cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

👑قناة طلاب العلم👑

#ቁርዐንና #ሀዲስን በሰለፎች አረዳድ የምናይበት እንዲሁም የተለያዩ #የሱና ኡስታዞች ሙሀደራ ምክር እና ቂርዐት የሚለቀቅበት ቻናል ነው። ከዚህም በተጨማሪ የተለያዩ #የንፅፅር እና #የሚያነቃቁ ፅሁፎች በአላህ ፍቃድ ይለቀቅበታል። ስሳሳት #በወንድምነት (ቁርዐንንና ሀዲስን ማስረጃ አድርጋችሁ) አርሙኝ። ሀሳብ አስተያየት እንዲሁም ተግሳፅ👉👉 @RACENS በዚህ ሊንክ ማቅረብ ትችላላችሁ።

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
200
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

አላሁ አክበር አጅብ ውስጣቸውን የሚያውቅ ይናገር!!! وشهد شاهد من أهلها أتدري إذا انجل الغبار أفرس تحتك أم حمار እንሻ አለህ ገና ይወጣል ሸራቸው ጉድ እኮ ነው https://telegram.me/Abufurayhan
نمایش همه...
1.74 MB
በአፄ ዮሃንስ ታሪክ ላይ የሚያጠነጥን መፅሀፍ ሊታተም ነው። ይሄን መፅሀፍ የሚያንቆለጳጵሱ ፀረሙስሊሞችን ስመለከት በታሪክ ድርሳናት ላይ ስለአፄ ዮሃንስ ያነበብኳቸው ስንኞች አቃጨሉብኝ። እስቲ ከመፅሀፍት ላጋራችሁ። ፣ ሸር ይደረግልኝ!! ሸር! ሸር! ፣ 1)ተክለፃዲቅ መኩሪያ "አፄ ዮሃንስና የኢትዮጵያ አንድነት" በሚለው የታሪክ መፅሀፉ ገፅ 200 ላይ በአፄ ዮሃንስ ስለተፈፀመው ግፍ በሚከተለው መልኩ ፅፏል ። ፣ "በኢትዮጵያ ያለው እስላም ሁሉ በክርስትና እንዲጠመቅ በየአውራጃው ትእዛዝ ስላስተላለፉ ፣በዚሁ በ1870 ዓመተምሕረት በያለበት ያለው እስላም ሁሉ በጭቃሹምና በመልከኛ ወደየአቅራቢያው ቤተክርስቲያን እየተነዳ በግድ እንዲቆርብ ተደረገ።" ፣ ቀጥሎም እንዲህ ይላል"ከእስላሞቹም መካከል የፈራው እየቆረበ ክርስትና ሲነሳ ፣የቀረው ከሀገሩ ከኢትዮጵያ ወደጎረቤት አገሮችና ያፄ ዮሃንስ ሥልጣን ወደማይደርስበት አውራጃ እየተሰደደ ይሸሽ ዠመር።" ፣ 2) ፕሮፌሰር ሃጋይ ኢርሊች "ዘ ሪቨር ኤንድ ዘ ክሮስ" በሚለው መፅሀፉ ገፅ 67 ላይ እንደፃፈው አፄ ዮሀንስ ግዳጅን ካወጀበት የቦሩሜዳ ጉባኤ ጀምሮ ባሉት ሶስት አመታት ውስጥ (ማለትም ከ1870 እስከ 1872) 50 ሺ ጀበርቲዎችና 