የሾፌሮች አንደበት
رفتن به کانال در Telegram
6 701
مشترکین
-324 ساعت
-217 روز
-7530 روز
آرشیو پست ها
6 701
እገታ
አሁን በ 13/04/2018 ከቀኑ 7 ሰአት አካባቢ በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር አስተዳደር በፎገገራ ወረዳ ከወረታ ጉማራ ባለው የመንገድ ክፍል ታንኳ ገብኤል መገንጠያ ላይ 2 አሽከርካሪዎች በዘራፊ ወንበዴዎች ታፍነው ተወስደዋል።
እዚሁ ቦታ ላይ በ11/4/2018 ዓም ሌሎች 2 ሾፌሮች ታፍነው መወሰዳቸው ይታዎቃል ይህ እገታ በተፈፀመበት በ300 ሜትር ርቀት አካባቢ የክልሉ ፀጥታ ሀይል አድማ ብተና አባላት የሚገኙበት ነው።
አጋቾችን ለማጥፋት ታጋቾችን ለማስለቀቅ ተደጋጋሚ እገታ የሚፈፀምባቸው ቦታዎችን ለይቶ አለመጠበቅ ዘራፊዎች ያሻቸውን እንዲያደርጉ እድልን ፈጥሮላቸዋል።
አጋች ዘና ብሎ ዋና መንገድ ላይ ቆሞ ያግተል ማንም አገትክ ብሎ የሚጠይቀው የሚያሳድደው አካል የለም ስልክ ተደዋውሎ በባንክ ሁሉ ገንዘብ ተቀብሎ ይለቃል ያለ ማንም ጠያቂ ህይወቱን ይመራል።
እገታ የሚፈፀምባቸው ቦታዎች እየታወቁ አለመጠበቅ ታጋችን ለማስለቀቅ ጥረትን አለማድረግ የአጋቾች ሰንሰለት ሩቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው።
ከወረታ ጉማራ በተደጋጋሚ እገታ እየተፈፀመ ቢሆንም እያገቱ ያለበትን ቦታ መጠበቅ ያስፈልጋል በቅርብ ርቀት ያሉ ህግ አስከባሪዎች ለማስለቀቅ ለመጠበቅ ሊንቀሳቀሱ ሊሰለፉ ይገባል።
6 701
ይህ ድሬ ደዋ መንገድ ደንገጎ ነው እንደምታዩት ጉም ነው በጥንቃቄ አሽከርክሩ። ወደ ቁሉቢ ገብርኤል ለንግስ የምትመጡ መንገዱ ዝናባማ እና ጉም ነው ጥንቃቄን አድርጉ።
13/04/2018
6 701
ይህ ሰው የወልድያ ከተማ ንግድ መምሪያ ሀላፊ ነው ወልድያ ላይ ናፍጣ እየቀዳችሁ ያላችሁ ሳምንት ሙሉ ሰልፍ ይዛችሁ ዋጋ ጭማሪ እስኪነገር የጠበቃችሁ ኑ እስኪ እንጠይቀው።
👉በመጀመሪያ ወልድያ ከተማ ከየትኛውም የክልሉ ከተማ ነዳጂ ከጅቡቲ ለማስገባት የፀጥታ ስጋት የሌለበት ነው ለጂቡቲም ቢሆን 590 ኪሎ ሜትር የሚርቅ ቅርብ የሚባል ነው ታዲያ በዚህ ከተማ እጥረት እንዴት ሊከሰት ይችላል ?
👉ንግድ መምሪያ ሀላፊው ገፃችን ላይ ይህንን ያያያዝነውን ሀሳብ ሰጦ አይተናል ምን ይላል እንደ ድሮው በሳልባትይ ሞልቶ መሸጥ ቀርቶባችሁ ነው ይላል እንግዲህ እንዲህ ያሉት ናቸው ተቋም እየመሩ ያሉት።
👉የዋጋ ጭማሪ እስኪነገር ማደያዎች ዘግተው የለም ሲሉ ቆሞ ሲመለከት የከረመ ከታሪፍ በላይ ሲሸጥ ማስቆም ያልቻለ ንግድ መምሪያ የምትሸጡት ቀርቶባችሁ እንጂ ችግር የለም ሊለን የደፈረ ምን ሆኖ ነው ?
