ኡመተ ረሱል
رفتن به کانال در Telegram
የአላህ ሰላም እና እዝነት በናንተ ላይ ይውረድ ውድ የአላህ ባሮች በዚህ #channel ላይ የተለያዩ ♥ ኢስላማዊ አስተምህሮቶች ♥ አስተማሪ ታሪኮች ♥ ቀልዶች እና ♥ ወቅታዊ አሳሳቢ ነገሮችን ወደናንተ እናደርሳለን ፨ ፨ ፨ ለማንኛውም አስተያየት @Ummate_resul_bot ይጠቀሙ
نمایش بیشتر1 977
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-2930 روز
آرشیو پست ها
1 977
عن أبي هريرة رضي الله عنه قال :
قال رسول الله ﷺ :
((مَنْ يَقُمْ لَيْلَةَ القَدْرِ إيمَانًا وَاحْتِسَابًا غُفِرَ لَهُ مَا تَقَدَّمَ مِنْ ذَنْبِهِ))
رواه البخاري.🍂
1 977
🎙
ይሄ የኔ የማዲህ ቢላል ፋሪስ የቴሌግራም ቻናል ነው...
የቴሌግራም ቻናሌ ቤተሰብ በመሆን አዳዲስና የድሮ ስራዎቼን ማግኘት ትችላላችሁ ❤️👇👇👇
1 977
عن عامر بن ربيعة رضي الله عنه ،
عن النبي ﷺ قال :
((مَا مِنْ مُسْلِمٍ يُصَلِّي عَلَيَّ إلَّا صَلَّتْ عَلَيْهِ المَلَائِكَةُ مَا صَلَّى عَلَيَّ ، فَلْيُقِلَّ العَبْدُ مِنْ ذَلِكَ أوْ لِيُكْثِرْ))
رواه ابن ماجه.🍂
«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ»🧡
1 977
💫💫
ለ አሽረል አዋኺር መረሳት የሌለባቸው 3 ነገሮች
💞💞
-ለመስራት ቀላል
-ቦታ የማይመርጡ
-ጊዜ የማይወስዱ
-ትልቅ አጅር የሚያስገኙ
💞💞
💌በየቀኑ ከኢሻዕ ቡሃላ ቢያንስ 1ብር ሰደቃ ላገኘነው ድሀ መስጠት
💮1ዱ ለሊት ለይለቱል ቀድር ላይ ስለምንሰጥ 84 ዓመት ሙሉ ሰደቃ የሰጠን ያህል ይፃፍልናል
💌ሁለት ረከዐ በየለሊቱ መስገድ
💮ለይለቱል ቀድር ላይ 84 ዓመት ሙሉ ለይል እንደቆምን ይፃፍልናል
💌ሱረቱል ኢኽሏስ 3 ጊዜ መቅራት
💮ሱረቱል ኢኽላስ 3 ጊዜ የቀራ ሰው ቁርአን ሙሉ እንደቀራ ይቆጠራል፡ ለይለቱል ቀድር ላይ ስንቀራ 84 ዓመት ቁርዓን እንዳከተምን ይፃፍልናል
💥ሱብሀነላህ!!
ይሄን ቪዲዮ ቢያንስ ለ30 በመላክ ተጠቃሚ አንዲሆኑ አድርጉ
Share
@osmanethiopia
@osmanethiopia
1 977
🔎~ለይለቱል ቀድር~🖇
▰▱▰▱▰▱▰▱▰▱
✅:አሏህ በቁርአኑ በሱረቱል ቀደር ላይ እንዲህ ብሏል፦
▽▽▽➷
إِنَّا أَنْزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةِ الْقَدْرِ)) القدر: ١))
እኛ (ቁርኣኑን) በመወሰኛይቱ ሌሊት አወረድነው፡
وَمَا أَدْرَاكَ مَا لَيْلَةُ الْقَدْرِ)) القدر: ٢))
መወሰኛይቱም ሌሊተ ምን እንደ ኾነች ምን አሳወቀህ?
لَيْلَةُ الْقَدْرِ خَيْرٌ مِنْ أَلْفِ شَهْرٍ)) القدر: ٣))
መወሰኛይቱ ሌሊት ከሺሕ ወር በላጭ ናት፡፡
تَنَزَّلُ الْمَلَائِكَةُ وَالرُّوحُ فِيهَا بِإِذْنِ رَبِّهِمْ مِنْ كُلِّ أَمْرٍ)) القدر: ٤))
በርሷ ውስጥ መላእክትና መንፈሱ በጌታቸው ፈቃድ በነገሩ ሁሉ ይወርዳሉ፡፡
سَلَامٌ هِيَ حَتَّى مَطْلَعِ الْفَجْرِ)) القدر: ٥))
እርስዋ እስከ ጎህ መውጣት ድረስ ሰላም ብቻ ናት፡
△△△➹
📖:በዚህ አያ ለይለቱል ቀድር ከሺ ወራቶች በላይ በላጭ እንደሆነች ተገልፃል። ታዲያ ማነው ከእኛ መካከል ይችን ሌሊት በኢባዳ በማሳለፍ የዚችን ሌሊት ሙሉ በረካዋን ለማግኘት የሚተጋ? ኢንሻአላህ አላህ ያሳካልናል
📗:በሰኺህ ሙስሊም በተዘገበው ሐዲስ ነብዩ(ﷺ) በመጨረሻዎቹ አስር ሌሊቶች ለይለቱል ቀድርን ሻቱ (ፈልጉ) ብለዋል።
🖊:በመጨረሻዎቹ የረመዷን ምሽቶች አብዝተን ቁርአን መቅራት ፣ አሏህን ማውሳት እና ዱአ ማብዛት ይኖርብናል። ምክኒያቱም የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ሶደቃ ወይም ዘካ የምንሰጥበት ፣ ነፍስያችነን የምንመረምርበት ፣ ዱአ አብዝተን የምናደርግበት ፣ መሃርታን የምንለምንበት ፣ ፆማችንን ሙሉ የምናደርግበት ጊዜ ነውና።
📌:በመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ጥረታችነን ወይም ኢባዳችነን እጥፍ እናደርግ ዘንድ አሏህ(ﷻ) የለይለቱል ቀድር ቀን መቼ እንደሆነ ደብቆታል።
➥:ነብዩ(ﷺ) በለይለቱል ቀድር አምኖበትና ከአሏህ ምንዳ እንደሚያገኝ ተስፋ አድርጎ ለሶላት የቆመ ሰው ያለፉት ወንጀሎቹ ሁሉ ይማሩለታል ብለዋል።
📗:በሰኺህ ሙስሊም በተዘገበው ሐዲስ ነብዩ (ﷺ) ከሌላው ጊዜ በበለጠ በመጨረሻዎቹ አስር ሌሊት በኢባዳ ላይ ይተጉ ነበር።
➯:በዚህ ጊዜ ከሰዎች ጋር ያላቸውን ግኑኝነት በመገደብ ዱአቸውን ያጧጡፉ ነበር። ነብዩ(ﷺ) ይህን ያደርጉ የነበረው ልባቸው የበለጠ አሏህ ጋር እንዲሆንና ህሊናቸውን ከአለማዊ ጉዳይ ለማላቀቅ ነበር።
📘:በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ የረመዷን የመጨረሻዎቹን አስር ቀናት መጀመሩን ተከትሎ ነብዩ(ﷺ) ጠንክረው ይሰራሉ፤ ሌሊቱን ሙሉ ሶላት ይሰግዳሉ። ቤተሰባቸውንም ለሶላት ይቀሰቅሱ ነበር።
1 977
Gize ye Allah stota nw be agebabu myaz yegna gdeta nw yalefut kenat alefu be krut kenay enberta teketari demoz mikefelew ye weru magebadja lay mehonun anzenga
ye tsomu alama ke mgb na wha takbo mwalu sayhon Allahn mfrat nw ke wenjeloch mrak na be ibada mtenaker yasfelgal
Resul s.a.w endih blewal jenet wst reyan yemibal ber ale ye kyama elet tsomegnoch besu ygebalu... Allah kenesu yadrgen
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
“የአላህ መልእክተኛን (ሰ.ዐ.ወ) ለይለቱል ቀድርን ካወኩኝ ምን ብዬ ዱዓ ላድርግ? ብዬ ጠየኩኝ። እርሳቸውም ‘አላህ ሆይ አንተ ይቅር ባይ ነህ። ይቅርታንም ትወዳለህ። ይቅር በለኝ!፤ በይ’ አሉኝ።” (ቲርሚዚ ዘግበውታል)
አላህ የተሻለ ያውቃል!
