cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

መንሀጀ ሰለፍ አላማችን ተውሂድን ማንገስሽርክን መዋጋት

አላህ ሀቅን በሀቅነቱ ያሳየን ምን ከተለው ያድርገን ባጢልን በባጢልነቱ ያሳየን ምንርቀው ያርገን አሚን አስተያየት ካለዋት ደግሞ 👇👇👇 @Menhageselafebot

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
266
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

✨የሴቶች አረፋ እና ተያያዥ ነጥቦች 🎙በሸይኽ ኢልያስ አህመድ (ሐፊዘሁላህ) @ustazilyas
نمایش همه...
የሴቶች አረፋ.mp31.17 MB
በተለያዩ የሐረም ሙአዚኖች ለግማሽ ሰዓት ያህል የተደረገ ተክቢራ! እነዚህን ቀናት በተክቢራ እናስውባቸው!
نمایش همه...
نصف_ساعة_مع_تكبيرات_العيد_من_كل_مؤذني_الحرم_المكي_من_مكبرية_المسجد.m4a24.93 MB
Repost from N/a
Photo unavailableShow in Telegram
https://t.me/nurmerkeznew አሰላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱ አስደሳች ዜና ክረምት ኮርስ ለታዳጊውች 👆👆👆👆👆👆
نمایش همه...
00:41
Video unavailableShow in Telegram
አል-ኑር ኢስላሚክ ኢንስትዮቴሽንየ(online)መድረሳ ቤትኛው ፕሮግራም መሳተፍ የፈልጋሉ 1-ከሰኞ እስከ ቅዳሜ ከምሽት 02:10-እሰከ ምሽቱ 05:00 ድረስ (በተመቾት ሰአት ገብተው ያሰማሉ ) 2-ቅዳሜና እሁድ ከቀኑ 07:00 - 09:30 በግል ለመቅራት ለመቅራት 3- ወይም እርሶ በሚመቾት ሰአት በመነጋገር *ቂኢዳ ለመቅራት እንደ አዲስም ወይም ተጅዊድ ለማስተካከል (ለጀማሪዎችትኩረት እንሰጣለን ) *ቁርአን ነዘር ለመቅራት ያለኻተመም አኽትሞም በተጅውድ ለመቅራት *ቁርአን ለመሀፈዝ *ከሰኞ እስከ ቅዳሜ በሚኖረን ፕሮግራም ተጅዊድን ጨምሮ የተለያዮ የተርቢያ የሀዲስ ኪታብ ፕሮግራም ይኖረናል 👇👇👇👇ለመመዝገብ እና ክፍያው ለማወቅ በቦቱ ላይ የለውን ጥያቄ በመሙላይ መመዝገብ ትችላላችሁ 👇👇👇 @Medrestunurbot @Medrestunurbot @Medrestunurbot @Medrestunurbot @Medrestunurbot ለበለጠ መረጃ 📲📱251938482616 https://t.me/alnurislamiclerning https://t.me/alnurislamiclerning
نمایش همه...
2.95 MB
الأحزاب 59 يَا أَيُّهَا النَّبِيُّ قُل لِّأَزْوَاجِكَ وَبَنَاتِكَ وَنِسَاءِ الْمُؤْمِنِينَ يُدْنِينَ عَلَيْهِنَّ مِن جَلَابِيبِهِنَّ ذَلِكَ أَدْنَى أَن يُعْرَفْنَ فَلَا يُؤْذَيْنَ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَّحِيمًا አንተ ነቢዩ ሆይ! ለሚስቶቸህ፣ ለሴቶች ልጆችህም፣ ለምእምናን ሚስቶችም ከመከናነቢያዎቻቸው በላያቸው ላይ እንዲለቁ ንገራቸው፡፡ ይህ እንዲታወቁና (በባለጌዎች) እንዳይደፈሩ ለመኾን በጣም የቀረበ ነው፡፡ አላህም መሓሪ አዛኝ ነው፡፡ Al Ahzab 59-63
نمایش همه...
