Nathan casting agency
رفتن به کانال در Telegram
The best place to get the best casting jobs Our services -casting models - for music clips - movies - series dramas - fashion shows - television shows Contact: 0920358051
نمایش بیشترأثيوبيا16 170دسته بندی مشخص نشده است
408
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 26
✍በሂክማ ጀማል
፡
፡
... ትምህርት ቤት ስንደርስ ከነ ሪቾ ጋር ተገናኘን ግን አልተነጋገርንም በዝምታ አለፋኝ ለሙአዝ ስለ እነ ሪቾ ነገርኩት ስለፈተናው የሆነውን ነገርኩት"ግን ለምን ተዘጋጋቹ ለምን አትነጋገሩም "አለኝ ምን ብዬ እነግረዋለሁ ጥያቄውን ስስማ በጣም ደነገጥኩ በአንተ ምክንያት ነው ከአንተ ጋር ስለሆንኩ ነው አልለው ነገር ግን እንደምንም
ፈገግ እያልኩ ከ ሂዊ ጋር ስለሆንኩ ነው መሰለኝ እኔጃ እኔም አላውቅም አልኩት ሙአዝ ፈገግ ብሎ ለኸይር ነው (ለበጎ) ነው አለኝ ወደየ ክፍላችን ሄድን የው እንደተለመደው እረፍት ሰአት ላየሸ ሳሉሉ ጋር ከሙአዝ ጋር ሄድን የተወሰነ አውርተን ምሳ ሰአት ላይ ሳሉ ቀድማን ወደ መስገጃው ቦታ እንደምትሄድና እዛው እንድንገናኝ ነግራን ተለያየን ምሳ ሰአት ላይ ሳሉን እንዳለችው መስገጃው ቦታ ላይ አገኘኃት ከሰገድን በኃላ ከወንዶቹ በኩል ለመናገር ጉሮሮውን የሚጠራርግ ሰው ሰማሁ እና ሁላችንም ተኩረታችንን ወደ እሱ አደረግን "አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ " አለ ሁሉም በህብረት መለሰለት ንግግሩን ቀጠለ " ዛሬ የመጣሁት የተጎዱ የተቸገሩትን የመርዳት እቅድ እንዳላቹ እህቴ ነግራኝ ነው እና እኔም አብሪያቹ ለመስራት ነው በማንኛውም ነገር የምችለውን ያህል ለመርዳት ነው እና ፈቃደኝነታችሁን ለመጠየቅ ያህል ነው ሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካትሁ "ብሎ ንግግሩን አበቃ ይሄ ለሳብ እኔን ከምንም በላይ አስደስቶኛል ምክንያቱም አንደኛ ነገር ንግግሬ ተቀባይነት ማግኘቱ ሁለተኛ ነገር ደግሞ የሚረዳን ሰው መገኘቱ ከአሁን በኃላ በጣም ጥሩ እንደሚሆንልን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ እና ሳሉ ደግሞ በየ አንድ ወሩ የተቸገሩትን ሰዎች የምንጠይቅበትን ሁኔታ አመቻችታለች እና አብሮን መምጣት የሚፈልግ ሰው ካለ እንዲያሳውቃት ተናግራ የዛሬን በዚህ አበቃን ፡፡
.
.... በዚህ ሁኔታ 1 ወር ሆነን እና የመጀመሪያውን ዙር ጥየቃ ቅዳሜ ቀን ለማድረግ ተስማማን እና አብዛኛው የጀምአው አባላት ተስማምተዋል አንድ ቦታ ብቻ እንዳይሆን ሳሉ ከፋፈለችን እኔ ከነ ሳሉ ጋር አልሄድኩም ከሌላኛው ቡድን ጋር ነበር የሄድኩት የኛ የጠየቅናቸው አንድ ብቸኛ የሆኑ ጠያቂ ያጡ የአልጋ ቁራኛ የሆኑ ባሌቴት ናቸው ስማቸውን አልነገሩንም በመጀመሪያ ወደ እቤታቸው ለመግባት ለማስፈቀድ ያህል በሩን ስናንኳኳ በሰለለ ድምፅ ማ.. ን.... ነ....ው አሉን መግባት ይፈቀዳል ? ብለን ጠየቅናቸው ይ...ግ..ቡ አሉን ወደ ውስጥ ገባን ቤቱ ከተፀዳ አመት የሆነው ይመስላል በየቦታው የወዳደቁ ያልታጠቡ መመገቢያ እቃዎች በየ ቦታው ተዝረክርከው ወድቀዋል ቤቱ አየር ከገኘ ስለቆየ ነው መሰል የሆነ የሚያስጠላ ሽታ አምጥቶዋል ሽታውን ምንም እንዳልመሰለን እያስመሰልን ፈገግ ብለን ወደ አልጋቸው ተጠጋን ቤቱ አንድ ክፍል ነው አልጋውም እዛው ነው ትንሽ ስለ ሁኔታቸው ከጠየቅናቸው በኃላ የመጣንበትን አላማ ነገርናቸው ኩምሽሽ ባለው ፊታቸው ላይ የደስታ ጭላንጭል አሳዩን የነገርናቸውን አላመኑንም ነበር እኛ እነሱ ለመርዳት ብቻ ብለን እንደመጣን ነገርናቸው