cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Getachew shiferaw

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
44 303
مشترکین
-1424 ساعت
-1417 روز
-87930 روز
توزیع زمان ارسال

در حال بارگیری داده...

Find out who reads your channel

This graph will show you who besides your subscribers reads your channel and learn about other sources of traffic.
Views Sources
تجزیه و تحلیل انتشار
پست هابازدید ها
به اشتراک گذاشته شده
ديناميک بازديد ها
01
Media files
4 4756Loading...
02
ኤርሚያስ ያችን በርቀቀቀቀቀቀቀቀት የምታበራውን ንፋስ የሚያውለበልባትን ሻማ ከትህነግ/ህወሓት ቀምቶ ለኦህዴድ ሸጣት! አሜን የጌታ ሰው😂😂😂 ያችኛዋ ኮምፓስ ተሳስቶብኝ ያየኋት ራዕይ ነች ብሏል😂
4 4700Loading...
03
Media files
9 11211Loading...
04
በሚሊዮን የሚቆጠር የራያና የወልቃይት መታወቂያ እየተሰራጨ ነው! ብልፅግና በአማራ ግዛቶች አስተዳደሮችን አፍርሶ "በፌደራል ስር ሆነው ሕዝበ ውሳኔ ይሰጥባቸዋል" ብሎ ነበር። እውነታው ግን ለትህነግ አሳልፎ ሰጥቶ የትግራይ ወጣት ህገወጥ የራያና ወልቃይት መታወቂያ በገፍ እየታተመ እየታደለው እንዲሰፍር እየተደረገ ነው። የፈለገ የትግራይ ስራ አጥ ወጣት የራያ ይሁን የወልቃይት መታወቂያ ይታደለዋል። ትህነግ በሀሰት በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃይ አለኝ ባለው መሰረት በአማራ ግዛቶች ህዝብ ለማስፈር በሚሊዮን የሚቆጠር መታወቂያ ተዘጋጅቶ እየተሰራጨ ነው። ብልፅግና በመከላከያ ስር ሆኖ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል ቢልም አሳልፎ ሰጥቶ መታወቂያ እየታተመ የህዝብን አሰፋፈር ለመቀየር እየተሰራ ነው። በግልፅ "መታወቂያ ውሰዱ" እየተባለ እየተሰጠ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ሆነ ብልፅግና በየዕለቱ መከርኩበት የሚለው ይህን አይልም። ይህ የጓዳ ውሉ ውጤት ነው! እርባና ቢሱ ብአዴን ደግሞ ዝምታን መርጧል።
9 23813Loading...
05
መታገያችሁን አትልቀቁላቸው! 1) ጦርነት ያወጀውና ንፁሃንን እየገደለ ያለው ብልፅግና ነው። "ጦርነት ይቁም" ሲባል ጦርነት የጀመረው አካል እንዲያስቆም አስቀድማችሁ ተከራከሩ። "ድርድር" ወዘተ ተብሎ ጦርነቱ ይቁም ሲባል "እሽ ነገር ግን.." ካላላችሁ መከራከሪያችሁን ወስዶ በሀሰት እናንተን ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ ሕዝብን ጦረኛ ያስመስልበታል። ጦርነት አውጆ፣ ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ሰላም ፈላጊ ይመስልበታል። 2) ከበርካታ ኃይል ጋር ጦርነት ውስጥ ያለው አገዛዙ ነው። ድርድር፣ ጦርነት ይቁም ወዘተ ሲባል የእሱን ጦረኝነት ርዕሰ አድርጋችሁ፣ ደጋግማችሁ እያስታወሳችሁ "ይሁን፣ ነገር ግን" እያላችሁ ቅድመ ሁኔታችሁን አጥብቁ። 3) አገዛዙ የህዝብ ጥያቄ ደፋቂ ነው። አደባባይ ይዞት የሚወጣው የህዝብ ጥያቄ የለም። ለቅድመ ድርድር እንኳን የሚነሱበትን ለመተግበር ጭንቅ የሚይዘው ነው። አዋጁን ለማንሳት የሚፈራ፣ እስረኛ ለመፍታት የማይደፍር ነው። ቅድመ ሁኔታና የህዝብ ጥያቄ እንደ በረዶ ለሚያሟሟው፣ የራሱን የወረዳ ፍርድ ቤት ለማያምን አገዛዝ "ድርድር" ወዘተ ተብሎ የሚኖር ቅድመ ክርክር በሚያጋልጠው መንገድ መጠቀም እንጅ አራጅ ሆኖ ሰላማዊ እንዲመስል ቦታ አትልቀቁለት። ሰላም ፈላጊ መስሎ እንዳይታይ አድርጉ። 4) አገዛዙ የምዕራባውያን አገራት ጋር ጥል ውስጥ የገባባቸው ጉዳዮች አሉ። በአማራ ላይ በከፈተው ጦርነት እንኳን ተቋሞቻቸው በትንሹም ጨፍጫፊ መሆኑን ለማሳየት ጥረዋል። ዲፕሎማሲ የጠፋበትንና የተበላሸበትን ቡድን "እነሱ ናቸው ሰላም የማይፈልጉት" የሚል ምስኪን እንዲመስል እድል አትስጡት። 5) ስልጣን ለመያዝ የጀግንነት ፍልሚያ ብቻ በቂ አይደለም። ዓለም አቀፍ ድጋፍ ያስፈልጋል። የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መልካም ፊት ያስፈልጋል። በህዝብ ላይ በደረሰው በደልም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች በዲፕሎማሲው ላይ ፊት አለማጥቆር አዋጭ ነው። ወስላታነት አይደለም። ተለማማጭነት አይደለም። 6) ዲፕሎማሲ ከራስ ይጀምራል።