fa
Feedback
ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶች

رفتن به کانال در Telegram

መንፈሳዊ ቻናል እንጋብዛቹ @EOTCY ምን አይነት ነገሮችን ነው የሚፈልጉት? ➢ የተለያዩ ትምህርቶችን ➢ መጣጥፎችን ➢ መንፈሳዊ ግጥሞችን ➢ ተከታታይ ትምህርቶችን ➢ ብሒለ አበው ➢ ወይስ ዜና ቤተክርስቲያን አሁኑኑ ይቀላቀሉን የኦርቶዶክስ ተዋህዶን ቀጥተኛ አስተምህሮ ያገኙበታል👇👇👇 @EOTCY

نمایش بیشتر
9 059
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+457 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
እራሳችንን እንይበት ለመንፈሳዊ ሕይወት አዲስ ስንሆን ገና ጥቂት ጸልየን ጥቂት ጾመን ጥቂት መጽውተን ሳለ ሩጫችንን ወደ መጨረሱ የተቃረብን ይመስለናል፤ ጉዟችንን በግማሽ እርምጃ ከመጀመራችን ከፍጻሜው ላይ የደረስን ያህል ይሰማናል "እኔን ምሰሉ" ማለት ያምረናል፤ ነገር ግን መንፈሳዊ ሕይወት የቱንም ያህል ብንሮጥበት ሁል ጊዜ እንደ ጀማሪ የሚያደርግ ረጅም ጎዳና ነው። ሰማንያ ዓመት በገዳም ሲጋደል የነበረው አባ ሲሶይ ነፍሱ ከሥጋው ልትለይ በቀረበች ጊዜ ብዙ መነኮሳት በአልጋው ዙሪያ ከበውት ሳለ ቅዱሱ "አምላኬ ሆይ፣ እባክህ ለንስሐ የሚሆን ጥቂት ጊዜን ስጠኝ❓" እያለ በልቅሶ ሲማጸን ሰሙት። በዚህ የተገረሙት መነኮሳቱ አባ ሲሶይን "አባታችን አንተ እድሜ ልክህን በንስሐ የኖርህ መምህረ ንስሐ ሆነህ ሳለ እንዴት አሁን ጥቂት የንስሐ ጊዜን ትለምናለህ?" ቢሉት፣ ቅዱሱም "ልጆቼ ይህን መንፈሳዊ ጥበብ (ንስሐን) ገና አሁን መጀመሬ ነው" አላቸው። ☞︎︎︎ ስለዚህ ሁልጊዜ እንዲህ እንበል "ጌታ ሆይ በመንፈሳዊ ሕይወት እኖር ዘንድ አስጀምረኝ፤ ገና ጀማሪ ሳለሁ ደርሻለሁ ከማለትም ሰውረኝ፤ መንገዱን ጀምሬ እንድቆም አትፍቀድልኝ፤ ወደ አንተ ሳበኝ፣ አሳድገኝ።" ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

​​ ​​እንኳን ለታላቁ ቅዱስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ☞︎︎︎ ልደት መልካም ዛፍ መልካም ፍሬን ያፈራልና ተክለ ሃይማኖትን የወለዱት ደጋጉ ጸጋ ዘአብ ካህኑና እግዚእ ኃረያ ናቸው። እርሱ በክህነቱ እርሷ በደግነቷ በምጽዋቷ ጸንተው ቢኖሩ እግዚአብሔር ጣፋጭ ፍሬን ሰጥቷቸዋል። በዳሞቱ ገዢ በሞተለሚ አደጋ ቢደርስባቸው ቅዱስ ሚካኤል ጸጋ ዘአብን ከሞት እግዚእ ኃረያን ከትድምርተ አረሚ (ከአረማዊ ጋብቻ) አድኗቸዋል። በሁዋላም የቅዱሱን መወለድ አብስሯቸዋል። ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት የጸነሱት መጋቢት 24 ቀን በ1206 ዓ/ም ሲሆን የተወለዱት ደግሞ ታሕሳስ 24 ቀን በ1207 ዓ/ም ነው። በተወለዱበት ቀንም ብዙ ተአምራት ተገልጸዋል። ቤታቸውም በበረከት ሞልቷል። ☞︎︎︎ ዕድገት የጻድቁ የመጀመሪያ ስማቸው "ፍሥሃ ጽዮን" ይሰኛል። ይሕንን ስም ይዘው አባታቸው ጸጋ ዘአብን ተከትለው አድገዋል። በተለይ ቅዱሳት መጻሕፍትን (ብሉያት: ሐዲሳትን) ተምረዋል። በሥጋዊው ጐዳናም ብርቱ አዳኝ እንደ ነበሩ ይነገራል። ዲቁናም ከወቅቱ ዻዻስ አባ ጌርሎስ ተቀብለዋል። ☞︎︎︎ መጠራት አንድ ቀን ፍሥሃ ጽዮስ ለአደን ወጥቶ ሲያነጣጥር ድንገት ከሰማይ አስደንጋጭ ድምጽ ተሰማ። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክት እያመሰገኑ በሚካኤል ክንፍ ተቀምጦ ወረደ። የወጣቱን አዳኝ ፍርሃቱን አርቆ ጌታችን ተናገረ። "ከዛሬ ጀምሮ ስምህ ተክለ ሃይማኖት (ተክለ ሥላሴ) ይሁን። ከዚህ በሁዋላ አራዊትን ሳይሆን ነፍሳትን ታድናለህ። ዘወትር ካንተ ጋር ነኝ" ብሎ በግርማ ዐረገ። ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዚህ ጊዜ በሁዋላ ሰዓትን አላጠፉም። ንብረታቸውን ለነዳያን በትነው በትር ብቻ ይዘው ቤታቸው እንደ ተከፈተ ወደ ምናኔ ወጡ። ☞︎︎︎ አገልግሎት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከዻዻሱ ቅስና ተቀብለው የወንጌል አገልግሎትን ጀመሩ። በመጀመሪያ ስብከታቸው እዚያው ሽዋ (ጽላልሽ) አካባቢ ብቻ በ10ሺ የሚቆጠሩ ሰዎችን አሳምነው አጠመቁ። ያን ጊዜ ኢትዮዽያ 2 መልክ ነበራት። 1ኛ. ዮዲት (ጉዲት) በፈጠረችው ጣጣና በእስላሞች ተጽዕኖ ወደ ደቡብ አካባቢ ያለው ነዋሪ አንድም ሃይማኖቱን ክዷል ወይም በባዕድ አምልኮ ተጠምዷል። 2ኛው. ደግሞ በዛግዌ ነገሥታት ጥረት ክርስትናና ምናኔ ተነቃቅቶ ነበር። ግማሹ ሃገር በጨለመበት ወቅት የደረሱት ሐዲስ ሐዋርያ አባ ተክለ ሃይማኖት በወጣት ጉልበታቸውና በኃይለ መንፈስ ቅዱስ ብዙ ቦታዎችን አደረሱ። ሕዝቡን: መሣፍንቱን ወደ ሃይማኖት መልሰው: ማርያኖችን (ጠንቁዋዮችን) አጥፍተዋል:: ☞︎︎︎ገዳማዊ ሕይወት ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት በወንጌል ብርሃን ኢትዮዽያን ከማብራታቸው ባለፈ ገዳማዊ ሕይወትንም አስፋፍተዋል። እርሳቸው ከሁሉ የተሻሉ ሳሉም በ3 ገዳማት በረድዕነት አገልግለዋል። እነዚህም በአቡነ በጸሎተ ሚካኤል ገዳም ለ12 ዓመታት: በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ዘሐይቅ ገዳም ለ7 ዓመታት: በደብረ ዳሞ ከአቡነ ዮሐኒ ጋር ለ7 ዓመታት: በአጠቃላይ ለ26 ዓመታት አገልግለዋል። በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ ከመነኮሱ በሁዋላም ወደ ምድረ ሽዋ (ዞረሬ) ተመልሰው በአንዲት በዓት ውስጥ ለ22 ዓመታት ቆመው ጸልየዋል። በተሰበረ እግራቸውም 6 ጦሮችን በግራና በቀኝ ተክለው ለ7 ዓመታት ጸልየዋል። ☞︎︎︎ ስድስት ክንፍ ኢትዮዽያዊው ጻድቅና ሐዋርያ ቅዱስ ተክለ ሃይማኖት ከኢትዮዽያ ወደ ኢየሩሳሌም ተጉዘው ከቅዱሳት መካናት ተባርከዋል። ጻድቁ ምድረ እሥራኤል የገቡት በየመንገዱ መንፈሳዊ ዘርን እየዘሩ: እያስተማሩና እያሳመኑ ነበር:: የወቅቱ ሊቀ ዻዻሳት አባ ሚካኤል ጋርም ተገናኝተው ቡራኬን ተሰጣጥተዋል። ዋናው ጉዳይ ግን ከዚህ በሁዋላ ነው ጻድቁ እመቤታችንና ጌታችን ከጽንሰታቸው እስከ ዕርገታቸው የረገጧቸውን ቦታዎች ሲመለከቱ በፍጹም ተደሞ እንባቸው ይፈስ ነበር። ምክንያቱም እግዚአብሔር ስላበቃቸው ተክለ ሃይማኖት የሚያዩት ቦታውን አልነበረም። በገሃድ:- -በቤተ መቅደስ ብስራቱን -በቤተ ልሔም ልደቱን -በቤተ ዮሴፍ ግዝረቱን -በፈለገ ዮርዳኖስ ጥምቀቱን -በቤተ አልዓዛር ተአምራቱን ይመለከቱ ነበር። የጉብኝታቸው የመጨረሻ ክፍል ወደ ሆነው ቀራንዮ ደርሰው ጌታቸውን እንደ ተሰቀለ ሆኖ ቢመለከቱት ከዓይናቸው ይፈስ የነበረው ቁጡ እንባ መልኩን ቀየረና ዓይናቸው ጠፋ። በዚያች ቅጽበት ስም አጠራሯ የከበረ እመቤታችን ድንግል ማርያም ፈጥና ደርሳ ተክልየን ወደ ሰማይ አሳረገቻቸው። በዚያም :- - የብርሃን ዐይን ተቀብለው - 6 ክንፍ አብቅለው - የወርቅ ካባ ላንቃ ለብሰው - ማዕጠንተ ወርቁን ይዘው - ከ24ቱ ካህናተ ሰማይም ተደምረው - ሥላሴን በአንድነቱና ሦስትነቱ ተመልክተው -"ስብሐት ወክብር ለሥሉስ ቅዱስ ይደሉ" ብለው መንበረ ጸባኦትን አጥነው ወደ መሬት ተመልሰዋል። ☞︎︎︎ ተዓምራት የተክልየ ተአምራት እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዛ ነው። ሙት አንስተዋል ድውያንን ፈውሰዋል አጋንንትን አሳደዋል እሳትን ጨብጠዋል በክንፍ በረዋል ደመናን ዙፋን አድርገዋል። ብዙ ደቀ መዛሙርትን አፍርተው ደብረ ሊባኖስን መሥርተዋል። በዚያም ሴትና ወንድ መነኮሳት እንደ ሕጻናት አብረው ኑረዋል። በዘመናቸው ሰይጣን ታሥሯልና:: ☞︎︎︎ ዕረፍት ጻድቅ: ሰማዕትና ሐዋርያ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ብርሃን ሆነው መከራን በብዙ ተቀብለው: እልፍ አእላፍ ፍሬን አፍርተው: በተወለዱ በ99 ዓመት: ከ8 ወር: ከ1 ቀናቸው ነሐሴ 24 ቀን በ1306 ዓ/ም ዐርፈዋል። ጌታ: ድንግል ማርያምና ቅዱሳን ከሰማይ ወርደው ተቀብለዋቸዋል። 10 ትውልድ የሚያስምር ቃል ኪዳንም ተቀብለዋል።   
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

