cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Orthodox Wallpaper ✝✝✝

የኦርቶዶክስ የሆነ ለስልኮ ፎቶ ከፈለጉ ይህንን ቻናል ይቀላቀሉ ይህንን ቻናል ለኦርቶዶክስ ቤተሰብ በመላክ ይተባበሩን@orthdoxswallper

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
2 864
مشترکین
+1224 ساعت
+767 روز
+59430 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
📌 ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዲህ አለ ✍️ "በምሰብክበት ጊዜ ስታጨበጭቡልኝ ሰው እንደመሆኔ በዚያ ቅጽበት ደስታና መደነቅ ይሰማኛል ወደ ቤቴ ሔጄ ያጨበጨቡልኝ ሰዎች ምንም ጥቅም እንዳላገኙ ሳስብ ግን ንግግሬ ሁሉ በከንቱ እንደቀረ ይሰማኛል፤ ስለዚህ ማጨብጨባችሁን የሚከለክልና ዝም ብላችሁ እንድትሰሙኝ ብቻ የሚያደርግ ሕግ ስለማስቀመጥ አስባለሁ" (On His Message 80) ✍️“ቤት ውስጥ የእንግዳ ማረፊያ ቤት ይኑርህ አልጋ አዘጋጅ ጠረጴዛና መቅረዝም ይኑረው ክርስቶስ ሊመጣና ሊያርፍበት የሚችልበት ክፍል አዘጋጅና "ይህ የክርስቶስ ክፍል ነው" በል ምድር ቤት ያለ ትንሽ ክፍልም ቢሆን እሱ አይንቀውም፤ ዕርቃኑን የሆነው እንግዳ የሚፈልገው መጠለያ ብቻ ነው"  (On Acts Homily 40.2) ✍️ “ለሞቱት ብቻ አናልቅስ፤ በቆሙት ብቻም አንደሰት ታዲያ ምን እናድርግ? ለኃጢአተኞች በሞቱ ጊዜ ብቻ ሳይሆን በቁማቸውም እናልቅስ፤ ስለ ጻድቃን ደግሞ በቁማቸው ብቻ ሳይሆን በሞቱም ጊዜ ደስ ይበለን ምክንያቱም ኃጢአተኞች ቆመውም ሞተዋል፤ ጻድቃን ግን ሞተውም ሕያዋን ናቸው" (On Phil. 3) ✍️ "ጴጥሮስ አለቀሰ ማልቀስ ብቻ ሳይሆን ምርር ብሎ አለቀሰ፤ ከዓይኑ በፈሰሰው ዕንባ ድጋሚ ተጠመቀ አምርሮ በማልቀሱም በዕንባው ኃጢአቱን አጠበ አንተም እንዲሁ አድርግ" (Paent 3.4) ✍️“ንብ ከሌሎች እንስሳት ሁሉ ትከበራለች፤ የምትከበረው ታታሪ ሠራተኛ በመሆንዋ ሳይሆን የምትሠራው ለሌሎች በመትረፉ ነው" 📌ምንጭ ✍️ ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ ግንቦት 12 2014 ዓ.ም
نمایش همه...
❤‍🔥 10👍 3
19🥰 8
20🙏 5🍓 3👍 2
በቦሌ ደብረ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ አመታዊ በአል በድምቀት እየተከበረ ይገኛል
نمایش همه...
21👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
#ዳግም ትንሣኤ ለምን ተባለ ? ቢባል፦ ዳግም ትንሣኤ የተባለበት ምክንያት፡- በአከባበር፥ በሥርዓት የመጀመሪያውን ትንሣኤ ስለሚመስል ነው፡፡ የትንሣኤ ዕለት የሚባለው የሚነገረው ቃለ እግዚአብሔር ሳይለወጥ በሙሉ በዚህ ቀንም ይደገማል፡፡ በዕለተ ትንሣኤው የነበረው ሥርዓተ ማኅሌትና ቅዳሴ፣ የነበሩት መዝሙራትና ምስባኮች በድጋሜ ስለሚዘመሩ አከባበሩ እንደ ቀደመው ( ከ8 ቀናት በፊት እንደነበረው)  ትንሣኤ ስለሆነ ዳግም (ሁለተኛ) ትንሣኤ አልነው እንጂ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዳግማዊ (ሁለተኛ ትንሣኤ) አለው ለማለት አይደለም።(Petros Ashenafi kebede)
نمایش همه...
🙏 11❤‍🔥 4👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
እናታችን ሆይ ልደትሽ ልደታችን ነው ❤ እንኳን አደረሳቹሁ ። !!!🙏 #ኦርቶዶክሳዊ #አእምሮ
نمایش همه...
