Chefie Bulbula Pre-Primary, Primary and Middle School
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
1 140
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+97 روز
+5130 روز
آرشیو پست ها
ቀን 18/10/2018 ዓ.ም
የተማሪዎች የውጤት መግለጫ ካርድ ያልወሰዳችሁ ስም ጠሪ መምህራን ዛሬ እንዲትወስዱ እናሳስባለን።
የ2018ዓ.ም ከክፍል ወደ ክፍል ዝውውር ፖሊሲ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳር ትምህርት ቢሮ የላከውን ከዚህ በላይ በተቀመጠው መሰረተረ ተፈጻሚ እንድታደርጉ እናሳስባለን
Repost from Digital Exellence (Bole edu )
ሰላም! እንዴት አደራችሁ
በ6ኛ እና በ 8ኛ ክፍል ፈተና በተያያዘ ለባለፈለው ሳምንት የተያዘ የኢ-ስኩል ሲስተም ትግበራ ወደዚህ ሳምንት የተሸጋገረ ሲሆን
በዚህ ሳምንት ትግበራችሁ የአንደኛ ሴሚስተር ቀሪ ውጤቶችን እንዲሁም የሁለተኛ ሴሚስተር ውጤት በማጠናቀር ወደ ሲስተም እንድታስገቡና ለ ቀጣይ ለሚደረገው የ Final Promotion እንድትዘጋጁ አደራ እንላለን::
የተማሪ ውጤት ያላስገባችሁ መምህራን ይህ የትምህርት ቢሮ አቅጣጫ ስለሆነ በወቅቱ በማስገባት ሀላፊነታችሁን እንፊትወጡ እንጠይቃለን። ሲስተም ላይ ያልገቡ ልጆች ካልይ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነገ በ17/10 መረጃቸውን ይዞ እንዲመጡ ቅጠሯቸው።
መልካም ቀን!
በዛሬ ዕለት ሰኔ 14/10/2018 ዓ.ም የጨፌ ቡልቡላ ቅደመ 1ኛ ደረጃ ት/ቤት ደረጃ ሁለት ያጠናቀቁ ህፃናትን በአማርኛ መርሃግብር ወ 87 እና ሴ 87 ድ 174 ህፃናት እንዲሁም በአፋን ኦሮሞ መርሃግብር ወ 17 ሴ 21 ድ 38 የቅድመ 1ኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ህፃናት በአጠቃላይ ወ =104 ሴ=108 ድ=212 ህፃናትን በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል ። እነዚህን ህፃናት ለዚህ ያበቃቸው ውድ የቅድመ 1ኛ ደረጃ አስተባባሪዎች ፣ መምህራን ፣ ሞግዚቶች ፣ የት/ቤታችን ወ.ተ.መ.ህ ኮሚቴዎች ፣ በየደረጃ ያላችሁ የትምህርት ባለሙያዎች ፣ ወላጆች እና የዕለቱ ተመራቂ ህፃናቶች እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን አብሮ ደስ አለን ።
Guyyaa har'aa caamsa, 14/10/2018 Manni Barumsaa Caffee Bulbulaa BSTD, daa'imman Barnoota Sadarkaa 1ffaan Duraa Xumuraan sagantaa Afaan Amharaatiin dhi =87 dub=87 Id =174 fi sagantaa Afaan /O tin dh=17 dub=21 Id =38 kan Eebise yoomuu ta'u ,akka waliigalatti daa'imman dhi =104 dub=108 Id =212 haala gaariidhan Eebiseera. Daa'imman kunneen akka guyyaa Eebbaa kanaaf gahan kan gootan Qindeesitoota Mana Barumsaa Caffee Bulbulaa BSTD, barsiisonni, Kununsitoonni Daa'immanii, Koreen Gamtaa Maatii, Ogeessonni Barnootaa sadarkaa adda addaa irra jirtan, maatiin daa'immanii fi daa'imman guyyaa har'aa Eebbifamtan hundi keessan bu'aa ifaajjii keessaniitin baga gammaddan baga waliin gammanne.
