የሾፌሮች አንደበት
رفتن به کانال در Telegram
6 943
مشترکین
+124 ساعت
-67 روز
-130 روز
آرشیو پست ها
6 943
ሞጆ ( ባቱ) ዝዋይ መንገድ አለምጤና አካባቢችግር አለ የሚል መልዕክት ደርሶናል ወደ አካባቢው የምትጓዙ ያለውን ሁኔታ ሳታጠሩ ከከተሞች አትውጡ።
28/09/2018
ምሽት 1:45
6 943
የባህር ዳር ከተማ የ 11/09/2018 የነዳጅ ድልድል
1) ዴልታ ቁ1 ናፍጣ= 22310==የኢንዱስትሪ እና ግብርና ምርቶች እና (100 የከተማ ታክሲ ብቻ
2) ሜሎስ ቤንዚን =7950==ባጃጅ
3) ፈ/ጊዎን ናፍጣ= 27823==ኢንዱስትሪና ግብርና ምርቶች፣ ታታ ደረቅ ጭነት
4) ታይም ናፍጣ=18759==ኢንዱስትሪና ግብርና ምርት
5) ኦላ(ፓፒረስ) ኢነርጅ ናፍጣ=28874== ኤክስፖርት፣ ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር የጫኑ
6) አፍሪካ ናፍጣ=53940==ኢንዱስትሪ እና ግብርና ምርት የጫኑ የግንባታ ቁሳቁስ የጫኑ እና የዘመን ኮንስትራክሽን ወደ ደባርቅ የሚሄድ አንድ ተሽከርካሪ
7) መሽ ቤንዚን= 25750==ባጃጅ፣ (የቢሮ እና የቤት ተሽከርካሪ በትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አቅራቢነት)
8) ኢላ ቤንዚን =18543==ባጃጅ
9) ጅአር ናፍጣ=66716==ሰባዊ ድጋፍ የጫኑ የኢንዱስትሪ እና የግብርና ምርቶችን የጫኑ (80 የመናኸሪያ ተሽከርካሪ ብቻ ይስተናገዳሉ)
ድምር ናፍጣ =283176
ቤንዚን= 55243
ማሳሰቢያ=_
1)የጸጥታ አና ቦቲ ተሽከርካሪዎች እየተረጋገጠ በሁሉም ማደያ ይስተናገዳል
2)የኮሪደር እና የተቋማት ተሽከርካሪዎች በደብዳቤ በተመደቡበት ይስተናገዳሉ
6 943
የባህር ዳር ከተማ የ09/09/2018 የነዳጅ ድልድል
1 ቶታል ቁ3 ናፍጣ= 1000=የማይስበው
ቤንዚን= 9120=የማይስበው
2 አምዴ ናፍጣ= 47163==የኢንዱስትሪ ወይም የግብርና ምርት የጫኑ እና የግንባታ ቁሳቁስ የጫኑ
ቤንዚን= 1500==የማይስበው
3 ሜሎስ ናፍጣ= 2022= የማይስበው
ቤንዚን= 35320==ባጃጅ
4 ፈ/ጊዎን ናፍጣ= 86030== የአፈር ማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር የጫኑ፣ የግንባታ ቁሳቁስ የጫኑ፣ሰባዊ እርዳታ የጫኑ፣
5 ቶታል ሸዋ ናፍጣ= 4200== ማሽኑ የማይሰራ
ቤንዚን=1455== የማይስበው
6 ,ኢላ ናፍጣ =12423==
ቤንዚን= 49875==ባጃጅ
7 ጅአር ናፍጣ= 3142==የማይስበው
ቤንዚን= 1800== የማይስበው