500ሺ የየጁ ኦሮሞዎች በግዳጅ ክርስትናን እንዲቀበሉ ተደርገዋል። ፣ 3)ፕሮፌሰር መስፍን "እንዘጭ! እምቦጭ! በሚለው መፅሀፉ ገፅ 57 ላይ ብዙዎችን የምናውቀው "ሞጣ ቀራኒዮ ምነው አይታረስ በሬሳላይ መጣሁ ከዚያ እስከዚህ ድረስ" የሚለው ቅኔ አዘል ስንኝ የተቋጠረው አፄ ዮሃንስ ጦሩን ወደጎጃም አዝምቶ መጠነሰፊ ጭፍጨፋ በማድረጉ ነበር ይለናል። ፣ 4)ጋዜጠኛና ደራሲ ተስፋየ ገብረአብ "የኑረነቢ ማህደር" በሚለው መፅሃፉ ገፅ 48 ላይ ይሄንን ሲያጠናክር እንዲህ ይላል "አፄ ዮሃንስ የጎጃሙን ንጉስ ተክለሃይማኖትን መማረክ ሳይችሉ ሲቀሩ ህዝቡን ወደማጎሳቆል ገቡ።በጥብቅ የተዋህዶ አማኝነታቸው የሚታወቁት አፄ ዮሃንስ ታቦት እንዲሰባብሩ ወታደሮቻቸውን አዘዙ። ፣ "…በጎዛምንና በማቻክል ታቦት ከመንበሩ እያስወጡ እንዲሰባበር ማዘዛቸው፣ቤተክርስቲያን እያስፈረሱ ፣ማገሩን እያስፈለጡ ማንደዳቸው፣ የቤተክርስቲያን ሳንቃ እያስነቀሉ ለጥይት ማብረጃ እንዲሆን ማድረጋቸው ያስጠረጥራል።በርግጥ አጤ ዮሃንስ ራሳቸውን እንደሚያቀርቡት ከሌሎች ነገስታት በላይ አማኝና እንደሚታወቁበት የተዋህዶ ኦርቶዶክስ እምነት ጠባቂ ነበሩ??" ጭፍጨፋው ሙስሊምና ክርስቲያንን የሚመርጥ አልነበረም። 5)በእውቀቱ ስዩም "ከአሜን ባሻገር" በሚለው መፅሀፍ ገፅ 197 ላይ ደግሞ አፄ ዮሃንስ ሲኖሩ የአዘቦ ሙስሊሞች በግዛቴ ውስጥ ሙስሊም ሊኖር አይገባም በሚል ጨፍጭፏቸዋል። አፄ ዮሃንስ እንዲህ አለ ፣ "ከግዛቴ ውስጥ አንዲት ሀገር አለች። ስምዋ አዘቦ የምትባል።በውስጥዋ ያሉ ሰዎች እስላምና ኦሮሞ ናቸው…ዘመትኩባቸው" ።በእውቀቱ ስዩም ደግሞ"የአዘቦ ሙስሊም ኦሮሞዎች ያፄ ዮሃንስን የሃይማኖት ፓሊሲ በመቃወማቸው በሰይፍ ተደብድበዋል" ፣ አፄ ዮሃንስ ለሙስሊም ያለው ጥላቻ በሀገር ውስጥ ብቻ የተገደበ አልነበረም። የጎረቤት ሱዳን ሙስሊሞችንም ከጣሊያን አስበልጦ እንዲዋጋ አድርጎታል። ከጣሊያን ጋር ያቀደውን ጦርነት ሰርዞ ከሱዳን መሃዲስቶች(ከደርቡሾች) ጋር ለመግጠም ወደ ጎንደር ያቀናው አብረውት የነበሩት ጳጳሳት ክርስቲያን የሆኑ ጣሊያኖችን ከምትዋጋ ሙስሊም ሱዳኖችን ብትዋጋ ይሻላል የሚል ምክር ስለሰጡት ነበር። የሆነው ሆኖ በስተመጨረሻ መተማ ላይ አንገቱን ተቆርጦ አይሞቱ ሞት ሞተ @tewhidySunaBguragDeaga @tewhidySunaBguragDeaga
نمایش همه...