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
Home ለይለቱል ቀድር
ለይለቱል ቀድር
ጥያቄ፡ ያለሁበት ለሊት ለይለቱል ቀድር መሆኑን እንዴት ማወቅ እችላለሁ? ይህን የተከበረ ለሊት እንዴትስ ላሳልፍ? ሶላት በመስገድ ወይስ ቁርአን በመቅራት?
መልስ፡ ቢስሚላሂ ረህማኒ ረሒም
ለይለቱል ቀድርን (የውሳኔዋን ለሊት) ህያው ማድረግ እንደሚወደድ የሚጠቁሙ ብዙ ሐዲሶች ተዘግበዋል። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ፡-
”من قام رمضان إيمانًا واحتسابًا غفر له ما تقدم من ذنبه “ ”ومن قام ليلة القدر إيمانًا واحتسابًا غفر له ما تقدم من ذنبه“
“(የአላህን ቃልኪዳን) እያመነና (ምንዳውን) እየተሳሰበ በረመዳን ለሊት የቆመ (የሰገደበት) ሰው ያሳለፈውን ወንጀል በሙሉ ይማራል።” “(የአላህን ቃልኪዳን) እያመነና (ምንዳውን) እየተሳሰበ ለይለቱል ቀድርን የቆመ (የሰገደበት) ሰው ያሳለፈውን ወንጀል በሙሉ ይማራል።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
ለይለቱል ቀድር የተባረከ ለሊት ነው። አላህ ወህይ (ራእይ) ለማውረድ መርጦታል። አላህ እንዲህ ይላል፡-
حم * وَالْكِتَابِ الْمُبِينِ * إِنَّا أَنزَلْنَاهُ فِي لَيْلَةٍ مُّبَارَكَةٍ إِنَّا كُنَّا مُنذِرِينَ
“ሐ.መ (ሓ ሚም)፡፡ አብራሪ በኾነው መጽሐፍ እንምላለን፡፡ እኛ (ቁርኣኑን) በተባረከች ሌሊት ውስጥ አወረድነው፡፡ እኛ አስፈራሪዎች ነበርንና፡፡” (አድ-ዱኻን 44፣ 1-3)
አላህ በዚህ አንቀፅ ውስጥ በመፅሀፉ (በቁርአን) ይምላል። በተባረከ ለሊት እንዳወረደውም ይናገራል። ይች ለሊትም ለይለቱል ቀድር ናት።
ለይለቱል ቀድር የተለያዩ ምልክቶች አሏት። በርሷ ውስጥ ሙስሊሞች የሚጠመዱባቸው የተለያዩ ሥራዎችም አሉ። በዚያ ቀን የሚሠሩ አምልኮዎችም ሌላ ጊዜ ከሚሠሩት ይበልጥ የላቀ ክብርና ደረጃ ያስገኛሉ።
ከለይለቱል ቀድር ምልክቶች መሀል የተወሰኑትን እንጥቀስ። ኢማም ኢብኑ ተይሚያህ ፈታዋ አል-ኩብራ ላይ እንዲህ ይላሉ፡-
“ለይለቱል ቀድር ከረመዳን የመጨረሻው አስር ቀናት ላይ የሚከሠት አንድ ለሊት እንደሆነ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ተነግሯል። ‘ከረመዷን ወር የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ውስጥ ነው ያለችው።’ ብለዋል፤ ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ)። በአስሩ የረመዷን ወር የመጨረሻ ቀናት በነጠላ የሚቆጠሩት ቀናት ላይ እንደሆነችም የሚጠቁሙ ሐዲሶችም እንዲሁ ተዘግበዋል። ነጠላነት ግን ካለፉት የረመዳን ቀናት ወይም ከሚቀሩት የረመዳን ቀናት አንፃር ሊታይ ይችላል። ስለዚህ ካለፈው አንፃር ካየነው ሀያ አንደኛው፣ ሀያ ሦስተኛው፣ ሀያ አምስተኛው፣ ሀያ ሠባተኛው እና ሀያ ዘጠነኛው ቀን ይበልጥ ለይለቱል ቀድር ሊሆኑ እንሚችሉ ይጠረጠራሉ። እነዚህ ብዙዎች የሚጠብቁበት አቆጣጠር ነው። ይሁንና የቀሩትን የረመዷን ቀናት በማሰብ ልንቆጥርም እንችላለን። ምክንያቱም ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ፡-
لتاسعة تبقى لسابعة تبقى لخامسة تبقى لثالثة تبقى
“እርሷ በሚቀሩት ሰባት፣ አምስት፣ ሦስት… ቀናት ውስጥ ትሆናለች።”
በዚህ መሠረት ወሩ ሠላሳ ቀን ከሆነ ከታች ወደ ላይ ሲቆጠር ጥንድ ቀናት የሚሆኑት ለሊቶች ከላይ ወደ ታች ሲቆጠር ለይለቱል ቀድር ሊሆኑ ይችላሉ። ማለትም ሀያ ሁለተኛው ለሊት ዘጠኝ ቀናት የሚቀሩት ለሊት ሊሆን ቻለ። ስለዚህ ሀያ አራተኛው ቀን ደግሞ ሰባት ቀናት የሚቀሩት ለሊት ሆነ… እያልን ልንሄድ ነው። ታላቁ ሶሐባ አቡ ሰዒድ አልኹድሪይ (ረ.ዐ)- በሶሒሕ እንደተዘገበው- ያለፈውን ሐዲስ በዚህ መልኩ ተረድተውታል።
በዚሁ መሠረት ወሩ በሀያ ዘጠኝ ካበቃ ደግሞ ሒሳቡ ከዚህ በፊት ከተጠቆሙት ቀናት ጋር ተመሳሳይ ቀናት ላይ ለይለቱል ቀድርን ልንጠብቅ ነው ማለት ነው። ስለዚህ ሙስሊም ሁሉ የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ውስጥ ለይለቱል ቀድርን በሙሉ ንቃት መጠበቅ ይገባል። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) “አስሩ የመጨረሻ ቀናት ላይ በንቃት ጠብቋት!” ብለዋል። በተለይም የመጨረሻዎቹ ሰባት ቀናት ላይ መጠበቁ በጣም ይጠነክራል። በተለየ ሁኔታ ደግሞ ሀያ ሰባተኛው ለሊት እንደሆነች ኡበይ ኢብኑ ከዕብ (ረ.ዐ) ይነግሩናል። ‘እንዴት አወቁ?’ ተብለው ቢጠየቁ ‘ነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) በነገሩን ምልክት ነዋ። የእርሷ (የለይለቱል ቀድር) ንጋት ላይ ፀሀይ ልብስ እንደሚታጠብበት ሳፋ (ጠሽት) ንፁህና ደካማ ሆና ትወጣለች። ሲሉ መልእክተኛው ነግረውናል።’
ኡበይ ኢብኑ ከዕብ ከነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) ይዘው የነገሩን ይህ ምልክት የታወቀ የለይለቱል ቀድር ምልክት ነው። ለሊቷ መሀለኛ የአየር ሁኔታ ያላትና ብርሀን ያላት መሆኗ ሌሎች ምልክቶች ናቸው። በእርግጥም አላህ ለአንዳንድ ሠዎች በመናም (በህልም) ሊያሳውቃቸውና ብርሀኗን ሊያሳያቸው ይችላል። ይህ ለይለቱል ቀድር ነው ብሎ የሚነግራቸው ሠው ሊልክባቸው ወይም ልቡን ከፍቶለት እውነት ለይለቱል ቀድር መሆኗን የሚለይበት ነገር ልቡ ውስጥ ሊጥልበት ይችላል።” የኢብኑ ተይሚያህ ንግግር እዚህ ላይ አበቃ።
በእለቱ የሙስሊሞች ሥራ ምን መሆን አለበት?