8 ዞብል ናፍጣ= 3000==ሪዘርብ
9 አቢሲኒያ ቤንዚን= 1200==የማይስበው
10 ኮከብ ናፍጣ= 2000==የማይስበው
ቤንዚን= 3000==ሪዘርብ
11 ቶታል ሰባታሚት ናፍጣ= 909==የማይስበው
12 ዴልታቁ2 ናፍጣ= 4094== የማይስበው
13 ዴልታ ቁ3 ናፍጣ= 16626==የግብርና ወይም የኢንዱስትሪ ምርጥ የጫኑ እና የግንባታ ቁሳቁስ የጫኑ
14 ኖክቁ4 ናፍጣ= 3900==ሪዘርብ
15 ኦላ(ፖፒረስ) ኢነርጅ ናፍጣ= 800==የማይስበው
16 አጅፕ ናፍጣ=16366==አገር አቋራጭ (የመናኸሪያ) ተሽከርካሪ
ቤንዚን= 1000== የማይስበው
17 አፍሪካ ናፍጣ= 500== የማይስበው
ቤንዚን== 2900== " "
18 መሽ ናፍጣ=2000 ==የማይስበው
19 ታይም ናፍጣ= 46074==ባለበት የሚውል
20 ኖክ ቁ 6 ናፍጣ= 23309== የከተማ ታክሲ፣ የዳጋ እስቲፋኖስ ገዳም ኩፐን የተጻፈላቸው፣በ8/9/2018 ኩፐን ተጽፎላቸው ያልተስተናገዱ
ድምር ናፍጣ= 298593
ቤንዚን=88195
6 943
የ06/09/2018 ባህር ዳር ከተማ የነዳጅ ምድብ
1 ሜሎስ ናፍጣ= 47053==ኤክስፖርት፣ምርጥ ዘር፣ ማዳበሪያ የጫኑ፣ የግንባታ ቁሳቁስ የጫኑ፣
ቤንዚን 6500
2 ቶታል ቁ3 ናፍጣ 1000 የማይስበው
ቤንዚ 9120 " "
3 አምዴ ናፍጣ 2000 የማይስብ
ቤንዚን= 1500 " "
4 ቶታል ሸዋ ናፍጣ =46352==የከተማ ታክሲ፣ የከተማ ባስ፣የመናኸሪያ ተሽከርካሪ፣ ኮሪደር የተመራላቸው፣ ቴሌ ውሃ መብራት ሀይል
ቤንዚን= 1455==የማይስበው
5 ኢላ ናፍጣ=3450==የማይስበው
ቤንዚን= 4000==ሪዘርብ
6 ጅአር ናፍጣ =4642== ከሪዘርብ የአልማኮን ቁሳቁስ የጫኑ 02 ተሽከርካሪዎች እና የመምሪያ የተመራላቸው ተሽከርካሪዎች።
ቤንዚን= 1800==የማይስበው
7 ዞብል ናፍጣ= 17732== የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርት የጫኑ እና የተመራላቸው ለኮሪደር ስራ
8 አቢሲኒያ ቤንዚን= 1200 =የማይስበው
9 ኖክ ቁ4 ቤንዚን=4500==ሪዘርብ
10 ኮከብ ናፍጣ= 2000==የማይስበው
ቤንዚን= 3000==ሪዘርብ
11 ቶታል ሰባታሚት ናፍጣ=909 ==የማይስብ
12 ዴልታ ቁ2 ናፍጣ= 4094 ==የማይስበው
13 ዴልታ ቁ3 ናፍጣ= 4708==
14 ኦላ ኢነርጅ (ፓፒረስ) ናፍጣ= 49410== የአሽከርካሪ ማሰልጠኛ ተቋማት ተሽከርካሪዎች፣ መዳኒት የጫኑ ፣ሰባዊ እርዳታ የጫኑ ፣የአረንጎዴ እና ደረቅ ቆሻሻ ተሽከርካሪዎች
15 አጅፕ ቤንዚን= 1000==የማይስበው
16 አፍሪካ ናፍጣ= 500 ==የማይስበው
ቤንዚን= 2900== " "