ማዶና ማዶ ሆኖ በዳያስፖራውም መሬት ላይ ያሉትን ፋኖዎች ለማጣላት የሚደረገውን ሂደት ቶሎ ማስቆም ተገቢ ነው። ስለ አራት ኪሎ እየተወራ ከሰፈር ሚሊሻ ጋር የሚደረገው ከልክ ያለፈ ወደኋላ መመለስ፣ የሀይማኖት አባቶች ጉዳይና ወዘተ ግዙፍ ጥያቄን ያነሰ ያስመስለዋል። አኩርፋችሁ የምትተውት፣ ስቃችሁ የምታልፉት፣ ትኩረት የማትሰጡት፣ ሽምግልና ልካችሁ ተው የምትሉት፣ የምትገጥሙት፤ ቀጠሮ የምትይዙለት ጠላት ይኖራል። ሁሉም አንዴ አይቻልም። ድርድር ማጋለጫም፣ ቀጠሮ ማስያዥያም፣ ከተቻለ ደግሞ ማሸነፊያም ነው። 7) እስር ቤት ሆነው ሊደራደሩ፣ ጫካ ሆነው ሊደራደሩ፣ ውጭ ሆነው ሊደራደሩ እየተባለ በቲክቶክ ወዘተ የሚነዛው ማሸማቀቅ የለበትም። ተመሳሳይ አቋም ይዞ ለድርድር ተገቢ መልስ መስጠት ነው የሚያዋጣው። ይህን ወጥመድ በጥንቃቄ ማለፍ ያስፈልጋል። ካልሆነ ምዕራባውያኑም አቅምና የህዝብ ድጋፍ ሳያንሳችሁ በዚህ ብቻ የተሳሳተ አቋም ይዘው የሚመስላቸውን አደራጅተው ለድርድር ይመጣሉ። አገራትም "ክብራችን ነኩ" ወዘተ ይላሉ። አገዛዙ ለእሱ የሚሆነውና የሚቀርበውን ካዘጋጀ ቆይቷል። ለአገዛዙ ኃይል ቦታ መልቀቅ ኪሳራ ነው። በጦርነቱ ብቻ ነው የምንገኘው የሚባል የነፃነት ትግል የለም። ተሳካም የቁማር አካል ሆነም ድርድሩም ወዘተ የትግል አካል ነው። ያለ ፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጦርነት ከመስዋዕትነት ያለፈ ሊሆን አይችልም። ፖለቲካና ዲፕሎማሲ መስዋዕትነትን ወደ ድል ያደርሱታል።
11 00911Loading...
06
Media files
12 5835Loading...
07
የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ነው! ትህነግ ወርሮ ይዞት በቆየውና አዲስ በወረረው የራያ ክፍል አርሶ አደሩን እያፈናቀለ መሬቱን በአስደንጋጭ ሁኔታ እየሸጠ ነው። ዳያስፖራ፣ ባለሀብት፣ ባለስልጣን፣ የባለስልጣን ዘመድ አዝመድ እየተከፋፈለው ነው። ራያም ሆነ ወልቃይትን የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ነው። ግዛቱ የእነሱ ስላልሆነ ነው ሕዝብን እያፈናቀሉ የራሳቸውን አባላት ጭምር ያማረረ መሬት ወረራ ውስጥ የገቡት። አይደለም ዋና ነዋሪ የሆነው አማራውን ተፈናቀለ የተባለ ፈርቶም ወንጀል ሰርቶም የሸሸውን ትግሬ እስካሁን አስመዝግቡ በተባሉት መሰረት አላስመዘገቡም። አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። ተፈናቃይ መልሱ ሲባሉ ታጣቂ የላኩት ለዝርፊያና ወረራ ነው። በመጀመሪያዎቹ ቀናት 50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለው በትህነግ የመሬት ወረራ፣ ዘረፋና በቀል ምክንያት ነው። ለ30 አመታት ህዝብ እያፈናቀለ መሬት ሲወር ኖሯል። በግልፅም "መሬቱንና ሴቶቻችሁን ነው የምንፈልገው" ሲል የኖረ አረመኔ ነው። አሁንም በተፈናቃይ ስም የሚደረገው ወረራ አላማው መሬት ወረራ ነው። ሕዝቡን ጠላታችን እያሉ፣ እየገደሉ፣ እያፈናቀሉ፣ እየዘረፉ ያሉት የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ስለሆነ ነው።
12 2436Loading...
08
Media files
15 7922Loading...
09
ይህን ያህል የህዝብ ጥላቻ ከየት የመነጨ ነው? ኤርሚያስ ለገሰ የትህነግ/ህወሓት አመራሮች በ60 ቀን ግምገማ ሲጠዛጠዙ ሁለት ወር ሙሉ በየቀኑ ዝግጅት ሲሰራ ስለ ልዩነት አንድ ጉዳይ አልጠቀሰም። እንዲያውም "ጭላንጭል ይታየኛል" ሲል ነበር። እነ ጃልመሮና ጃል ሰኚ የሚባሉት ሲጣሉ ስለ ልዩነት ያለው ነገር የለም። የኦሮሚያ ብልፅግና ሲቧደን ቢውል ኤርሚያስ ስለ ልዩነት አይጠቅስም። የትህነግ ታጣቂ የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ተሳትፏል ሲባል ትህነግን ሱዳን ድረስ ተከትሎ ሄዶ አስተባብሎለታል። ሌላው ቀርቶ ብርሃኑ ጁላና ታደሰ ወረደ መካከል ልዩነት እንዳይፈጠር ወዘተ እያለ ለትህነግ ሲጠነቀቅ ይውላል። አማራ ላይ ግን የሀሰት ዘመቻውን ይከፍታል። ራሱ ተከፍሎት እርስ በእርስ ለማጋጨት የፃፈውን ሰነድ ለአማራ ይሰጠውና አመት ሙሉ ይለፋደድበታል። ሰሞኑን ደግሞ የፋኖ አመራሮች ልዩነት የፈጠሩ መስሎት ጮቤ እየረገጠ ነው። በቀደም የ2 ሰዓት ፕሮግራም ሰርቶበት አልበቃውም። ትናንት ለ3 ሰዓት የሚጠጋ ፕሮግራም ሰራበት። ይህም አልበቃውም ከዛ ልዩነት ያሰፋል ካለው መካከል በደንብ ይጠቅመኛል ያለውን ርዕሱን ጎላ አድርጎ ሰቀለው። አማራን የሚጎዳ የሚመስለውን እያንዳንዱን ክር እነ በረከት ባስተማሩት ውስልትና መሰረት ሲመዝ ይውላል። ይህን የመሰለ የማይፈን የህዝብ ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው? ቢከሰስ ለጠበቃ የከፈለለት አማራው!