ለሊቱ የተባረከ ለሊት ነው። ከአንድ ሺህ ወራት በላይ ዋጋ ያለው ለሊትም ነው። አላህ -ልክ ጁምዓ ውስጥ ያለችውን፣ ዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝባትን ውድ ሰዓት እና ታላቁን ስሙን (ኢስሙል አዕዘምን) እንደደበቀ ሁሉ- ለይለቱል ቀድርንም ደብቋታል። የመደበቃቸው ምስጢርም ሠዎች እነሱን ለማግኘት እንዲጥሩ ለማድረግ ነው። በእርግጥ ለይለቱል ቀድር መች እንደሆነ በውል ባይታወቅም አስሩ የመጨረሻ ቀናት ውስጥ መሆኑን አሳልፈናል። ስለዚህ እርሷን ለማግኘት አስሩን የመጨረሻ ቀናት ለሊቶች በሙሉ በዚክር፣ በዱዓ፣ ቁርአን በመቅራት፣ ሶላት በመስገድ… ማሳለፍ ያስፈልጋል።
የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) አስሩ የመጨረሻ የረመዳን ቀናት ውስጥ -ከምንም ጊዜው በላይ- ለዒባዳ ይጠነክራሉ። ቁርኣን ያነባሉ። ሶላት ያበዛሉ። ዱዓ ላይ ይጠነክራሉ። ቡኻሪ እና ሙስሊም አዒሻን (ረ.ዐ) ዋቢ በማድረግ እንደዘገቡት:-
أن النبي صلى الله عليه وسلم كان إذا دخل العشر الأواخر أحيا الليل وأيقظ أهله وشد المئزر
“የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) አስሩ የረመዳን የመጨረሻ ቀናት በሚገቡ ጊዜ ለሊቱን ህያው ያደርጋሉ። ቤተሰቦቻቸውን ያነቃሉ። ሽርጣቸውን ያጠብቃሉ።” (ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል)
በአህመድና በሙስሊም ዘገባ:-
كان يجتهد في العشر الأواخر ما لا يجتهد في غيرها
“መልእክተኛው (ሰ.ዐ.ወ) በሌላ ጊዜ ከሚያደርጉት አምልኮ በላቀ ሁኔታ በእነዚህ አስር ቀናት ውስጥ ያደርጋሉ።” (አህመድና ሙስሊም ዘግበውታል)
ለይለቱል ቀድርን እንድንጠብቅ የአላህ ነብይ (ሰ.ዐ.ወ) ብዙ ጊዜ ቅስቀሳዎችን አድርገዋል። ከሰዪዲና አቡሁረይራህ እንደተዘገበው የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “(የአላህን ቃልኪዳን) እያመነና (ምንዳውን) እየተሳሰበ ለይለቱል ቀድርን የቆመ (የሰገደበት) ሰው ያሳለፈውን ወንጀል በሙሉ ይማራል።” ስለዚህ ይህ ሐዲስ ለሊቱን በሶላት ማሳለፍ እንሚወደድ እያስተማረ ነው።
ያን ቀን ዱዓ እንድናደርግ የሚቀሰቅሱ ሐዲሶችንም እናገኛለን። ቲርሚዚ አዒሻን (ረ.ዐ) ዋቢ አድርገው ባስተላለፉት ሐዲስ
قلت: يا رسول الله، أرأيت إن علمت أي ليلة ليلة القدر ما أقول فيها؟ قال: قولي: اللهم إنك عفو تحب العفو فاعف عني
1 977
ኢዕቲካፍ
ኢዕቲካፍ፡- ድንጋጌው፣ መስፈርቶቹ፣ የሚያበላሹት እና ጊዜው
ኢዕቲካፍ፡- ድንጋጌው፣ መስፈርቶቹ፣ የሚያበላሹት እና ጊዜው
ጥያቄ፡- ብዙ ጊዜ ኢዕቲካፍ የማድረግ ልምድ ቢኖረኝም በተጨባጭ ስለኢዕቲካፍ የማላውቃቸው ነገሮች ሞልተዋል። በኢዕቲካፍ ወቅት የሚፈቀድልኝ ነገሮች ምንድን ናቸው? በኢዕቲካፍ ወቅት ሐራም የሚሆኑብ ነገሮችስ ምንድን ናቸው? ለስራ እየወጣሁ ተመልሼ መግባት እችላለሁ?…
መልስ፡- ቢስሚላሂር-ረሕማኒር-ረሒም አል-ሐምዱሊል-ላሂ ረብ-ቢል ዓለሚን ወስ-ሶላት ወስ-ሰላም ዐላ ረሱሊላህ
ኢዕቲካፍ ወደ አላህ የሚያቃርብ መልካም ተግባር ነው። ሱናም ነው። በተለይም በረመዷን ውስጥ እጅግ ከሚወደዱ ተግባራት መሀል አንዱ ነው። በተለይም ደግሞ በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት እጅግ የጠበቀ ሱና ነው። ምክንያቱም ለይለቱል-ቀድር (የውሳኔዋ ለሊት) ያለችው በእነዚህ አስርት ቀናቶች ውስጥ ነውና።
ኢዕቲካፍ እንደማንኛውም አምልኮ መስፈርቶች (ሹሩጥ)፣ ስነስርዐቶች (አዳብ)፣ የሚያፈርሱት ነገሮች እና በውስጡ የሚፈቀዱ ነገሮች አሉት።
በፊሊስጢን ውስጥ በሚገኘው ኢስላማዊ ዩኒቨርሲቲ መምህር የሆኑት ኡስታዝ፣ ዶክተር ሳሊም አሕመድ ሰላማ እንዲህ ብለዋል፡-
ኢዕቲካፍ ማለት፡-
በቋንቋ ትርጉሙ አንድን ነገር አጥብቆ መያዝ ማለት ነው። በሸሪዓ ትርጓሜው ደግሞ መስጂድን አለመልቀቅ፣ ወደ አላህ ለመቃረብ በሚል ኒያ እርሱ ውስጥ መቆየት ማለት ነው።
የኢዕቲካፍ ድንጋጌ
ኢዕቲካፍ በሸሪዓው ውስጥ የተደነገገ ስለመሆኑ በዑለሞች መካከል ስምምነት አለ። ኢዕቲካፍ ስለጾም የተጠቀሱ አንቀጾች መሀል በቁርኣን ውስጥ ተጠቅሷል። አላህ እንዲህ ይላል፡-