17 መሽ ናፍጣ = 2000== የማይስበው
ቤንዚን= 1900 ==" "
ድምር ናፍጣ = 169902
ቤንዚን= 11500
የ6/9/2018 የውሎ የነዳጅ ስርጭት ይህን የመስላል።
6 943
እነዚህ ተሽከርካሪወች ዛሬ በ04/09/2018 ከማንኩሽ ግልገል ሲጓዙ የተጠቁ ወንበዴወች ብዛት ያለው ሾፌር ተሳፋሪን በመግደል በማፈን መኪኖቹን አቃጠለው የሄዱ ናቸው። ነፍስ ይማርልን ፍትህ እንሻለን።
ጎበዝ ልብን ይሰብራል
6 943
የባህር ዳር ከተማ የ 05/09/2018 የነዳጅ ድልድል
1)ታይም ናፍጣ= 2175== የማይስብ
2) ፈ/ጊዎን ናፍጣ= 406== የማይስብ
3) ቶታል ሸዋ ቤንዚን= 1455== የማይስብ
4)ኢላ ናፍጣ= 3450==የማይስበው
ቤንዚን= 23921== ዛሬ ያልተስተናገዱ ተርፈው ያደሩ ፋራ ሞተሮች እና ባጃጅ
5) ጅአር ናፍጣ =16825== የቢሮ ተሽከርካሪዎች፣ የአልማኮን ቁሳቁስ የጫኑ 02 ሲኖዎች እና የውሀ ቢሮ ቁሳቁስ የጫኑ 04 ተሽከርካሪዎች
ቤንዚን= 1800== የማይስበው
6) ዞብል ናፍጣ= 50749= የኤክስፖርት ምርት የጫኑ፣ የአፈር ማዳበሪያ የጫኑ፣ ምርጥ ዘር የጫኑ፣ ኮንባይነር፣ ትራክተሮች እና የመናኸሪያ መኪኖች፣ ኮሪደር፣አ/አደር፣ተኪ ምርት አምራጮች
7)አቢሲኒያ ቤንዚን= 1200==የማይስበው
8) ኮከብ ናፍጣን= 2000== የማይስብ
ቤንዚን= 8000==ባጃጅ
9)ቶታል ሰባታሚ ናፍጣ ==909 ==የማይስበው
10) ዴልታቁ2 ናፍጣ= 4094==የማይስበው
11) ዴልታ ቁ3 ናፍጣ= 4708==የማይስበው
12) አጅፕ ቤንዚን= 3800==ሪዘረብ
13) አፍሪካ ናፍጣ= 44460==የኢንዱስትሪ እና የፋብሪካ ምርት የጫኑ እና የከተማ ታክሲ እና የከተማ ባስ፣ ኮሪደር፣ አ/አደር፣ ለተለያዩ ተቋማት ጀነሬተር
ቤንዚን= 2900=የማይስብ
14)መሽ ናፍጣ == 2000== የማይስበው
ቤንዚን= 1900== የማይስበው
15)ቶታልቁ3 ናፍጣ= 1000== የማይስበው
ቤንዚን=9120 ==የማይስብ
16)አምዴ ናፍጣ =2000 ==የማይስብ
ቤንዚን=1500 ==የማይስብ
17)ሜሎስ ናፍጣ= 2087==የማይስብ
ቤንዚን= 6500 " "
18)ኖክ ቁ4 ቤንዚን=25400==የህዝብ ዳማስ
ድምር ናፍጣ= 116737
ቤንዚን=61121
⛽️የ5/9/2018 የውሎ የነዳጅ ስርጭት ይህን ይመስላል በጥብቅ ዲሲፕሊን እንድትመሩት አሳስባለሁ
6 943
በኦሮሚያ ክልል ከመተህራ ወለንጪቲ መሀከል በ04/09/2018 በጥይት ተመተው የሞቱ ታፍነው የተወሰዱም እንዳሉ መልዕክት እየደረሰን ነው አጣርተን በዝርዝር ይዘን እንመጣለን።
6 943
+3