👉ወልድያ ላይ ዛሬም ለማደያ ብር ከተከፈለ በመኪናም በተሳቢ ሳልባቲዮም ፉል እንደሚደረግ ጠፍቶት ነው ምኑን ነው ፉል ማድረግን ያስቀረው? ብር ከፍለን ፉል እንድናደርግ ነው አመቻችቶ የሰጠን እንጂ።
👉እናንተ ሆን ብላችሁ በሚመስል መልኩ የሚቀዳ ሊትር ተመናችሁ ማደያዎች ከተተመነው በላይ ለመቅዳት ከፍተኛ ብር እየጠየቁ መቅዳት ላይ ናቸው ህጉ ለምዝበራ ምቹ ሁኔታን ፈጠረ እንጂ መቸ ብልሹ አሰራርን አስቀረ ????
👉ተጨማሪ ነዳጂ ለመቅዳት ብር ከከፈላችሁ ችግሩ የራሳችሁ ነው ይላል ፁህፉ አያችሁ ማደያዎች ተጨማሪን ነዳጂ ከተተመነው ውጭ እንዳይሰጡ የሚቆጣጠርበት አሰራር የሚከታተል ባለሙያ እንደሌለ ያመላክታል ንግግሩ ለምዝበራ በሩን ከፍቶ ነው የተወው።
👉ጠይቁት እስኪ ሲኖ ካሶኒ ከ70 እስከ 100 ሊትር የሚል የት የሚሰራበት የት የሚደርስበት ነው ? ከወልድያ ጋሸና እንደማያደርስ ያውቀዋል ግን 70 ሊትሩ ?
6 701
ሰሌዳ የጠፋው
ኮድ 3 ኢት A08290 የሚል የመኪና ሰሌዳ የጠፋው በ 0918741970 ደውሎ መውሰድ ይችላል ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።
6 701
የሹፍርናን የሙያ ስነ ምግባር ምንነት የማያውቁ ለሌላው የማይጨነቁ አሽከርካሪዎችን ማየት የተለመደ እየሆነ ነው።
የት ይቀደማል ይደረባል የሚለውን ሳያውቁ መኪና ወንበር ላይ የሚቀመጡ ለዜጎች ህይወይ መጥፋት ለሀገር ሀብት ውድመት ዋና ምክንያት ናቸው።
6 701
ኮድ 3 ኢት B 11738 የሆነ ሰሌዳ የጠፋው በ 0920033762 ወይንም 0934405457 ደውሎ መውሰድ ይችላል።
A 44744 የሚል ታርጋ የጠፋው በ 0910752012 ደውሎ መውሠድ ይችላል ሲል መልዕክት አድርሰውናል።
6 701
ከአዳይቱ በግምት 10 እስከ 15 ኪሎ ሜትር ላይ ዛሬ ንጋት 06/02/08 ወደ ኡንዱፎ መውጫ የታጠቁ ሌቦች እያስቆሙ ብዛት ያለው ሾፌር ዘርፈዋል ደብድበዋል የሚል ብዛት ያለው መልዕክት ደርሶናል። የአፋር ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ይህንን ችግር በማየት አጥፊዎችን ለመቅጣት ሊንቀሳቀስ ይገባል።
6 701
ከጁቡቲ ጋላፊ መንገደ አህያ ሜዳ አካባቢ ዝናብ ዘንቧል ማታ ባትመጡ ይመራጣል። መንገደ ተባለሸተዋል ሲል መልዕክቱን አድርሶናል።
30/01/2018
6 701
መንገዱ ተጨናንቋል
ከአየርጤና ካራ በግራ እና ቀኝ ባሉ መስመሮች አየተሰራ ባለው መንገድ ምክንያት ተጨናንቋል።
አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን ይጠቀሙ!