وَلَا تُبَاشِرُوهُنَّ وَأَنتُمْ عَاكِفُونَ فِي الْمَسَاجِدِ
“እናንተም በመስጊዶች ተቀማጮች ስትኾኑ አትገናኙዋቸው፡፡” (አል-በቀራ 2፤ 187)
ነብዩም (ሰ.ዐ.ወ.) የረመዷን የመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት ላይ ኢዕቲካፍ ያደርጉ እንደነበር ተዘግቧል። ባረፉበት የመጨረሻው ዓመት ላይ ግን- አቡሁረይራ እንዲህ ይላሉ- “የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) በረመዷን አስርት ቀናት ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር። ባረፉት አመት ላይ ግን ሃያ ቀናት ኢዕቲካፍ አድርገዋል።”
የኢዕቲካፍ ብይኑ (ሁክም)፡-
ኢዕቲካፍ ወደ አላህ የሚያቃርብ ሱና የአምልኮ ዘርፍ ነው። በተለይም በረመዷን ጥብቅ አምልኮ ነው። በተለይም በመጨረሻዎቹ አስርት ቀናት ውስጥ በጣም የጠበቀ ሱና ነው። ምክንያቱም በእነዚህ አስርት ቀናት ውስጥ ለይለቱል-ቀድር ትገኛለች። ነገርግን ስለት ባደረገ ሰው ላይ ግዴታ ይሆናል። ማለትም ሰውየው ኢዕቲካፍ ለማድረግ ከተሳለ ዋጂብ ይሆናል።
የኢዕቲካፍ ሸርጦች፡-
ሙስሊም መሆን
አዕምሮ ጤነኛ መሆን
የመለየት እድሜ (ተምዪዝ/ስድስት ወይም ሰባት ዓመት መሙላት)
ኒያ ማድረግ
መስጂድ ውስጥ መሆኑ
ከወር አበባ፣ ከድህረ ወሊድ ደም እና ከጀናባ ንፁህ መሆን
በኢዕቲካፍ ወቅት የሚወደዱ ነገሮች (ሙሰታሃባት)፡-
የአምልኮ ተግባራት ማብዛት። ሶላት፣ ቁርኣንን ማንበብ፣ የዒልም ሰዎችን መፅሀፍት ማንበብ፣ በመስጂዱ ውስጥ የሚሰጡ ምክሮችን እና ትምህርቶችን መከታተል።
ዋዛ ነገርን (ማላ የዕኒን) መተው። ከክርክር፣ ከስድድብ፣ ከትችት፣ ከሃሜት እና ነገር ከማሳበቅ መራቅ።
በመስጂዱ ውስጥ አንድ ስፍራን አጥብቆ መያዝ። ቦታ አለመቀያየር።
በኢዕቲካፍ ወቅት የሚፈቀዱ ነገሮች (ሙባሃት)፡-
የግድ ለሆኑ ጉዳዮቹ መውጣት። ለምሳሌ፡- ለመፀዳዳት፣ ህመም ላይ ካለ ለህክምና፣ ኢዕቲካፍ ያደረገበት መስጂድ ጁሙዓ የማይሰገድበት ከሆነ ጁሙዐ ለመስገድ…
መስጂድ ውስጥ መብላት፣ መጠጣት እና መተኛት ይችላል። ነገርግን የመስጂዱን ንፅህና መበከል ሐራም ነው።
የሚፈቀዱ ንግግሮችን መናገር ይቻላል።
ፀጉር ማበጠር፣ ጥፍር መቁረጥ፣ አካሉን ማፅዳት፣ ጥሩ ልብስ መልበስ እና ሽቶ መቀባትም ይቻላል።
በኢዕቲካፍ ጊዜ የሚጠሉ ነገሮች (መክሩህ)፡-
መሸጥና መግዛት
ኃጢያት ያለበትን ነገር መናገር
አምልኮ ነው ብሎ አስቦት ከሆነ ዝም ማለት
ኢዕቲካፍን የሚያፈርሱት ነገሮች (ሙብጢላት)፡-
አውቆ- ያለጉዳይ- ከመስጂድ መውጣት
ወሲብ መፈፀም
በእብደት ወይም በስካር አዕምሮን መሳት
የወር አበባ እና የድህረ ወሊድ ደም መከሰት
አላህ ይጠብቀንና ከኢስላም መውጣት (ሪድ-ዳ)
የኢዕቲካፍ መጀመሪያ እና መጨረሻው፡-
ሰውየው ወደ መስጂድ ገብቶ ኢዕቲካፍ መስጂድ ውስጥ በመቆየት ወደ አላህ ለመቃረብ ከነየተ እስከሚወጣ ድረስ ኢዕቲካፍ ላይ እንዳለ ይቆጠራል። የመጨረሻዎቹን አስርት የረመዷን ቀናት ኢዕቲካፍ ለማድረግ ከነየተ ኢዕቲካፍ ወደሚያደርግበት ስፍራ በአስራ ዘጠነኛው ቀን ፀሃይ ከመጥለቋ በፊት መግባት አለበት። ሲወጣም የወሩ መጨረሻ ላይ ፀሀይ ከጠለቀች በኋላ- ማለትም በዒድ ለሊት- መውጣት አለበት።
የኢዕቲካፍ ጥቅሙ፡-
ኢዕቲካፍ ማድረግ የነብዩን ሱና ህያው ማድረግ ነው። ተከታታይ የአምልኮ ተግባራት ላይ በማሳተፍም ልብን ህያው ያደርጋል። ሰውየው ከራሱ ጋር የመገለል እና እስትንታኔ የማድረግ እድል ያገኝበታል። ያለፈውን ሂደቱን ገምግሞ እርምት ለመውሰድ እና መጪውን ጊዜ በተሻለ ሁኔታ ወደ አላህ የመቅረብ ወኔ እንዲያገኝ ያስችለዋል። ኢዕቲካፍ የልብ ብርሃን ነው። ብዙ መልካም ነገሮች ያስገኛል። በአላህ እዝነትም ከፍታና ደረጃንም ይጨምራል። በተለይም በአስርቱ የረመዷን የመጨረሻ ቀናት ሲሆነ ለይለቱል-ቀድርን ያስገኛል። ለይለቱል-ቀድርን ያገኘ ሰው ከአንድ ሺህ በላይ የሆኑ ወራትን አግኝቷል።
አላሁ አዕለም!
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
አነጋጋሪው ሴቶች ያወጡት ነሺድ.... ክሊፑ ላይ ያየሁትን ማመን አቃተኝ 🙊ይድረስ ለሚመለከተዉ አካል ሁሉ ኧረ ወደየት እየሄድን ነው ከ18 አመት በታች የሆነ ክሊፑን እንዲያዩት አይመከርም!!