አስደሳች ዜና‼️ አስደሳች ዜና‼️ አስደሳች ዜና‼️ የመዲናው ጃሚዐቱል ኢስላሚያ የተቅዲም በሩን ከዛሬ ጀምሮ ክፍት አድርጓል‼️ ሁለት ወር ከ20 ቀን ባለው ግዜ ተቅዲም/apply አድርጉ! ይህ ማለት ረቢዓ–ሳኒ መጨረሻ ላይ ይዘጋል‼️ ተቅዲም/Apply ለማድረግ👇👇 القبول والتسجيل الجامعة الإسلامية بالمدينة https://minhatee2.iu.edu.sa/ ------- በየጊዜው ስለ ኢስላማዊ ስኮላርሺፕ የምለቃቸውን መረጃዎችን ለመከታተል ከታች ባለው ሊንክ ፔጁን join ያድርጉ። አላህ ለጠለበተል ዒልም እንዲወፈቁ ሰበብ ያድርገን! 👇👇👇👇👇👇 https://t.me/joinchat/AAAAAFUFDzHMVLZ7BanGuQ አላህ ይወፍቀን! Abu Hanif RM
نمایش همه...
بسم الله الرحمن الرحيم مركز ابن عباس لتحفيظ القرآن الكريم 09/02/2014 🌷🌷 በቀን 07/02/2014 በተለቀቀው ማስታወቂያ መርከዝ ኢብኑ አባስ የቁርአን ተህፊዝና ኢስላማዊ እውቀት ማእከል ለ 10 ልጆች ነፃ የትምህርት እድል ማዘጋጀቱን አስታውቆ እነደነበረ ይታወቃል ይህን ተከትሎ በርካታ ተማሪዎች ተመዝግበው የተፈተኑ ሲሆን ተቋሙ ባስቀመጠው መስፈርት መሰረት ውድድሩን በመለፍና መስፈርቱን በማሟላት የእድሉ ባለቤት የሆኑት ተማሪዎች የሚከተሉት ናቸው :— 👇👇👇👇👇👇 ① ሙፍቲ መሀመድ 👉 ከሀረር ② ረያን ጀማል 👉ከጉንችሬ(ወርሳባቴ) ③ አብዱ ራህማን ኑረላህ 👉ከስልጤ(ዶቤ) ④ መሀመድ ሱልጣን 👉 ከሞጣ ⑤ አሚር ሙስጠፋ 👉ከጎንደር ⑥ አህመድ መሀመድ ዐሊይ 👉ከወሎ ⑦ አህመድ ሁሰይን 👉ከአፋር ⑧ አብዱ ረዛቅ አህመዲን 👉 ከቃጥባሬ ⑨ አሚር ኢብራሂም 👉ከኮንቦልቻ 🔟 ሀምዛ ሁሰይን 👉 ከወሊሶ ማሳሰቢያ📢 ከላይ ስማቸው የተዘረዘሩ ተማሪዎች እሰከ ቀን 12/02/2014 በማእከሉ ቅጥር ግቢ ተገኝታችሁ አስፈላጊውን ነገር እንድታሟሉ ስናሳውቅ እስከተጠቀሰው እለት የማትገኙ ከሆነ ተቋሙ የራሱን አማራጭ እንደሚወስድ ያሳስባል። 🪴 መርከዙ 🏫 @merkaz_ibnuAbas 👆👆👆👆👆👆👆 ይህን በመጫን የመርከዙ ቻናል ቤተሰብ ይሁኑ
نمایش همه...