በጣም ደስ አላቸው ብዙም ሰአት ሳንጅ አምስታችንም ስራyy ተመዳድበን መስራት ጀመርን ሌላ እኔ እና ሰአዳ ቤቱን ነበር የምናፀዳው እና በቅድሚያ ገላቸውን እንድናጥባቸው ጠየቅናቸው በአንዴ ፈቃደኛ አልሆኑልንም አግባብተናቸው አለሳልሰን ጠይቀናቸው በመጨረሻ ተስማሙልነሸ እና አጠብናቸው ንፁህ ልብስ ይዘን የመጣነው ልብስ ነበር እሱን ለብሰው ፀሀይ ላይ ተቀመጡ ጠዋትም ስለነበር ፀሀዩ ብዙም አይጎዳም ነበር እና እነሱን ውጪ ተቀምጠው ቤቱን በሚገባ አፅድተን ጨረስን ሁለቱ አብረውን የመጡት ልብስ እያጠቡ ነበር እኛ ስነጨርስ አነሱን አገዝናቸው ብዙም ሳይቆይ ስራውን ጨራረስን የተወሰነ ብርም ይዘን መተናል ብሩን የሰጠን መርዳት የሚፈልገው ልጅ እንደሆነ ሰምቻለሁ ልብሶቹን እንዲደርቁ አድርገን አሰጣናቸው አንዷ ብቻ ነች ብቻዋን የሰራችው እሷም ምግብ እያበሰለች ነበር 7፡30 ሲሆን ስራችንን ጨርሰን ሁላችንም በህብረት ሰገድን ምሳ አብረናቸው በላን ከምሳ በኃላ ቤቱን አጫጭሰን ብና አፍልተን ስናጫውታቸው አስከ አስር ሰአት ቆየን ሰግደን ልንሄድ እንደሆነ ነገርናቸው የመረቁንን ምርቃት መፃፍ በጣም ይከብዳል በግጥም መልክ አድርገው አዘነቡልን እኛም እጃችንን ዘርግተን አሚን... አሚን አልን ምቃታቸውን ከጨረሱ በኃላ ሁላችንንም ሳሙን ለመውጣት ወደ በሩ ስንሄድ ሴትየዋ አለቀሱ እንባቸውን ሳይ ሆዴ ተላወሰ በድጋሚ ወደ ወደ አልጋቸው ሄጄ እማማ ለምን ያለቅሳሉ እየመጣን እንጠይቆታለን እባኮን አያልቅሱ እማማ አልኳቸው " ልጄ ወድጄ መሰለሽ የማለቅሰው " ይገባኛል እማማ በቅርቡ እንመጣለን አብሽሩ አታልቅሱ
"ብቸኝነት የሚባል ነገር አይገጠማቹ ሂዱ እሺ አላህ ይከተላቹ " አሉን አሚን ብለን ወጣን፡፡
፡
፡
ይቀጥላል
>>>>>
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 25
✍ በሂክማ ጀማል
፡
፡
.... ወደ እነ ሳሉ ቤት ሄድን እቤት ውጤቷን ሲሰሙ በጣም ነው የተደሰቱት የእኔን ያህል ባይሆንም የእኔን ያህል ማንም አልተደሰተም ሳሉም ብትሆን ፡፡ ከሳሉ ወንድም ጋር በትንሹ ተግባብተናል ከእቶቿም ጋርም በትንሹም ቢሆን ተግባብተናል ቀኑን ፈታ ብለን አሳለፍነው ደስ የሚል ቀን ነበር ስርአታቸው መከባበራቸው ጨዋታቸው ሁሉም ነገራቸው በጣም ደስ ይላል፡፡ሁሌም አብሪያቸው መሆንን ተመኘሁኝ በአእምሮዬ የምስለው አይነት ቤተሰብ ነው አብሪያቸው ስላለሁ በጣም ደስ ብሎኛል ግን ምን ያደርጋል ዘላቂ አይደለም የግድ ወደ እዛ ወደ ቀዘቀዘው ቤት መመለስ አለብኝ ወደ አስራ አንድ ሰአት አካባቢ እኔ ወደ ቤት ተመለስኩ፡፡ ያው እንደተለመደው የአጎቴ ሚስት በንግግሯ አቀባበል አድርጋልኝ ገባሁ እቤት ስገባ አጎቴ አልነበረም ብዙም ሳይቆይ መጣ "ሙናዬ" አለኝ አጎቴ የሰሞኑ ሁኔታ አላማረኝም ሙኒ ነበር ዛሬ ደግሞ ሙናዬ ይሁን እኔም በምላሹ ወዬ አጎቴ ብዬው ከጓዳ ወጣሁ የአጎቴ ሚስት እና አጎቴ አብረው ሳሎን ቤት ነበሩ "እሰይ ዛሬ ደግሞ ንግግራቹ ሁሉ በ "ዬ" ሆነ እንዴ " አለች የአጎቴ መሳቅ አልፈለኩም ነበር ግን ንግግሯ ሳቄን አመጣው መቆጣጠር አልቻልኩም ነበር ሳቄን ለቀኩት ከ እኔ ተከትሎ አጎቴም ሳቀ የአጎቴ ሚስት በሁኔታዬ በጣም ተናዳብኛለች የምር እኔ ግን እሷን ለማናደድ ፈልጌ አልነበረም የሳኩት ንግግሯ ስላሳቀኝ እንጂ ከተቀመጠችበት ተነስታ እኛን እዛው ትታን ወደ ውጪ ወጣች፡፡ አጎቴ ደገመው ሙናዬ ነይ ወደዚህ ብሎ የተቀመጠበት ቦታ ላይ በእጁ መታ መታ እያደረገ ምልክት ሰጠኝ እኔም እሺ ብዬ ከአጎቴ አጠገብ ተቀመጥኩ እጄን በእጁ ይዞ ወደ እራሱ አስጠጋኝ እጁን በፀጉሬ በኩል አሳልፎ ከደረቱ አቀፈኝ ምን ተገኘ ዛሬ ግራ ገብቶኝ እንደሚያደርገኝ እየሆንኩለት ነው
....ሙኒ ..... አለኝ አጎቴ
....ወዬ አጎቴ