ሙሉ video ለማግኘት ክፈት የሚለውን ይጫኑ😱
1 977
#ረመዷን_18
በዛሬው ተመሳሳይ ቀን ማለትም በሂጅራ አቆጣጠር በ21ደኛው አመት በረመዷን በ18ተኛው ቀን ላይ ነበር ... ታላቁ የጦር መሪ "ኻሊድ ኢብኑ ወሊድ" (ረዲየሏሁ ዐንሁ) ይችን ዓለም የተሰናበቱት።
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
ዘካቱልፊጥር (ክፍል 1)
ብዙ ሙስሊሞች ስለሚሰሯቸው የአምልኮ ተግባራት በቂ ግንዛቤ የላቸውም። በተለይም ዘካቱልፊጥርን የመሠሉ በአመት አንዴ የሚከሠቱ አምልኮዎች በአግባቡ ሲተገበሩ አይስተዋልም። በመሆኑም ይችን ትንሽ ፅሁፍ ትጠቅማለች ብለን ፅፈናታል።
ዘካቱልፊጥር ምንድን ነው?
ዘካቱልፊጥር የረመዳን ፆም መገባደጃ ላይ የሚሠጥ ሶደቃ (ምፅዋት) ነው። በነፍስ ወከፍ እያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። “ሰደቀቱል-ፊጥር”፣ “ሰደቀቱ ረመዳን” እና “ዘካቱል-በደን” ተብሎም ይጠራል- ዘካቱልፊጥር።
መች ተደነገገ? አስፈላጊነቱስ?
ዘካቱልፊጥር ከሒጅራ በኋላ ሁለተኛው አመት ላይ ተደነገገ። እንደ አብዝሀ ዑለሞች እምነት ዘካቱልፊጥር ግዴታ (ዋጂብ) ነው። ጥቂቶች የጠበቀ ሱና (ሱና ሙአከዳ) እንጂ ግዴታ አይደለም የሚል አቋም አላቸው። ግዴታ ለመሆኑ የሚቀርቡ መረጃዎች በርካታ ናቸው። ከነርሱ መሀል ጥቂቶቹን እናንሳ። በቅድሚያ ከቁርአን፡-
وَالَّذِينَ فِي أَمْوَالِهِمْ حَقٌّ مَّعْلُومٌ
لِّلسَّائِلِ وَالْمَحْرُومِ
“እነዚያም በገንዘቦቻቸው ላይ የታወቀ መብት ያለባቸው የኾኑት። ለለማኝ ከልመና ለሚከለከልም (መብት ያለባቸው የኾኑት)።” (አል-መዓሪጅ 70፤ 24-25)
ከሐዲስ ደግሞ ይኸኛውን እንይ፡- ከዐብዱላህ ኢብኑ ዐባስ እንደተዘገበው
فَرَضَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم زَكَاةَ الْفِطْرِ؛ طُهْرَةً لِلصَّائِمِ مِنَ اللَّغْوِ وَالرَّفَثِ، وَطُعْمَةً لِلْمَسَاكِينِ، مَنْ أَدَّاهَا قَبْلَ الصَّلاةِ فَهِيَ زَكَاةٌ مَقْبُولَةٌ، وَمَنْ أَدَّاهَا بَعْدَ الصَّلاةِ فَهِيَ صَدَقَةٌ مِنَ الصَّدَقَاتِ
“ዘካቱልፊጥር ፆመኛ ከአልባሌ ንግግርና ከረፈስ (የወሲብ ወሬዎች) እንዲፀዳበትና ለድሆች ምግብ እንዲሆን የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) ደንግገውታል። ከሰላት በፊት የሠጠ ሰው ተቀባይነት አለው። ከሰላት በኋላ የሠጠ ሰው ግን እንደማንኛውም ሰደቃ ትሆንለታለች።” (አቡ ዳዉድና ኢብኑ ማጃህ ዘግበውታል፤ ሃኪም ሀዲሱን በቡኻሪ መስፈርት ሶሂህ ብለውታል)
የፊጥር ዘካ የፆመኞችን ፆም ይጠግናል። በሠላሳው የፆም ቀናት ወቅት ከተናገራቸው መጥፎ ንግግሮች፣ ከአጓጉል ቀልዶች ማበሻ በመሆን ፆሙን እንደማሟያና መጠገኛ ሆኖ ፅዱ እና ንፁህ ያደርገዋል። ከዚህም ሌላ ዘካተልፊጥር በውስጡ ከፍተኛ የሆነ ማህበራዊ ጥቅም ይዟል። ድሆችና ችግረኞች በተባረከው የዒድ ቀን ለልመና እንዳይሠማሩና የሰውን እጅ ከማየት ተብቃቅተው ተደስተው እንዲውሉ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል።
ማን ላይ ነው ግዴታ የሚሆነው? ምን ያህል ነው መጠኑ?
ከኢብኑ ዑመር (ረ.ዐ) እንደተዘገበው፡-
فَرَضَ رَسُولُ اللَّهِ صلى الله عليه وسلم زَكَاةَ الْفِطْرِ صَاعًا مِنْ تَمْرٍ أَوْ صَاعًا مِنْ شَعِيرٍ، عَلَى الْعَبْدِ وَالْحُرِّ، وَالذَّكَرِ وَالأُنْثَى، وَالصَّغِيرِ وَالْكَبِيرِ، مِنْ الْمُسْلِمِينَ، وَأَمَرَ بِهَا أَنْ تُؤَدَّى قَبْلَ خُرُوجِ النَّاسِ إِلَى الصَّلاةِ
“የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ.) -ባሪያና ጨዋን፣ ወንድና ሴትን፣ ህፃንና አዋቂን ሳይለዩ- ዘካቱል-ፊጥርን በማንኛውም ሙስሊም ላይ ግዴታ አድርገዋል። ዘካው የሚሠጠው አንድ ቁና ተምር ወይም አንድ ቁና ገብስ ነው። ሰዎች ለሰላት ወደ መስገጃ ቦታ ከመውጣታቸው በፊት ዘካው እንዲሰጥም አዘዋል።” (ቡኻሪና ሙስሊም)
ይህ ሐዲስ የረመዳንን ፆም ያጠናቀቀ ሙስሊም በዒዱ ቀን ምን እንደሚጠበቅበት ያስተምራል። ፆሙን በትጋት የጨረሰና የአላህን ሽልማት የሚጠባበቅ ሙስሊም ዘካውን እስካላወጣ ድረስ ፆሙ በሠማይና በምድር መሀል ተንጠልጥሏል። ስለዚህ ለራሱና ሊቀልባቸው ግዴታ ለሚሆንበት ሠዎች (ሚስት፣ ልጅ፣ ወላጆች…) እድሜና ፆታ ሳይለይ ዘካቱልፊጥር ሊያወጣላቸው ይገባል። ዘካውን ልቡ ዘና ብሎና ነፍሱ ተደስታ ማውጣት አለበት።
የዘካው መጠን ትንሽ ነው። አንድ ቁና (ሷዕ) ለአንድ ሰው ብቻ። አንድ ሷዕ ግምቱ 2.25 ኪ.ግ. (ሁለት ኪሎ ግራም ከሩብ) ተብሏል። እህሉ አብዝሀ የሀገሩ ሰዎች እንደቀለብነት ከሚጠቀሙበት አይነት ይሁን። ሙስሊም ሆኖ የረመዳን አንዲት አፍታን ያገኘ ሠው ሁሉ እዚህ ግዴታ ውስጥ ይካተታል። ስለዚህ ከዒድ ለሊት (ሠላሳኛው ቀን ፀሀይ ከመጥለቁ) በፊት ለተወለደ ህፃን ሳይቀር ዘካቱልፊጥር ሊወጣለት ይገባል። ዘካው ወንድና ሴትን ጨዋና ባሪያንም አይለይም። ግዴታውን የሚሸከመው የራሱንና ወጪያቸውን ሸፍኖ ሊያስተዳድራቸው ግዴታ የሚሆንበትን ሠዎች የሃያ አራት ሠዐት ቀለብ ችሎ ትርፍ ያለው ሰው ብቻ ነው። ሃብት የሌለው ደሃ ሳይቀር ለራሱና ለቤተሰቡ የዒድ ለሊትና ቀኑን የሚበላው ቀለብ ካለው ዘካቱልፊጥር እንዲያወጣ ይገደዳል። በዚህ የአምልኮ ተግባር ኡመቱ ሁሉ የመስጠት ባህሉን ያዳብራል። የቸርነት ባህሪን ያካብታል። የመረዳዳትና የመተጋገዝ ባህሉም በሚያምርና በሚያስደንቅ ሁኔታ ይፋ ይሆናል።
1 977
አነጋጋሪው ሴቶች ያወጡት ነሺድ.... ክሊፑ ላይ ያየሁትን ማመን አቃተኝ 🙊ይድረስ ለሚመለከተዉ አካል ሁሉ ኧረ ወደየት እየሄድን ነው ከ18 አመት በታች የሆነ ክሊፑን እንዲያዩት አይመከርም!!