በማድያ እንዲራገፍ ተጭኖ የመጣዉን ናፍጣ በህገወጥ መንገድ በግለሰብ ድርጅት ዉስጥ እያራገፈ የነበረ ነዳጅ ጫኝ ቦቴ መኪና ተያዘ።
ግንቦት 02/2018 ዓ,ም (ይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግኑኝነት)
በጌዴኦ ዞን በይርጋጨፌ ከተማ በኖክ ማድያ እንድራገፍ ተጭኖ የመጣ ቦት መኪና ሠለዳ ቁጥር ኢት 40507ET የሆነ በህገወጥ መንገድ በግለሰብ ድርጅት ዉስጥ ከሌልቱ 9:00 ሰዓት በሚሆንበት አሳቻ ሰዓት በመጠቀም ከቦት ወደ በርመል እያራገፈ ፖሊስ ባደረገዉ በብርቱ ትግል እጅ ከፈንጅ ልያዝ መቻሉን የከተማ ፖሊስ አዛዥ ተወካይ ም/ኢ/ር ሙሉዓለም ተሰማ ገልጿል።
የተያዘው ናፍጣ በቁጥር 15 በርመል በሊትር ከ3000 ሺህ ሊትር በላይ ናፍጣ የተሞላበት ስሆን 20 ቦዶ ሮቶ እና ከእነ መሳቢያ ቁሳቁስ ሦስት ግለሰቦችም ጭምር መያዛቸዉን ኢንስፔክተሩ ተናግረዋል።
ዘገባ የይርጋጨፌ ከተማ ፖሊስ ህዝብ ግኑኝነት ነዉ።
6 943
ዛሬ ባህርዳር ከተማን ጠይቁልን
⛽️1400 ኪሎ ሜትር ለሚጓዝ 200 ሊትር የት ይድረስበት ብላችሁ አጠናችሁት ?
⛽️565 ክሎ ሜትር 200 ሊትር የት ይገባበታል ብላችሁ ነው የተመናችሁ ??
⛽️ማነው ተማኙ በምን ስሌት የመኪኖችን የነዳጅ ፍጆታ በሊትር በኪሎ ሜትር ያውቀዋል እውነት ተማኙ ??
ባህር ዳር ከተማ ላይ ከተተመነልህ በላይ እንድንቀዳልህ በሊትር እስከ 500 ብር ትከፍላለህ የሚሉ ማደያወች እያስቸገሩ እየመዘበሩን ነው ሲሉ ብዙ አሽከርካሪወች መልዕክት እያደረሱን ነው።
ጥናቶችን የሚያጠኑ አካላቶች በቂ ትምህርት ዝግጅት በሚያጠኑት ጉዳት ግንዛቤ እና እውቀት ሳይኖራቸው ባለ ድርሻ አካላትን ሳያካትቱ ውሳኔ የሚወስኑ ስህተትን እንጅ መፍትሄን አያቀርቡም እየሆነ ያለው ይህ ነው።
የከተማ አስተዳደሩ ያስቀመጠውን የሊትር ተመን ሊያነሳ ይገባል ህገወጥነትን መከላከል ከሆነ አላማው አህን ላይ እየተዘረፍን ያለነው የከተማ አስተዳደሩ ንግድ መምሪያ ባስቀመጠይ ይህንን ሊትር ብቻ በሚል ለመዝባሪ በተመቸ አሰራር ነው።
ማደያወች ላይ ለቀናት ቆመን ወረፋ ደርሶን ስንገባ ኤክስፖርት ጭነን ረጅም ርቀት የሚሄድ ግብአቶችን ተሸክመን 200 ሊትር ብቻ ነው ባህር ዳር ከተማ ንግድ መምሪያ እንድንቀዳ ያዘዘን ከ200 ሊትር በላይ ያለን እንድንቀዳላችሁ ከፈለጋችሁ በሊትር እስከ 500 ብር ክፍያን መክፈል አለባችሁ የሚሉ ማደያወች በከተማው ተስፋፍተዋል።
⛽️በመጀመሪያ የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር 200 ሊትር የሚል ተመንን ያወጣው ምንን ተንተርሶ በየትኛው ባለሙያ አስጠንቶ ነው ??