አንድ ዓይነ ሥውር በእጁ ደማቅ ብርሃን ያለው ፋኖስ ይዞ በጨለማ በመንደር ውስጥ እየሔደ ነው:: አንድ ሰው ድንገት ሲያልፍ አየውና ፋኖሱን ሲያይ ተገርሞ ጠየቀው:: "ይቅርታ ወንድሜ:: በእጅህ ፋኖስ አብርተህ ይዘሃል:: እንዳትደናቀፍ ነው እንዳልል እንደማይህ ዓይነ ሥውር ነህ:: የማታይ ከሆነ የፋኖሱ ብርሃን ምን ይጠቅምሃል?" አለው:: "ልክ ነህ የፋኖሱን ብርሃን አላይም:: የምይዘው እኔ በጨለማ ውስጥ ስሔድ እንዳልደናቀፍ አይደለም:: ሆኖም በጨለማ ውስጥ ብርሃን ሳልይዝ ከሔድኩ ሰዎች እኔን ስለማያዩኝ ከእኔ ጋር እንዳይጋጩ ወይንም እንዳይደናቀፉ ነው:: ፋኖሴንን ከያዝሁ በብርሃኑ እኔን ያዩኛል" ብሎ መለሰለት:: ወዳጄ በዚህች ጨለማ ዓለም ስትሔድ የልብህ ዓይን በመታወሩ ምክንያት የማታያቸው ብዙ እንቅፋቶች አሉ:: "ኸረ እኔ ዕውር አይደለሁም" ካልክ "ሀብታም ነኝና ባለጠጋ ሆኜአለሁ አንድም ስንኳ አያስፈልገኝም፡ የምትል ስለ ሆንህ፥ ጐስቋላና ምስኪንም ድሀም ዕውርም የተራቆትህም መሆንህን ስለማታውቅ" ነው:: (ራእ 3:17) #በጨለማው_ዓለም_ስትሔድ_ለራስህ_ብቻ_ሳይሆን_ለሌሎችም_ማሰብ_ትገደዳለህ:: እውነተኛውን ፋና #ክርስቶስን በጉያህ ከያዝክ ሰዎች እሱን አይተው በአንተ ከመሰናከል ይድናሉ:: አለዚያ ግን በአንተ ምክንያት የሚደናቀፈው ሰው ብዙ ነው:: .......እነሆ የተወደደችው ሰዓት አሁን ነው፥ የመዳን ቀን አሁን ነው --1ኛ ቆሮ 6፥2 🟢 @eotcy 🟢 🟡 @eotcy 🟡 🔴 @eotcy 🔴

መቅደስህን አጥራ
በሕይወትህ ለሚመጡ ሰዎች ቦታ ፈልግላቸው ቅኔ ማህሌት ነው❓ ወይስ ቅድስት❓ ወይስ መቅደስ❓ ያንተ ስም ያንተ ማንነት ለሰዎች አጀንዳና ርዕሰ ጉዳይ እንዲሆን አትፍቀድ ❗️ ለራስህ ድንበርና ልኬት ይኑርህ ለፍቅርህም ለጥላቻህም ልክ ይኑረው ለነገሮችም ቁጥብ ሁን ሳቅና ለቅሶህም ለሌሎች ትዝብት እንዳይሆን ተጠንቀቅ❗️ ሰዎች በማንነትህ ላይ እንዳይረማመዱብህ ከፈለከ መቅደስህን አጽዳው:: ለሰው እንደ ቤ/ክ 3 ክፍላት አሉት:: 1.ቅኔ ማህሌት:- ሊቃውንትና ንዑሰ ክርስቲያን እንደሚቆምበት አንተም ውስጥ ትውውቅህ ንዑስ ለሆኑና ትውውቅህ ጥቂት ለሆኑ ሰዎች የሚኖርህ ቦታ ሊኖረው ይገባል። 2.ቅድስት፦ የቆራቢ ምዕመናን መቆሚያ ሲሆን ባንተም ውስጥ አጠገብህ ሆነህ ጓዳና ምስጢርህን በመጠኑ ሚያቁ የተመረጡ ወዳጆች ብቻ የምታኖርበት የልብ ቦታ ነው። 3.መቅደስ፦ ደግሞ ክህነት ያላቸው ብቻ የሚገቡበት ሲሆን ባንተ ሕይወትም ውስጥ ብቸኛ ጓደኞች ብቸኛ ወዳጆች ምትላቸው የፍቅርህን ሥልጣን አንተን መተቸት መውቀስ የፈቀድክላቸው ገመናህን የሚሸፍኑ  የተመረጡ ወዳጆች ቦታ ቅድስተ ቅዱሳን ነው።       ስለዚህ ሰው ከሆንክ የመጣውን ሰው ሁሉ መቅደስህ ውስጥ አታስገባ መቅደስህን አጽዳው በፈረሰው በኩል ማይቆምልህ ምስጢርህን ማይጠብቅልህ የእሱ አብሮ መሆን ችግር ለሆነብህ መቅደስህን አጽዳው❗️❗️    ቤትህን ቤተሰብህን ትዳርህን ሁሉን ኑሮህን ለሁሉ አትግለጥ ቁጥብነት ይኑርህ❗️  ለኑሮህ መንጦላዕት /መጋረጃ/ ይኑረው የራስህን ሕይወት አንተ ሳትፈቅድለት እንዲያጤንህ አትፍቀድለት❗️
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2   

አራቱ ወንጌላውያን በምን ይመሰላሉ ❓ ፩. ወንጌላዊው ቅዱስ ማቴዎስ ፦ በገጸ ሰብእ ይመሰላል፡፡ይኸውም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከአብርሃምና ከዳዊት ዘር መወለዱን ለማስረዳት ከአብርሃም እስከ ቅድስት ድንግል ማርያም ድረስ በሰፊው ስለጻፈ ነወ፡፡ ፪. ወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ፦ በገጸ አንበሳ ይመሰላል፡፡ይኸውም በግብጽ የነበሩትን የአንበሳ ጣኦታት በስብከቱ አጥፍቶ አንበሳ እጓለ አንበሳ የተባለውን ክርስቶስን በመስበኩ ነው፡፡ ፫. ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ፦ በገጸ ላህም ይመሰላል፡፡ ይኸውም ጌታችን  መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በከብቶች በረት መወለዱን በዕለተ ልደቱም የከብት እረኞች ከመላእክት ጋር መዘመራቸውን ከሌሎች ወንጌላውያን ሰፋ አድርጎ ስለሚተርክ ነው፡፡ ሉቃ.፪፥፰-፲፰ 4. ወንጌላዊዉ ቅዱስ ዩሐንስ ፦ በገጸ ንስር ይመሰላል፡፡ ይኸውም ንስር ከሌሎች አዕዋፋ ሁሉ ተለይቶ ወደ ላይ መጥቆ ይበራል፡ በላይም ሆኖ በመሬት ላይ ያሉትን ረቂቃን ነገሮችን አጣርቶ መመልከት ይችላል፡፡ቅዱስ ዩሐንስም ወንጌሉን ሲጽፍ ከወንጌላውያኑ አጻጻፍ በተለየ በምሥጢረ ሥላሴ ይጀምራል፡ስለ ሥጋዌም ሲጽፍ ወደ ላይ መጥቆ በማሰብ ቅድመ ዓለም ስለነበረው ቃል ይተርክና "ያ ቀድሞ የነበረው ቃል ሥጋ ሆነ" በማለት ይጽፋል፡፡ ዮሐ.፩፥፲፬
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
JOIN https://t.me/eotcy

ከበሮ ለምን ይጮሀል❓
የኔታ ለተማሪዎቻቸው አንድ ጥያቄ አቀረቡ "ልጆች ከበሮ ለምን ይጮሀል❓" የኔታ ....በቆዳ ስለተወጠረ ነው" አለ አንድ ተማሪ የዳዊት ማህደሩን በእጁ አንጠልጥሎ ለመመለስ እየቸኮለ። የኔታም "አይደለም አሉ" ሌላኛው ተማሪም "የኔታ ከእንጨት ስለ ተሠራ ነው" አለ የለበሰውን ለምድ ከፍ ከፍ እያደረገ የኔታም ትንሽ ዝም ካሉ በኋላ "አይደለም አሉ" ተማሪው ሁሉ ማውጣት ማውረድ ጀመሩ በሀሳብ ተወጠሩ። ኁሉም የመጣለትን እና የገመተውን መናገር ቀጠለ ግን የሚመልስ ጠፋ። አንድ የኁሉንም ምላሽ በእርጋታ ይሰማ የነበረ ተማሪ እጁን አወጣ። " እሽ ልጄ " አሉ የኔታ ድምፁን ከፍ አደረገና "የኔታ እድሉን ስለ ሰጡኝ አመሰግናለሁ" ብሎ እጅ ከነሳ በኋላ "የኔታ ከበሮ የሚጮኸው "ባዶ ስለሆነ ነው"❗️ አለ። የኔታም የልጁን ምላሽ በማድነቅ ከወንበራቸው በመነሳት ልጄ ተባረክ አሉ። ተማሪዎቹም በጭብጨባ አጀቡት። የኔታም ቀጠል አደረጉና ልጆች "ባዶ የሆነ ነገር ሁሉ ይጮሀል በውስጡ የሆነ ነገር ያለው እቃ ግን አይጮህም። የተማረም ሰው እንዲሁ ነው። እውቀት ያለው አይጮህም፣ ጥበብ ያለው አይጮህም፣ ምንጊዜም ባዶ የሆነ ሰው ሲጮህ፣ ጥበብ የሌለው ሲፎክር እውቀት የሌለው ሲያቅራራ ይታያል። እና ልጆቼ እናንተ "ባዶ" እንዳትሆኑ እውቀትን ጨምሩ፣ በእውቀት ላይ ጥበብን፣ በጥበብ ላይ እግዚአብሔርን መፍራት ጨምሩ። ምድራችንን በማስተማር እና በመስበክ የሞሉ ግን 'ባዶ' የሆኑ። ምድሪቱን በዝማሬ የሞሉ በሃይማኖት እና በምግባር ግን 'ባዶ' የሆኑ። ጌታ ሆይ ጌታ ሆይ የሚሉ ግን ጌታ የማያውቃቸው እንደ ሰው ተፈጥረው እንደ እንሰሳ በደመ ነፍስ የሚኖሩ ሰዎች ፣ በዝተዋልና" ብለው ቁጭ አሉ። ተማሪዎቹም የኔታን አመስግነው ትምህርታቸውን ቀጠሉ።
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2

✔ በምጸልይበት ጊዜ ሐሳቤ አይሰበሰብም ✔ እንዲህ ከሆነ መጸለይ ቢቀርብኝስ❓        አጭር አስተማሪ ታሪክ ነው አንብቡት https://t.me/eotcy     ☞︎︎︎ ልቡናውን ሰብስቦ መጸለይ ያቃተው አንድ ደቀ መዝሙር አረጋዊውን አባት እንዲህ ሲል ይጠይቃቸዋል፡- “አባቴ የጸሎት መጽሐፍ ይዤ ስጸልይ ልቡናዬ አይሰበሰብልኝም፤ አፌ ቢያነበውም ልቡናዬ ግን ይበታተናል፡፡ እኔ ደግሞ ዝም ብዬ ሳስበው፦ ቅዱሳን በፍጹም ሐሳባቸው እያሰቡና እያራቀቁ እንባንና ጸጸትን እየጨመሩ የጻፉትን እኔ በልቤ ሌላ እያሰብኩ በአፌ ብቻ ባነበንበው እንደ ገደል ማሚቶ ፊደሉ አፌ ላይ  እየነጠረ ይሄዳል እንጅ ጸሎትም አይሆንልኝም ፡፡ ☞︎︎︎ ስለዚህ አባቴ የአፍ ብቻ ጸሎቴ ቅድመ እግዚአብሔር የማይደርስ ከሆነ ጸሎቴን ብተወው ይሻላል ወይስ ባልተወው ይሻላል?" ብሎ ጠየቃቸው። አረጋዊው አባትም እንዲህ ሲሉ አስረዱት፡- ☞︎︎︎ “አየህ ልጄ ዐይነ ስውር ሰው በዘንጉ ምድር እየመታ ሲሄድ ከመንገድ ላይ ያለ እባብ ለጊዜው የበትሩን ድምጽ ሰምቶ ይመታኛል ብሎ ይሸሻል እንጅ ዐይነ ስውር ነው አላየኝም ብሎ ባለበት አይጠብቀውም። ስለዚህ አንተም አስተውለህ ብትጸልይ መልካም ቢሆንም ለጊዜው ግን ጭራሽ ከምታቆመው  በአፍህ ውስጥ ያለው የቃለ እግዚአብሔርን መንኳኳት የሚሰሙ አጋንንት መሸሻቸው አይቀርምና መቼም ቢሆን ጸሎትህን አትተው፡፡ አጋንንትንም ማባረር አንድ ታላቅ ጥቅም ነውና፡፡ ብዙ ከመጸለይህም አንጻር አንዳንድ ጊዜ ልብህ የሚወድቅባት ቃል ተጠራቅማ ወደ እግዚአብሔር ታደርስሃለች። ☞︎︎︎ እናም ልጄ ልብህ ምንም ዝርው ቢሆንም አፍህም የልዑል እግዚአብሔር ፍጥረትነውናይህንንምእንዳታቆመው። አሁን አንዱን ይዘህ ወደፊት ደግሞ ሁለቱንም ለማገናኘት መጣር ይኖርብሃል እንጅ አንተው በዳይ አንተው አኵራፊ ሆነህ ጭራሽ ከአምላክ ርቀህ የጠላት ሰይጣን መጫወቻ እንዳትሆን በማለት መለሰለት:: ስለዚህ እኛም በምጸልይበት ጊዜ ልቤ አይሰበሰብም  እንዲህ ከሆነ መጸለይ ቢቀርብኝስ ❓ ብላቹሁ እንዳታቆሙ እህት ወንድሞቼ "...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2 https://t.me/eotcy

እግዚአብሔር ዝም ይላል 👉አልአዛር ሲታመም ዝም 👉ሲሞት ዝም 👉 ሲቀበር ዝም 👉ከተቀበረ ሦስት ቀን ሆነው ዝም በአራተኛው ቀን መጣ ከሞት አሰነሳው። ✍️ መፃጉዕ 38 ዓመት ያልጋ ቁራኛ ሆነ ዝም ሰው የለኝም እያለ ጮኸ አሁንም ዝም ግን ሰዓቱ ሲደርስ እራሱ የማርያም ልጅ ኢየሱስ ክርስቶስ የተሸከመችውን አልጋውን አሸከመው። እረስቶናል ብለን ተስፈ ስንቆርጥ በሰው ያለን ተስፋ ሲሟጠጥ እግዚአብሔር በዝምታ ይመጣል እግዚአብሔር ለነብዬ ኤልያስ በምን አይነት ሁኔታ እንደተገለጸለት እናስታውስ 4 ነገሮች ተከስተው ነበር. ። (1ነገ 19÷11) 1.ትልቅና ብርቱ ነፍስ ተራሮችን ሰነጠቀ አለቶችንም ሰበረ 2.የምድር መናወጥ ሆነ 3.እሳትም ሆነ በእነዚህ በሶስቱ ውስጥ እግዚአብሔር አልነበረም አራተኛው ትንሽ የዝምታ ድምጽ ሆነ በዚህ በዝምታ ድምጽ ውስጥ እርሱ እግዚአብሔር ነበር እግዚአብሔር ዝም ብሎ ይመጣል በእርሱ ብቻ መደገፋችን እርግጠኛ ሲሆን ይመጣል ቢዘገይም የሚቀድመው የለምና ከዓይን ጥቅሻ ፈጥኖ ይመጣል እርሱም አይዋሽም ቢዘገይም በእርግጥ ይመጣልና ታገሡ እርሱ አይዘገይም። (ትንቢተ ዕንባቆም 2:3፤) ✍️እግዚአብሔር ዝም ብሎ የሚያክም ሐኪም ነው። ✍️እግዚአብሔር ዝም ብሎ የሚፈውስ ባለ መድኃኒት ነው። ✍️ሰው በንግግር ያደክማል እግዚአብሔር ግን በዝምታ ያክማል። ✍️ ለሁሉም ጊዜ አለው እግዚአብሔር የሚናገርበት ጊዜ አለው። ✍️ ደግሞም እግዚአብሔር ዝም ብሎ ሰው የሚናገርበት ጊዜም አለ የበረሃው ኮከብ ቅዱስ እንጦንስ "እኔ ስናገር እግዚአብሔር ዝም ይላል እግዚአብሔር ሲናገር ደግሞ እኔ ዝም እላለሁኝ "እንዳለ በተደነቀ ዝምታ የምትኖር አስታዋሸ እግዚአብሔር ሆይ እናመሰግንሃለን። ✍️አንተ በዝምታ ውስጥ መልስ አለህና እናከብርሃለን። ✍️እንደማይሰማ ዝም ብትልም እንደማይሰጥ ብትዘገይም እንደማይገደው ብታልፍም ዓላማ አለህና ተመስገን። ✍️ የቀኑን ምልክት በማየት አለባበሴን ባስተካክልም የዘመኑ ምልክት ግን ሳይገባን በአንደበታችን  በከንቱ ሸንግለንሃልና ይቅር በለን። ✍️ ዓለም ስትንጫጫ ዝም ማለትን አስተምረን እንደ ኃጢአታችን ሳይሆን እንደ  ቸርነትህ ማርን። ✍️የሰው ልጅ በሰው ልጅ የሚያደርገውን መጨካከን ከኢትዮጵያ ሀገራችን አስወግድልን። ✍️የድሆችን እንባ የሚያብስ ጠፍቷልና እግዚአብሔር  አንተ በቸርነትህ ይቅር ብለህ ከመከራ ፣ከሰቆቃ ታደገን ከአንተ ውጭ የሚታደገን ማንም የለንምና። 👉አባ ኒሉስ የተባሉ አባት የዝምትን ጥቅም ሲያስረዱ፦ ጸጥታን የሚወድ ሰው የጠላት ቀስት ሊነካው አይችልም። 👉 ነገር ግን ወደ ጭንቅንቅ የሚጓዝ ኹል ጊዜ ይቆስላል።" 👉  ጸጥታን በማፍቀር የጠላትን ቀስት ማምለጥ እንደሚቻል የሚያስረዱን። 👉ዲያብሎስን በዝምታ ማራቅና ማሰር እንችላለን በንግግር ግን ሊያቆስለንና በሞትና በሕይወት መካከል አድርጎን ሊሔድ ይችላል። 👉ዝምታ ጠላትን የማራቅና ወጥመዱን የማፍረስ ኃይል አለው። 👉ከዚህ በተጨማሪ  ጳጳሱ አንጄሎስ "አንዳንዴ ዝምታ ስለኾነ ጉዳይ ለመናገር ያለን እጥረት የሚያመለክት አይደለም። 👉ነገር ግን እግዚአብሔር ትክክለኛውን የመልስ ዕድል እስኪሰጥ የሚደረግ ብልሀት ያለበት ማቋረጥ ነው እንጂ።" በማለት ዝምታ ያለውን ጥቅም ያስረዱናል። 👉በዚህ አባት ትምህርት መሠረት ማንም ሰው ስለኾነ ጉዳይ በማወቁ ምክንያት ብቻ መናገር የለበትም። 👉በእርግጥ የእርሱ አለመናገር ለጥቅም እንጂ ለሌላ አይደለም። 👉 እኛ ብዙ ጊዜ የሚቸግረን ስሜታችንን ተቆጣጥረን፤ ውስጣችንን መርምረን፤ በመናገራችን መጠቀም አለመጠቀማችንን በደንብ አለመፈተሻችን ነው። 👉 በመናገራችን ብቻ የምናስበው ነገር የሚሳካ ስለሚመስለን፤ ከመጠን አብዝተንና ቸኩለን ተናግረን ጉዳትን ራሳችን ላይ እናመጣለን። 👉ይህ ጉዳት ምናልባት ለጊዜው ላይታየን ይችላል፤ ቀስ እያልን ስንሔድ ግን ልንረዳው እንችላለን። 👉ከዚህ ኹሉ በላይ ደግሞ ዝምታን ሽንፈት አድርገን ማሰባችን በራሱ ትልቅ ችግር ነው። 👉ወዳጄ ሆይ! ዝምታ ጩኽት የሌለው ነው ብለህ ካሰብክ ተሳስተሀል። 👉ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ዝምታን እንዲህ ይገልጹታልና፦” (ዝምታ ጮኽ ያለ ለቅሶ ነው። 👉እንግዲህ ወንድሜ በዝምታ ውስጥ ያለው ጩኽት ታላቅ መኾኑን በመረዳት ተለማመደው። 👉የዝምታ ጩኽት እስከሰማይ የመድረስ ኃይል ያለው ብርቱ ነው። 👉 እግዚአብሔርም ሙሴን አለው ለምን ትጮኽብኛለህ? ዘጸ 14፥15 በማለት ሙሴ በዝምታ የጮኽው ጩኽት በእግዚአብሔር ዘንድ መሰማቱን መጽሐፍ ያስረዳናል። 👉 በመናገር ከምንፈጽመው ይልቅ በዝምታ የምንፈጽመው ጩኽት በእግዚአብሔር ዘንድ የበለጠ ተወዳጅነት አለው። 👉ዝምታ ወዴት እንደምትመራ ብናውቅ ኖሮ የምንወዳጃት ይመስለኛል። 👉ዝምታ ወደ በጎ ምግባር የምትመራ ከኹሉም ፈጣኗ መንገድ ናት። 👉በዝምታ የሚሳፈሩ ሰዎች የቅድስናን ተራራ ፈጥነው ይወጡታል። 👉 ዝምታ ወደቅድስና ለመግባትም በር ከፋች ናት። 👉የዚህችን ታላቅ መሣርያ ኃይል ባለመረዳታችን ምክንያት ቀኑን በሙሉ የማይጠቅሙንን ነገሮች ስንናገር እንውላለን። 👉ልበ አምላክ የተባለው ቅዱስ ዳዊት ስንኳ "በአንደበቴ እንዳልስት አፌን እጠብቃለሁ አልሁ፥ ለበጎ እንኳ ዝም አልሁ፣ እንደማይሰማ ደንቆሮና በአፉ መናገር እንደማይችል ድዳ ኾንኹ።" በማለት ይናገራል ።       መዝ 38፥1-2። 👉 እንግዲያውስ አሳክቶ መናገር የሚችለው ቅዱስ ዳዊት በአንደበቴ እንዳልስት ብሎ ከመናገር ራሱን ከከለከለ። 👉 ከኃጢአት በቀር የማንናገር እኛማ እንዴት የበለጠ ዝም ልንል እንዲገባን መገንዘብ አለብን። 💠 @eotcy