13 1876Loading...
10
ባለቤቶቹ አልሸፋፈኑትም! የትህነግ ታጣቂ የሱዳን መደበኛ ኃይል አካል ሆኗል! ከስር ያለውን መረጃ ያጋራው አባቱ በሱዳን አምባሳደር የነበረ፣ የጌታቸው ረዳ ደጋፊ አክቲቪስት ነው። መረጃው የትህነግ/ህወሓት ታጣቂ በሱዳን ጦርነት ከመሳተፍ አልፎ እንደ ሱዳን መደበኛ ጦር የሱዳን ተቋማትን እየጠበቀ ስለመሆኑ ነው። በሱዳን ያለው የትህነግ/ህወሓት ኃይል ለጊዜያዊ ጦርነት ሳይሆን የሱዳንን ተቋማት እስከመጠበቅ የደረሰ አብሮ መስራትና መታመን ድረስ የደረሰ ነው። ጉዳዩ አልቡርሃንን የመደገፍ ጉዳይ አይደለም። አብረው እየሰሩ ነው። እንደ መደበኛ ጦር ተቋም እየጠበቁ ነው። ይህ የትህነግ ጦር ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ወደ ትግራይ እንዲያልፍ ተጠይቆ የነበር ቢሆንም "ጦር የለኝም" ያለው ትህነግ/ህወሓት "ይቆይ ብሎ በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲሳተፍ አድርጎታል። ብልፅግና ደግሞ ይህን የመሰለ የፈጠጠ ሀቅ "አጣራለሁ" እያለ ይቀልዳል። ባለቤቶቹ ይህን የመሰለ መረጃ በመ
14 3515Loading...
11
Media files
17 3509Loading...
12
ነገሩ ይበልጥ ግልፅ ሆኗል! ለእነ አልቡርሃን መሳሪያ የሚያቀብለው ባለሀብት ታስሯል። የትህነግ/ህወሓት ባለስልጣን ሚስጥር ያወጣብን ጌታቸው ረዳ ነው ሲል ከስሷል። 1) ሰሞኑን ታደሰ ወረደ ቀርቦ በተናገረበት ሚዲያ ከሶስት ወር በፊት ጌታቸው ረዳ ከስልጣን ያባረረው የህወሓት አመራርም ቀርቦ ጌታቸው ሚስጥር እንዳወጣ ጠቁሟል። ሚዲያውም ርዕሱን በግልፅ ጌታቸው ለአረብ ኢሜሬትስ ባለስልጣናት መናገሩን በሚገልፅ መልኩ ነው ያስቀመጠው። 2) የህወሓት ባለስልጣን የሆነው አባዲ ዘሙ ልጅ ዳዊት ገብረእግዚያብሔር የሚባለው የሞንጆሪኖ ወንድም በሌላ አገር በኩል ወደ ትግራይ ሲገባ የተቀበለው ጌታቸው ረዳ እንደሆነና ከእነ ጌታቸው አሰፋ ጨምሮ ከትህነግ/ህወሓት አመራሮች ጋር መምከሩን ሰሞኑን ፅፎ ነበር። ይህ ባለሀብት በትህነግ የስልጣን ዘመን ለመከላከያ ጭምር መሳሪያ ደላላ የነበረ ሲሆን ከትህነግ/ህወሓት ጋር በነበረው ጦርነት ለትህነግ በሱዳን በኩል በአልቡርሃን ድጋፍ መሳሪያ አስገብቷል። ከአረብ አገር የመሳሪያ ደላላዎች ጋር የሚሰራ ሰው ነው። በጦርነቱ ወቅት ከትግራይ በጀት መዳቢዊ እህቱ ሞንጆሪኖ ነበረች። በአንድ ግምገማቸው ሞንጆሪኖ ወደ ሱዳን የላከችው የፀረ ድሮን መግዢያ መበላቱ ታምኖበታል። ዳዊትና እህቱ በሱዳን በኩል በአልቡርሃን እገዛ መሳሪያ ሲገዙ የከረሙ ናቸው። አሁንም ለአልቡርሃን መሳሪያ ማስገባታቸውን መቀጠላቸው ተሰምቷል። 3) የኤርትራ ደህንነት መስሪያ ቤት መረጃ የሚሰጠው አንድ ሁነኛ የኤርትራ ሚዲያ ደግሞ ባለሀብቱ በቅርቡ የሱዳን ጦርነት ወቅት ለአልቡርሃን መሳሪያ እያስገባ እንደሆነ ተደርሶበታል ብሏል። በዚህ ምክንያት ሰሞኑን ባለሀብቱ የታሰረው በአረብ ኢሜሬትስ ሲሆን አረብ ኢሜሬትስ የፈጥኖ ደራሹ ደጋፊ፣ ትህነግ በእነ ዳዊት በኩል ለአልቡርሃን መሳሪያ አድራሽ ሆነው የጥቅም ግጭት ውስጥ እንደገቡ ተፅፏል። የኤርትራው ደህንነት ምንጭ ዳዊት የተያዘው ከመቀሌ በወጣ ሚስጥር እንደሆነ ገልፆአል። 4) የትህነግ/ህወሓት አክቲቪስቶች ደግም ባለሀብቱን ያስያዘው ጌታቸው ረዳ ነው ብለው እየፃፉ ነው። 5) ለአልቡርሃን መሳሪያ የሚያቀርበው የሞንጆሪኖ ወንድም በህገወጥ መንገድ ድንበር አቆራርጦ ትግራይ ገብቶ ከትህነግ/ህወሓት አመራሮች ጋር መነጋገሩ ከዚህም ከፍ ያለ አላማ መኖሩን ያሳያል። ሰሞኑን የታሰረው ጅቡቲ ውስጥ ነው ወዘተ የተባለው ከትግራይ በጅቡቲ በኩል ሲሸኙት ይሁን ደጋግሞ ሲመላለስ አልታወቀም። ነገር ግን ወደ ትግራይ የተመላለሰበትን አላማ ለመደበቅ "ጅቡቲ ያለውን ፕሮጀክቱ ሲጎበኝ ተያዘ" እያሉ ለመሸፋፈን ጥረዋል። አጠር ሲል! 1) ትህነግ ከታጣቂ አልፎ በትጥቅም ከአልቡርሃን አቅርቦት በማገዝ ጋር መሆኑን አመራርና አባላቱ አምነዋል። 2) እነ ጌታቸው ረዳ ከትህነግ/ህወሓት አላማ ስለተለዩ ሳይሆን በአካሄድ ልዩነትና ስልጣን ጉዳይ በሱዳን ጦርነት መሳተፋቸውን ያመኑ መሆኑን። 3) በጊዜያዊ ስልጣን ከጌታቸው ረዳ ጋር ልዩነት ያላቸው ጌታቸው ረዳ አሳልፎ ሰጠን ማለታቸውን 4) የትህነግና የአልቡርሃን ጉዳይ የዓለም አቀፍ መሳሪያ ዝውውርንም የሚጨምር፣ በዚህ ጉዳይ በተጨባጭ የተሳተፈው ባለሀብት መታሰሩንም የሚያሳይ ነው። 5) ባለሀብቱ ለሱዳኑ ጀኔራል መሳሪያ ከማቅረብ አልፎ በህገወጥ መንገድ ድንበር አቆራርጦ ትግራይ ድረስ መጥቶ ከእነ ጌታቸው አሰፋ ጋር የመከረው መቀሌ ናፍቃው ሊሆን አይችልም።
16 35811Loading...