ሙሉ video ለማግኘት ክፈት የሚለውን ይጫኑ😱
1 977
ህይወትን ተመለከትኳት
ድንቅ ምክር በሼኽ ኻሊድ ራሺድ
አማርኛ ትርጉም
ተከታታይ የሸህ ኻሊድን ትርጉም ለማግኘት ዩቱዩብ ፔጃችንን ሰብስክራይብ አድርጉ
https://youtu.be/FxlomdO0zuc
1 977
የበድር ዘመቻ‼️
============
✍️ በሒጅሪያ የዘመን አቆጣጠር የዛሬ 1439 ገደማ በፊት ወደኋላ ስንመለስ፣
ለሙስሊሙ አለም አንድ ፋና ወጊ ቀንን እናስታውሳለን።
313 ገደማ የሚሆኑ ሙስሊሞች፣ ወደ 950 ገደማ የሚጠጉ የቁረይሽ አጋሪያንን በበድር ላይ ጦርነት ገጥመዋል።
ይህ ጦርነት የተካሄደው መልዕክተኛው ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ከመካ ወደ መዲና በተሰደቱ በሁለተኛው አመት፣ እለተ ጁሙዓ በወርሃ ረመዳን 17, ልክ የዛሬ 1439 አመት በፊት ነበር።
በጎርጎረሳውያኑ አቆጣጠር March 13, 624 G.C መሆኑ ነው።
*
✔️የቁረይሽ ሙሽሪኮች ሙስሊሞችን አላስቀምጥ ብለው ከመካ አባረሯቸው።
ሙስሊሞቹ መካ ላይ ግፍ ሲበዛባቸው በየቦታው ተሰደቱ።
ወደ መዲናም ከነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ጋር አቀኑ።
መዲና ላይ ሙስሊሞቹ ተመችቷቸው መቀመጣቸውን ያወቁ ጊዜ፣ ቁረይሾች አሁንም ከመዲና ማጥፋት አለብን ብለው ጦር ሰብቀው ተነሱ።
ለጦርነቱ በጣም ተዘጋጅተው ብዙ የጦር መሳሪያ ይዘዋል።
ሙስሊሞቹ ግን ምንም አልያዙም ከአላህ እርዳታ ውጭ።
በዚህ እለት እነ አቡበከር፣ ዑመር፣ ዓልይ፣ ሐምዛ፣ ሙስዐብ ኢብኑ ዑመይር፣ ዙበይር ኢብኑል አዋም፣ አማር ኢብኑ ያሲር፣ አቡዘር አልጚፋሪይና ሌሎችም ታላላቅ ሶሐቦች ተገኝተዋል።
👉ጦርነቱ ተጀመረ።
አላህ አማኞችን ረዳ።
ወደ አምስት ሺህ መላኢካዎችን አላህ ለሙስሊሞቹ ረዳት ሰጣቸው።
ከሙስሊሞቹ አስራ አራት ሶሐቦች ተገደሉ።
ከቁረይሽ ሙሽሪኮች ግን ወደ ሰባ የሚሆኑ አጋሪያን ተገደሉ።
||
በመጨረሻም ዲሉ ለሙስሊሞች ሆነ።
የመጀመሪያው መዕረካም ነበር። ከዚያን ጊዜ በፊት ሙስሊሞች የሚኖሩት እየተሰቃዩና እየተገፉ ነበር። አምልኮ የሚፈጽሙት ተደብቀውም ነበር።
የዚያን ቀን ጀምሮ ግን ይበልጥ አንገታቸውን ቀና አደረጉ። ልባቸው ይበልጥ በተስፋ ተሞላ። ወኔያቸው ጨመረ።
የአጋሪያኑን ትቢያነት አወቁ። ቀኑ ለሙስሊሞች ፈር ቀዳጅ ነበር።
ቀኑ የዲል ቀን ነው፣ ሁልግዜም ይዘከራል።
እለቱ ሐቅና ባጢል የለየበት የፉርቃን ቀን በመባልም ይታወቃል።
በሐዲሥ ላይ እንደመጣው አላህ የበድር ጦርነት ላይ የተሳተፉትን ጀነት እንደሚያስገባቸው ተነግሯል።
✍️ክስተቱን አላህ ቁርኣን ላይ እንዲህ ሲል አስፍሮታል፥
"በበድርም፣ እናንተ ጥቂቶች ሆናችሁ ሳለ አላህ በእርግጥ ረዳችሁ፤ አላህንም ታመሰግኑ ዘንድ ፍሩት።
ለምእመናን ጌታችሁ በሦስት ሺህ መላእክት የተወረዱ ሲሆን ቢረዳችሁ አይበቃችሁንም? በምትል ጊዜ (አስታዉስ)።
አዎን፣ ብትታገሡና ብትጠነቀቁ ከዚህም ፍጥነታቸዉ (ጠላቶቻችሁ) ቢመጡባችሁ፣ ጌታችሁ ምልክት ባላቸዉ፣ አምስት ሺህ መላእክትን ይረዳችኋል።
አላህም (እረዳታዉን) ለናንተ ብስራትና ልቦቻችሁ በርሱ እንዲረኩ እንጂ አላደረገዉም፤ ድልም መንሳት አሸናፊ ጥበበኛ በሆነዉ አላህ ዘንድ እንጅ ከሌላ አይደለም !!
(ድልን ያጐናጸፋችሁ) ከነዚያ ከካዱት ከፊልን ሊቆርጥ (ሊያጠፋ)፣ ወይም ሊያዋርዳቸዉን ያፈሩ ሆነዉ እንዲመለሱ ነዉ !!"