⛽️ለምሳሌ ከባህር ዳር ጅቡቲ ኤክስፖርት የጫነ መኪናን 200 ሊትር ብቻ ስጡት ያላችሁ የት እንንዲደርስበት ነው ? አሁን ላይ ከባህር ዳር ጅቡቲ ጉዞው በፀጥታ ችግር ምክንያት በአዲስ አበባ ነው ጠቅላላ ርቀቱም 1490 ኪሎ ሜትር ነው ታድያ ይህንን ያህል ርቀት ለሚጓዝ መኪና 200 ሊትር ብቻ የተመነው በምን ሙያዊ ቁጥራዊ ስሌት ነው ??
⛽️ለአዲስ አበባ አትክልቶችን ሌሎች ግብአቶችን የጫኑ ተሽከርካሪወችስ 565 ኪሎ ሜትር ለሚደርስ መንገድ 200 ሊትር ናፍጣ እንዲቀዱ ብላችሁ የተመናችሁ የት እንዲደርስበት አስባችሁ በየትኛው ባለሙያ አስጠንታችሁ ነው ??
ሌላው 200 ብላችሁ እናንተ ብትተምኑም ማደያወች በድርድር በተጨማሪ ከፍተኛ ብር በሊትር እስከ 500 ብር እያስከፈሉ ፉል ማድረግ ባላቆሙበት እናንተ ያንን የሚቆጣጠር አሰራር ባልዘረጋችሁበት የተመን አሰራራችሁ ከህገወጥ ጋር ተባብራችሁ ለምዝበራ ምቹ ሁኔታን ነው የፈጠራችሁ ቢባል ውሸት አይሆንም።
አንድ መኪና ተራው ደርሶት ማደያ ከገባ በቤቱ ሳልባቲዮ ፉል የማድረግ መብት ሊከበርለት ይገባዋል ከተማ አስተዳደሩ የተገበረው ግን የማይቆጣጠረው ለምዝበራ ምቹ ሆኖ ህዝብ እየተዘረፍ ያለበትን አሰራር ሊያስቀር ይገባል።
200 ሊትር ብቻ አላችሁ የት ሊደርስበት ብትባሉ ምንድን ነው መልሳችሁ አንድ ስራ በባለሙያ ነው ሊሰራ የሚገባው የተሽከርካሪን የነዳጅ ፍጆታ የጉዞ ርቀት የማያውቁ አካላት በምን መስፈርት ነው ተማኝ ሆነው ዘርፉን ለችግር የሚዳርጉት ??
ባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ይህንን ተሽከርካሪን ለምዝበራ አመቻችቶ የሰጠን አሰራር ሊያስቀር ህዝብን ከምዝበራ ሊከላከል ይገባል አሁን ላይ ከተማው ውስጥ ትልቁ የመመዝበሪያ ምክንያት ንግድ መምሪያው የስቀመጠው ግን የማይቆጣጠረው ይህንን ያህል ብቻ ቅድ የሚል አሰራር ነው ሊታረም ይገባል።
ይህ ችግር በባህር ዳር ብቻ ሳይሆን በሌሎችም ከተሞች ያለ በመሆኑ ሁሉም ይህን ለመዝባሪ የተመቸን አሰራር ሊያርም ይገባዋል።
ቴሌግራም :-https://t.me/voiceOfDrivers
ቲክቶክ:-https://www.tiktok.com/@yeshoferoch?_r=1&_t=ZS-96DhD7XQ8BT
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/share/1FhkAdt2Q5/?mibextid=wwXIfr
ፌስቡክ:-https://www.facebook.com/share/17ccYosEuS/?mibextid=wwXIfr
6 943