ውድ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የቴሌግራም ቻናል ተከታዮቻችን እንደምን ቆያችሁ በፍልሰታ ጾም ምክንያት ተቋርጦ የነበረው አገልግሎታችን ከዛሬ ጀምሮ ባማረና ከበፊቱ በሰፋ ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል እርሶም ለ
ውድ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ የቴሌግራም ቻናል ተከታዮቻችን እንደምን ቆያችሁ በፍልሰታ ጾም ምክንያት ተቋርጦ የነበረው አገልግሎታችን ከዛሬ ጀምሮ ባማረና ከበፊቱ በሰፋ ወደ አገልግሎቱ ተመልሷል እርሶም ለወዳጆ በማጋራት ኦርቶዶክሳዊ ትምህርቶችን ያስፋፉ https://t.me/eotcy https://t.me/eotcy

በጣም አስተማሪ  ታሪክ🙏 ይነበብ ‼️ አንድ ሰው በበረሃ እየተጓዘ እያለ የያዘው ውሃ አልቆበት በውሃ ጥም ይያዛል ቀስ በቀስ ውሃ ጥሙ ሰውዬውን እያደከመው ይመጣል በስተመጨረሻ ከአንድ የውሃ ጉርጓድ ጋር ይደርሳል ጉርጓዱ በጣም ጥልቅ ነበረ ውሃ ይኑረው አይኑረው አይታይም፡፡ ከዚያም ከጉርጓዱ ጎን አንድ አሮጌ የውሃ መሳቢያ ሞተር አለ ሞተሩ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ ሰፍሯል፡፡ ‹‹ይህ የውሃ መሳቢያ ሞተር የሚሰራው በውሃ ነው›› ይላል፡፡ ከሞተሩ ጎን አንድ ጆግ ሙሉ ውሃ ተቀምጧል ጆጉ ላይ እንዲሁ አንድ ጽሁፍ ሰፍሯል ‹‹ወዳጄ ሆይ ይህንን ጆግ ውሃ ሞተሩ ውስጥ ጨምረው ሞተሩ ብዙ ውሃ ያወጣልሃል ታዲያ አደራ አንተም እንዳንተ ላለ ሌላ መንገደኛ ይጠቅማልና ውሃው ከጉርጓዱ ሲወጣልህ ጆጉን ሞልተህ ማስቀመጥን አትርሳ›› ይላል፡፡ በጆግ ያለውን ውሃ ሞተሩ ውስጥ ልጨምረው ወይስ ልጠጣው❓ እዚጋር ሰውዬው በሁለት ሃሳብ ተወጠረ ‹‹አንደኛ ይህ ሞተር አርጅቷል ጨምሬው ባይሰራ ይህንንም ውሃ አጣሁ ማለት ነው ሞትኩ ማለት ነው☹️ ስለዚህ ልጠጣውና ህይወቴን ላድን ፡ ደሞ ማሳሰቢያውስ ውሃው ያለሞተር አይሰራም እንደኔ ውሃ የተጠማ ሰው ቢመጣ ይህንን ማንቀሳቀሻ ከጠጣሁት ይሞታሉ›› 😭😭ብሎ ለራሱም ለሌሎቹም አሰበና በሃሳብ ተወጠረ በስተመጨረሻ በብዙ ጭንቀት ተወጥሮ ትልቅ ውሳኔ ወሰነ እንዲህ አለ ወደሞተሩ ብጨምረው ይሻላል ከሰራ ጥሩ ካልሰራ ግን እሞታለሁ እንጂ በፍፁም ‹‹ውሃውን ይህንን ጆግ ውሃ ጠጥቼ ሄጄ ዘለዓለሜን ስለዚህ ጉርጓድና ይህንን ውሃ አተው ስለሚሞቱ ሰዎች እያብኩ መኖር አልፈልግም›› ❌አለ፡፡ ከዚያም የጆጉን ውሃ ወደ አሮጌው ሞተር ውስጥ ጨመረውና የሞተሩን ማስነሻ ተጫነው፡፡ ሞተሩም ድምፅ እያሰማ ውሃ የማውጣት ስራውን ጀመረ፡፡ ሰውዬው ተደነቀ🤭 የሚፈልገውን ያህል ጠጣ አካባቢው በሙሉ በውሃ እራሰ ከጠበቀው በላይ አካባቢው ሁሉ ውሃ በውሃ ሆነ😃 ከዚያም በተባለው መሰረት እሱም ጆጉን በውሃ ከሞላው ቦሃላ ጆጉ ላይ ፅሁፍ ጨመረበት ‹‹እመኑኝ በትክክል #ይሰራል›› አለ፡፡ 🟢🟡🔴 እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው ለራስ ማሰብ በህይወት መኖር ነው ለሌላው ማሰብ ግን ሰው መሆን ነው‼️ያለህን ሳትሰስት ከሰጠህ በእጥፍ ድርቡ ፈጣሪ ይሰጥሃል፡፡ ሰውዬው ጆግ ውሃ ሰቶ አካባቢን የሚያርስ ውሃ እንደተቸረው አንተም የምትሰጣት ጠብታ  ከልብህ ከሆነ በእጥፉ ይሰጥሃል፡ ቅዱሱ መጽሐፍ እንዲ ይለናል  በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካፈልስ ድረስ እምነት ሁሉ ቢኖረኝ ፍቅር ግን ከሌለኝ ከንቱ ነኝ። ድሆችንም ልመግብ ያለኝን ሁሉ ባካፍል፥ ሥጋዬንም ለእሳት መቃጠል አሳልፌ ብሰጥ ፍቅር ግን ከሌለኝ ምንም አይጠቅመኝም። ፍቅር ይታገሣል፥ ቸርነትንም ያደርጋል፤ ፍቅር አይቀናም፤ ፍቅር አይመካም፥ አይታበይም፤ የማይገባውን አያደርግም፥ የራሱንም አይፈልግም፥ አይበሳጭም፥ በደልን አይቆጥርም፤ ከእውነት ጋር ደስ ይለዋል እንጂ ስለ ዓመፃ ደስ አይለውም፤ ሁሉን ይታገሣል፥ ሁሉን ያምናል፥ ሁሉን ተስፋ ያደርጋል፥ በሁሉ ይጸናል። ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል። 1ኛ ቆሮንቶስ 13÷1-8   መስጠትን ብቻ ሳይሆን አሰጣጥህ ወሳኝነት አለው፡፡ አንዳንዴ ከመንጠቅ የማይተናነስ መስጠትም አለ‼️ ምናደርጋቸው ነገሮች ሁሉ በፍቅር ይሁን መልካም ቀን ꧁  ይ🀄 ላ 🀄ሉ ꧂ https://t.me/eotcy