بسم الله الرحمن الرحيم مركز ابن عباس لتحفيظ القرآن الكريم 🌐ታላቅ የምስራች 📌 ነፃ የትምህርት እድል በኢብነ አባስ የቁርዓን ሒፍዝና ኢስላማዊ ዕውቀት ማዕከል መርከዙ ኢስላምን ለመርዳት ካለው ጥልቅ ፍላጎትና ቁርኣን ተደራሽ እንዲሆን ካለው ፅኑ አላማ ከተመሰረተ 2007 አንስቶ እስካሁን የበኩሉን አስተዋፆ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል። ዛሬም በ2014 ዓ·ል አስር ልጆችን በነፃ የትምህርት ዕድል ፕሮግራም ተቀብሎ በዚህ ዓመት ለማስተማር ዝግጅቱን አጠናቆ ይህን ማስታወቂያ ሲለቅ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል። ⛔️ማሳሰቢያ:– የዚህ እድል ተጠቃሚ ለመሆን ተቋሙ ያስቀመጣቸው መስፈርቶች:– ➤ ትምህርት ቤቱ ያስቀመጠውን ፈተና ማለፍ። ➤ እድሜው ከ14–18 ዓመት የሆነ። ➤ ቁርኣንን በማየት(ነዘር)የቀራ። ለዚህ የትምህርት እድል መወዳደር የምትፈልጉ ከጥቅምት 8/2014 ጀምሮ እሰከ ጥቅምት 13/2014 ዓ·ል የምዝገባ ጊዜ መሆኑን አውቃችሁ ከላይ የተጠቀሰውን መስፈርት የምታሟሉና ፈተናውን ለመፈተን የተዘጋጃችሁ በተጠቀሰው ቀን በመዓከሉ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተገኝታችሁ መፈተንና መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን። ☎️ለበለጠ መረጃ:– 0911008271 0910192594 0912941706 @merkaz_ibnuAbas
نمایش همه...
📖 የኦን ላይን ሐለቀተል ቁርዓን ፕሮግራም ወንድም ጀላሉ ሁሰይን 📌ዘውትር: – ረቡእ እና ሀሙስ ከመግሪብ እስከ ኢሻእ 🕌🕌በፉሪ ሰልሰቢል መስጂድ የሚሰጠው የሀለቀተል ቁርአን ፕሮግራም በቴሌግራም ቻናል ቀጥታ ስርጭት የሚተላለፍ ይሆናል 👉ቂርአቱ ከሱረቱ አል ናስ ጀምሮ ለጀማሪዎች በሚመጥን መልኩ ስለሆነ ሚሰጠው ፕሮግራም አድርገው ይከታተሉ ተጠቃሚውም እንዲሰፋ ቻናሉን ሼር ያድርጉ #Quran online @bin_Husseynfurii 👆👆👆👆👆👆👆
نمایش همه...
» ታዲያ ይህች ውድ እናትሽ የታላቁ ነቢይ ድንቅና ውድ የሆነችው ምስታቸው ዓኢሻ፣ ለዚህ ህዝብ ዲኑን ያስተማረችው ምርጧ የዚህ ህዝብ እናት መውሊድን አክብራለች?! የትና መቼ? » ለመሆኑ በአለባበስሽ፣ በአመጋገብሽ፣ በአነጋገርሽ፣ ነቢዩ ﷺ ያዘዙሽን ፈፅመሻል? » ብረት እንደሚገፋ ወንድ ሰውነትሽን ወጣጥረሽ፣ እንደ አርሶ አደር (ገበሬ) ቁምጣ የሆነ ቁርድ ለብሰሽ፣ ሰርግ ሳይኖር ሰርግ አስመስለሽ ድቤ እየደበደብሽ የሞቱበትን ቀን እያከበርሽ ነው እወዳቸዋለሁ ምትይኝ?! ቤትሽ ውስጥ አህያ ቢኖርና መሳቅ ቢችል ይህን ሰምቶሽ ሁሌ እያስታወሰ በተግባርሽ ይስቅብሽ ነበር። » ለመሆኑ ነቢዩ ﷺ "ሽቶ ተቀብታ ከቤቷ የወጣች ሴት ዝሙተኛ ናትና ወደ ቤቷ ተመልሳ የጀናባ ትጥበትን ትታጠብ።" እያሉ፣ ተቀባብቶ መውጣቱ ሀራም መሆኑን እያወቅሽ፣ ተቀብተሽ እየወጣሽ ተመልሰሽም እንደ ጀናባ ትጥበት መታጠብ ሳትችይ ነው እንዴ ስለምወዳቸው ነው መውሊዳቸውን የማከብረው ምትይው? ትንሽ እንኳን ሀፍረት አይሰማሽም በአላህ?! አትሸማቀቂም?! ይልቅ ወደራስሽ ተመለሺ፣ ሱናቸውን ካላወቅሽ ተማሪ!! ቁርኣንና ሀዲስን በትክክለኛ ሰዎች ተማሪ። ተግብሪው። ዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ለባሏና ለተወዳጁ ነቢይ ፍቅሯን እና ውዴታዋን የገለፀችበት መንገድ (እሱም ችለሽ ከተገበርሺው) በቂሽ ነው!!! እሷ የገለፀችበትን መንገድ ለማወቅ ከፈለግሽ፣ ቁርኣንና ሀዲስን ሳያጭበረብሩ በትክክል በሚያስተምሩ ሰዎች ላይ መማር ነው። ⑦ » አላህ ዲኑን ሙሉ አድርጌዋለሁ እያለ ነው፣ አንተ ከዲኑ ውጪ የሆነውን መውሊድን አከብራለሁ ስትል፣ ከአላህ በላይ በዲኑ ላይ ህግ አወጣለሁ ስለ ዲኑም አውቃለሁ እያልከ ነውን?? "ዑለማዎች እንዲከበር አዘዋል" አትበለኝ!! ⑧ » የትኛዎች ዑለማዎች ናቸው? እነዚያ መንገዱን ተሳስተው አሳሳቾች ናቸው? ነቢዩ ﷺ ጠመው አጥማሚ መጥፎ የጥመት ዓሊሞች ያሉዋቸው ናቸው? ⑨ » ወይስ ከነቢዩ ﷺ ዲኑን አቀበት ቁል ቁለቱን፣ ጋራ ሸንተረሩን፣ ወጥተው ወርደው ቸነፈር እያሰቃያቸው፣ ወርሰው በትክክል ያስወረሱንን እንደ እነ ኢማሙ ሻፊዒይና ኢማሙ አህመድ ያሉ ብርቅዬ የጨለማ ማብራት የነበሩ ከዋክብቶችን ነው ምትለኝ? » እነሱ መውሊድን አክብረዋልን? የታለ ማሰረጃህ? ኢማሙ አቡ ሀኒፋ፣ ኢማሙ ሻፊዒይ፣ ኢማሙ አህመድ፣ ኢማሙ ማሊክ አክብረዋል???? ይልቅ በትክክል የአላህ እና የመልእክተኛው ﷺ ወዳጅ ነኝ ካልን፣ በምን እንደሚገለፅ እንዲህ በማለት አላህ በተቀደሰው ቃሉ መልሱን በአጭሩ አስቀምጦታል:- ﴿قُل إِن كُنتُم تُحِبّونَ اللَّهَ فَاتَّبِعوني يُحبِبكُمُ اللَّهُ وَيَغفِر لَكُم ذُنوبَكُم وَاللَّهُ غَفورٌ رَحيمٌ﴾ آل عمران ٣١ “በላቸው:- አላህን የምትወዱ እንደሆናችሁ #ተከተሉኝ፣ አላህ ይወዳችኋልና። ኃጢያቶቻችሁንም ለናንተ ይምራልና። አላህ መሃሪ አዛኝ ነው።” ኣል ዒምራን 31 እውነት ከልባችን አላህን እና መልእክተኛውን ﷺ የምንወድ ከሆነ ውዴታችን መግለፅ የምንችለው በትክክል መልእክተኛውን በመከተል ብቻና ብቻ ነው!!። ብዙ ማለት ብፈልግም፣ ብዙ ሰው ረጅም ፅሁፍ ማንበብ ስለማይወድ እዚህጋ ለማቆም እገደዳለሁ። ✍🏻ኢብን ሽፋ: ረቢዐል አወል 1/1442 ዓ. ሂ #Join ⤵️ የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join ያድርጉና ይቀላቀሉ https://telegram.me/IbnShifa https://telegram.me/IbnShifa
نمایش همه...