..... እስከዛሬ በጣም እንደተከፋሽብኝ አውቃለሀ ሲል ኸረ አጎቴ በጭራሽ አልኩት ያው እኛ ሀበሾች ስንባል የቱንም ያህል ብንበደል የበደለን ሰው ፊት እንዳልተበደልን ማስመሰል የተለመደ ነው
.... ሙኒ አታቋርጪኝ
...... እሺ አጎቴ
....እና ሙኒ ሁሉንም ነገር ዛሬ እነግርሻለሁ አባትሽ ከመሞቱ በፊት ሆስፒታል ውስጥ ሆኖ እንደ ልጄ እንዳሳድግሽ ቃል አስገብቶኝ ነበር እና እስከ ዛሬእንደ ልጅ አላሳደኩሽም ምንም አይነት ፍቅር አሳይቼሽ አላውቅም አንቺን ለመንከባከብ ፈንታ ስበድልሽ ኖሪያለሁ እና ሙኒ ከዛሬ ጀምሮ እንደ አጎት ሳይሆን እንደ አባትሽ ሆኜ ለሳድግሽ እፈልጋለሁ ለ እሰከ አሁኑም በጣም ይቅርታ ሙኒ አፋ በይኝ አለኝ ይሄን ሲያወራ ከደረቱ እንዳቀፈኝ ጆሮዬን ሰጥቼ እያዳመጥኩት ነበር ግን ድንገት እንባዬ መንታ መንታ ዱብ ዱብ ማለት ጀመረ ስደሰትም ማለቀስ ሲከፋኝም ማልቀስ ነው የሚቀናኝ ይሄ ግን አላውቅም ደስ ብሎኝ ይሁን ከፍቶኝ የማለቅሰው አላውቅም መልኩን እንኳ በቅጡ የማለውቀው አባቴ ናፍቆኝ ይሁን አጎቴ እንዲህ ስላለኝ ተደስቼ ይሁን አላውቅም አጎቴ ከእቅፋ አውጥቶኝ እንባዬን እያበሰልኝ ይቺ በእኔ ምክንያት ለመጨረሻ ጊዜ የምታወርጃት የእንባ ዘለላ ነች ብሎ ግንባሬን ሳመኝ ፡፡ እንዳይከፋው ብዬ ፈገግ እያልኩኝ ከአጠገቡ ተነሳሁ ፡፡ ዛሬ አጎቴ እንዴት እንዲህ እንዳለኝ እያሰብኩ ወደ ውስጥ ገባን እኛ ሰዎች ሁሌም ቢሆን ከሰዎች ጉድለትን ፈላጊዎች ነን መጥፎ ሲሆኑብን መጥፎነታቸውን እንደምናወራው ሁሉ ጥሩ ሲሆኑልን መልካምነታቸውን ከመናገር ይልቅ ለምን ለእኛ መልካም ሊሆኑ እንደቻሉ በማሰብ ያን ጥሩነታቸውን ለመጥፎ ስራቸው ከለላ ለማድረግ የሚጠቀሙበት ወይም ሌላ ስም ነው የምንሰጠው እኔም ከዚሁ አሎጣሁም አጎቴ ከምን ተነስቶ በአንዴ ጥሩ ሊሆንልኝ ይችላል ብቻ እንጃ ከኃላው ከመጀመሪያው በላይ የሆነ መጥፎ ነገር እንዳያመጣ ፈርቻለሁ ፡፡ መደሰት ይሁን መከፋት እንዳለብኝ አላወኩም .....
..... ዛሬ በጠዋት ነው የነቃሁት በጠዋቱም ምን እንደሆነ ባላውቅም ፍንድቅድቅ ብያለሁ ሁሉም ነገር ቀሎኛል፡፡ ሌላ ጊዜ ትምህርት ቤት ከምሄድበት ሰአት ቀድሜ ነው የወጣሁት ከሙአዝ ጋር የምንጠባበቅበት ቦታ ላይ ሙአዝን ቀድሜው ደረሰኩ እሱ አንደሚጠብቀኝ እኔም ቆሜ መጠበቅ ጀመርኩ ትንሽ እንደቆምኩ አቁነጠነጠኝ ባለሁበት እንቀሳቀስ ጀመረ ረጅም ሰአት የቆምኩ መሰለኝ ግን አልመጣም ምን ሆኖ ነው ቆየ እኮ የአላፊ አግዳሚው አይን እየገረፈኝ አንዳንድ ስራ ፈት ደግሞ "ቆየብሽ፣ ምነው በጠዋቱ ቀጠርሽው፣ አንቺን የመሰለች ቆንጆ እንዴት ያስጠብቃል፣ እሱ ከቆየ ለምን አብረን አንሄድም ....." እያሉ አሳቀቁኝ ቆይ ፍቅረኛ ብቻ ነው መጠበቅ የሚቻለው ሴት ጓደኛዬስ ብትሆን የምጠብቀው በማያገባቸው ነገር እየገቡ ምን አስለፈለፋቸው ብሽቆች ተስፋ ቆርጬ ለመሄድ ሳስብ ሙአዝን ከሩቁ ተመለከትኩት ኮስተር ብዬ አጠገቤ እስኪመጣ ጠበኩት አጠገቤ ሲደርስ ትቼው ሄድኩ ምነው ሙኒ ዘጋሽኝ እኮ
.... ለምን ቆየህ ስንት ሰአት እንደቆምኩ እኮ
..... በሌላ ቀን ሰአቴ ነው የወጣሁት ደግሞ በጊዜ እንደምትወጪ አልነገርሽኝ እሺ ካጠፋሁ ይቅርታ ሙኒ አታኩርፊኝ
..... ጥፋተኛዋ እኔ እንደሆንኩ አሁን ነው የገባኝ ይሄን ሁሉ ጊዜ እሱ ሰመጠብቀኝ አንድም ቀን ተኮሳትሮብኝ አያውቅም ሁሌም በፈገግታ ነው የሚቀበለኝ እኔ ግን እርሜን አንድ ቀን ብጠብቀው እንዴት እንዴት እንዳደረገኝ በራሴ አፈርኩ ሀሳቡን ለማስቀየር ያህል ከት ብዬ ሳኩኝ
.... ምነው ሙኒ ምን የሚያስቅ ነገር አደረኩኝ
..... የምር ያኮረፍኩኝ መስሎህ ነበር እንዴ ብዬ ሳቄን ቀጠልኩኝ
.... እያሾፍሽብኝ ነው አይደል ሙኒ
.... ሳይሆን እንዴት እንደምትሆን ልይህ ብዬ ነው
.... ፈገግ እያለ አንቺ አዛ ድጋሚ እንዲህ እንዳታደርጊ እሺ ብሎኝ እሱም ሳቀ ጥሩነቱ እንዳሰብኩት ሀሳቡን አስቀይሬዋለሁ ብልሀት ማለት ይሄ አይደል እራሴን እንዲህ እያልኩ ልፎግር እንጂ......
