fa
Feedback
Mega Projects Construction Office

Mega Projects Construction Office

رفتن به کانال در Telegram

ይህ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትልልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ መረጃ እና መልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

نمایش بیشتر
2 079
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
+930 روز
آرشیو پست ها
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሂዷል። በተካሄደው መርሃ ግብር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የግዥ ቡድን መሪ አቶ ሃብታሙ በዙ በሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ላይ “አይቤን ማን ወሰደው” በሚል ርዕስ ከለውጥ ጋር ተያይዞ በህይወታችን የሚያጋጥሙንን ማንኛዉንም የህይወት ውጣ ውረድ እንዴት ማለፍ እንዳለብን የሚያትት አጭር ሰነድ አቅርበው ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤቱ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሰራተኞች በመድረኩ ተገኝተው የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ ተካፋይ ሆነዋል፡፡

ዛሬ ከሁሉም የከተማችን የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተክለናል! ፈጣሪ ኢትዮጵያን አና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
+9
ዛሬ ከሁሉም የከተማችን የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር ተክለናል! ፈጣሪ ኢትዮጵያን አና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ስለመራቆት፣ ልመናን እና ተረጂነትን ስለማቆም ከመናገር ባሻገር ተግባራዊ የሆነ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም እየፈጠርን ነው ሲሉ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ተናገሩ። ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፣ የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳደሮች፣ የሁለቱ ከተማ አስተዳደር ከንቲባዎች እንዲሁም ሚኒስትሮች በተገኙበት በአዲስ አበባ የወንዝ ዳርቻ ልማት የችግኝ የተከላ መርሃ ግብር ተካሂዷል። ‘’በመትከል ማንሰራራት’’ በተሰኘው የዘንድሮው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ ፤ በእርግጥ ለኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ነው በማለት ለዚህም የወንዞቹን፣ የተራሮቹን ማንሰራራት ጠቅሰዋል። ይህ የኢትዮጵያ ማንሰራራት በሃገር ውስጥ እውቀት በልጆቿ ጥረት መሆኑ ያኮራናል ያሉት ከንቲባዋ፤ የዛሬ 7 ዓመት አካባቢ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ይህንን የአረንጓዴ አሻራ እንቅስቃሴ ሲያስጀምሩ  ኢትዮጵያ በቢሊየኖች በደን ትሸፈናለች ብሎ ለማመን ያስቸግር ነበር ብለዋል። በአዲስ አበባ ደረጃ የደን ሽፋን ከ2.8 በመቶ ተነስቶ 22 በመቶ ላይ መደረሱን ከንቲባዋ ተናግረዋል። ትናንትና እነዚህ ወንዞች በካይ ነበሩ ያሉት ከንቲባዋ፤ ዛሬ ውበትን በተላበሱት የወንዝ ዳርቻዎች እየተከልን ያለነው ምግባችንን ሲሆን ለነገ ስለ ሩሮ ውድነት፣ ስለድርቅ፣ ስለመራቆት ልመናን እና ተረጂነትን ስለማቆም ከመናገር ባሻገር ተግባራዊ የሆነ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል አቅም እየፈጠርን ነው ብለዋል። ዛሬ የተተከሉ ወደፊት ለምግብነት የሚውሉ ችግኞች ነገ የስራ እድል ይፈጥራሉ ያሉት ከንቲባዋ፤ በተጨማሪም በዙሪያው ያሉ አዳዲስ ፕሮጀክቶች በርካታ የስራ እድል የሚፈጥሩ እንደሆኑ አመላክተዋል። በሸክላ እና የሸማ ስራዎች የሚታወቁት እንጦጦና እና ሽሮሜዳ ታሪካቸው እንዳይረሳ፤ ከዛም ባለፈ የስራ እድል በመፍጠር መሸጋገር እንዲችል፤ በዘመነ መልክም ኤክስፖርት ለማድረግ በሚያስችል ደረጃ ከተፈጥሮ ጋር ተስማምተው የአፈር ጥበቃው እና የስነ ምህዳሩ ጥበቃ እና ከስራ እድል ጋር ተዋህዶ የተሰራ ነው። አዲስ አበባ በተሟላ መልኩ በነገው እለት የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሃግብርን ወደ ማስጀመር እንደምትገባ የጠቆሙት ከንቲባዋ፤ እንደልማዳችን ካቀድነው በላይ እናሳካለን ብለዋል።