የማይቀደም ቦታ ቀድማችሁ የማይደረብ ቦታ ደርባችሁ ዝግ የመንገድ ላይ መስመርን ረግጣችሁ አታሽከርክሩ እያለን ቀን በቀን እንጮሀለን ብትሰሙን መልካም ነበር።
ከስር ያለውን መልዕክት አድርሶናል
ሾፌር ነኝ አጋጣሚ በሚኒባስ ተሳፍሬ ዛሬ 11/07/2018 ከአዲስ አበባ ወደ ሸኖ እየሄድኩኝ ነበር ከአሌልቱ አልፎ ፊቼ የምትባል ከተማ ከመግባታችን በፊት ዳገት ከርቭ ይበዛዋል መንገዱ አተን ሁሌ እንደምትለው አንዱ የተሳቢ ሹፌር ዳገት ላይ በዛላይ ኩርባላይ ደርቦ ገባ ከላይ የሚመጣ ሚኒባስ ጋር ተጋጩ ይህ አደጋም ደረሰ ከሚኒባሱ የተጎዳ ሰው አለ ወደ ጤና ጣቢያ ተወስደዋል በእርጋታና በማስተዋል እናሽከርክር። ይላል መልዕክቱ።
ጎበዝ ደርቤ ደርቤ እያልን ብዙ እንጮሀለን ሰሚ በማጣታችን እንዲህ ያሉ አደጋወችን እናስተናግዳለን ይህ ተሳቢ እንደሚታየው የሰው መስመር ውስጥ ገብቷል ዝግ መስመሩንም ረግጦ አልፎታል በራሱ እኮ ዝጉ መስመር የተሰመረ ደርቦ ማለፍ ክልክል ነው ለማለት ነበር።
እናስተውል
6 943
መፍትሄ ካለው መልዕክት አድርስልኝ እኔ የአይሱዚ ሹፊር ነኝ ከ አዲስ አበባ ባህር ዳር ነው እምሰራው የገጠመኝን ላካፍልህ
አዲስ አበባ መውጫ እንጦጦ ላይቢያጆው ላይ እና ከፍ ብሎ ማታ ስዓት ሲለቅን ለመውጣት ወይም ለሊት ላይ ቋሚ ስራቸው የሆነ የገንዘብ መቀበያ ያረጉ ፓትሮል የያዙ የፓሊስ አባላት አሉ።
እኔ አጋጣሚ ለባህር ዳር ጭኜ እየወጣሁ ፓትሮሉ አጂፕ ማደያው አካባቢ ቆሞ ነበር እየወጣን የነበርነው መኪኖች መብዛቱን አዩና አልፈውን ሄደው አስቆሙኝ ከዛ አንደኛው መጣና ደረሰኝ ይዘህ ና አለኝ አኔም ያለኝን ደረሰኝ ይዤ ወረድኩ ፒካፑ መኪና ላይ ለነበረው ሰጠሁት ሁሉንም ደረሰኞች አየና አንደኛውን ደረሰኝ ከተቆረጠ 5ቀን አልፏል ገቢዋች ቢይዙህ እስከ 60.000 ብር ነው ምትከፍል ብለው በጣም አንገራገሩኝ አጉላሉኝ እኔም መጨረሻ ላይ ገንዘብ እንደፈለጉ ስለገባኝ 5000 ተቀብለው ሂድ አሉኝ ..እሚገርመው እኔ ብቻ ነኝ ይሄ የደረሰብኝ ብየ አላስብም ለሊቱን ሙሉ ነው ፓትሮል ይዘው እየወረዱና እየወጡ በዚ መንገድ ከ ሹፊር ገንዘብ እሚቀበሉት Addis Ababa Police Ethiopian Federal Police የሸገር ሲቲ ፖሊስ መምሪያ ይህንን የምዝበራ ሂደት እንዲያስቆሙ አሳውቁልን የሚል መልዕክት ደርሶናል።
6 943
የማህበራችን የሙያ አጋራችን አቶ ጥላሁን ንብረት ባደረበት ህመም ምክንያት በህክምና ሲረዳ ቢቆይም ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል።