13
Media files
23 05610Loading...
14
በራሳቸው አክቲቪስት ተጋለጡ! የእነ ጌታቸው ረዳ የቅርብ ሰው፣ ዳዊት ከበደ ትህነግ በመግለጫ ሊያስተባብለው የማይችለውን ሚስጥር አውጥቷል። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ትህነግ/ህወሓት ከአልቡርሃን ጋር ሆኖ ወጋኝ በማለቱ ማስተባበያ የተሰጠ ቢሆንም ውስጥ አዋቂያቸው ዳዊት ግን የባሰ ነገር ይዞ መጥቷል። ጌታቸው ረዳ UAE ሄዶ ከአልቡርሃን ጋር ሆነው እየተዋጉ መሆኑን አምኖ እንደመጣ አስቀምጧል። ዳዊት ከበደ። የሱዳኑ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ጌታቸው ረዳ ካመነ በኋላ ነው መግለጫ ያወጣን ይላችኋል የትህነግ ሚስጥረኛ። ጌታቸው ረዳ አልቡርሃንን እኛ እየደገፍነው እንገኛለን ብሎ በትህነግ/ህወሓት ላይ መረጃ አውጥቷል ብሎ ነው የፃፈው። የሰሞኑ ማስተባበያ በህወሓት አመራሮች ዘንድ ጌታቸው ረዳ ነው ጠቋሚ እየተባለ እንደሆነ ነው የተገለፀው። ትህነግ/ህወሓት በሱዳን ጉዳይ እጁ እንደሌለበት ቢናገርም ውስጥ አዋቂያቸው ግን እነ ደብረፅዮን የሰጡትን መረጃ ፅፎታል። ስለሆነም ራሱ ጌታቸውረዳ ከአልቡርሃን ጋር እየሰራን ነው ብሎ አምኗል። ይህን ዜና ሊያስተባብሉ የጣሩት እነ ኤርሚያስ ለገሰ ውሃ በላቸው ማለት ነው።
23 08811Loading...
15
Media files
22 27720Loading...
16
ብልፅግና ይህን ጉድ መሸፈን አይችልም! ፈፅሞ! ታደሰ ወረደ ሳይሸፋፈን ጥሬውን ዘርግፎታል። "ትጥቅ አልፈታንም። ፍቱ ያለንም የለም።" ታጣቂም በሰፋሪ ስም ይመለሳል ታደሰ ወረደ ወደ አማራ ግዛቶች ተፈናቃይ ተብሎ ይመለስ የተባለው ሰፋሪ እንደሆነ ሳያስበው አውጥቶታል። ወልቃይትና ራያን የማያውቁ ከተለያዩ የትግራይ ክፍሎች የነበሩ አካላት ናቸው ተፈናቃይ ተብለው እንደ አዲስ የሚሰፍሩት። ሊያስተካክል ሞክሯል። እውነታው ግን አምልጦታል። በጓዳ ውል የተፈፀመውን ታደሰ ወረደ ተናግሮታል። ብልፅግና ይህን መረጃ ማስተባበል አይችልም።
21 47310Loading...
17
Media files
24 3306Loading...
18
የሱዳን ዋና ዋና ሚዲያዎችኀ ትህነግ/ህወሓት የአልቡርሃን ቆጥረኛ ሆኖ በሱዳን እየተዋጋ መሆኑን ቀዳሚ አጀንዳ አድርገዋል። ይህን ቅጥረኛ ኃይል ነው ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ተፈናቃይ ብላችሁ መልሱ እየተባለ ያለው።
21 6293Loading...
19
Media files
20 4305Loading...
20
የፕሪቶሪያ ስምምነት መቆመሪያቸው ነው! ስምምነቱ እነ ጌታቸው ረዳ ከአማራ ለመንጠቅ የሚፈልጓቸውን ግዛቶች "የተወረሩ" አይላቸውም። "አወዛጋቢ" ነው የሚላቸው። በዚሁ ስምምነት መሰረት የጥላቻና የጦርነት ቅስቀሳ የተከለከለ ነው። በትህነግ በኩል ፈራሚው ጌታቸው ረዳ ግን አሁንም "ወራሪ" እያለ እየፃፈ ነው። የሰላም ስምምነት ተብሎም ለእሱ አማራ ወራሪ ነው። ስምምነቱ መቋመሪያ ካርድ እንጅ እንደማያከብሩት ይታወቃል። በጓዳ ግዛቶቹን አሳልፎ ለመስጠት የሚስማማው የአብይ አገዛዝም በስምምነቱ መሰረት ባቋቋመው ኮሚቴ ይህን እንደማይገመግም ይታወቃል። የአማራ ክልል ጉልት ካድሬ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት በስሩ እንዲቆይ የተወሰነውንም አስተዳደር አፍርሶ ትግራይ ውስጥ አንድ ቀበሌ በቅጡ ለማያስተዳድረው፣ ስካይ ላይት መቀመጫውን ላደረገው ጌታቸው ረዳ አሳልፎ ሰጥቷል። በዚህ ከቀጠለ አብይ አጠቃላይ አማራ ክልልን ለጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ቢሰጠውም ከዝምታ የተሻለ ከአማራ ክልል ካድሬ እንደ አማራጭ የሚቆጠር ስልት ያለ አይመስልም። በዚህ በዓል መልዕክት ቀርቶ በሌላም ጊዜ በአማራ ላይ አፍ መክፈትን የህዝብ መሰብሰቢያ ካደረጉት የትህነግ አመራሮች ውጭ ጦርነት እየቀሰቀሰ ያለ አይመስልም። ለትንሳኤ በዓል መልዕክት እንኳን አማራን በለመዱት ክፍታፍነታቸው ከመዝረፍና ከመውቀስ የሚመለሱ አይደሉም።
21 0064Loading...