በመዲናዋ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የኢንዱስትሪ መንደር… የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ መንደር ለአገ
+9
በመዲናዋ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ እየተገነባ የሚገኘው የኢንዱስትሪ መንደር… የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ ግንባታው እየተጠናቀቀ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ መንደር ለአገልግሎት ለማብቃት በትኩረት እየተሰራ ነው አሉ፡፡ ከንቲባ አዳነች በአዲስ አበባ ከተማ በ7 ቢሊየን ብር ወጪ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘውን የኢንዱስትሪ መንደር ጎብኝተዋል፡፡ በዚህ ወቅትም የነዋሪዎችን ጥያቄ የምንመልሰው የሚታዩ ፣ የሚጨበጡ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ በማተኮር ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ 93 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የኢንዱስትሪ መንደሩ የመጀመሪያው ምዕራፍ ከ120 በላይ ሼዶች እንዳሉት አስረድተዋል፡፡ ሼዶቹ ለብረታብረት ሥራ፣ ለእንጨት ውጤቶች፣ ለጨርቃ ጨርቅ፣ ለፕላስቲክ እና ለኬሚካል ማምረቻነት፣ የምርት ማሳያ እና መሸጫ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ ናቸው። የኢንዱስትሪ መንደሩ ግንባታ የመስሪያ ቦታ ችግርን ከማቃለል ባሻገር የማኑፋክቸሪንግ ምርቶችን በሀገር ውስጥ በመተካት የውጭ ምንዛሪ እጥረትን ለመፍታት ያስችላል ነው ያሉት፡፡ በተጨማሪም ሰፊ የሥራ ዕድልን ለመፍጠርና የኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥ ረገድ ሚናው ጉልህ ነው ያሉት ከንቲባዋ÷ የግንባታው 2ኛ ምዕራፍ ለአግሮ ፕሮሰሲንግ ምርቶች የሚሆኑ ሼዶችን የያዘ ነው ብለዋል። የኢንዱስትሪ መንደሩ ከዚህ ቀደም ከነበሩት ሼዶች በተለየ ሁኔታ ዘመናዊ ቴክኖሎጂን እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ግብዓቶችን እንዲጠቀም ተደርጎ እየተገነባ ነው። ከቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ በጥቂት ደቂቃ መድረስ የሚያስችል አዲሱ የአቃቂ ቦሌ ካርጎ መንገድ ላይ እና ምርት ማጓጓዝን ታሳቢ ያደረገና ስትራቴጂክ ስፍራ ላይ እንደሚገኝም የከንቲባ ጽ/ቤት ለፋና ዲጂታል ገልጿል፡፡

የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መ
+8
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የሰኞ ማለዳ ከስራ ሰዓት መግቢያ በፊት የሚያዘጋጀውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብር አካሂዷል። በተካሄደው መርሃ ግብር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት የዲዛይን፤የመሬት መሰረተ ልማት ዝግጅትና ክትትል ቡድን መሪ አርክቴክት ታደለ በቀለ ሰዎች እራሳችንን መጠየቅ የሚገቡን ፣ ሰው የሚያደርጉን ነገሮች? ፣ለምን እንደምንኖር?፣ በህይወታችን ምን እንደምንፈልግ? ፣ትክክል እና ስህተት መንድነው?፣ የወደፊት ህይወታችን ምን እንደሚሆን? የሚሉ ሀሳቦች እና ሌሎች የሰው ልጅ እራሱን የሚጠይቃቸው ጉዳዮችን አስመልክቶ በሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ላይ አቅርበው ተሞክሯቸውን አጋርተዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤቱ በየደረጃው ያሉ አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላት እና አጠቃላይ ሰራተኞች በመድረኩ ተገኝተው የዕውቀት ሽግግር መርሀ ግብሩ ተካፋይ ሆነዋል፡፡