ወንድማችን የሙያ አጋራችን የማህበራችን አባል የሆነው አቶ ጥላሁን ለማህበሩ እድገት ለአሽከርካሪው መብት መከበር የበኩሉን የተወጣ ብርቱ ንቁ ደግ እና አስተዋይ አባላችን ነነር።
ማህበባችን ለዚህ አባላችን ቤተሰቦች ለወዳጅ ዘመዶች እንዲሁም ለማህበራችን አባሎች መፅናናትን እንመኛለን።
ጣና የከባድ መኪና አሽከርካሪዎች የምያ ማኅበር
6 943
ኑ የፈጣሪን ድንቅ ስራ እዩ
645 ኪሎ ሜትር ከመኪና ስር
ይህ ታዳጊ እድሜው 10 አመት ሲሆን 645 ኪሎ ሜትር መንገድን ከአውቶብስ ስር ስር ብረት በመያዝ ይህንን ሁሉ እርቀት ተጉዞ ጉዳት ሳይደርስበት በፈጣሪ ቸርነት ሊደርስ ችሏል።
ጉዳዮ እንዲህ ነው ከደምቢደሎ አዲስ አበባን ተሳፋሪ ይዞ ለመጓዝ ከሌሊቱ 10 ሰአት ህዝብን ጭኖ በመውጣት ላይ ካለ ፐብልኪክ ባስ ስር ይህ ታዳጊ ደምቢደሎ ላይ ከስር በመግባት ብረት ይዞ ይደበቃል። ማንም ሳያየው ብዙ ርቀትን ይጓዛል ሆለታ አካባቢ ሲደርስ ይዳከም እና ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት ድምፅ ያሰማል ይህንን ድምፅ የሰሙ ተሳፋሪዎች ጥቆማ በመስጠታቸው ድምፅ መስማታቸውን በማሳወቃቸው መኪናው ቁሞ ሲፈተሽ ይህ ታዳጊ ከስር ይወጣል በፈጣሪ ቸርነትም ምንም ሳይሆን ይገኛል።
ጎበዝ ይህንን ትምህርት ወስዳችሁ ጉዞ ከማድረጋችሁ በፊት የመኪናችሁን ስር ፈትሻችሁ ተነሱ ሰላም ደረሰ እንጂ ይህ ታዳጊ ወድቆ ህይወቱ ቢያልፍ ሾፌሩ ከመጠየቅ አይድንም ነበር።
ይህንን ጉዳይ አስኮ ላይ ፖሊስ ጣቢያ እንዳመለከቱ መልዕክት አድራሻችን ነግረውናል።
6 943
እገታ
አሁን በ 13/04/2018 ከቀኑ 7 ሰአት አካባቢ በአማራ ክልል በደቡብ ጎንደር አስተዳደር በፎገገራ ወረዳ ከወረታ ጉማራ ባለው የመንገድ ክፍል ታንኳ ገብኤል መገንጠያ ላይ 2 አሽከርካሪዎች በዘራፊ ወንበዴዎች ታፍነው ተወስደዋል።
እዚሁ ቦታ ላይ በ11/4/2018 ዓም ሌሎች 2 ሾፌሮች ታፍነው መወሰዳቸው ይታዎቃል ይህ እገታ በተፈፀመበት በ300 ሜትር ርቀት አካባቢ የክልሉ ፀጥታ ሀይል አድማ ብተና አባላት የሚገኙበት ነው።
አጋቾችን ለማጥፋት ታጋቾችን ለማስለቀቅ ተደጋጋሚ እገታ የሚፈፀምባቸው ቦታዎችን ለይቶ አለመጠበቅ ዘራፊዎች ያሻቸውን እንዲያደርጉ እድልን ፈጥሮላቸዋል።
አጋች ዘና ብሎ ዋና መንገድ ላይ ቆሞ ያግተል ማንም አገትክ ብሎ የሚጠይቀው የሚያሳድደው አካል የለም ስልክ ተደዋውሎ በባንክ ሁሉ ገንዘብ ተቀብሎ ይለቃል ያለ ማንም ጠያቂ ህይወቱን ይመራል።