21
Media files
16 4792Loading...
22
የባልደራስን ንቁ አባላት ያሳሰረው ኤርሚያስ ለገሰን ተንኮል ተመልከቱ! የኤርሚያስ ወዳጅ የነበረው ቴድሮስ ፀጋዬ ሰሞኑን ኤርሚያስ የባልደራስ ንቁ አባላትንና የአዲስ አበባ ወጣቶችን እየጠቆመ እያሳሰረ እንደሚገኝ በቀጥታ ስርጭት ተናግሯል። ይህን የባልደራስ የቅርብ አመራሮችም አረጋግጠውልኛል። ትናንት የሰራውን ፕሮግራም እንኳን ተመልከቱ። ያሳሰራቸው የባልደራስ ንቁ አባላት መካከል ናቲን ፎቶ የፊት ገፅ ላይ ሆን ብሎ አቀናብሮ ከሚከሳቸው የፋኖ አባላት ጋር አቅርቧል። ኤርሚያስ ለፕሮፖጋንዳ የሚጠቀምበትን እያንዳንዱን ጉዳይ የሚያውቅ ሰው ነው። የፊት ገፅ ሲያሰራ ምን ማስተላለፍ እንደፈለገ ግልፅ ነው። ከሰላማዊ መንገድ ውጭ የትጥቅ ትግሉ ላይ ፈፅሞ የሌሉበትን ወጣቶች ፎቶ ሾፕ እየሰራ ጭምር የሀሰት ጥቆማውን እውነት ለማስመሰል እየሰራ ያለ አደገኛ ሰው ነው። ከቅርቡ የአዲስ አበባ ክስተት በኋላ አዲስ አበባ ላይ ሽብር የሚፈፅሙት የከተማው ተወላጆች ጭምር አሉ ብሎ የአዲስ አበባን ወጣት በሀሰት ከስሷል። በተለይ በተለይ ባልደራስ ሰልፍና ስብሰባ ሲያደርግ ንቁ እንቅስቃሴ ያደርጉ የነበሩ፣ በሚዲያ ያግዛል ተብሎ መረጃ የሚሰጡትና ለፓርቲው ሰላማዊ እንቅስቃሴ በተለያያዩ የማህበራዊ ሚዲያ ግሩፕ ውስጥ የነበሩትን ለአገዛዙ እየጠቆመ አሳስሯል። የባልደራስ አመራሮችም ያረጋገጡት መረጃ ነው።
20 2553Loading...
23
Media files
16 16612Loading...
24
ይህንማ አላያችሁትም! አላያችኋትም! ታደሰ ወረደ በቀደም አብይ ጋር ተሰብስቦ፣ ትናንት ደግም ከሳምንት በፊት "መወገድ አለበት" ብላ ፕሮግራም ከሰራችው ሴትዮ ጋር አመሸ። በቀደም ተመስገን ጥሩነህ ጋር ተገማግም፣ ተመስገን በጀኖሳይድ መጠየቅ አለበት ካለችው ጋር ተመሰጋገነ። እንዲች ናትና! በነገራችን ላይ ታደሰ ወረደ ከኮሚቴው ጋር የሚገማገመውን ለትህነግ/ህወሓት ሚዲያዎች ያደርሳል። ትናንት ማታ ግምገማውን በሙሉ ለኤርሚያስ ሰጥቶ ለእነሱ በሚጠቅም መልኩ አሰራው፣ ራሱ ደግሞ በዚህ ሚዲያ ቀረበ። ልጨምርላችሁ! በዚህ ሚዲያ ለታደሰ የቀረበው ጥያቄ ኤርሚያስ የሰራበት ነው።
15 7358Loading...
25
Media files
23 6502Loading...