[ኢብን ሽፋ Ibn Shifa]

እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ! በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ! ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ! ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

“እነሆም፥ ከጻፎች አንዳንዶቹ በልባቸው፦ ‟ኢየሱስ አምላክ ነኝ ብሎ እያሰበ መሆን አለበት” አሉ።” ኢየሱስም አሳባቸውን አውቆ ‟ስለ ምን በልባችሁ እንዲህ ያለ ሰይጣናዊ ነገር ታስባላችሁ?” አላቸው — ማቴዎስ 9÷3-4 (CEV Bible) ▸ አዎ እንዲህ ያለ ነገር ማሳብ በራሱ ሰይጣናዊ አሳብ ነው። https://t.me/mahircomp123
نمایش همه...
ቻናላችንን #join እንዲሁም ፖስቶቹን #share በማድረግ ይተባበሩን። http://t.me/TulabAlilm http://t.me/TulabAlilm ግሩፓችንንም #join በማለት #ይቀላቀሉ!! https://t.me/Tulab_Al_ilm_Group https://t.me/Tulab_Al_ilm_Group
نمایش همه...
نمایش همه...
👑قناة طلاب العلم👑

አስተውል አንተ የአላህ ባሪያ!!! ~ ሰዎች ዘንድ ለመወደድ ስትለፋ ጌታህ ዘንድ እንዳትጠላ ተጠንቀቅ። ~ ለምትወዳቸው ሰወች ክብር ስታበዛ የጌታህን ክብር እንዳትነካ ተጠንቀቅ። ~ ሰወችን በመውደድ ብቻ ስትጠመድ የጌታህን ውዴታ እንዳትነፈግ ፍራ! ጥላቸው ማለት አይደለም ውዴታህ በልክ ይሁን! ~ እውነት ለመናገር ከሰወች ጥቅምን አትፈልግ! ሰወችን ለማስደሰት አትዋሽ! ለህሊናህ እረፍት አስበህ እውነተኛ ሁን! ~ የራስክን ደስታ ለማሞቅ ለሌሎች ሃዘን ሰበብ አትሁን! በሌሎች ደስታ ተደሰት! ከምቀኝነት እራቅ! ~ ለጥፋት መሆንን እንጂ መባልን አትፍራ! ሆኖ ለመገኘት እንጂ ለመባል አትድከም። ~ ፍርድ ለመስጠት ከመወሰንህ በፊት ዳኛ ለመሆን አቅሙ እንዳለክ እራስክን ጠይቅ። ~ ለመውቀስ ከመቸኮል ለማጣራት ሞክር ! መልስ ከመስጠትህ በፊት ጥያቄውን አስተንትን! ~ ማንነትህን ለማሳወቅ በአፍህ ከመናገር ይልቅ ስራበት! ተግባርህ ያስረዳ! ~ መልካም ለመሆን አትምረጥ። ለሁሉም መልካም ሁን አትጎዳበትም። ~ ክብርን ለማግኘት ክብር ከሌለው ተግባር ተቆጠብ! ~ ሀቅን እንጂ ሰወችን አትከተል። ~ መኖርህን ስታይ መሞትህንም አትርሳ! ኖረህም የሚጠቅምህን ስትሞትም የሚከተልህን ስራ!! ┈┈•••✿❒🌹❒✿••• ┈┈ ቻናላችንን #join እንዲሁም ፖስቶቹን #share በማድረግ ይተባበሩን። http://t.me/TulabAlilm http://t.me/TulabAlilm ግሩፓችንንም #join በማለት #ይቀላቀሉ!!

https://t.me/Tulab_Al_ilm_Group

https://t.me/Tulab_Al_ilm_Group

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.