እውነተኛ ደቀ መዝሙር መሆን የጀመርኩት አሁን ነው 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ቅዱስ አግናጢዮስ ወደ ሞት እየተወሰደ ወደ ሮም የተላከ ጥቅልል ( ደብዳቤ )     ✍  በሰውነቴም በልቤም ሀይል እንዳገኝ ጸልዩልኝ በእርግጥ ክርስቲያን ሆኜ ለመገኘት እንጂ በስም ብቻ ክርስቲያን መባል አይበቃኝምና በአፍ ብቻ ሳይሆን በእውነት ፈቃደኛ መሆን ያስፈልገኛል እውነተኛ ክርስትና ብርቱ በመሆን የሚገለጥ ነው እንጂ በዝምታ አይደለም ።     ✍ እናንተ ካልከለከላችሁኝ ለአምላኬ ለመሞት መሆኔን በሰው ሁሉ ፊት እመሰክራለሁ ስለዚህ አላግባብ እንዳታስቡልኝ እለምናችኋለሁ ወደ እግዚአብሔር እንድደርስ የአራዊት ጉርሻ ብሆንም እንኳ የእግዚአብሔር የስንዴ ቅንጣት ነኝ የአራዊትም ጥርሶች ቢፈጩኝ ለኢየሱስ ክርስቶስ ንፁህ እንጀራ እሆናለሁ ።   ካንቀላፋሁ በኋላ ለማንም ሰው ሸክም እንዳልሆን ሰውነቴ በሙሉ ይለቅ አራዊት መቃብሬ እንዲሆኑ ይምጡብኝ እንዲይዙኝም እናንተ አነሳሷቸው በመሞቴ በክርስቶስ ነጻነት አገኛለሁ ስለዚህ አንዳች ምድራዊና አላፊ ነገር መመኘት እንደማያስፈልገኝ ተረድቻለሁ ።      ✍ ገና በመንገድ ላይ ሳለሁ በባህር በየብስም ሌትና ቀን አሁንም ከአራዊት ጋር እየታገልኩ ነኝ የአስር ነብሮች ቁራኛ ነኝ ማለት ከወታደሮች ጋር ነው ያለሁት እነርሱም መልካም ነገር ቢያደርጉላቸው የባሰውን ክፋት የሚያሳዩ ናቸው ይሁንና በእነርሱ ማጉላላት ልምምድ አገኛለሁ በዚህ ግን እጸድቃለሁ ማለቴ አይደለም ።     ✍ እውነተኛ ደቀ መዝሙር መሆን የጀመርኩት አሁን ነው የሚታይም ሆነ የማይታይም ማንም ሰው በምቀኝነት ዓይን አይመልከተኝ ልድረስ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እሳት መስቀል የአውሬ ብዛት መጨፍጨፍ የአጥንቶቼ መበታተን የብልቶቼ መሰባበር የሰውነቴ መጨፍጨፍ ሁሉ የሰይጣን ስቃይ ይምጣብኝ ብቻ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ልድረስ ።    የቅዱስ አግናጢዎስ በረከቱ ይደርብን አሜን https://t.me/eotcy

🕊 † እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ የጽንሰት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ፤ አደረሰን። † በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! † † 🕊 ቁጽረታ [ጽንሰታ] ለማርያም 🕊 † ይህችን ዕለት አበው ሊቃውንት "ጥንተ መድኃኒት፤ የድኅነት መነሻ ቀን" ሲሉ ይጠሯታል:: ስለ ምን ነው ቢሉ:- ለዓለም ድኅነት ምክንያት የሆነች የአምላክ እናቱ የተጸነሰችበት ዕለት በመሆኑ ነው:: አንድም ከአዳም ስሕተት በኋላ ያለ ጥንተ አብሶ የተጸነሰች የመጀመሪያ ሰው እርሷ ናትና እንዲህ ይላሉ:: "ለጽንሰትኪ በከርሥ: እንበለ አበሳ ወርኩስ: ወለልደትኪ እማኅጸን ቅዱስ::" "ድንግል ሆይ! መጸነስሽ ያለ በደል ነው: የተወለድሽበት ማኅጸንም ቅዱስ ነው::" [መጽሐፈ ሰዓታት, ኢሳ.፩፥፱ ፣ መኃ.፬] ይሕች ዕለት ለኢያቄምና ለሐና ብቻ ሳይሆን ለፍጥረት ሁሉ የተስፋ ድኅነት ቀን ናትና ሐሴትን ልናደርግ ይገባል:: የእመቤታችን መጸነስስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- ከነገደ ይሁዳ የሚወለድ ቅዱስ ኢያቄም የሚባል ደግ ሰው ከነገደ ሌዊ [አሮን] የተወለደች ሐና የምትባል ደግ ሴት አግብቶ: በሕጉ ጸንተው: በሥርዓቱ ተጠብቀው ይኖሩ ነበር:: ነገር ግን በዘመኑ ሰዎች "ልጅ የላችሁም" በሚል ይናቁ ነበር:: ኦሪታውያን ልጅ የሌለውን "ኅጡአ በረከት-ከጸጋ እግዚአብሔር የራቀ" ነው ብለው ያምኑ ነበር:: ኢያቄምና ሐና ልጅ እንዲሰጣቸው ሲያዝኑ: ሲጸልዩ ዘመናቸው አልፎ አረጁ:: እነሱ ግን የሚያመልኩት የአብርሃምና ሣራን አምላክ ነውና ተስፋ አልቆረጡም:: የለመኑትን የማይነሳ ጌታ በስተእርጅናቸው ድንቅ ነገርን አደረገላቸው:: አንድ ቀን ርግቦች ከጫጩቶቻቸው ጋር ሲጫወቱ የተመለከተች ቅድስት ሐና ፈጽማ አለቀሰች:: "እንስሳትና አራዊትን: እጽዋትን በተፈጥሯቸው እንዲያፈሩ የምታደርግ አምላክ ምነው ሐናን ድንጋይ አድርገህ ፈጥረሃታልን?" ብላ አዘነች:: ይህን የተመለከተ ቅዱስ ኢያቄም ወደ ተራራ ወጥቶ ሱባኤ ያዘ:: ለአርባ ቀናትም ሲጸልይና ሲማለል ቆየ:: በአርባኛው ቀን ሁለቱም ሕልምን ያልማሉ:: እርሱ:- ነጭ ርግብ ሰማያትን ሰንጥቃ ወርዳ: በሐና ቀኝ ጆሮ ገብታ: በማኅጸኗ ስትደርስ አየ:: እርሷ ደግሞ :- የኢያቄም በትር አብቦ: አፍርቶ: ጣፋጭ ፍሬውን ሰው ሁሉ ሲመገበው ታያለች:: ቅዱስ ኢያቄም ከሱባኤ እንደ ተመለሰ ያዩትን ተጨዋውተው "ፈቃደ እግዚአብሔር ይሁን" አሉ:: ለሰባት ቀናትም በጋራ እግዚአብሔርን ሲለምኑ ሰነበቱ:: በሰባተኛው ቀን [ማለትም ነሐሴ ፯] መልአከ ብሥራት ቅዱስ ገብርኤል ክንፉን እያማታ ወደ እነርሱ ወረደ:: "ዓለም የሚድንባት: የፍጥረት ሁሉ መመኪያ የሆነች ልጅ ትወልዳላችሁ" ብሏቸው ተሠወራቸው:: እነርሱም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑ:: እንደ ሥርዓቱም በዚህች ቀን አብረው አድረው እመ ብርሃን ተጸነሰች:: "ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተጸነስኪ" "ድንግል ሆይ! ኃጢአት ባለበት ሥጋዊ ፍትወት የተጸነስሽ አይደለም" እንዳለ ሊቁ:: [ቅዳሴ ማርያም] † 🕊 ቅዱስ ጴጥሮስ ሊቀ ሐዋርያት 🕊 † ዳግመኛ ይህች ዕለት የቅዱስ ጴጥሮስ መታሰቢያ ናት:: ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመዋዕለ ስብከቱ በዚህች ቀን ደቀ መዛሙርቱን ወደ ቂሣርያ ፊልጶስ ይዟቸው ሔደ:: በዚያም ጌታ ከእነሱ ራቅ ብሎ ተቀምጦ ነበርና የማይሰማቸው መስሏቸው እርስ በእርስ ይከራከሩ ገቡ:: የክርክራቸው መነሻ ደግሞ ጌታችን ነበር:: የዋሃን [ገና ምሥጢርን ያልተረዱ] ነበሩና አንዱ ተነስቶ "ኤልያስ ነው": ሌላኛው "ሙሴ": ሦስተኛው "ኤርምያስ ነው" በሚል ተከራከሩ:: ቅዱስ ጴጥሮስ ለብቻው ቆሞ ነበርና ጠርተው "ሃሳባችንን አስታርቅልን:: ለአንተስ ማን ይመስልሃል?" አሉት:: አረጋዊው ሐዋርያም ተቆጣቸው:: "እናንተ እንደምታስቡት እርሱ ከነቢያት አንዱ ሳይሆን "እግዚአ ነቢያት-የነቢያት ፈጣሪ ነው" አላቸው:: ወዲያውም ጌታ ጠርቷቸው ወደ እርሱ ቀረቡ:: ቸር አምላክ "ለምን ተጠራጠራችሁኝ" ብሎ መገሰጽ ሲችል እንዳይደነግጡ ጥያቄውን በፈሊጥ አደረገ:: "የሰውን ልጅ ሰዎች ማን ይሉታል?" አላቸው:: እነርሱም በልባቸው ያለውን የሌላ አስመስለው ተናገሩ:: ጌታችን "እናንተስ ማን ትሉኛላችሁ?" ቢላቸው ጸጥ አሉ:: ገና ሃይማኖታቸው አልጸናም ነበርና:: በዚያን ጊዜ ቅዱስ ጴጥሮስ ተነስቶ "አንተ ውእቱ ክርስቶስ ወልደ እግዚአብሔር ሕያው-አንተ የሕያው እግዚአብሔር የባሕርይ ልጁ ክርስቶስ ነህ" አለው:: [ማቴ.፲፮፥፲፮] ይህች ቃል የክርስትና ሃይማኖት መሠረት ናትና ጌታችን "አንተ ዓለት ነህ" ብሎ የቤተ ክርስቲያንን በዚህ እምነት ላይ መመስረት ተናገረ:: ለቅዱስ ጴጥሮስም "መራሑተ መንግስት-የመንግስተ ሰማያት መክፈቻ ቁልፍ [ሥልጣን]" ተሰጠው:: ሊቀ ሐዋርያትነትንም ደረበ:: ዛሬ ለበርካቶቹ የጸነነባቸው ይሔው እምነት ነው:: ኢየሱስ ክርስቶስን "አምላክ ወልደ አምላክ: ወልደ ማርያም: አካላዊ ቃል: ሥግው ቃል: ገባሬ ኩሉ: የሁሉ ፈጣሪ"ብለው ካላመኑ እንኳን ጽድቅ ክርስትናም የለም:: † 🕊 አፄ ናዖድ ጻድቅ 🕊 † ሃገራችን ኢትዮጵያ ምስፍና ከክህነት: ንግሥናን ከጽድቅ ያጣመሩ ብዙ መሪዎች ነበሯት:: ከእነዚህ አንዱ ደግሞ አፄ ናዖድ ናቸው:: ጻድቁ ንጉሥ የነገሡት ከ1487 እስከ 1499 ዓ/ም ሲሆን ለእመቤታችን በነበራቸው ልዩ ፍቅር ይታወቃሉ:: ካህን እንደ ነበሩም ይነገራል:: ዛሬ ሁላችን የምንወዳትን ጸሎት [ሰላም ለኪ: እንዘ ንሰግድ ንብለኪ . . .] የደረሷት እርሳቸው ናቸው:: ትልቁን መልክአ ማርያምም ደርሰዋል:: ይህ መልክእ ጣዕሙ ልዩ ነው:: የጻድቁ ንጉሥ ሚስት [ማርያም ክብራ] : ልጆቻቸው [አፄ ልብነ ድንግልና ቡርክት ሮማነ ወርቅ] እጅግ መልካም ክርስቲያኖች ነበሩ:: ንጉሡ አፄ ናዖድ ከባለሟልነት የተነሳ ድንግል ማርያምን "እመቤቴ ስምንተኛው ሺ መቼ ይገባል? ጊዜውስ እንዴት ያለ ነው?" አሏት:: እመ ብርሃንም በአካል ተገልጻ የዘመኑንና የሰውን ክፋት ነገረቻቸው:: ንጉሡም አዝነው "እመቤቴ! ከዛ ዘመን አታድርሺኝ" አሏት:: በዚህ ምክንያት የስምንተኛው ሺህ ዘመን መስከረም 1 በ1500 ዓ/ም ሊገባ እርሳቸው ነሐሴ 7 ቀን በ1499 ዓ/ም ዐርፈዋል:: https://t.me/eotcy ጌታችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ የድንግል እናቱን ጣዕም: ፍቅር: የቅዱስ ጴጥሮስን ሃይማኖትና የአፄ ናዖድን በረከት ያሳድርብን::     † ወስብሐት ለእግዚአብሔር †     † ወለወላዲቱ ድንግል †     † ወለመስቀሉ ክቡር †