26
የሚገርሙ፣ የሚያሳዝኑም ጉዳዮች ናቸው! 1) የጌታቸው ረዳ ጊዜያዊ አስተዳደር ከመቀሌ ውጭ ተንቀሳቅሶ ስብሰባ ማድረግ እንደማይችል ራሱ ጌታቸው ለትግራይ ሕዝብ ተናግሯል። ትግራይን የሚያስተዳድረው ከጦርነቱ በፊት የነበረው፣ ወንጀለኛ የተባለው መዋቅር ነው። ይህን ጌታቸው ረዳ በሚዲያ ወጥቶ ያረጋገጠው ነው። ይህ ህገወጥ መዋቅር ስለሆነ ነው ጊዜያዊ አስተዳደር ማዋቀር ያስፈለገው። ትግራይ ውስጥ ከመቀሌ ውጭ ስብሰባ እንኳ ማድረግ የማይችለው የጌታቸው ረዳ አስተዳደር፣ በህጋዊ ስምምነት የተሰጠውን ትግራይን እንዳያስተዳድር ተደርጎ፣ በማያገባው ከትግራይ ውጭ ያሉትን የአማራ ግዛቶች እንዲያስተዳድር ነው የተደረገው። ሰሞኑን ትህነግ በወረራቸው የአማራ አካባቢዎች ጊዜያዊ አስተዳደሩ መዋቅሩን አሰማርቷል። ትህነግ ለጊዜያዊ አስተዳደሩ የፈቀደለት የወረራ አላማ ስለሆነ ነው። ትግራይ ውስጥ አንድም ቀበሌ እንዳያስተዳደር የተደረገው ጌታቸው የአማራን አካባቢዎች ግን በህገወጥ መንገድ እንዲይዝ ተደርጓል። 2) ሰሞኑን በትግራይ ፖለቲካ አጀንዳ የሆነ ጉዳይ አለ። ትህነግ የአማራ አካባቢዎች ተወልደው ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደላችሁም" እንዳላቸው የጊዜያዊ አስተዳደሩ አመራር ረዳኢ ሓለፎም ቃል በቃል ተናግሯል። የትግሬ ካባ የሚሰጠንም የሚቀማንም ሌላ ቡድን አለ ብሏል። የአድዋውን ቡድን ነው። ታዲያ ራያ ያደጉትን አመራሮቹን "ትግሬ አይደሉም። ባንዳ ናቸው።" ወዘተ እያለ የሚፈርጅ ራያን መሬቱንና መሬቱን ብቻ እንደሚፈልግ ግልፅ ነው። አመራሮቹን በጠላትነት የፈረጀ ለሕዝቡማ ያለው ጥላቻን መገመት ቀላል ነው። በተደጋጋሚ በተግባርም የታየ ነው። 3) ራያን የወረረው የትህነግ ታጣቂ "አርሚ 24" ይባላል። መከላከያን በመታበት ጥቅምት 24 የተሰየመ ነው። መከላከያ የተገደለበትን ቀን ማስታወሻ ያደረገውን ኃይል ነው እያገዘ የሚገኘው። 4) የሰላም ስምምነቱ ያለ ምንም ማወላዳት የደነገገው፣ የጊዜ መንዛዛት ያልተቀመጠበት የትጥቅ መፍታት ነው። በማያሻማ መልኩ በአንድ ወር ውስጥ ትጥቅ ይፍቱ ተብሎ ነበር። ጭራሽ አስታጠቋቸው። መከላከያ ትግራይን ይረከብ ተብሎ ነበር። ጭራሽ መከላከያ ከትግራይ ወጥቶ አማራ ላይ ዘምቶ፣ ትጥቅ መፍታት የነበረበት ትህነግ አማራ ክልልን በኃይል እንዲይዝ ተደረገ 5) ትህነግ ባለፉት ወረራዎች ዘረፋ የሚፈፅሙትን በየጦሩ አደራጅቶ አሰማርቷል። በዘረፉት ልክ ጥቅም አግኝተዋል። እንደ ጀግና ታይተዋል። ይህ ኃይል ግን ወደ ትግራይ ተመልሶ አረመኔ ሆነ። የአርሶ አደር በሬ አርዶ መብላት፣ የተቋማትን ብረታብረት መዝረፍ ወዘተ። ሰሞኑን የትግራይ ክልል ውሃ መሳቢያ ብረቶች እየተዘረፉ መሆኑ በስፋት እየተሰራጨ ነው። ይህን የራሴ የሚለውን ትግራይን እየዘረፈ ያለ ኃይል ነው ጠላቴ ወደሚለው አማራ ይዘውት የመጡት። ከራያ ብቻ ከ50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለውም ይህ አረመኔ ኃይል በሚፈፅመው ወንጀል ምክንያት ነው። ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው አማራ ላይ ነው!
17 2377Loading...
27
Media files
17 8935Loading...
28
የወረራ ዝግጅት! ራያን የወረረው ትህነግ ጠለምትንና ወልቃይትን ለመውረር ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ይገኛል። በዚህም መሰረት በሱዳን በኩል፣ አርሚ 11 ጠለምትን ለመውረር፣ አርሚ 17 ወልቃይትን ለመውረር ዝግጅት ላይ ነው፣ አርሚ 35 ከአክሱም ወደ ሽሬ የተንቀሳቀሰ ሲሆን ጥቅምት 24 መከላከያን የመቱበትን ማስታወሻ ያደረጉት "አርሚ 24" ደግሞ ራያን የወረረው ነው። ይህ በሆነበት ብልፅግና የአማራ አስተዳደሮችን በሕገወጥ መልኩ አፍርሶ በተፈናቃይ ስም የወረራ በር እየከፈተና እያገዘ ይገኛል። እንደ ገለልተኛ "ትጥቅ መፍታት አለባቸው" እያለ የሚቀልደውም ዝግጅታቸውን ስለማያውቅ አይደለም። ማዘናጊያ ነው። በሌላ በኩል በተቃዋሚም ሆነ በሌላ ስም ትህነግ ጋር ስምምነት ለመፈፀም የሚደረግን ሂደት የህዝብ ለህዝብ እያስመሰለ፣ የትህነግን ወረራ የሚያድበሰብስም የትህነግና ብልፅግናን የጓዳ ውልና የወረራ አላማ የሚያስፈፅም የአማራ ጠላት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል።
18 22511Loading...
29
Media files
16 99828Loading...
01:11
Video unavailableShow in Telegram
ኤርሚያስ ያችን በርቀቀቀቀቀቀቀቀት የምታበራውን ንፋስ የሚያውለበልባትን ሻማ ከትህነግ/ህወሓት ቀምቶ ለኦህዴድ ሸጣት! አሜን የጌታ ሰው😂😂😂 ያችኛዋ ኮምፓስ ተሳስቶብኝ ያየኋት ራዕይ ነች ብሏል😂
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
በሚሊዮን የሚቆጠር የራያና የወልቃይት መታወቂያ እየተሰራጨ ነው! ብልፅግና በአማራ ግዛቶች አስተዳደሮችን አፍርሶ "በፌደራል ስር ሆነው ሕዝበ ውሳኔ ይሰጥባቸዋል" ብሎ ነበር። እውነታው ግን ለትህነግ አሳልፎ ሰጥቶ የትግራይ ወጣት ህገወጥ የራያና ወልቃይት መታወቂያ በገፍ እየታተመ እየታደለው እንዲሰፍር እየተደረገ ነው። የፈለገ የትግራይ ስራ አጥ ወጣት የራያ ይሁን የወልቃይት መታወቂያ ይታደለዋል። ትህነግ በሀሰት በሚሊዮን የሚቆጠር ተፈናቃይ አለኝ ባለው መሰረት በአማራ ግዛቶች ህዝብ ለማስፈር በሚሊዮን የሚቆጠር መታወቂያ ተዘጋጅቶ እየተሰራጨ ነው። ብልፅግና በመከላከያ ስር ሆኖ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል ቢልም አሳልፎ ሰጥቶ መታወቂያ እየታተመ የህዝብን አሰፋፈር ለመቀየር እየተሰራ ነው። በግልፅ "መታወቂያ ውሰዱ" እየተባለ እየተሰጠ ነው። የፕሪቶሪያ ስምምነት ሆነ ብልፅግና በየዕለቱ መከርኩበት የሚለው ይህን አይልም። ይህ የጓዳ ውሉ ውጤት ነው! እርባና ቢሱ ብአዴን ደግሞ ዝምታን መርጧል።
نمایش همه...