አዲስ አበባ፦ለአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት እየሆነች ያለች ከተማ! የአፍሪካ ህጻናት ጥበቃ ኮንፈረንስ ላይ እየታደሙ ያሉ የተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ፖሊሲ አውጪዎች፣ተመራማሪዎች እና ለጋሾች የአዲስ አበ
+9
አዲስ አበባ፦ለአፍሪካ ከተሞች ተምሳሌት እየሆነች ያለች ከተማ! የአፍሪካ ህጻናት ጥበቃ ኮንፈረንስ ላይ እየታደሙ ያሉ የተለያዩ ሀገራት ሚኒስትሮች፣ፖሊሲ አውጪዎች፣ተመራማሪዎች እና ለጋሾች የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፎርሜሽን ስራዎች ጎብኝተዋል። ተሳታፊዎቹ የኮሪደር እና አጠቃላይ የከተማ መልሶ ማልማት፣ የአፍሪካ ነጻነት ምልክት የሆነውን የዓድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም እና የህጻናት ልማት ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ጎብኝቸዋል። ለሚዲያዎች አስተያየት የሰጡት ጎብኚዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እያከናወነ የሚገኘው ሁለንተናዊ ልማቶች ዜጎችን ማዕከል ያደረጉ፣ የአከባቢ ጥበቃን ያስቀደሙ እና ለትውልድ ተሻጋሪ መሆናቸውን ገልጸዋል። አያይዘውም በእያንዳንዱ የልማት ስራዎች ውስጥ ለህዝብ የጋራ ቦታዎች (Public places) እና የነገ ሀገር ተረካቢ ለሆኑ ህጻናት የተሰጠው ተጨባጭ ትኩረት ለሁሉም የአፍሪካ ከተሞች ትልቅ አብነት ነው ብለዋል።

በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ የተሰሩ ሁለት የጥናት ውጤቶች ላይ ምክክር ተካሄደ ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥ
+8
በፕሮጀክት ጽ/ቤቱ  የተሰሩ ሁለት የጥናት ውጤቶች ላይ ምክክር ተካሄደ ሰኔ 12 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት በአገልግሎት አሰጣጥ እንዲሁም የፕሮጀክት ግንባታ ሂደት ግምገማ ጥናት ዉጤቶችን የተቋሙ አመራሮች እና የማኔጅመንት አባላት በተሳተፉበት መድረክ አነስተኛ አውደ ጥናት ተካሂዷል። የጥናት ስራዎቹን የሰሩት የፕሮጀክት ጽ/ቤቱ ቢዝነስ ልማት ዘርፍ ጥናት ቡድን እና ሌሎች የተቋሙ ጥናት ቡድን አባላት የጥናት ውጤቶቹን ሰነድ ከጅማሮ እስከ የጥናት ውጤቱ ግኝት ያለውን ሂደት የተከተለ ሰፊ  ገለፃ እና ማብራሪያ ለመድረኩ ተሳታፊዎች አድርገዋል። የጥናት ቡድኑን ገለፃ እና ማብራሪያዎች ተከትሎ የተቋሙ የቢዝነስ ልማት ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ከሳሁን አለሙ ፣ የምህንድስና ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ እቴነሽ አበበ(ኢ/ር)   እንዲሁም የአስተዳደር እና ፋይናንስ ዘርፍ ምክትል ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ወሰን መግራ  የአውደ ጥናቱን መድረክ አወያይተዋል፤ገንቢ ሀሳብ አስተያየት ሰጥተዋል። አመራሮቹ በሰጡት አስተያየት፤ ለተሰራው ስራ እውቅና ሰጥተው፤ቀጣይ ባለው ጊዜ የጥናት ውጤቶቹ  ዳብረው እና የጥናት ግኝት አሰረጂነታቸው ይበልጥ አሳማኝ እና ሰፊ ትንታኔን ያካተቱ ሆነው እንዲቀርቡ ምክረ ሀሳብ ሰጥተዋል። ሌሎች የማኔጅመንት አባላትና የአውደ ጥናቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ለጥናት ውጤቱ ይበጃል ያሉትን ሀሳብ አስተያየት ጠቅሰው፤ በተቋም አቅም የተሰሩት የጥናት ውጤቶች ሊበረታቱ የሚገቡና ለጥናት ቡድኑም ምስጋና ይገባል ብለዋል። በማጠቃለያም የቀረቡት የጥናት ውጤቶቹ በተሳታፊዎች የተሰጡ ሀሳብ አስቴየቶች ተካተውና ይበልጥ ዳብረው ሁሉም ሰራተኞች ባሉበት በድጋሚ ቀርቦ እንደሚተች አጽንኦት ተሰጥቶዋል።

