሳችሁን ለመከላከል አስፈላጊውን ሁሉ እንድታደረጉ እናሳስባለን። ጎንደር  ጭልጋ ከሰረባ ሻውራ ጣቁሳ ድርስ ላሊበላ ብልብላ ኤርፖርቱን ይዞ ጠላት መረጃ እንደሰበሰበ መረጃ ስለደረሰን በዚህ አካባቢ የምትንቀሳቀሱ ፋኖች በሚቀጥሉት ቀናት በእግረኛ ወይንም በከባድ መሳሪያ ወይንም በድሮን ጥቃት ሊኖር ስለሚችል አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንድታደረጉ እናሳስበለን:: (ምንጭ ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን)
نمایش همه...
👍 13🙏 2
Photo unavailableShow in Telegram
#እንዴት_አደራችሁ🙏🙏 // ጐንደር ቆላድባ ከተማ | አይምባ የድል ዜና ..‼️‼️ በማዕከላዊ ጎንደር ምስራቅ ደምቢያ ወረዳ ቆላድባ ከተማ አይባ ከሚባል ቦታ ላይ ደጃች ማሩ ብርጌድ ከመቶ በላይ አድማ ብተናና ከሀያ በላይ የሚሊሻ አባላትን ማርኳል። አንድ ፓትሮል አብይ ጦር ጋይቷል። በዚህ የተበሳጨው የአብይ መከላከያ አይምባ ላይ ጦርነት ከፍቶ የአካባቢው አርሶ አደር በጥሩንባ እየተጠራራ የአብይን ጦር በልኩ እያናገረው ነው !!! ውጊያ ቀጥሏል!!
نمایش همه...
👍 17
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.