መታገያችሁን አትልቀቁላቸው! 1) ጦርነት ያወጀውና ንፁሃንን እየገደለ ያለው ብልፅግና ነው። "ጦርነት ይቁም" ሲባል ጦርነት የጀመረው አካል እንዲያስቆም አስቀድማችሁ ተከራከሩ። "ድርድር" ወዘተ ተብሎ ጦርነቱ ይቁም ሲባል "እሽ ነገር ግን.." ካላላችሁ መከራከሪያችሁን ወስዶ በሀሰት እናንተን ብቻ ሳይሆን ሰላማዊ ሕዝብን ጦረኛ ያስመስልበታል። ጦርነት አውጆ፣ ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ሰላም ፈላጊ ይመስልበታል። 2) ከበርካታ ኃይል ጋር ጦርነት ውስጥ ያለው አገዛዙ ነው። ድርድር፣ ጦርነት ይቁም ወዘተ ሲባል የእሱን ጦረኝነት ርዕሰ አድርጋችሁ፣ ደጋግማችሁ እያስታወሳችሁ "ይሁን፣ ነገር ግን" እያላችሁ ቅድመ ሁኔታችሁን አጥብቁ። 3) አገዛዙ የህዝብ ጥያቄ ደፋቂ ነው። አደባባይ ይዞት የሚወጣው የህዝብ ጥያቄ የለም። ለቅድመ ድርድር እንኳን የሚነሱበትን ለመተግበር ጭንቅ የሚይዘው ነው። አዋጁን ለማንሳት የሚፈራ፣ እስረኛ ለመፍታት የማይደፍር ነው። ቅድመ ሁኔታና የህዝብ ጥያቄ እንደ በረዶ ለሚያሟሟው፣ የራሱን የወረዳ ፍርድ ቤት ለማያምን አገዛዝ "ድርድር" ወዘተ ተብሎ የሚኖር ቅድመ ክርክር በሚያጋልጠው መንገድ መጠቀም እንጅ አራጅ ሆኖ ሰላማዊ እንዲመስል ቦታ አትልቀቁለት። ሰላም ፈላጊ መስሎ እንዳይታይ አድርጉ። 4) አገዛዙ የምዕራባውያን አገራት ጋር ጥል ውስጥ የገባባቸው ጉዳዮች አሉ። በአማራ ላይ በከፈተው ጦርነት እንኳን ተቋሞቻቸው በትንሹም ጨፍጫፊ መሆኑን ለማሳየት ጥረዋል። ዲፕሎማሲ የጠፋበትንና የተበላሸበትን ቡድን "እነሱ ናቸው ሰላም የማይፈልጉት" የሚል ምስኪን እንዲመስል እድል አትስጡት። 5) ስልጣን ለመያዝ የጀግንነት ፍልሚያ ብቻ በቂ አይደለም። ዓለም አቀፍ ድጋፍ ያስፈልጋል። የፖለቲካና የዲፕሎማሲ መልካም ፊት ያስፈልጋል። በህዝብ ላይ በደረሰው በደልም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች በዲፕሎማሲው ላይ ፊት አለማጥቆር አዋጭ ነው። ወስላታነት አይደለም። ተለማማጭነት አይደለም። 6) ዲፕሎማሲ ከራስ ይጀምራል።ማዶና ማዶ ሆኖ በዳያስፖራውም መሬት ላይ ያሉትን ፋኖዎች ለማጣላት የሚደረገውን ሂደት ቶሎ ማስቆም ተገቢ ነው። ስለ አራት ኪሎ እየተወራ ከሰፈር ሚሊሻ ጋር የሚደረገው ከልክ ያለፈ ወደኋላ መመለስ፣ የሀይማኖት አባቶች ጉዳይና ወዘተ ግዙፍ ጥያቄን ያነሰ ያስመስለዋል። አኩርፋችሁ የምትተውት፣ ስቃችሁ የምታልፉት፣ ትኩረት የማትሰጡት፣ ሽምግልና ልካችሁ ተው የምትሉት፣ የምትገጥሙት፤ ቀጠሮ የምትይዙለት ጠላት ይኖራል። ሁሉም አንዴ አይቻልም። ድርድር ማጋለጫም፣ ቀጠሮ ማስያዥያም፣ ከተቻለ ደግሞ ማሸነፊያም ነው። 7) እስር ቤት ሆነው ሊደራደሩ፣ ጫካ ሆነው ሊደራደሩ፣ ውጭ ሆነው ሊደራደሩ እየተባለ በቲክቶክ ወዘተ የሚነዛው ማሸማቀቅ የለበትም። ተመሳሳይ አቋም ይዞ ለድርድር ተገቢ መልስ መስጠት ነው የሚያዋጣው። ይህን ወጥመድ በጥንቃቄ ማለፍ ያስፈልጋል። ካልሆነ ምዕራባውያኑም አቅምና የህዝብ ድጋፍ ሳያንሳችሁ በዚህ ብቻ የተሳሳተ አቋም ይዘው የሚመስላቸውን አደራጅተው ለድርድር ይመጣሉ። አገራትም "ክብራችን ነኩ" ወዘተ ይላሉ። አገዛዙ ለእሱ የሚሆነውና የሚቀርበውን ካዘጋጀ ቆይቷል። ለአገዛዙ ኃይል ቦታ መልቀቅ ኪሳራ ነው። በጦርነቱ ብቻ ነው የምንገኘው የሚባል የነፃነት ትግል የለም። ተሳካም የቁማር አካል ሆነም ድርድሩም ወዘተ የትግል አካል ነው። ያለ ፖለቲካና ዲፕሎማሲ ጦርነት ከመስዋዕትነት ያለፈ ሊሆን አይችልም። ፖለቲካና ዲፕሎማሲ መስዋዕትነትን ወደ ድል ያደርሱታል።
نمایش همه...
የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ነው! ትህነግ ወርሮ ይዞት በቆየውና አዲስ በወረረው የራያ ክፍል አርሶ አደሩን እያፈናቀለ መሬቱን በአስደንጋጭ ሁኔታ እየሸጠ ነው። ዳያስፖራ፣ ባለሀብት፣ ባለስልጣን፣ የባለስልጣን ዘመድ አዝመድ እየተከፋፈለው ነው። ራያም ሆነ ወልቃይትን የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ነው። ግዛቱ የእነሱ ስላልሆነ ነው ሕዝብን እያፈናቀሉ የራሳቸውን አባላት ጭምር ያማረረ መሬት ወረራ ውስጥ የገቡት። አይደለም ዋና ነዋሪ የሆነው አማራውን ተፈናቀለ የተባለ ፈርቶም ወንጀል ሰርቶም የሸሸውን ትግሬ እስካሁን አስመዝግቡ በተባሉት መሰረት አላስመዘገቡም። አላማቸው ተፈናቃይ መመለስ አይደለም። ተፈናቃይ መልሱ ሲባሉ ታጣቂ የላኩት ለዝርፊያና ወረራ ነው። በመጀመሪያዎቹ ቀናት 50 ሺህ በላይ ሕዝብ የተፈናቀለው በትህነግ የመሬት ወረራ፣ ዘረፋና በቀል ምክንያት ነው። ለ30 አመታት ህዝብ እያፈናቀለ መሬት ሲወር ኖሯል። በግልፅም "መሬቱንና ሴቶቻችሁን ነው የምንፈልገው" ሲል የኖረ አረመኔ ነው። አሁንም በተፈናቃይ ስም የሚደረገው ወረራ አላማው መሬት ወረራ ነው። ሕዝቡን ጠላታችን እያሉ፣ እየገደሉ፣ እያፈናቀሉ፣ እየዘረፉ ያሉት የሚፈልጉት መሬቱን ብቻ ስለሆነ ነው።
نمایش همه...
ይህን ያህል የህዝብ ጥላቻ ከየት የመነጨ ነው? ኤርሚያስ ለገሰ የትህነግ/ህወሓት አመራሮች በ60 ቀን ግምገማ ሲጠዛጠዙ ሁለት ወር ሙሉ በየቀኑ ዝግጅት ሲሰራ ስለ ልዩነት አንድ ጉዳይ አልጠቀሰም። እንዲያውም "ጭላንጭል ይታየኛል" ሲል ነበር። እነ ጃልመሮና ጃል ሰኚ የሚባሉት ሲጣሉ ስለ ልዩነት ያለው ነገር የለም። የኦሮሚያ ብልፅግና ሲቧደን ቢውል ኤርሚያስ ስለ ልዩነት አይጠቅስም። የትህነግ ታጣቂ የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ተሳትፏል ሲባል ትህነግን ሱዳን ድረስ ተከትሎ ሄዶ አስተባብሎለታል። ሌላው ቀርቶ ብርሃኑ ጁላና ታደሰ ወረደ መካከል ልዩነት እንዳይፈጠር ወዘተ እያለ ለትህነግ ሲጠነቀቅ ይውላል። አማራ ላይ ግን የሀሰት ዘመቻውን ይከፍታል። ራሱ ተከፍሎት እርስ በእርስ ለማጋጨት የፃፈውን ሰነድ ለአማራ ይሰጠውና አመት ሙሉ ይለፋደድበታል። ሰሞኑን ደግሞ የፋኖ አመራሮች ልዩነት የፈጠሩ መስሎት ጮቤ እየረገጠ ነው። በቀደም የ2 ሰዓት ፕሮግራም ሰርቶበት አልበቃውም። ትናንት ለ3 ሰዓት የሚጠጋ ፕሮግራም ሰራበት። ይህም አልበቃውም ከዛ ልዩነት ያሰፋል ካለው መካከል በደንብ ይጠቅመኛል ያለውን ርዕሱን ጎላ አድርጎ ሰቀለው። አማራን የሚጎዳ የሚመስለውን እያንዳንዱን ክር እነ በረከት ባስተማሩት ውስልትና መሰረት ሲመዝ ይውላል። ይህን የመሰለ የማይፈን የህዝብ ጥላቻ ከምን የመነጨ ነው? ቢከሰስ ለጠበቃ የከፈለለት አማራው!
نمایش همه...
ባለቤቶቹ አልሸፋፈኑትም! የትህነግ ታጣቂ የሱዳን መደበኛ ኃይል አካል ሆኗል! ከስር ያለውን መረጃ ያጋራው አባቱ በሱዳን አምባሳደር የነበረ፣ የጌታቸው ረዳ ደጋፊ አክቲቪስት ነው። መረጃው የትህነግ/ህወሓት ታጣቂ በሱዳን ጦርነት ከመሳተፍ አልፎ እንደ ሱዳን መደበኛ ጦር የሱዳን ተቋማትን እየጠበቀ ስለመሆኑ ነው። በሱዳን ያለው የትህነግ/ህወሓት ኃይል ለጊዜያዊ ጦርነት ሳይሆን የሱዳንን ተቋማት እስከመጠበቅ የደረሰ አብሮ መስራትና መታመን ድረስ የደረሰ ነው። ጉዳዩ አልቡርሃንን የመደገፍ ጉዳይ አይደለም። አብረው እየሰሩ ነው። እንደ መደበኛ ጦር ተቋም እየጠበቁ ነው። ይህ የትህነግ ጦር ከፕሪቶሪያ ስምምነት በኋላ ወደ ትግራይ እንዲያልፍ ተጠይቆ የነበር ቢሆንም "ጦር የለኝም" ያለው ትህነግ/ህወሓት "ይቆይ ብሎ በሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት እንዲሳተፍ አድርጎታል። ብልፅግና ደግሞ ይህን የመሰለ የፈጠጠ ሀቅ "አጣራለሁ" እያለ ይቀልዳል። ባለቤቶቹ ይህን የመሰለ መረጃ በመ
نمایش همه...