ትዉልድ ተሻጋሪዉ የፒያሳ መልሶ ማልማት ! በመሀል አራዳ ከታሪካዊው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ጋር ተሰናስሎ 3 ግዙፍ እና ዘመናዊ ሞሎች፣ አፓርትመንቶች ከአራዳ ፓርክ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ጋር ተናበ
+9
ትዉልድ ተሻጋሪዉ የፒያሳ መልሶ ማልማት ! በመሀል አራዳ ከታሪካዊው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ጋር ተሰናስሎ 3 ግዙፍ እና ዘመናዊ ሞሎች፣ አፓርትመንቶች ከአራዳ ፓርክ እና የወንዝ ዳርቻ ልማት ጋር ተናበዉ አካባቢዉን ሁሉ አስውበው መንፈሳችንን ሊያድሱ፣ ኢኮኖሚያችንን ሊያነቃቁ ፣ ሰፊ የስራ እድል ሊፈጥሩ እና ተወዳዳሪ ሊያደርጉን በፍጥነት እና በጥራት እየተገነቡ ነዉ። ሶስቱ የሀገራችንን የግብይት ክፍተት የሚዘጉት ሞሎች በከተማ አስተዳደሩ እና የግል ሴክተር አጋርነት እየተገነቡ ሲሆን እነሱም - የአራዳ ሌግዠሪ ሞል፣አዲስ ግራንድ ሞል እና ኦሊ ሞል ናቸዉ። ከነዚህ ዉስጥ ዛሬ በአይነቱ ልዩ ፣ ለሀገራችን የመጀመሪያው እና ግዙፍ የሆነውን የአራዳ ሌግዠሪ ሞል ግንባታን የመስክ ላይ ግምገማ አድድርገናል። ባደረግነው ግምገማም ግንባታው ከተጀመረ ገና 7 ወራትን ያስቆጠረ ቢሆንም ስራው በጥራትና በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ እየተከናወነ መሆኑን ተገንዝበናል። ግንባታዉ ሲጠናቀቅ የከተማችንን ገቢ ለማሳደግ፣ የስራ ዕድልን ለመፍጠር፣ የውጭ ምንዛሪን ለማስገኘት እና ሁሉን አይነት ግብይት ከአንድ ስፍራ ማከናወን የሚያስችል እና ሌሎች አገልግሎቶችን ያሟላ በመሆኑ ያለው ፋይዳ የጎላ ይሆናል። አዲስ አሰራርን በመቀበል እና “አብሮ ሰርቶ ዉጤታማ መሆን ይቻላል” ብላችሁ በማመን ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በአጋርነት አብራችሁን እየሰራችሁ ያላችሁ የግል ሴክተሮች ከልብ እናመሰግናለን። ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ ከንቲባ አዳነች አቤቤ

የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ ሰኔ 9 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዘወትር ሰኞ ማለዳ ከስራ መግ
+8
የሰኞ ማለዳ የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ተካሄደ ሰኔ 9 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት ዘወትር ሰኞ ማለዳ ከስራ መግቢያ ሰዓት በፊት የሚያካሂደውን የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መርሃ ግብር ዛሬሰኔ 9 ቀን 2017 ዓ.ም አካሂዷል፡፡ በትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ /ቤት የማህበረሰብ ጥናት ከፍተኛ ባለሙያ የሆኑት አቶ ዘላለም አዲስ “ ሳቅ እና ምናብ ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀ ሰነድ አቅርበው ሰራተኞችን ቁም ነገር እያስጨበጠ ብዙ ሳቅና ፈገግታን የሚያጭሩ የስነ ጽሁፍ ተሞክሯቸውን ለፕሮጀክት ጽ/ቤቱ አመራሮችና ሰራተኞች አጋርተዋል፡፡ ለ28ኛ ጊዜ በተካሄደው የሰራተኞች የዕውቀት ሽግግር መድረክ ላይ የአዲስ አበባ ትላልቅ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጽ/ቤት አመራሮች፣ የማኔጅመንት አባላትና አጠቃላይ የተቋሙ ሰራተኞች ተገኝተዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ የተከፈተው የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ክፍል በምስል
+9
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተገኙበት በይፋ የተከፈተው የሳይንስ ሙዚየም ቋሚ ኤግዚቢሽን ክፍል በምስል