ጾመ ፍልሰታ (ጾመ ፍልሰታ) ፍልሰታ ፆም(ጾመ ማርያም) ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር የፍልሰታ ፆም ከነሀሴ 1እስከ15 ነው ቤተ ክርስትያናችን እደሚገለፀው @eotcy "እመቤታችን ያረፈችው ጥር 21ቀን ነው ሐዋርያት በድኗን ሊቀብሯት ወደ ጌተሰማኒ ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ አይተዋቸው በተኗቸው በዚህ ጊዜ መላእክት የእመቤታችንን አስክሬን ወስደው በገነት አኑረውታል በ8ወር በነሀሴ ሐዋርያት አስክሬኗን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በፀሎትና በምህላ ቀብረዋታል በዚህ የቀብር ስነስርዓት ላይ ከ12 ሐዋርያት አንዱ ቶማስ አልነበረም። ቅዱስ ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ እየሩሳሌም ሲመጣ ያገኛታል በዚህ ጊዜ ትንሳኤዋን ሌሎች ሐዋርያቶች አይተው ለእሱ የቀረበት መስሎት ተናዶ በፊት የልጅሽን ትንሳኤ ሳላይ ቀረው አሁን ደግሞ የአንቺን ትንሳኤ ሳላይ ቀርቼ ነበር ብሎ ከደመና ሊወረወር ቃጣው በዚህ ጊዜ እመቤታችን ቶማስን አፅናንታ ከእሱ በቀር ሌላ ትንሰኤዋን እንዳላየ ነገረችው። @eotcy ቶማስም ሐዋርያት ወዳሉበት እየሩሳሌም በደረሰ ጊዜ እመቤታችንን ቀበርናት ብለው ነገሩት እሱም አውቆ ምስጥሩን ደብቆ አይደረግም ሞት በጥር በነሀሴ መቃብር አላቸው ለማሳየትም መቃብር ሲከፍቱ አጧት በዚህ ጊዜ"እመቤታችን ተነስታ አርጋለች ብሎ ሁኔታውን ተረከላቸው ለምስክርም ይሆናል ብሎ የሰጠችውን (ሰበኗን) አሳያቸው ሰበኗንም ለበረከት ቆራርጠው ተከፋፍለው ወደ ሀገረ ስብከት ተበታትነዋል በዓመቱ ትንሳዬሽን ቶማስ አይቶ እንዴት እኛ ይቅርብን ብለው ከነሀሴ 1 ጀምሮ ሱባዬ ገቡ በነሀሴ14ቀንም ትኩስ በድን አድርጕ አምጥቶ ሰጣቸው ከቀበሯትም በጟላ በነሀሴ16 ተነስታለች በዚህ ቀን ጌታ ቀድሶ እመቤታችንም በልጇ እጅ ቆርባለች ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሐዋርያት ቤተክርስትያን የእመቤታችንን በረከት ለማግኘት ይህች ጊዜ ትፆማለች። የእመቤታችን በረከቷ አማላጅነቷ ከሁላችንም ጋር ይሁን እናትነቷ ይብዛብን አሜን አሜን አሜን መልከም የፍልሰታ ፆም ይሁንልን ሀገራችንን ሰላም ታድርግልን አሜን ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲተ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር @eotcy

..የመቁረብ ተራው የማነው
...ሁሉጊዜ ፍልስታ በመጣ ቁጥር ትልቁ የልጆች ጥያቄ ተራው የማን ነው  የወንዶች ነው የሴቶች ነው ❓ ኧረ ግዴታ በዚህ ፍልስታ ሦስቴ መቁረብ አለብኝ    ልብሴ አልታጠበም ምን ላድርግ ውሃ እኛ ሰፈር የለችም ገላይንስ ሳልታጠብ  እማዬ ነገ ካልቆረብክ ከጓደኞቼ  አንሳለው ድንቅ የቅናት መንፈስ ይህ ያክል ጊዜ መቁረብ አለብኝ የእኛ ተራ ነው ከሰው እንዳላንስ እያሉ በትጉ የጌታን ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙን ልክ እንደ ኒቆዲሞስ የመሻት ስሜት ዛሬ ግን ይህን መሻት ሰይጣን ከልቦናችን አስወጥጦ የወጣትነት ጊዜያችን እያባከነብን  ነው መቼ ይሆን ተራው የማን ነው ብለን የምንጨነቀው❓ መቼ ይሆን ተራችንን በጉጉት የምንጠብቀው  መቼ ይሆን ክርስቶስ ወደ ሕይወታችን በጉጉት የምንጠራው ልክ እንደ ዘኪዮስ በጉጉት እርሱን ለማየት ዛፍ ላይ የምንወጣው ተፈጥሮ ወጣትነት ሳያግደን ወደ ጌታ  ቅዱስ ሥጋና ክቡር ደሙ የምንቀርበው
በዚህ ፍልስታ የማን ተራ ይሆን❓
ክርስቶስ ወደ ሕይወቱ በንስሐ ተዘጋጅቷ የሚጠራው የማን ተራ ይሆን ለታላቅ ክብር የሚጠራው የማን ተራ ይሆን  ከሰው ከፍ የማለት የሞት ተራ ሳይደርሰን የቅዱስ ሥጋ የክብር ደሙ ተራ ይድረሰን "...ጌታ ሆይ ቅዱስ ሥጋህን ክቡር ደምን የምቀበለው ብቁ ስለሆንኩ ሳይሆን ስለሚያስፈልገኝ ነው "
"...........እነሆ፥ የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ የመዳን ቀን አሁን ነው" --2ኛ ቆሮ 6፥2
Https://t.me/eotcy

* ማርያም * የእመቤታችን ስም ብዙ ትርጓሜ የያዘ ሲሆን ከእነዚህም መካከል የተወሰኑትን እንመለከታለን። #ማ - ማለት #ማህደረ_መለኮት (የመለኮት ማደሪያ ) ማለት ነው። #ር- ማለት #ርግብየ_ይቤላ የዋሂት የሰለሞን ርግብ ፣ በጥፉት ውሃ ጊዜ ለኖህ የለመለመ የወይራ ቅጠል በአፏ ይዛ የጥፉት ውሃ መጉደሉን ያበሰረች ለምህረት የመጣች ርግብ ማለት ነው። #ያ - ማለት #ያንቃዐዱ_ኀቤኪ ፣ በአንቺ አማላጅነት ያመኑ ሁሉ ቅድስት ሆይ ለምኝልን እያሉ ወዳንቺ ይለምናሉ ማለት ነው። #ም - #ምስአል_ወምስጋድ ወመስተስረዬ ኃጢአት፡ኃጢያትን ለማስተሰረይ ምህረትን ከፈጣሪ ዘንድ እያማለድሽ የምታሰጪ ማለት ነው። @eotcy #ማርያም ፦ ማለት #መርሕ_ለመንግስተ_ሰማያት ማለትነው። በዚህ ዓለም ያለ በስጋ አይነ ስውር የሆነ ሰው መሪ በትር እንደሚያስፈልገው ሁሉ ወደ ሰማያዊዉ ዓለም ለሚጓዙ ሁሉ መሪ የሆነችና በታመነው አማላጅነቷ መርታ ወደ መንግስተ ሰማያት የምታስገባ ስርየተ ኃጢያትን በረከተ ስጋንና በረከተ ነፍስን ከልጇ ከወዳጅዋ ከኢየሱስ ክርስቶስ እየለመነችና እያማለደች የምታሰጥ ማለት ነው ። #ማርያም ፦ ማለት #ፍፅምት ማለት ነው ። ለጊዜው መልክን ከደምግባት ጋር አስተባብራ ተገኝታለችና ፍፃሜው ግን ንፅሀ ስጋን ንፅሀ ልቡናን ንፅሀ ነፍስን አስተባብራ ተገኝታለችና። ፍፅምት ትባላለች። @eotcy #ማርያም ፦ ማለት #ፀጋ_ወሐብት ማለት ነው ። ለጊዜው ለእናቷ ለቅድስት ሀና ለአባቷ ለቅዱስ ኢያቄም ጸጋ ሐብት ሆና ማለት የስለት ልጅ ሆና ከፈጣሪዋ ተሰጥታለችና ። ፍፃሜው ግን በዕለተ አርብ ጌታችን መስቀል ላይ ሆኖ በወንጌላዊዉ ቅዱስ ዮሐንስ አማካኝነት በአለም ላለን ክርስቲያኖች ሁሉ እናት ሆና ተሰጥታለችና። @eotcy #ማርያም ፦ ማለት #ማሪ ማለት በዕብራይስጥ #እመቤት ማለት ነው ። #ሐም ፦ ማለት ደግሞ #ብዙሀን ማለት ነው ። በዕብራይስጥ #ማሪሐም ማለት #የብዙሀን_እመቤት ማለት ነው። የዓለም ሁሉ እመቤት የሆነች የእናት አማላጅ ናትና። የአባ ኤፍሬም ውዳሴ ፣ የአባ ሕርያቆስ ቅዳሴ ፣ የያሬድ ውብ ዜማ የነብያት ትንቢት የሀዋሪያት ስብከት ፡ የመላዕክት እህት የሰማዕታት እናት የሆነችው ማርያም ከፊት ትምራቹ ከሁዋላ ትከተላቹ ከግራ ከቀኝ ትቁምላቹ ። በጨነቃችሁ ነገር ሁሉ አለው ትበላቹ ከፈጣሪ ዘንድ ታማልዳቹ። @eotcy