[አሉ ዒምራን፥ 123-127]
||
"ከጌታችሁ ርዳታን በፈለጋችሁ ጊዜ፣ እኔ በሺህ መላእክት ተከታታዮች ሲሆኑ እረዳችኋላሁ ሲል ለናንተ የተቀበላችሁን (አስታውሱ)።
አላህም (ይኽንን ርዳታ) ለብስራትና ልቦቻችሁ በርሱ ሊረኩበት እንጂ ለሌላ አላደረገውም፤ ድልም መንሳት ከአላህ ዘንድ እንጂ ከሌላ አይደለም፤ አላህ አሸናፊ ጥበበኛ ነውና። "
[አል አንፋል፥ 9-10]
||
በጥቅሉ ከበድር ዘመቻ ብዙ የምንማረው አለን።
1) የበላይ ለመሆንና ዲልን ለመጎናጸፍ በቁጥር መብዛት አያስፈልግም።
በቁጥር በነበር ሙስሊሞች ከሙሽሪኮች በሶስት እጅ ያነሱ ነበሩ።
ዋናው ትክክለኛ እምነትና በአላህ ላይ እውነተኛ የሆነ ቁርጥ ተመኪነት ነው።
*
2) አላህ ካልረዳህ በቁጥር ብትበዛም ትሸነፋለህ።
ለምሳሌ አጋሪያኑ ሶስት እጥፍ በቁጥር ይበልጡ ነበር።
*
3) ድል ለመጎናጸፍ የግድ ተወርዋሪ ሚሳኤልና የጦር ካምፕ ሊኖርህ አይገባም።
የቁረይሽ አጋሪያን በዘመኑ አለ የተባለን የጦር መሳሪያን ታጥቀው ተዘጋጅተው ነበር፣ ግን ተሸነፉ።
||
በአጠቃላይ፣ እኛ በገንዘብም ይሁን በጦር መሳሪያ ከከሐዲያን አንጻር ትንሽ ያለን ብንሆንም፣
እውነተኛ አማኝ ከሆንን እናሸንፋለን።
አለበለዚያ ግን ሁልጊዜም እንዋረዳለን፣ የፈለገ ያክል በቁጥር ብንበዛም፣ ተወንጫፊ ሚሳኤል ቢኖረንም ዋጋ የለውም።
||
አሁንም ቢሆን በዘመነኛ ነገሮች ከመለከፍ ተቆጥበን፣
የዚያን ዘመን ትውልድ አርአያችን እናድርግ።
የነርሱን ፈለግ እንከተል።
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
ቀደምት ሙሰሊም ሳይንቲስቶችና ተመራማሪዎች
ኢብኑ ነፊስ (1213-1288 እ.ኤ.አ)
ዐላእ አድ-ዲን አቡ አል ሀሠን ዓሊ ኢብኑ አቢ አል ሀዝም አል ቀርሺ አል ደመሽቂ አልሚስሪ ይባላል፡፡ የተወለደው እ.ኤ.አ በ607 በደማስቆ ከተማ ነው፡፡ ትምህርቱንም የተማረው በኑረዲን አዝ-ዘንኪ በተመሠረተው የህክምና ኮሌጅ ሆስፒታል ነው፡፡ በህክምናው ትምህርት ዙሪያ መምህሩ የነበረው ሙሀዘብ አድ ዲን አብዱል ረሂም ሲሆን ከህክምናው ትምህርት ሌላ ኢብኑ ነፊስ የህግ ትምህርትን፣ የሥነ-ፅሁፍንና ሥነ-መለኮትን ትምህርት ተከታትሏል፡፡
በፊቅሂ እውቀትም በሻፊዒይ መዝሀብ እውቀቱ የበቃ (ኤክስፐርት) ሲሆን የታወቀ ሃኪምም ነበር፡፡
በህክምናና በህግ እውቀት ከፍተኛ ትምህርት ካገኘ በኋላ ወደ ካይሮ በመጓዝ በታዋቂው ናስሪ ሆስፒታል በዋና ሥራ አስኪያጅነት የተሾመ ሲሆን እዚያም ሣለ ለታዋቂው የቀዶ ጥገና ባለሙያ ኢብኑ አል ቁፍ አል መሲሂን ጨምሮ ለበርካታ የህክምና ጠበብቶች ሥልጠና ሠጥቷል። ከዚህም ሌላ በካይሮ በሚገኘው መንሱሪያ ትምህርት ቤት ግልጋሎት ሠጥቷል፡፡ የሞተውም እ.ኤ.አ በ678 ሲሆን የግል ቤቱን፣ ቤተ-መፅሃፍቱንና ክሊኒኩን ለመንሱሪያ ሆስፒታል በስጦታነት አበርክቷል፡፡
የኢብኑ አን-ነፊስ ዋነኛ አስተዋፅኦዎቹ በህክምና ዙሪያ ያተኮሩ ናቸው፡፡ አቀራረቦቹም በቀደሙት ሥራዎች ላይ ዝርዝር አስተያየቶች መፃፍን፣ እነሱን በጥልቀት መመርመርንና የራሱን ወጥ የሆኑ አስተዋፅኦዎች መጨመርን ያካትታሉ፡፡ ጉልህ ተፅእኖ ከነበራቸው ትላልቅ ወጥ ሥራዎቹ መካከል ከሦስት ምእተ አመታት በኋላ በዘመናዊው ሣይንስ እንደገና የተደረሠበት የደም ዝውውርን ማግኘቱ ይጠቀሳል፡፡ ሣንባ ውስጥ የሚገኙትን ነገሮች በትክክል ለመግለፅ የመጀመሪያው ሰው ሲሆን ስለ ብሮንካይ ምንነት፣ በሰው ልጅ የደም ቱቦዎችና በአየርና በደም መካከል ስለሚከሠተው አጠቃላይ ሁኔታ በዝርዝር አስፍሯል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ልብ ላይ የሚገኘውን የኮሮናሪ አርተሪን (ልብ ላይ የሚገኝ የደም ሥር) ጥቅም በመግለፅ የልብ ጡንቻዎችን የሚመግብበትን ሁኔታ ተንትኗል፡፡
አሽ-ሻሚላ ፊ አጥ-ጢብ የሚባለው ባለ ብዙ ጥራዝ መፅሃፉ ሦስት መቶ ክፍሎችን ሊይዝ የሚችል እንሣክሎፒዲያ ተደርጎ የተቀረፀ ሲሆን በመሞቱ ምክኒያት ሊጠናቀቅ አልቻለም፡፡ የእጅ ፅሁፎቹ ግን ዛሬም ድረስ በደማስቆ ይገኛሉ፡፡ በአይን ህክምና ዙሪያ የተፃፈው መፅሃፉ ወጥ የሆነ የራሱ አስተዋፅኦው ሲሆን ዛሬም ድረስ አለ፡፡ ነገር ግን እጅግ ሊታወቅ የቻለው መፅሃፉ ሙጃዝ አልቃኑን የሚባለው ሲሆን በሱ ዙሪያ በርካታ ማብራሪዎችም ተፅፈዋል፡፡ ከሱ ማብራሪያዎች መካከል አንዱ በሂፖክራተስ መፅሃፍ ላይ የጻፈው ነው፡፡ የኢብኑ ሲናን ቃኑን አስመልክቶ ዛሬም ድረስ ያሉ በርካታ ጥራዞችን ፅፏል፡፡ እንደዚሁም በሁነይን ኢብኑ ኢስሃቅ መፅሃፍ ላይም ማብራሪያ ፅፏል፡፡ ሌላው ታዋቂውና የሱ ወጥ ጥንቅር አስተዋፅኦ የሆነው መፅሃፍ ምግብ በጤና ላይ ስለሚያሣድረው ተፅእኖ የሚዳስሰው ኪታብ አልሙኽታር ፊ አል አግዚያ የሚባለው ነው፡፡