❤‍🔥 18 13
Photo unavailableShow in Telegram
ልደታ ለማርያም
نمایش همه...
❤‍🔥 31🙏 16
ልደታ ለማርያም
نمایش همه...
❤‍🔥 12 3🍓 2
Photo unavailableShow in Telegram
ልደቷ (ልደታ ለማርያም፦ ግንቦት አንድ ቀን ) በተአምረ ማርያም መቅድም ላይ "ልደቷ መስከረም ዐሥር ቀን ነው የሚሉ አሉ እኛ ግን በተረዳ ነገር ከአባቶቻችን በተማርነው ግን ቦት አንድ ቀን" የሚል ተጽፎአል። በመጀመሪያ ደረጃ ቁኑ ላይ "መቼ ነው?" የሚለውን ክርክር ምን አመጣው የሚለውን ብቻ እንኳ ብንመለከተው ጉዳዩ የመታሰቢያ ቀን የበዓል ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን ። በምዕራባውያን በዓሉን የሚያከብሩት በእነርሱ አቆጣጠር መስከረም ስምንት (September Eight ) ነው ። ይኽም ከላይ ከጠቀስነው ከመስከረም ዐሥር ቀን ጋር ይቀራረባል ። የሁለቱም ቀን ልዩነት በምን ምክንያት እንደተፈጠረ መመርመር የዚህ ጽሑፍ ዋና ጉዳይ ባለመሆኑ እንተወዋለን ። የእኛ ተአምረ ማርያም መቅድም የበዓላትን አመጣጥ በሚመለከት የሚናገረው ግን ምን ያህል ጥናትና ምርምር ያለበት ጉዳይ እንደሆነም ያመላክታል ። እንደ ኦክስፎርድ ክርስቲያን መዝገበ ቃላት ከሆነ ምዕራባውያን በዓሉን መስከረም ስምንት ለምን እንደሚያከብሩት አያውቁም ። እንዲያውም "መሰከረም ስምንት ለበዓሉ የተመረጠበት ግን አይታወቅም " ይላል ። ይኽም ማለት በዓሉን የሚያከብሩት በልደቷ ዕለት እንዳልሆነ ፍንጭ ሰጭ መረጃ ሆኖ ያገለግላል ። (በዓላት ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ገጽ 149-150) #ኦርቶዶክሳዊ #አእምሮ
نمایش همه...
👍 8❤‍🔥 3 3
Photo unavailableShow in Telegram
የትንሣኤ ማግስት ረቡዕ አልአዛር ይባላል፦ "…ሞቶ የነበረው የማርታና የማርያም ወንድማቸው አልዓዛር ጌታችንና አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መግነዝ ፍቱለት፣ መቃብር ክፈቱለት ሳይል ሰማይና ምድርን፣ ብርሃንና ጨለማን በፈጠረበት በቃሉ ብቻ ተናግሮ፣ አልአዛር፣ አልአዛር ተነሥ በማለት ከሞት ያስነሣበት ዕለት የሚታሰብበት ዕለት ነው። ዮሐ 11፥40 "…ጌታችን አልአዛርን ከሞት ያስነሣው መጋቢት 17 ቀን ነው። በዚሁ ቀን መታሰቢያ እንዳያደርጉለት የግርግር ወራት ሆነ። መጋቢት 22ም ሆሳዕና ሆነ። መጋቢት 23ም ርግመተ በለስ አንጽሖ ቤተ መቅደስ ሆነ። በዓሉ ከበዓል ይዋል ብለው አበው የውኃ በዓል ከውኃ ብለው ቃና ዘገሊላን ከጥምቀት ጥግ ጥር 12 እንዳዋሉ ሁሉ ትንሣኤው ከትንሣኤ ጋራ እንዲሄድ በጌታ ትንሣኤ ማግሥት በሚመጣው ረቡዕ በዛሬው ዕለት እንዲከበር አደረጉ። የጌታን ትንሣኤ አክብረን ዛሬ የአልአዛርን ስናስብ እኛም ትንሣኤ እንዳለን እናስባለን እና የዛሬውን ቀን አልአዛር ብለን እናከብረዋለን። • ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን ~በዐቢይ ኀይል ወሥልጣን • አሰሮ ለሰይጣን ~ አግአዞ ለአዳም • ሰላም ~ እምይእዜሰ • ኮነ ~ ፍስሐ ወሰላም።
نمایش همه...
👍 9🥰 4