፡
፡
ይቀጥላል
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 24
✍ ሂክማ ጀማል
፡
፡
.... እንደማይደርስ የለምና እሁድ ደረሰ እኔ እንኳን ለማንም መናገር አልፈለኩም ነበር ምክንያቱም ሁሌም ቢሆን ውጤት አሪፍ ስላልሆነ አጎቴ ይናገራኛል አሁንም ተመሳሳይ ነገር ነው የሚያጋጥመኝ ግን ግድ ሰርቴፍኬት ለመቀበል ወላጅ ያስፈልጋል ለአጎቴ ነገሬዋለሁ ሁላችንም ትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ነን ፕሮግራሙ እኪጀመር በጣም ጓጓጉቻለሁ ብዙም ሳንቆይ ወደ አዳራሹ እንድንገባ ተነገረን ወደ አዳራሹ ገባን ለሳሉ የመጣው የሳሊሀ ወንድም ነው የመጣው እኔ እና ሳሉ ከሳሉ ወንድም ጋር ተቀመጥን አጎቴ ከፊት ለፊታች ተቀመጠ የትምህርት ቤቱ እርእሰ መምህር የመክፈቻ ንግግር አደረገ እና አንዳንድ ነገሮችን አውርተው ከቆዩ በኃላ ወደ መጨረሻው ፕሮግራም ደረሱ ያው የመጨረሻው ፕሮግራም የውጤት አሰጣጥ ፕሮግራም ነው በየክፍሉ እየተጠራ ሶስተኛ የወጡትን መጀመሪያ ከዚያም ሁለት በመጨረሻ አንደኛ ለወጡ ተማሪዎች እየተሰጠ እነ ሳሉ ቤት ክፍል ተደረሰ ሶስተኛ የኸጣችው ሴት ነበረች እሷ መድረክ ላይ ወጥታ የተዘጋጀላትን ሽልማት ተቀበለች ሁለተኛም የወጣችው አንደዛው አንደኛ የወጣውን ለማወቅ አፌን ከፍቼ ስጠባበቅ ምንም ሳይናገሩ ወደ ቀጣዩ ክፍል አለፈ ለምነሸ አለፈ ሳሉ አንደኛ እንደምትወጣ በጣም እርግጠኛ ነኝ ታዲያ ለምን አለፏት የፕሮግራም መጨረሻ ላይ ደረሱ ማይኩን እርእሰ መምህሩ ተቀብለው ጎሮሮቸውን ጠራርገው መናገር ጀመሩ" ያኮራችን ተማሪ አለች ከዘጠነኛ ክፍል የእሳን ውጤት ያህል ማንም አላመጣም " ብለው ተማሪ "ሳሊሀ ኡስማን " ብለው ሳይጨርሱ ከተቀነጥኩበት ወንበር ብድግ ብዬ ተነሳሁ ለምን ውጤቱ የኔ ነው እንዴ የደስታ ብዛት እንባዬ መንታ መንታ ይወርድ ጀመር ሳሉ ወደ መድረኩ ሄዳ የተዘጋጀላትን ሽልማት ተቀበለች ሰው ግን እንዴት በሰው ውጤት እንዲህ ይደሰታል እሷ እራሱ እንደ እኔ ደስተኛ አትመስለኝም ሳሉ ከመድረኩ ወርዳ አጠገቤ ስትመጣ እንደ ፋርማሲ እባብ ተጠመጠምኩባት ለረጅም ሰአት አቀፍኳት ወንድሟሙ አድናቆቱን ነገሯት ከ አዳራሹ ወጣን እኔ የእኛ ክፍልእርእሰ መምህር ወደ አለበት ቦታ ሄጄው ጤቴን ተቀበልኩ ውጤቱ አሪፍ አይሁን እንጂ ለእኔ ግን በጣም ትልቅ ነው ከምንም ተነስቶ ከመካከለኛ ተማሪዎች እኩል መሆን ኢንሸአላህ በቀጣዩ አሪፍ ከሚባሉ ተማሪዎች ተርታ እሰለፋለሁ አጎቴን ውጤቴን ተቀበለኝ እንደጠበኩት አልተናገረኝም ፈገግ አለልኝ የሚገርም ለውጥ ነው ሙኒ በርቺ አለኝ የምር አጎቴ ነው እንደዚህ ያለኝ ሲገርም .....