እገታ የሚፈፀምባቸው ቦታዎች እየታወቁ አለመጠበቅ ታጋችን ለማስለቀቅ ጥረትን አለማድረግ የአጋቾች ሰንሰለት ሩቅ መሆኑን የሚያመላክት ነው።
ከወረታ ጉማራ በተደጋጋሚ እገታ እየተፈፀመ ቢሆንም እያገቱ ያለበትን ቦታ መጠበቅ ያስፈልጋል በቅርብ ርቀት ያሉ ህግ አስከባሪዎች ለማስለቀቅ ለመጠበቅ ሊንቀሳቀሱ ሊሰለፉ ይገባል።
6 943
ይህ ድሬ ደዋ መንገድ ደንገጎ ነው እንደምታዩት ጉም ነው በጥንቃቄ አሽከርክሩ። ወደ ቁሉቢ ገብርኤል ለንግስ የምትመጡ መንገዱ ዝናባማ እና ጉም ነው ጥንቃቄን አድርጉ።
13/04/2018
6 943
ይህ ሰው የወልድያ ከተማ ንግድ መምሪያ ሀላፊ ነው ወልድያ ላይ ናፍጣ እየቀዳችሁ ያላችሁ ሳምንት ሙሉ ሰልፍ ይዛችሁ ዋጋ ጭማሪ እስኪነገር የጠበቃችሁ ኑ እስኪ እንጠይቀው።
👉በመጀመሪያ ወልድያ ከተማ ከየትኛውም የክልሉ ከተማ ነዳጂ ከጅቡቲ ለማስገባት የፀጥታ ስጋት የሌለበት ነው ለጂቡቲም ቢሆን 590 ኪሎ ሜትር የሚርቅ ቅርብ የሚባል ነው ታዲያ በዚህ ከተማ እጥረት እንዴት ሊከሰት ይችላል ?
👉ንግድ መምሪያ ሀላፊው ገፃችን ላይ ይህንን ያያያዝነውን ሀሳብ ሰጦ አይተናል ምን ይላል እንደ ድሮው በሳልባትይ ሞልቶ መሸጥ ቀርቶባችሁ ነው ይላል እንግዲህ እንዲህ ያሉት ናቸው ተቋም እየመሩ ያሉት።
👉የዋጋ ጭማሪ እስኪነገር ማደያዎች ዘግተው የለም ሲሉ ቆሞ ሲመለከት የከረመ ከታሪፍ በላይ ሲሸጥ ማስቆም ያልቻለ ንግድ መምሪያ የምትሸጡት ቀርቶባችሁ እንጂ ችግር የለም ሊለን የደፈረ ምን ሆኖ ነው ?
👉ወልድያ ላይ ዛሬም ለማደያ ብር ከተከፈለ በመኪናም በተሳቢ ሳልባቲዮም ፉል እንደሚደረግ ጠፍቶት ነው ምኑን ነው ፉል ማድረግን ያስቀረው? ብር ከፍለን ፉል እንድናደርግ ነው አመቻችቶ የሰጠን እንጂ።
👉እናንተ ሆን ብላችሁ በሚመስል መልኩ የሚቀዳ ሊትር ተመናችሁ ማደያዎች ከተተመነው በላይ ለመቅዳት ከፍተኛ ብር እየጠየቁ መቅዳት ላይ ናቸው ህጉ ለምዝበራ ምቹ ሁኔታን ፈጠረ እንጂ መቸ ብልሹ አሰራርን አስቀረ ????
👉ተጨማሪ ነዳጂ ለመቅዳት ብር ከከፈላችሁ ችግሩ የራሳችሁ ነው ይላል ፁህፉ አያችሁ ማደያዎች ተጨማሪን ነዳጂ ከተተመነው ውጭ እንዳይሰጡ የሚቆጣጠርበት አሰራር የሚከታተል ባለሙያ እንደሌለ ያመላክታል ንግግሩ ለምዝበራ በሩን ከፍቶ ነው የተወው።
👉ጠይቁት እስኪ ሲኖ ካሶኒ ከ70 እስከ 100 ሊትር የሚል የት የሚሰራበት የት የሚደርስበት ነው ? ከወልድያ ጋሸና እንደማያደርስ ያውቀዋል ግን 70 ሊትሩ ?
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