30/01/2018
9:20
6 701
ሰሌዳ የጠፋችሁ
ኮድ 3 ኢት A-06694
ኮድ 3 ኢት A 19016
ኮድ 3 ኢት A 29136
ኮድ 3 ኢት 80127
እነዚህ የመኪና ሰሌዳዎች ውስጥ የጠፏችሁ አሶሳ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ መምሪያ መጥቶ መውሰድ ይችላሉ ።
6 701
የሾፌሮች አንደበት ገፅ በፌስቡክ በቴሌግራም እና በቲክቶክ የተለያዩ መረጃዎችን የማስጠንቀቂያ መልዕክቶችን እያጋራ መቆየቱ ይታዎቃል አሁን በስፋት በጥራት ዘርፉን የመጠነ ስራን ለመስራት የዩቲዮቭ ገፅ ከፍተን ብቅ ብለናል እስካሁን 340 ሰዎች ሳብስክራይብ አድርገውናል እርስዎም ይህንን ሳብስክራይቭ በማድረግ ለቀጣይ ስራችን ጉልበት ይሁኑን።
https://m.youtube.com/@voiceofdriverset?fbclid=IwRlRTSANU3NhleHRuA2FlbQIxMQABHmBkD9IuT6ibElvVTHjTmuJh17pg7M4R5WjKtXOXVn-Z8O1P1QXa0aTiawAu_aem_MG71FssJFHwYLOKGfI969w
የፌስቡክ ገፃችን ከ 440,000 በላይ ተከታይ አለው ስለዚህ እዚህ ያላችሁ ሳብስክራይቭ በማድረግ ተቀላቀሉን
6 701
ኮረቸራ ወደ ጅቡቲ የላክ
ዛሬ ማለትም 29/01/2018 ከድሬደዋ ሀበሻ እንድ ሰው አስቁሞኝ እባክህ መኪና ተበላሽቶብኝ ነው እቃ ወስድልኝ አለኝ ወደ ጅቡቲ እካው ኮነችራ ነው ስልኬን ተቀብሎ እኔም እቃውን ተቀብየ ጉዞየን ቀጠልው ሰውየው አልደውልም ስልክ ተሳስቶ መሰለኝ እና መኪናው እንዳይጉላላ አድራሻየ ጅቡቲ 77358806 እት 0927692599 አሁን ጅቡቲ ነኝ ጭኘ ስለምወጣ እንዳይጉላላ ብታደርሱልኝ ስል በአክብሮት እጠይቃለው
6 701
+2
ሸካ ዞን አስፖልት ምን እንደሆነ በመልክ አናውቀውም እያሉ ነው የመንገድ መሰረተ ልማት አለመሰራት በህዝቡ እንቅስቃሴ የእለት ኑሮ ላይ ትልቅ እንቅፋት እና ጉዳት እያደረሰብን ነው ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል።
6 701
ይህ እና እንዲህ ያሉ ጉድጓዶች ከጎሮ መብራት ወደ ሰሚት አቅጣጫ በብዛት አሉ በዛ ላይ በጭራሽ ስለማይታዩ አደጋ
ከመፈጠሩ በፊት ቢስተካከል የሚል መልዕክት ደርሶናል።
የብረት መዝጊያዎችን የሚሰርቁ ሀላፊነት የጎደላቸው ሌቦች ሁሉም በጋራ ሊከላከላቸው ይገባል።
6 701
በአማራ ክልል በሰሜን ጎጃም ዞን በመራይ እና ቢኮሎ አባይ መሀከል ባለው የመንገድ ክፍል ዛሬ 29/01/2018 ዓም 6 ሾፌሮች መሳሪያ በታጠቁ ዘራፊዎች ታፍነው መወሰዳቸው መልዕክት ደርሶናል።
ይህ የመንገድ ክፍል በተደጋጋሚ ብዛት ያለው አሽከርካሪ እየታገታ ለፍቶ ያፈራውን ገንዘብ ተበድሮ እዳ ገብቶ እየከፈለ ነው።
6 701
ይህ አሽከርካሪ ኡስማኢል ኡመር ይባላል የአምቡላንስ ሹፌር ነው ለስራ ከባቲ ወጣ ብሎ በታጠቁ ወንበዴዎች ተገድሏል ሲሉ መልዕክት አድርሰውናል። በነገራችን ላይ የባቲ ወረዳ የአምቡላንስ ሹፌር በጥይት በወንበዴ ሲገደል በቅርብ ወራት ይህ 3ኛው ነው።
በመጀመሪያ መትሀራ አካባቢ ተገድሏል ይህ እና አንድ ሌላ ሹፌር እዛው ባቲ ዙሪያ ተገድለዋል በአሽከርካሪዎች ላይ እየደረሰ ያለ አፈና ግድያ ትኩረት በመነፈጉ አጥፊን ለመቅጣት የሚንቀሳቀስ አካል ባለመኖሩ ችግሩ እንዳይቆም አድርጎታል።
የዘምባባ መገጨት በሚዲያ በሚጮህበት በእግረኛ መንገድ ላይ መኪና ሄደ የሚል ዜና በሚራገብበት የሰው ልጂ የሾፌር ሞትን በዝምታ ማየት የጭካኔ የውድቀት ማሳያ ምልክት ነው ሰውን አሳንሶ ከቁስ አርክሶ ማየት የሰባዊነት ማጣት ነው።
ነፍስ ይማርልን