....እቤት እየጠበቁኝ ነው አብረን እንሂድ አይ ሳሉ ዛሬ ይቅርብኝ ሌላ ቀን እሄዳለሁ መሄድ ፈልጊያለሁ ግን አጎቴ አብሮኝ ስላለ ፈርቼ ነው ስትለምነኝ አይቶ ሙኒ እሺ በያት ግን እንዳትቆይ አለኝ ኸረ አጎቴ ዛሬ ምን ተገኘ ለሰላመህ ያድርገው እያልኩ በሆዴ ፈገግ እያልኩለት እሺ አጎቴ ብዬ እነ ሳሊሀን ተቀላቀልኳቸው እና አብረን ሄድን.....
፡
፡
ይቀጥላል
@Readgeneration
#የጥብሱ_ሽታ_ያስከፍላል
........
አንድ ቀትር ረሃብ የጎዳው ጎልማሳ አንዲት ደረቅ ዳቦ በእጁ ይዞ የሚበላበትን ነገር ለመለመን በመንገድ ዳር ወደሚገኝ ምግብ ቤት ተጠግቶ ይቆማል።ብዙም ሳይቆይ ከምግብ ቤቱ የሚወጣው የተጠበሰ ስጋ ሽታ አፉን በምራቅ ይሞላውና ዳቦውን በምግቡ ሽታ እያጣጣመ መብላት ጀመረ። በዚህ መሐል ግን የምግብ ቤቱ ባለቤት ነገሩን ይረዳና ሲሮጥ ወጥቶ የደሀውን አንገት አንቆ ያሸተተበትን እንዲከፍል ይወዘውዘው ጀመር። ደሀውም ምንም ገንዘብ በኪሱ እንደሌለ ይነግረውና እንዲለቀው ካልሆነም ወደዳኛ እንዲሄዱ ይጠይቀዋል። የምግብ ቤቱም ባለቤት ወደዳኛ ይዞት ይቀርባል። ዳኛው ነገሩን በሚገባ ካዳመጠ በላ <<ደሀው ያሸተተበትን ይከፍል ዘንድ ተገቢ ነው>> በማለት ፍርዱን ይሰጥና የምግብ ቤቱ ባለቤት ወደእሱ እንዲጠጋ ያዘዋል። የምግብ ቤቱ ባለቤትም እንደታዘዘው ወደዳኛው ሲጠጋ ፈጠን ብሎ ከኪሱ ሣንቲም ያወጣና በጆሮው ላይ አቃጭሎ ድምፁን አሰምቶ ወደኪሱ ከተተው:<<እነሆ ለደሀው እኔ ከፍየለታለሁ ወደ ቤታችሁ ሂዱ!>>አለ።
ግራ የተጋባው የምግብ ቤቱ ባለቤት: <<ዳኛ ሆይ የሳንቲምህን ድምፁን አሰማኸኝ እንጂ መች ሰጠኸኝ>>አለው። ዳኛውም መልሶ <<ድሀውም ምግብን አሸተተ እንጂ አልበላም እኮ!>>ሲል መለሰለት።
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 23
✍በሂክማ ጀማል
፡
፡
.......ሙአዝን እንደሌላ ግዜው ነው ያገኘሁት ምንም የተቀየረ ነገር የለም ከአሁን አሁን ጠየቀኝ ብዬ ስጠብቅ ምንም ሳይናገረኝ ተመለስን በነገራችን ላይ ውጤታችን በጣም አሪፍ ነበር ግን ትንሽ የኔ ከነ ሙአዝ ውጤት ያንሳል ከሳሊሀ ውጤት ደግሞ የሙአዝ ያንሳል ብቻ አልሀምዱሊላህ አሪፍ ውጤት ነው ከዚህ በኃላ የምንገናኘው ከ አስራ አምስት ቀን በኃላ ነው ሳሉን ቁርአን ቤት አገኛታለሁ ሙአዝን ግን አላገኘውም በጣም ይናፍቀኛል፡፡ ግን ለምን አልጠየቀኝም አላየውም ይሆናል ወይስ እኔን እንዳይከፋኝ ብሎ አስቦ ነው ውስጤን በጣም እየከነከነኝ ነው ለማንኛውም ከአስራ አምስት ቀን በኃላ ስለማገኘው ምን አልባት እስከዛ ይረሳው ይሆናል ቢረሳልኝ ምኞቴ ነው .......