የማጠቃለያ ፈተና ፕሮግራም ሐሙስ (04/10/2018 ዓ.ም) ነው ግቢ ውስጥ የተለጠፈው። ያላያችሁ ካላችሁ እዚህ አለላችሁ።
የ2018 ዓ.ም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና በጨፌ ቡልቡላ 1ኛ እና መካከለኛ ደረጃ ት/ቤት የለምንም ችግር በዛሬ ዕለት በሠላም ተጠናቋል ። ለፈተና አስፈፃሚ አካለት የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል ።
Repost from E-School Project-AAEB Group
Update:
The first semester mark entry deadline has been extended until the end of this week( Jun 20 2026).
Repost from N/a
📚 የተፈታኞች መብትና ግዴታ ✅
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ደንብና ሥርዓት አከባበር እንዲሁም የመልስ ወረቀት አጠቋቆርና ተዛማጅ ሁኔታዎችን አስመልክቶ በሚሰጡ ገለፃዎች ላይ የመሣተፍ ግዴታ አለበት።
📚 ተፈታኙ በገለፃው ላይ ባለመሳተፉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ኃላፊነቱን ይወስዳል።
📚 ተፈታኙ/ኟ የሰራበትን የመልስ ወረቀት ለፈታኙ በመስጠት የጥያቄ ወረቀቱን ይዞ መውጣት ይችላል
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የፈተና ጥያቄዎቹን መስራት ከመጀመሩ በፊት በፈተና የመልስ መስጫ ወረቀት ላይ የግል መለያ መረጃዎችን በሙሉ ግልፅ በሆነ ሁኔታ በቅደም ተከተል ጽፎ ማጥቆር ይኖርበታል (በተለይ የመለያ ቁጥር እና የትምህርት አይነት ኮድ)።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ የራሱን ችሎታና ዕውቀት ተጠቅሞ መስራት ይጠበቅበታል፡፡
📚 የሚሠራባቸው የጥያቄና የመልስ መስጫ ወረቀቶች ለሌሎች ተፈታኞች ዕይታ የተጋለጡ እንዳይሆኑ ሸፍኖ መስራት ይኖርበታል
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ሞባይል፣ ካልኩሌተርና የመሳሰሉ ማንኛውንም ዓይነት የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን ይዞ ወደ ፈተና ክፍል መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው ።
📚 እያንዳንዱ ተፈታኝ ይህንን አውቆ በቅድሚያ አስፈላጊውን ጥንቃቄ ማድረግ አለበት ።
📚 ይህንን ባለማድረጉ ምክንያት በፈተና አሰጣጥ ዙሪያ ለሚያጋጥመው ችግር ተፈታኙ ራሱ ኃላፊነቱን ይወስዳል።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ በመፈተን ላይ እያለ ፈተናውን እንዳይሠራ የሚያውኩ ሁኔታዎች ቢያጋጥመው በፈታኙ ሲፈቀደለት ችግሩን በመግለጽ አስፈላጊውን እርዳታ ማግኘት ይችላል ይሁንና በማንኛውም ምክንያት ለባከነ ጊዜ ተጨማሪ ሰዓት አይፈቀድም
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ከሚጀመርበት ጊዜ ተኩል ሰዓት /30 ደቂቃ/ ቀደም ብለው ከመፈታኛው ቦታ በመገኘት መቀመጫቸውን መያዝ አለባቸው።
📚 ፈተናው ከተጀመረ ከ15 ደቂቃ በኋላ የሚመጣ ተፈታኝ ወደ ፈተናው አዳራሽ መግባት አይፈቀድለትም።
📚 ማንኛውም ተፈታኝ ፈተናው ተጀምሮ 45 ደቂቃ ሳይሞላ ፈተናውን ሠርቶ ቢያጠናቅቅም እንዲወጣ አይፈቀድለትም።
📚 ይሁን እንጂ ፈተናው ከተጀመረ ከ45 ደቂቃ በኋላ ከፈተና አዳራሹ ለመውጣት እንዲፈቀድለት ሲጠይቅ የመልስ ወረቀቱን ለፈታኙ አስረክቦ በጸጥታ እንዲወጣ ይፈቀድለታል።
📚 ፈተናው ሊጠናቀቅ ከ10 ደቂቃ ያነሰ ጊዜ ሲቀረው የሚጨርስ ተፈታኝ የሁሉም ተፈታኞች የመልስ ወረቀቶች እስኪሰበሰቡና ለፈተናው የተፈቀደው የጊዜ ገደብ አብቅቶ እስኪደወል ድረስ በቦታው ተቀምጦ እንዲቆይ ይደረጋል።
📚 ፈተናው በሚሰጥበት ጊዜ ማንኛውም ተፈታኝ ትክክለኛ ያልሆነ የተቀደደ ወይም የተበላሸ የፈተና ጥያቄ ጥራዝ ከገጠመው ወይም የተሰጠው የመልስ ወረቀት የተበላሸ ከሆነ ወይም በራሱ እጅ ቢበላሽበት እጁን አንስቶ በመጠየቅ ሲፈቀድለት ሊያስቀይር ይችላል።
ለተፈታኞች የተፈቀዱ
✅ እርሳስ
✅ የተማሪዎች የደንብ ልብስ (UNIFORM)
✅ ADMISSION CARD
✅ ላጲስ፣ መቅረጫና ማስመሪያ
ለተፈታኞች የተከለከሉ
❌ ስልክ ይዞ መግባት አይቻልም
❌ ካልኩሌተር
❌ የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎችን
❌ ሰዓት
❌ በሀኪም ከታዘዘ ውጪ የሆኑ መነጽሮች
❌ የሚነበቡ ጽሁፎች በሙሉ
ማሳሰቢያ
ለት/ቤታችን ትምህርት ክፍል ተጠሪዎች እና መ/ራን በሙሉ
1. የማጠቃለያ ፈተና ዛሬ (04/10/2018 ዓ.ም) ተባዝቶ ተቆጥሮ ዝግጁ መሆኑን ማረጋገጥ፣
2. ያለቁትን የውጤት ትንተና ከስር ከስር ገቢ ማድረግና እስከ ቀን 12/10/2018 ዓ.ም ድረስ በቴሌግራም @negussieteriesa መላክ፣
3. የመፅሐፍ ግምገማ እስከ ዛሬ (04/10/2018 ዓ.ም) ከቀኑ 11:00 በሶፍትና በሃርድ ኮፒ ፈርሞ ገቢ ማድረግ፣ እና
4. ውጤት ታርሞ ተማሪው እንደወቀ ሲስተም ላይ ማስገባት እንዲሁም ሌሎች የማጠቃለያ ስራዎችን መስራት እንዳይዘንጋ።
የተማሪ ውጤት ከሲስተም ላይ ፕሪንት ተደርጎ እያንዳንዱ ተማሪ ፈርሞበት ነው ክሊራንስ የሚፈረመው። በመሆኑ የአንድም ተማሪ ውጤት ሲስተም ላይ ባይገባ ክሊራንስ የማይፈረምና ኢፊሸንሲም የማይሞላ መሆኑ ታሳቢ ይደረግ።
የ2018_ዓ_ም_ከተማ_አቀፍ_የ8ኛ_ክፍል_ፈተና_የሚፈትኑ_መምህራን_ምደባ.pdf1.15 KB
የ2018_ዓ_ም_8ኛ_ክፍል_ከተማ_አቀፍ_ፈተና_በፈተና_ቆጣሪነት_የተመደቡ_መምህራን.pdf3.86 KB
የ2018_ዓ_ም_የ8ኛ_ክፍል_ከተማ_አቀፍ_ፈተና_አስፈፃሚ_ሱፐርቫይዘሮች_ምደባ.pdf0.68 KB
ለ6ኛ_ክፍል_ፈተና_በቆጣሪነት_የተመደቡ_መምህራን_ምደባ_2018.pdf0.33 KB