እናቶቻችን አሃዱ ሳይባል ውስጥ ለመግባት ነው  የሚሮጡት እኛሳ ወደዬት ይሆን የምንሮጠው ፡፡ ልሩጥ አይደክመኝም! ©ታደለ ሲሳይ ============== ጉልበቴ ቢደክም፣ ቢዝል ሰውነቴ የነፍሴ ብርታቷ፣ ናት እና እመቤቴ ልሩጥ ወደ ቤቷ፣ ትቀደስ ሕይወቴ። .................... ልሩጥ አይደክመኝም፣ ልሂድ ስሟን ልጥራ የጨለመው ልቤ፣ በእመቤቴ ይብራ። ...................... ነፍሴ ብትቆሽሽ፣ ቢከስም ምግባሬ አኑሮኛልና፣ ከዱሮ እስከዛሬ ከእናቱ ጋራ ነው፣ ውሎዬና አዳሬ። .................. ልሩጥ አይደክመኝም፣ ልጓዝ ወደ ቤቱ ነፍሴን ያድሳታል፣ ቅዳሴ ማእጠንቱ። ................. ቢዘል ከንቱ ጉልበት፣ ቢደክም ተፈጥሮ ያፈረ ሰው የለም፣ ከእርሷ ጋራ ኖሮ። ...................... ሞት መጥቶ ሳይቀድመኝ፣ ሥጋ ሳይሆን አፈር ነፍሴ ከሥጋዬ፣ በዕድሜ ሳትባረር ልሩጥ አይደክመኝም፣ ልሂድ ወደ እግዚአብሔር። ................... ሞት መጥቶ ሳይቀድመን፣ ሳንሆን ሬሳ ኑ አብረን እንሩጥ፣ አብረን እንነሳ።😍🙏 https://t.me/eotcy

ስለ እርስዋ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል ፤ የክብርዋ ከፍታ ግን ያስቸግረኛል፡፡ ከቶ ምን ባደርግ ይሻለኛል❓ በቅድስና ውበት ስለተሞላችው ንጽሕት ትሕት እናገር ዘንድ አንደበቴ ብቁ አይደለም፡፡ ..
ስለ እርስዋ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል ፤ የክብርዋ ከፍታ ግን ያስቸግረኛል፡፡ ከቶ ምን ባደርግ ይሻለኛል በቅድስና ውበት ስለተሞላችው ንጽሕት ትሕት እናገር ዘንድ አንደበቴ ብቁ አይደለም፡፡ ... የተራ ቀለማት መዋሐድ ለማይመጥኗት ለዚህች እጅግ ክብርት እንዴት ያለ ሥዕልን ልሣል? ውበትዋ ከእኔ መጠበብ በላይ ነው ፤ አእምሮዬም እንዲሥላት አልፈቅድለትም❗️ የድንግል ማርያምን ክብርዋን ከመግለጥ ፀሐይን ከነብርሃንዋና ከነሙቀትዋ መሣል ይቀልላል፡፡ ምናልባት የፀሐይ ጨረር በሥዕል ሊቀመጥ ይችል ይሆናል፡፡ ስለ እርስዋ የሚነገረውን ነገር ግን አሟልቶ ለመስበክ አይቻልም፡፡ እርስዋን ከነማን ጋር መመደብ ይቻላል? ከደናግል ጋር? ከቅዱሳን ጋር? ከንጹሐን ጋር? ካገቡ ሴቶች ጋር? ከእናቶች ጋር? ከአገልጋዮች ጋር? እነሆ የድንግልናን ማኅተም ከወተት ጋር የያዘ ሰውነትዋን እዩ! መውለድዋንም ከታተመ ማኅፀንዋ ጋር እዩ! ከደናግል መካከል ናት ስል ሕፃን ይዛ ስታጠባ አያታለሁ! ከዮሴፍ ጋር ትኖራለች ስል በጋብቻ ቃልኪዳን እንዳልታሠረች አያለሁ! ስለ እርስዋ እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል ፤ የክብርዋ ከፍታ ግን ያስቸግረኛል፡፡ ከቶ ምን ባደርግ ይሻለኛል? ስለ እርስዋ ለመናገር ብቁ እንዳልሆንሁ በግልፅ እናገራለሁ፡፡ ከፍቅር የተነሣ ግን ተመልሼ መናገር ያምረኛል፡፡... ሱራፌል ከእሳቱ የሚሸሸጉለትን የእርሱን ከንፈሮች በቡሩካን ከነፈሮችዋ የሳመች እርስዋ የተባረከች ናት❗️ ዓለማት ሕይወትን የጠጡበትን ምንጭ እርሱን ያጠባች እርስዋ የተባረከች ነች።           ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ 𝚓𝚘𝚒𝚗 👉  https://t.me/eotcy

        የኪዳነ ምሕረት ዓመት የዘንድሮው ጾመ ፍልሰታ ብዙ ጥይቄ የሚመለስበት እንዲሆን እንጠብቃለን:: እመቤታችን በፍልሰትዋ ከሀገራችንም ከቤተ ክርስቲያናችንም የፈለሰውን ሰላምና ፍቅር በምልጃዋ እንድትመልስልንና የእርስዋን ትንሣኤ ሐዋርያት ባዩበት ጾም እኛም የቤተ ክርስቲያናችንንና ተስፋ የማንቆርጥባትና ብዙ ታውፋንያዎች የተረባረቡባትን የሀገራችንን ትንሣኤ የምናይበት ያድርግልን:: የድንግሊቱን ትንሣኤ የማያምኑ እንዳሉ ሁሉ የቤተ ክርስቲያንና የሀገር ትንሣኤ ከዚህ በኋላ ተስፋ የለውም የሚሉም ይኖራሉ:: እኛ ግን በቶማሳዊ የእምነት ደመና ላይ ሆነን የቤተ ክርስቲያንንና የሀገርን የሰላም ትንሣኤ እንጠብቃለን:: የሀገራችንን ችግር የሚፈታ ምንም ዓይነት ምድራዊ ጠቢብ የለም ጠቢበ ጠቢባን ልዑል እግዚአብሔር እርሱ ብቻ እጁን እንዲያስገባና እጅዋን ወደ እርሱ የምትዘረጋውን ሀገር "ወዳጄ ሆይ ተነሽ" ብሎ እንዲያስነሣት እንጠብቃለን:: በዕንባ የቀረበ ጸሎት የማይፈጽመው ነገር የለምና 2017 የኪዳነ ምሕረት ዓመት እንዲሆን በዚህ ሱባኤ እንማጸናለን:: ሱባኤውን የስርየት ያድርግልን የነደደውን እሳት ያብርድልን ለግፉዓን የሚበቀልላቸው አምላክ ፍትሕ ርትዕን ያድርግልን::  2017 ዓ.ም. የኪዳነ ምሕረት (የምሕረት ቃልኪዳን) ዓመት ይሁንልን https://t.me/eotcy