አስከዛሬ ምን አዲስ ነገር አልገጠመኝም ቤት ስለምውል ነው መሰለኝ የተለመደ ነገር ነው ጠዋት ተነስቶ መስገድ ቁርስ በለቼ የቤት ስራ መስራት እስከ ስድስት ሰአት ስራዬን እጨርሳለሁ ምሳ ከተበላ በኃላ አንዳንዴ ቡና አፈላለሁ ካልሆነ ቁርአን የተወሰነ አጠናለሁ አስር ሰአት ሲደርስ የአስርን ሰላት ሰግጄ ቁርአን ቤት እሄዳለሁ በቃ እንዲህ እያደረኩ ይመሻል አስራ አምስት ቀን ሙሉ እንዲህ ነው ያሳለፍኩት ዛሬ ክላስ ገብተናል ሙአዝ በጣም ናፍቆኝ ነበር ዘልዬ ብጠመጠምበት ምኞቴ ነበር ግን አልችልም ገና ዛሬ ሙአዝ የእናቴ ልጅ ስላልሆነ ቅር አለኝ የአንድ እናት ልጅ ብንሆን እንደፈለኩኝ አቅፈው ነበር ብቻ ይሁን ሳሉን ትምህርት ቤት አገኘናት ሰላም ተባብለን አንዳንድ ነገሮችን አውረትን ተለያየን ፡፡
... ሂዊ ዛሬ አልመጣችም ለነገሩ ብዙም ተማሪ አልገባም ዛሬ ስለሆነ ሰለተጀመረ ነው መሰለኝ ፡፡ እረስቼው የሙአዝ ጓደኛ ዳዊት ትምህርት ካቆመ በጣም ቆይቷል ለሙአዝ ጠይቄው ሱስ ውስጥ እንደገባ ነገረኝ እና ያው ሙድ ነው ምናምን ብለው እንደ ሚያደርጉት ማለት ነው የምር በጣም ያስጠላል ለነገሩ ውስጡ ለገባ ሰው የቱንም ያህል ጎጂ ቢሆንም ሊታየው አይችልም በሰአቱ የሚያገኘውን ደስታ ብቻ ነው ማየት የሚችለው ጥቅሙንና ጉዳቱን ማመዛዘን አይቻልም ከውጪ ሆኖ ሲመለከቱት ብቻ ነው ምን ያህል ጎጂ እንደሆነ የሚገባን ብቻ ያሳዝናል ፡፡
ውጤት አርብ እንደሚነገርና ወላጆች የሚሰበሰብት ደግሞ እሁድ እንደሆነ ዛሬ ተነገረን ውጤት ለመቀበል ብዙም ፍላጎት የለኝም ምክንያቱም ከፋይናል ውጪ ምንመ የሰራሁት ነገር የለም ወርሀዊ ፈተናዎችን አልሰራሁም በዛ ላይ ያልተፈተንኳቸውም ፈተናዎች ስላሉ ውጤቱ አሪፍ እንደማይሆን አውቃለሁ ባልቀበል ደስ ይለኛል ግን የግድ መቀበል ስላለብኝ እቀበላለሁ ፡፡
ጁምአ ቀን እንደተባለውም ውጤት ተነገረ ጥሩነቱ ከአንድ እሰከ አስር ለወጡ ተማሪዎች ብቻ ነው የተነገረው እኔ እሁድ ነኝ ማለት ነው ማወቄ ባይቀርም ቀኑ መርዘሙ ግን አስደስቶኛል ፡፡ ውጤት ከተነገረን በኃላ የሳሉን ውጤት ለማወቅ ስለጓጓሁ ወደ እነሱ ክፍል ሄድኩ የነሳሊሀ ክፍል ተማሪዎች ውጪ ላይ ተቀምጠዋል ወደ ውስጥ ስገባ ሳሊሀ ከክፍል ጓደኞቿ ጋር አገኘኃት ወደ እሷ እየተጠጋሁ
....እእ ሳሉ ውጤት
..... አንደኛ ወጣች
አለኝ ጓደኞቿ
....ኸረ ውሸታም እውነታቹን ነው ወይኔ ሳሉ እኔ አለምንም በጣም ደስ ብሎኝ ሳሉን አየተፍለቀለኩ አቀፍኳት
ሁሉም ሳቁ ምን ነው አልኳቸው እየሳቁ ነው ማንም አልመለሰልኝ እስኪጨርሱ ጠበኳቸው ሳሊሀ "ሙኒዬ አውቀው ነው እሺ እኛ ውጤት አልተነገረንም የክፍል ሀላፊያችን አልመጣም "
አለችኝ እንደ መናደድ እያደረገኝ እሺ አልኳት አስተማረወሸ ስላልመጣ እሁድ ነው ውጤቷን የምታውቀው የሙአዝን እንወቅ ብለን እነ ሙአዝ ክፍል ሄድን መአዝ አሪፍ ውጤት ነው ከክፍሉ ሶስተኛ ነው የወጣው በውጤቱ ደስ ብሎኛል አሁን የሳሉን ለማወቅ በጣም ጓጓሁ ምክንያቱም የሙአዝ እንዲህ ከሆነ የእሷን ደግሞ አሰብኩት መቼ ነው እሁድ ......
፡
፡
ይቀጥላል
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 22
✍በሂክማ ጀማል
፡
፡
.... ዝግጅቱ የተዘጋጀው መጀመሪያ ሴሜስተር መጠናቀቁን አስመልክቶ ነበር፡፡ በየሳምንቱ ጀምአ ቀን ሙሉ ከጀምአው የሚሰበሰብ ብር አለ ፡፡እኔ ግን ገና ዛሬ ነው ያወኩት ምን ያህል እንደተሰበሰበ ሲቆጥሩ ነው ያወኩት ፡፡ግዳጅ ስለሌለው ሁሉም የቻለውን ያህል መስጠት ይችላል ሁሉም ያለውን ሳይሳቀቅ ይሰጣል ከእኔ ውጪ ማለቴ ነው፡፡ ጥፋተኛ ነኝ ብዬ አላስብም ምክንያቱም ምንም የማውቀው ነገር የለም ማንም አልነገረኝ ፡፡ኸረ ዛሬ ሌላም አዲስ ነገር አጋጥሞኛል የማለውቃቸው ነገሮች እየበዙ ነው መሰለኝ ሳሊሀ የሴቶች ጀምአ አሚር (መሪ) መሆኗን ሙአዝም የወንዶች ጀምአ አሚር መሆናቸውን ተነገረኝ ፡፡ ይገርማል እኔ ምንም የማለውቀዋ ልጅ ከ እነሱ እኩል ሳወራ አላፍርም ደግሞ እኮ ሳሉን ታናሼ ብዬም ጠርቻታለሁ ወይ አለማወቅ የተሰበሰበው ብር ለሚስኩኖች ለደካሞች ይከፉፈላል እና አንድ አንድ ብር ሳይሆን የሚሰጠው ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን መቋቋሚዪ ይሆናል ተብሎ የሚታሰብ ያህል ነው የሚሰጠው ፡፡የሚረዱት ጎዳናላይ ወጥተው የሚለምኑትን ሳይሆን የሰው ፊትን ፈርተው በወደቀ ቤት ውስጥ ያለ ማንም አለሁ ባይ አስታዋሽ የሚኖሩ የተረሱ ሰዎችን ነው የሚረዱት በእዚህኛው ቢያንስ ለአራት ሰው ለመስጠት የሚያስችል ብር አሰባስበዋል ይሄ በተማሪ አቅም በቂ ነው ለሚቀጥለው እኔም እገባበታለሁ ፡፡ሀሳቡ በጣም ተመችቶኛል ትንሽም ነገር ብትሆን ለሰዎች መስጠት የራሱ የሆነ ደስታ አለው በተለይ ደግሞ የተሰጠው ሰው ፈገግ ብሎ መመልከት በጣም ያስደስታል በእርግጥ እኔ ገንዘብ የለኝም ግን ደግሞ ለመርዳት የግድ ገንዘብ መኖር አለበት ብዬ አላምንም፡፡ ለነ ሙአዝ አንድ ሀሳብ አቅርቤላቸው ተስማምተዋል ያቀበረብኩት ሀሳብ
" አሁን እናንተ ገንዘብ ሰብስባቹ ነው የምትሰጡት ይሄ በጣም ጥሩ ነው ግን ገንዘቡን ሰብስባቹ ለመስጠት ብቻ ነው ሰዎቹ ቤት የምትሄዱት እንደዚህ ከሚሆን በሳምንት ወይም በአስራ አምስተ ቀን ለምን እየሄድን አንጠይቃቸው የሚንከባከብ ሰው የሌላቸው ሰዎችን የቻልነውን ያህል ቤታቸውን ማፅዳት ሊሆን ይችላል ልብሳቸውን ማጠብ ፣የራሳቸውንም ንፅህና ብንጠብቅላቸው ወይም ሌሎች ነገሮችንም ብናደርግላቸው ምን አልባት ከምንሰጣቸው ገንዘብ በላይ ይሄ ለእነሱ በጣም አስፈላጊ ሊሆን ይችላል ብዬ አስባለሁ፡፡"
... በዚህ ሀሳብ ሁለቱም ተስማምተው ለሁሉም ተማሪዎችም እኔ ያልኳቸውን ነገሯቸው ፡፡ ይህን ለማድረግ ፈቃደኛ የሆነ ሰው እንዲያሳውቃቸው ተናገሩ፡፡ይህን የነገርኳቸው ከፕሮግራሙ በፊት ብር ሲቆጥሩ ነበር ሀሳቤን ስለተቀበሉኝ ደስ ብሎኛል ፡፡
.... ዛሬ የሰራሁት ስራ ስህተት መሆኑ የገባኝ ከቆየ በኃላ ነው ሙአዝ ዋሌቱን ከኪሱ አውጥቶ እንድይዘው ሰጠኝ ሲሰጠኝ ዋሌቱ ክፍት ነበር "ሙአዝ" ብዬ ጠራሁት
.....ወዬ ሙኒ
..... ዋሌትህን ማየት ይቻላል
...... አዎ ሙኒ አንድ ሁለት ፎቶ ብታገኚ ነው ሌላ ምንም የለውም ከፈለግሽ እይው
.... እሺ ብዬ ከፈትኩት እንዳለውም ፊት ለፊት ላይ ፎቶ ነበር ፡፡ሙአዝ ከሳሊሀ ጋር እየተነጋገረ የሆነ ነገር እየፃፈ ነው፡፡ ትኩረቱ ወደ እኔ እንዳልሆነ ሳውቅ ከዋሌቱ ላይ ሁለት ፎቶ ወሰድኩበት ወደ አምስት የሚጠጋ ፎቶ ነበር፡፡ ለምን ወሰድኩበት? እኔ እንጃ ሁለቱን ፎቶዎች ወስጄ ዋሌቱን አስቀመጥኩለት ሙአዝና ሳሊሀ ፅፈው ጨረሱ መአዝ ወረቀቱን እያጣጠፈ ምን አገኘሽበት ? ደነገጥኩ ምን ወሰድሽ ያለኝ መስሎኝ ኸረ ምንም አሎሰድኩም ሙአዝና ሳሊሀ ተያይተው ሳቁ ያዪኝ መስሎኝ ፎቶውን አውጥቼ ልሰጣቸው ነበር ኸረ ሙኒ ወሰድሽ ሳይሆን ምን አገኘሽ ነው ያልኩት ደግሞ ብቶስጅስ ምን ችግር አለው ግን የሚወሰድ ምንም ነገር የለውም እንጂ ብቶስጅም ችግር የለውም፡፡ ኡፍፍፍፍፍ ትንፍስ አልኩ አላዩኝም ማለት ነው ቤት ከገባሁ በኃላ አንዱን ፎቶ ዲያሪዬ ላይ ለጠፍኩት አንዱን ደግም ከእኔ ፎቶ ጋር በጣም አቀራርቤ እንስ በእርስ አነባብርኳቸው አትኩሮ ላላየው ሰው አብረን የተነሳን ነው የሚመስለው ቆራርጬ አስተካክዬ ነው የለጠፍኩት፡፡ ከለጠፍኩት በኃላ ግን ደበረኝ ለምን ሰረኩት ምን ያደርግልኛል አሁን ሙአዝ ከዋሌቱ ውስጥ ፎቶውን ሲያጣ ምን እንደሚል እንጃ ምን አይነት ሰው ነኘ ግን ሳናድ መውሰድ አልነበረብኝም ስህተት ነው አሁን አልመልስለት ነገር ልመልስ እንኳን ብል አንዱን ፎቶ ቆርጬዋለሁ ባልቆርጠው እራሱ ምን ብዬ እመልስለታለሁ ይደብራል አርብ ፈተና ጨርሰን ሰኞ የፈተና ውጤት ለመቀበል እንሄዳለን ሰኞ ሙአዝ ምን እንደሚለኝ እንጃ ......