የኢብኑ አን-ነፊስ ሥራዎች በያኔውን ዘመን የነበረውን እውቀት በእጅጉ ከመዋሃዳቸውም በላይ አበልፅገውታልም፡፡ ከዚህም ባለፈ መልኩ በምሥራቁም ሆነ በምእራቡ ዓለም በነበረው በያኔው የህክምና ሣይንስ ላይ ከፍተኛ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ ሆኖም ከመፅሃፎቹ መካከል አንደኛው ብቻ ነው ወደ ላቲን የተተረጎመው፡፡ በመሆኑም ከፊል ሥራዎቹ ለአውሮፓ ሣይታወቁ ለረጅም ዘመናት ኖረዋል፡
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
ቀደምት ሙሰሊም ሳይንቲስቶችና ተመራማሪዎች
ኢብኑ ነፊስ (1213-1288 እ.ኤ.አ)
ዐላእ አድ-ዲን አቡ አል ሀሠን ዓሊ ኢብኑ አቢ አል ሀዝም አል ቀርሺ አል ደመሽቂ አልሚስሪ ይባላል፡፡ የተወለደው እ.ኤ.አ በ607 በደማስቆ ከተማ ነው፡፡ ትምህርቱንም የተማረው በኑረዲን አዝ-ዘንኪ በተመሠረተው የህክምና ኮሌጅ ሆስፒታል ነው፡፡ በህክምናው ትምህርት ዙሪያ መምህሩ የነበረው ሙሀዘብ አድ ዲን አብዱል ረሂም ሲሆን ከህክምናው ትምህርት ሌላ ኢብኑ ነፊስ የህግ ትምህርትን፣ የሥነ-ፅሁፍንና ሥነ-መለኮትን ትምህርት ተከታትሏል፡፡
በፊቅሂ እውቀትም በሻፊዒይ መዝሀብ እውቀቱ የበቃ (ኤክስፐርት) ሲሆን የታወቀ ሃኪምም ነበር፡፡
በህክምናና በህግ እውቀት ከፍተኛ ትምህርት ካገኘ በኋላ ወደ ካይሮ በመጓዝ በታዋቂው ናስሪ ሆስፒታል በዋና ሥራ አስኪያጅነት የተሾመ ሲሆን እዚያም ሣለ ለታዋቂው የቀዶ ጥገና ባለሙያ ኢብኑ አል ቁፍ አል መሲሂን ጨምሮ ለበርካታ የህክምና ጠበብቶች ሥልጠና ሠጥቷል። ከዚህም ሌላ በካይሮ በሚገኘው መንሱሪያ ትምህርት ቤት ግልጋሎት ሠጥቷል፡፡ የሞተውም እ.ኤ.አ በ678 ሲሆን የግል ቤቱን፣ ቤተ-መፅሃፍቱንና ክሊኒኩን ለመንሱሪያ ሆስፒታል በስጦታነት አበርክቷል፡፡
የኢብኑ አን-ነፊስ ዋነኛ አስተዋፅኦዎቹ በህክምና ዙሪያ ያተኮሩ ናቸው፡፡ አቀራረቦቹም በቀደሙት ሥራዎች ላይ ዝርዝር አስተያየቶች መፃፍን፣ እነሱን በጥልቀት መመርመርንና የራሱን ወጥ የሆኑ አስተዋፅኦዎች መጨመርን ያካትታሉ፡፡ ጉልህ ተፅእኖ ከነበራቸው ትላልቅ ወጥ ሥራዎቹ መካከል ከሦስት ምእተ አመታት በኋላ በዘመናዊው ሣይንስ እንደገና የተደረሠበት የደም ዝውውርን ማግኘቱ ይጠቀሳል፡፡ ሣንባ ውስጥ የሚገኙትን ነገሮች በትክክል ለመግለፅ የመጀመሪያው ሰው ሲሆን ስለ ብሮንካይ ምንነት፣ በሰው ልጅ የደም ቱቦዎችና በአየርና በደም መካከል ስለሚከሠተው አጠቃላይ ሁኔታ በዝርዝር አስፍሯል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ልብ ላይ የሚገኘውን የኮሮናሪ አርተሪን (ልብ ላይ የሚገኝ የደም ሥር) ጥቅም በመግለፅ የልብ ጡንቻዎችን የሚመግብበትን ሁኔታ ተንትኗል፡፡
አሽ-ሻሚላ ፊ አጥ-ጢብ የሚባለው ባለ ብዙ ጥራዝ መፅሃፉ ሦስት መቶ ክፍሎችን ሊይዝ የሚችል እንሣክሎፒዲያ ተደርጎ የተቀረፀ ሲሆን በመሞቱ ምክኒያት ሊጠናቀቅ አልቻለም፡፡ የእጅ ፅሁፎቹ ግን ዛሬም ድረስ በደማስቆ ይገኛሉ፡፡ በአይን ህክምና ዙሪያ የተፃፈው መፅሃፉ ወጥ የሆነ የራሱ አስተዋፅኦው ሲሆን ዛሬም ድረስ አለ፡፡ ነገር ግን እጅግ ሊታወቅ የቻለው መፅሃፉ ሙጃዝ አልቃኑን የሚባለው ሲሆን በሱ ዙሪያ በርካታ ማብራሪዎችም ተፅፈዋል፡፡ ከሱ ማብራሪያዎች መካከል አንዱ በሂፖክራተስ መፅሃፍ ላይ የጻፈው ነው፡፡ የኢብኑ ሲናን ቃኑን አስመልክቶ ዛሬም ድረስ ያሉ በርካታ ጥራዞችን ፅፏል፡፡ እንደዚሁም በሁነይን ኢብኑ ኢስሃቅ መፅሃፍ ላይም ማብራሪያ ፅፏል፡፡ ሌላው ታዋቂውና የሱ ወጥ ጥንቅር አስተዋፅኦ የሆነው መፅሃፍ ምግብ በጤና ላይ ስለሚያሣድረው ተፅእኖ የሚዳስሰው ኪታብ አልሙኽታር ፊ አል አግዚያ የሚባለው ነው፡፡
የኢብኑ አን-ነፊስ ሥራዎች በያኔውን ዘመን የነበረውን እውቀት በእጅጉ ከመዋሃዳቸውም በላይ አበልፅገውታልም፡፡ ከዚህም ባለፈ መልኩ በምሥራቁም ሆነ በምእራቡ ዓለም በነበረው በያኔው የህክምና ሣይንስ ላይ ከፍተኛ ለውጥ አምጥተዋል፡፡ ሆኖም ከመፅሃፎቹ መካከል አንደኛው ብቻ ነው ወደ ላቲን የተተረጎመው፡፡ በመሆኑም ከፊል ሥራዎቹ ለአውሮፓ ሣይታወቁ ለረጅም ዘመናት ኖረዋል፡
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
1 977
ሱቢህ መስጂደል አቅሳ ሲሰግዱ የነበሩት ላይ መስጂድ ድረስ በመግባት
ጥቃት የፈፀሙትን ወሰኽ የእስራኤል ወታደሮች ጀግኖቹ ፍልስጤማዊያን
በወታደሮቹ ጥይት እየተተኮሰ እንኳን ባሉበት ባላቸው ውጊያውን ሳይሸሹ
ተጋፍጠዋል # የጀግንነት_ተምሳሌቶች ፍልስጤማዊያን
#share #ሼር
#Join
Https://t.me/smithhk
