Sheger fm ሸገር ሬድዮ
Sheger fm ሸገር የናንተዉ ነው፡፡
نمایش بیشتر- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
در حال بارگیری داده...
Download the latest Ethiopian Music Videos. For audio join @Music_Ethiopia For comment-> @Jhanoy
በአባይ ግድብ ላይ የኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የግብፅ ድርድር ከግድቡ ግንባታ ጎን ለጎን እየተካሄደ ነው፡፡ግብፅም የምታቀርበው ምክንያት ማባሪያ ባይኖረውም፣ ውሃ የሚቋጥር ሀሳብ ባለመሆኑ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አመዛዛኝ ለሆነ ሁሉ ግልፅ ነው፡፡ግብፅ ለምታራምደው እኔ ብቻ ልጠቀም ለሚለው አቋም ድጋፍ ከአባይ ውጪ ምንም ዓይነት ውሃ የማገኝበት መንገድ የለም የሚል ነው፡፡
የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት የወጣውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አተገባበርን ተከትሎ የፀጥታ ሀይሎች እየወሰዱ ያሉት እርምጃ ተመጣጣኝ አለመሆኑና የሰብአዊ መብት ጥሰት ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፡፡በሌላ በኩል አንዳንድ የመንግስት ስራ ሀላፊዎች ምንም ዓይነት የመብት ጥሰት እንዳልተፈፀመ በመገናኛ ብዙሃን ሲናገሩ ይደመጣል፡፡ ይህን በተመለከተ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በምዕመኖቼ ላይ ደርሷል ያለችውን የመብት ጥሰት በመግለጫ አውጥታለች፡፡
ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም በአለም የቡና መጠጫ ጠረጴዛ ላይ ተቆልቶ እና ተፈጭቶ ያልተቀመሱላት የቡና ፍሬዎች ለመጀመርያ ግዜ እንደተመረጡላት ተሰማ።በአሜሪካ የካፕ ኦፍ ኤክሰለንስ ውድድርን ለመጀመርያ ጊዜ የኢትዮጵያ ቡናዎች ለመግዛት 140 የሚሆኑ ገዥዎች እንደተመዘገቡላት እና አለም ላይ አንቱ በተባሉ የቡና ቀማሾች እንደተዳኙላት የቡናና ሻይ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አዱኛ ደበላ ለሸገር ነግረዋል።
ከ2 ወር ባነሰ ጊዜ ውስጥ የህዳሴው ግድብ የውሃ ሙሌት እንደሚጀመርና በመጠኑ የኤሌክትሪክ ሀይል ማመንጨት በዚያኛው አመት እንደሚጀመር በኢትዮያ በኩል ይፋ ሆኗል፣ አካሄዱን በተመለከተና ከኢትዮጵያ የቀረበውን ሀሳብ የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቀበልም ማለታቸው ተሰምቷል፡፡
Copy Right © 2013-2017 Sheger FM 102.1. All Rights Reserved.
ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ የሰጠቻት ከአንድ ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ በሽታውን ለመከላከል በብርቱ እንደሚያግዝ ታምኖነታል፡፡ ከዚህም ባለፈ የጥሪቱ ልገሳ የሁለቱን ሀገሮች ወዳጅነት የበለጠ ያበረታዋል ተብሏል፡፡በፈረንሳይ የልማት ኤጀንሲ በኩል 40 ሚሊዮን ዩሮ እንደተሰጠ በፈረንሳይ ከኢትዮጵያ ኤምባሲ የመረጃ መረብ ተመልክተናል፡፡
Copy Right © 2013-2017 Sheger FM 102.1. All Rights Reserved.