፡
፡
ይቀጥላል
ያልተፈታ ህልም
ክፍል 21
✍በሂክማ ጀማል
፡
፡
... ወደ ቤት ከገባሁ በኃላ መስራት መስራት ያለብኝን ነገር ሰራርቼ ያለፈኩትን ቁርአን እየደጋገምኩ ማጥናት ጀመርኩ የተወሰነ ካጠናሁ በኃላ በጀርባዬ አልጋ ላይ ተኝቼ የቀን ውሎዬን ሳስብ አብዛኛውን ጊዜዬን ከ ሳሉ ጋር ነው ያሳለፍኩት ግን የሆነ የጎደለ ነገር እንዳለ እየተሰማኝ ነው ምን እንደሆነ በጭራሽ አልመጣልኝም በድጋሚ የቀን ውሎዬን አንድ በአንድ ማስታወስ ጀመርኩ ዛሬ ሙአዝን አላገኘሁትም እሱ ነው
ቅር ያለኝ ዛሬ ሙአዝ ትምህርት ቤት አልመጣም ለምን እንደሆነ ባላውቅም .... ከተኛሁበት ተነስቼ ይቺን ለሙአዝ ጫር ጫር አደረኩለት
.
ቀን ሆኖ እንዳልነጋ ፣ነበር የኔ ሂወት፣
ሰው ሲንቀሳቀስ ፣እኔ በቆምኩበት፣
በዛ በጨለማ፣ከድቅድቁ መሀል ፣
መራመድ አቅቶኝ፣ተገትሬ ቆሜ ከመንገዱ መሀል፣
ሻማ እንደያዘ ሰው፣ድንገት አንተ መጥተህ፣
መንገዴን አብረተህ፣ ጨለማዬን ገፈህ ፣
ከመሀል መንገድ ላይእንዳልቀር ባክኜ፣ አለሁልሽ ብለህ
ከጨለማው ወጣሁ ፣አንተን ተከትዬ፣
.
...እሱን ሙሉ ለሙሉ ባይገልፀውም በትንሹ የሞከርኩት ነው ሙአዝን ከ ሰኞ በስተቀር አላገኘውም እንግዲህ ልቻለው ሰአቱ እየሄደ ነው አጎቴ ከስራ መጥቶዋል እራት ከበላን በኃላ ትንሽ ቆየተን ተኛን ፡፡
.... ቅዳሜና እሁድን ቤት ውስጥ አሳለፍኩ ቅዳሜ ቀን ሳሉ እንዳለችው አንድ ደረጃ ከፍ አድርጋኛለች ደስ ይላል እሁድ ስላልነበር ቀኑ ሙሉ እቤት ነው ያሳለፍኩት ፡፡ ዛሬ ሙአዝን አግኝቼዋለሁ እንደ ሌላ ቀን የሚጠብቀኝ ቦታ ላይ ተገናኘን ለምን አርብ እንደቀረ ጠየኩት የንጋት ሰላት ከሰገድኩ በኃላ ተኝቼ እንቅልፍ ይዞኝ ሄደ እና ረፈደብኝ እኔ ደግሞ ምን ሆንክ ብዬ ነበር እሺ የኔ አሳቤ ትምህርት ቤት ስደርስ ሳሊሀ ትምህርት ቤት በራፍ ላይ ቆማ ነበር ሰላምታ ተለዋውጠን ትንሽ እንደቆምን ሁላችንም ወደየ ክፍላችን እንድንገባ ተነገረን ሂዊ ስንገባ መጣች እኔ እና ሂዊ አብረን ገባን መአዝና ሳሊሀም ወደየ ክፍላቸው ሄዱ ፈተናውን 2፡30 ጀምርን ግማሽ ያህል ከሰራን በኃላ እነ ሪች መጡ ፈታኙ አላስገባም ብሏቸው ተመለሱ በእርግጥ ሰአቱ በጣም ሄዷል ግን ቢገቡ ደስ ይለኝ ነበር ፈተናው ብዙም አልከበደኝም ነበር አብዛኛውን የተዘጋጀንበት ነው የመጣው
ተናውን ጨርሼ ስወጣ እነ ሪቾ ኮሊደሩ ላይ ቆመው አገኘኃቸው ብንጣላም ላናግራቸው ሄድኩ ሁሉም ፊታቸውን አዞሩብኝ በፈገግ እያልኩ እንድታወሩኝ አይደለም የመጣሁት እርእሰ መምህሩ ቢሮ ሄዳቹ አናግሩት እሱ ሊያስፈትናቹ ይችላል ብያቸው ደረጃውን መውረድ ጀመርኩ እነሱም ተከትለውኝ ወረዱ ወደ እርእሰ መምህሩ ቢሮ ሲሄዱ ሌሎች ያረፈዱ ተማሪዎችም ውስጥ እየተፈተኑ ነበር ሪች ቀደም ቀደም ብላ ሄዳ ወደ ቤሮው ገባች እርእሰ መምህሩ እዛው ቆይ የሚል ምልክት አሳያት እሺ ብላ መግቢያው ላይ ቆመች እሱ ወደ ውጭ ወጥቶ አወራት አይሆንም አላቸው ባለፈው ፈርማችኃል ይሄ ሁለተኛ ጥፋት ነው አትፈተኑም ብሏቸው ወደ ቢሮው ገባ የምር አሳዝነውኛል ብከፋባቸውም የመጀመሪያውን ቀን ፈተና እንዲህ አሳለፍን ሳምንቱን ሙሉ በተመሳሳይ መልኩ ተፈትነን ጨረስን ፡፡ ጁምአ ቀን ከጁምአ በኃላ በጀምአ የተዘጋጀ ዝግጅት እንዳለ እነ ሳሊሀ ነግረውኝ ወደ ዝግጅቱ ሄድን፡፡
፡
፡
ይቀጥላል