☞ ሱባዔ ምንድ ነው ❓
ሱባኤ በሰዋሰው ትርጉሙ "ሰባት"ማለት ሲሆን በመንፈስ አተረጋጎም አንድ ሰው ከዚህ ቀን እስከ ዚህ ቀን በጸሎት ከፈጣሪየ ጋር እገናኛለሁ ብሎ የሚያቅደው መንፈሳዊ ዕቅድ ነው ፡፡ ሰባት ቁጥር በእስራኤላውያን ዘንድ በሥራም በቃልም የሚገለጥ ፍጹም ቁጥር ነው፡፡ ለምሳሌ ፦ ፈጣሪ ዓለማት እግዚአብሔር በሰባተኛው ቀን ሥነ ፋጥረትን ከመፋጠር ማረፋ ፥ለጸሎት የሚተጉ ምዕመናን በቀን ለሰባት ጊዜ ማመስገናቸው የሰባት ቁጥር ፋጹምነት ያመለክታል ፡፡ [ዘፍ 2*2 , መዝ 118*164 ] አንድ ሰው 7 ቀናት ቢጾም "አንድ ሱባኤ ጾመ" ይባላል ፡፡
☞ ሱባኤ መቼ ተጀመረ ❓
የተጀመረው ከውድቀት በሓላ በመጀመርያው ሰው በአዳም ነው፡፡ ቅዱሳን መላእክት አዳምን ጸሎት እንዳስተማሩት የቤተ ክርስቲያናችን መዛግብት ያስረዳሉ በምላሹም ከልጅ ልጅህ ተወልጄ ስጋን ለብሼ ከ 5 ቀን ተኩል በኋላ አድንሃለሁ የሚለውን ቃል ኪዳን የሰማው ሱባኤ በመግባቱ ነው፡
☞ ሱባዔ ለምን❓
የሰው ልጅ ሓጢአት በሚስማማው የሥጋ ሰውነቱ ዘወትር ፈጣሪውን ይበድላል ፡፡ በፈፀመው በደል ኀሊናው ይወቅሰዋል ይጸጸታል ፡፡በመጀመርያ ደፋሮ በሰራው ሀጥያት በኋላ ይደነግጣል ይህ በማንኛውም ሰብአዊ ፋጥረት ኀሊና ውስጥ የሚፈራረቅ ክስተት ነው ፡፡ በዚህ ግዜ የፈጣሪውን ይቅርታ ለማግኝት ያስባል ይተክዛል፡፡ ሰው በደፋርነቱ የኃያሉን አምላክ ትእዛዝ ተላልፎ አለም ሲያስጨንቀው  ሸክሙን የሚያቃልልበትና የሚያስወግድበት  መንፈሳዊ ጥበብ ከቸሩ ፈጣሪ ተሰጥቶታል፡፡ ይህውም በጥቂት ድካም ሥጋ ያልተወሰነ ጸጋ እግዚአብሔር የሚያገኝበት ሥርዓት ሱባኤ ነው፡፡   ➊  እግዚአብሔርን ለመማጸን ፦ ማንኛውም ሰው ሱባኤ ሲገባ በቁርጥ ወደ ፈጣሪው የሚያቀርበው ተማፅኖ ሊኖረው ይገባል ፡፡ ምንም የምንጠይቀው ( የምንማፀነው) ነገር ሳይኖር ሱባዔ ብንገባ የምናገኝው መልስ አይኖርም ፡፡ ስለዚህ ሱባኤ ከመግባታችን በፊት ፦ሱባዔ የምንገባው ለምንድን ነው ❓  በማለት እራሳችንን መጠየቅ ይኖርብናል ፡፡ ➋ የቅዱሳንን በረከት ለመሳተፍ ቅዱሳን አባቶችና እናቶች የተጋደሉትን ተጋድሎ በማዘከር ቃል ኪዳን በተሰጣቸው ገዳማትና አድባራት የሚገባ ሱባኤ የቅዱሳን በረከት ተካፋይ ያደርጋል፡፡ በጾመ ነብያት የነብያትን ፤ በጾመ ሀዋርያት የሀዋርያትን ፤በጾመ ፋልሰታ የእመቤታችንን በረከት ለመሳተፋ ሱባኤ መግባት የነበረ ነው፡፡
☞ የሱባኤ አይነቶች
1 የግል ሱባኤ ( ዝግ ሱባኤ)  ፦ አንድ ሰው ብቻውን አመች ቦታ ማንም ሳያየው በግሉ የጸሎት በአቱን ዘግቶ በሰቂለ ኀሊና ሆኖ ፈጣሪው ብቻ እንዲያየው በኀቡዕ የሚፈፅመው ሱባኤ ነው ፡፡ 2 ,የማህበር ሱባኤ  ፦ ካህናት ምዕመናን ወንዶች ሴቶች ሽማግሌወች ፤ወጣቶች ፤በአንድ ሆነው በቤተ ክርስትያንና አመች በሆኑ ቦታወች ሁሉ ተሰብስበው የሚገብት ሱባዔ ነው፡፡ 3 , የአዋጅ ሱባዔ ፦ በሀገር  ላይ ድንገተኛ አደጋ ፤ አባር ቸነፈር ጦርነት ሲነሳ እንዲሁም በማህበረ ምዕመናን ላይ አስጊ የሆነ መቅሰፋት ሲከሰት እግዚአብሔር መዓቱን በምህረት ቁጣውን በትዕግስት እንዲመልስ የሚያዝ የሱባዔ አይነት ነው፡፡
☞ ቅድመ ዝግጅት
ሱባኤ ከመግባታችንም ሆነ ከገባን ግዜ እንዲሁም ከጨረስን በኋላ ምእመናን ቅድመ ዝግጅት ማድረግ ይገባናል ፡፡ ➊  ሱባኤ ከመግባት አስቀድሞ ፩ በመጀመርያ ሱባዔ የምንገባበትን ምክንያት ለይቶ ማወቅ ያስፈልጋል ፡፡ ፪ ሱባኤ ለመግባት የወሰንበትን ምክንያት ከለየን በኋላ ምክንያታችንን ይዘን የንስሃ አባታችንን ማማከር ያስፈልጋል፡፡ ፫ ለምን ያህል ቀናት መቆየት እንዳለብን መወሰን ያስፈልጋል ፡፡ሱባኤ ከዚህ እስከዚህ እቆያለሁ ብለን ዕቅድ የምንይዝበት ነው፡፡ ፬ ወቅትና ቦታ መምረጥ ተገቢ ነው፡፡በቤተ ክርስቲያናችን በአብዛሀኛው ግዜ ሱባኤ የሚገባው በአጽዋማት ወቅት በመሆኑ ይህንን መለየት ነው ፡፡ምክንያቱም በጾም ወቅት ብዙ አባቶች ጸሎት የሚይዙበት ስለሆነ ፀሎታችን ከእነርሱ ጋር አብሮ ያርግልናልና ነው፡፡ እዚህ ላይ በማንኛውም ግዜ ሱባኤ አይያዝም ለማለት አይደለም በማንኛውም ግዜ ፈተና ያጋጠመው ሰው ሱባዔ ሊይዝ ይችላል፡፡ ➋  በሱባኤ ግዜ  ሀ. በጸሎት ሰአት ዓምድና ግድግዳ ሳይደገፉ መቋሚያ ሳይዙ በሁለት እግር ቀጥ ብሎ በመቆም መጸለይ ይኖርብናል፡፡ እንዲሁም ፊትን ወደ ምስራቅ መልሶ መቆም ወደ ግራ ወደ ቀኝ አለመዟዟር በሰቂለ ህሊና ኾኖ መጸለይ ይገባል፡፡ ለ . በቅደም ተከተል መፀለይ ይገባል በመጀመርያ አአተብ ከሚለው ተጀምሮ አቡነ ዘበሰማያትን ጠቅሶ ጸሎተ ሀይማኖትን መጨረስ ፡፡ሰግዱ እና ስለ መስቀል በሚያነሳው ላይ እየሰገዱና እያማተቡ መጸለይ ፡፡ በማስቀጠል አቡነ ዘበሰማያት ፤መዝሙረ ዳዊት ውዳሴ ማርያም ሌሎችንም ማስከተል ከዚያ 41 ግዜ ኪራላይሶ ይባላል ፡፡ ሐ.  በሱባዔ ግዜ ከተራሚው የሚጠበቀው ነገር ሐጢአቱን እያሰበ ማዘን ማልቀስ ለእያንዳንዱ በደል ማልቀስ ማዘን ይገባዋል ፡፡ መ.  በመጨረሻም ሱባዔ የገባው ሰው ሱበዔውን ሳይጨርስ ወይም አቋርጦ ከማንኛውም ሰው ጋር ፈፅሞ መገናኝት የለበትም ፡፡ ➌ ከሱባዔ በኋላ ላቀረብነው ተማፅኖ እግዚአብሔር የሚያደርግልንን ነገር  መጠበቅ ይኖርብናል ፡፡ "ሱባዔ" የገባ ሰው ሁሉ ራዕይ ላያይ ይችላል፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መልስ አሰጣጥ ለማንም ግልጽ አይደለም ፡፡ ከሱባዔ በኋላ መጀመሪያ የምናገኝው የህሊና ሰላም ነው  ፡፡ ይህ ትልቅ የአምላክ ስጦታ ነው  ፡፡ ከዚህ ባሻገር ሱባኤ ገብተን ያሰብነውን  ካላገኝን ዳግመኛ ተዘጋጅተን እስከ መጨረሻው ሰዓት በመማፀን መጽናት ይኖርብናል፡፡፡    መልካም የሱባዔ ጊዜ ይሁንላችሁ

እውነተኛ ደቀ መዝሙር መሆን የጀመርኩት አሁን ነው 👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇 ቅዱስ አግናጢዮስ ወደ ሞት እየተወሰደ ወደ ሮም የተላከ ጥቅልል ( ደብዳቤ )     ✍  በሰውነቴም በልቤም ሀይል እንዳገኝ ጸልዩልኝ በእርግጥ ክርስቲያን ሆኜ ለመገኘት እንጂ በስም ብቻ ክርስቲያን መባል አይበቃኝምና በአፍ ብቻ ሳይሆን በእውነት ፈቃደኛ መሆን ያስፈልገኛል እውነተኛ ክርስትና ብርቱ በመሆን የሚገለጥ ነው እንጂ በዝምታ አይደለም ።     ✍ እናንተ ካልከለከላችሁኝ ለአምላኬ ለመሞት መሆኔን በሰው ሁሉ ፊት እመሰክራለሁ ስለዚህ አላግባብ እንዳታስቡልኝ እለምናችኋለሁ ወደ እግዚአብሔር እንድደርስ የአራዊት ጉርሻ ብሆንም እንኳ የእግዚአብሔር የስንዴ ቅንጣት ነኝ የአራዊትም ጥርሶች ቢፈጩኝ ለኢየሱስ ክርስቶስ ንፁህ እንጀራ እሆናለሁ ።   ካንቀላፋሁ በኋላ ለማንም ሰው ሸክም እንዳልሆን ሰውነቴ በሙሉ ይለቅ አራዊት መቃብሬ እንዲሆኑ ይምጡብኝ እንዲይዙኝም እናንተ አነሳሷቸው በመሞቴ በክርስቶስ ነጻነት አገኛለሁ ስለዚህ አንዳች ምድራዊና አላፊ ነገር መመኘት እንደማያስፈልገኝ ተረድቻለሁ ።      ✍ ገና በመንገድ ላይ ሳለሁ በባህር በየብስም ሌትና ቀን አሁንም ከአራዊት ጋር እየታገልኩ ነኝ የአስር ነብሮች ቁራኛ ነኝ ማለት ከወታደሮች ጋር ነው ያለሁት እነርሱም መልካም ነገር ቢያደርጉላቸው የባሰውን ክፋት የሚያሳዩ ናቸው ይሁንና በእነርሱ ማጉላላት ልምምድ አገኛለሁ በዚህ ግን እጸድቃለሁ ማለቴ አይደለም ።     ✍ እውነተኛ ደቀ መዝሙር መሆን የጀመርኩት አሁን ነው የሚታይም ሆነ የማይታይም ማንም ሰው በምቀኝነት ዓይን አይመልከተኝ ልድረስ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ እሳት መስቀል የአውሬ ብዛት መጨፍጨፍ የአጥንቶቼ መበታተን የብልቶቼ መሰባበር የሰውነቴ መጨፍጨፍ ሁሉ የሰይጣን ስቃይ ይምጣብኝ ብቻ ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ልድረስ ።    የቅዱስ አግናጢዎስ በረከቱ ይደርብን አሜን https://t.me/eotcy