033-Al­Ahzab 2.mp31.28 MB
Repost from N/a
ከረጀብ ወር ጋር የሚያያዙ ደካማ ሐዲሦች ~~~ ከረጀብ ጋር ብዙ መሰረተ ቢስ ቅጥፈቶችና ደካማ ሐዲሦች አሉ። ለምሳሌ ያክል፦ [1ኛ]፡- رجب شهر الله وشعبان شهري ورمضان شهر أمتي “ረጀብ የአላህ ወር ነው። ሸዕባን የኔ ወር ነው። ረመዷን ደግሞ የህዝቦቼ ወር ነው።” አልባኒ ደካማ እንደሆነ ገልፀዋል። [አዶዒፋህ፡ 4400] [2ኛ]፡- ረጀብ ሲገባ እንዲህ ይሉ ነበር፡- اللهم بارك لنا في رجب وشعبان، وبلغنا رمضان “አላህ ሆይ! ረጀብንና ሸዕባንን ባርክልን። ረመዷንን አድርሰን።” ነወዊይ በ“አዝካር”፣ ዘሀቢይ በ“ሚዛን” ደካማ እንደሆነ ብይን የሰጡ ሲሆን አልባኒም “ደካማ ነው” ብለዋል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 4395] [3ኛ]፡- فضل شهر رجب على الشهور كفضل القرآن على سائر الكلام “የረጀብ ወር በሌሎች ወራት ላይ ያለው ብልጫ ቁርኣን በሌሎች ንግግሮች ላይ እንዳለው ብልጫ ነው።” ኢብኑ ሐጀር “መሰረተ ቢስ ቅጥፈት ነው ብለዋል። [4ኛ]፡- خمس ليال لا ترد فيهن الدعوة أول ليلة من رجب، وليلة النصف من شعبان، وليلة الجمعة، وليلة الفطر، وليلة النحر “አምስት ሌሊቶች በነሱ ውስጥ የተደረገ ዱዓእ አይመለስም። የመጀመሪያው የረጀብ ሌሊት፣ የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት፣ የጁሙዐ ሌሊት፣ የዒደል ፊጥር ሌሊት እና የዒደል አድሓ ሌሊት ናቸው።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 1452] [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 2852] [5ኛ]፡- رجب شهر عظيم يضاعف الله فيه الحسنات، فمن صام يوما من رجب، فكأنما صام سنة، ومن صام منه سبعة أيام، غلقت عنه سبعة أبواب جهنم، ومن صام منه ثمانية أيام، فتحت له ثمانية أبواب الجنة، ومن صام منه عشرة أيام، لم يسأل الله شيئا إلا أعطاه إياه، … “ረጀብ አላህ መልካም ምንዳዎችን የሚያነባብርበት ታላቅ ወር ነው። ከረጀብ አንድ ወር የፆመ ሰው አመት እንደፆመ ነው። ከሱ ሰባት ቀናትን የፆመ ሰባቱ የጀሀነም በሮች ይዘጉለታል። ከሱ ስምንት ቀናትን የፆመ ስምንቱ የጀነት በሮች ይከፈቱለታል። ከሱ አስር ቀናትን የፆመ አላህን የሆነ ነገር አይጠይቅም፣ እሱኑ የሰጠው ቢሆን እንጂ፣ …” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [አዶዒፋህ፡ 5413] [6ኛ]፡- إن في الجنة نهرا يقال له رجب ماؤه أشد بياضا من اللبن وأحلى من العسل من صام يوما من رجب سقاه الله من ذلك النهر “በጀነት ውስጥ ረጀብ የሚባል ወንዝ አለ። ውሃው ከወተት የነጣ፣ ከማር የጣፈጠ ነው። ከረጀብ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ ከዚያ ወንዝ ያጠጣዋል።” አልባኒ “መሰረተ ቢስ” ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 1902] [7ኛ]፡- صوم أول يوم من رجب كفارة ثلاث سنين، والثاني كفارة سنتين، والثالث كفارة سنة، ثم كل يوم شهرا “የረጀብን የመጀመሪያ ቀን መፆም የሶስት አመት ወንጀል ያብሳል። ሁለተኛው የሁለት አመት ያብሳል። ሶስተኛው ደግሞ የአመት ያብሳል። ከዚያም እያንዳንዱ ቀን የወር ነው።” አልባኒ ደካማ ብለውታል። [ዶዒፉል ጃሚዕ፡ 3500፣ 5649] [8ኛ]፡- لا تغفلوا عن أول جمعة من رجب فإنها ليلة تسميها الملائكة الرغائب “ከረጀብ የመጀመሪያ ጁሙዐ አትዘናጉ። እርሷ መላእክት ‘አረጋኢብ’ ብለው የሚጠሯት ሌሊት ነች።” ‘ሶላተ ረጋኢብን’ በተመለከተ ነወዊይ እንዲህ ብለዋል፡- “እርሷን የፈጠረን ሰው አላህ ይርገመው! እርሷ አስቀያሚ ቢድዐ ነች!” [ሸርሑ ሙስሊም] በተጨማሪም እሷንና የሸዕባን አጋማሽ ሌሊት ሶላትን አስመልክተው “… ቢድዐና አስቀያሚ ፈጠራዎች ናቸው። በ‘ቁቱል ቁሉብ’፣ ‘ኢሕያእ ዑለሚዲን’ ኪታብ ውስጥ ስለተጠቀሱ ማንም እንዳይሸወድ። እነሱን በሚጠቁመው ሐዲሥም እንዲሁ (እንዳይሸወድ)። ምክንያቱም ሁሉም ውድቅ ነውና” ብለዋል። [አልመጅሙዕ፡ 3/548] [9ኛ]፡- أن رسول الله -ﷺ- لم يصم بعد رمضان إلا رجبًا وشعبان “የአላህ መልእክተኛ ከረመዷን በኋላ ረጀብንና ሸዕባንን እንጂ አልፆሙም።” ኢብኑ ሐጀር በጣም ደካማ ነው ብለውታል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 12] [10ኛ]፡- من صلى المغرب في أول ليلة من رجب ثم صلى بعدها عشرين ركعة يقرأ في كل ركعة بفاتحة الكتاب، وقل هو الله أحد مرة، ويسلم فيهن عشر تسليمات، أتدرون ما ثوابه؟ قال: حفظه الله في نفسه وأهله وماله وولده، وأجير من عذاب القبر، وجاز الصراط كالبرق بغير حساب ولا عذاب “በረጀብ የመጀመሪያ ሌሊት መግሪብን ሰግዶ ከዚያም በእያዳንዷ ረከዐ ፋቲሐንና ቁል ሁላሁ አሐድን አንድ ጊዜ እየቀራ፣ በአስር ተስሊማት እያሰላመተ ሃያ ረከዐ የሰገደ ሰው ምንዳው ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ? አላህ በነፍሱም፣ በቤተሰቡም፣ በገንዘቡም፣ በልጁም ይጠብቀዋል። ከቀብር ቅጣትም ይጠበቃል። ሲራጥንም ያለ ሂሳብና ያለ ቅጣት እንደ ብልጭታ ያቋርጧል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/123] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 20] [11ኛ]፡- من صام من رجب وصلى فيه أربع ركعات ... لم يمت حتى يرى مقعده من الجنة أو يُرى له “ከረጀብ ፁሞ፣ በሱ ውስጥ አራት ረከዓዎችን የሰገደ ሰው … በጀነት ውስጥ መቀመጫውን ሳያይ ወይም ሳይታይለት አይሞትም።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/124] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 21] [12ኛ]፡- إن شهر رجب شهر عظيم، من صام منه يومًا كتب الله له صوم ألف سنة ... “የረጀብ ወር ታላቅ ወር ነው። ከሱ አንድ ቀን የፆመ ሰው አላህ አንድ ሺ አመት ፆም ይመዘግብለታል።” ኢብኑል ጀውዚና ኢብኑ ሐጀር መሰረተ ቢስ ቅጥፈት እንደሆነ ገልፀዋል። [አልመውዱዓት፡ 2/206-207] [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 26] ከረጀብ ጋር የሚያያዙት ዘገባዎች እነዚህ ብቻ አይደሉም። እነዚህን ለምሳሌ ያክል ይዘን ሌሎቹንም ጭምር በሚመዝን የዓሊሞች ንግግር ልቋጭ:— 1/ አልሓፊዝ ኢብኑ ሐጀር - ረሒመሁላህ - “የረጀብን ወር ልዩ ብልጫም፣ መፆሙን ወይም ከፊሉን በተለየ እንዲፆም፣ ወይም ከሱ ውስጥ የተገደበን ሌሊት በሶላት ማሳለፍን፣… የሚጠቁም ለማስረጃነት የሚበጅ ትክክለኛ ሐዲሥ አልተላለፈም" ብለዋል። [ተብዪኑል ዐጀብ፡ 6 እና 8] 2/ አልሓፊዝ አቡ ዐብዲላህ ሙሐመድ ኢብኑ አቢ በክር አዲመሽቂይ (691 ሂ.) ደግሞ “እያንዳንዱ የረጀብን ፆም እና ከፊል ሌሊቶቹን መስገድን የሚጠቁም ሐዲሥ ውሸት፣ ቅጥፈት ነው” ብለዋል። [አልመናሩል ሙኒፍ፡ 1/96] ልብ በሉ! በዚህ ወር ውስጥ ፆምና ሶላት አይኑር ለማለት አይደለም። ወሩን ከሌሎቹ ወራት በተለየ መልኩ መያዝ አይገባም ነው አጠቃላይ
نمایش همه...
النحل وَضَرَبَ اللَّهُ مَثَلًا قَرْيَةً كَانَتْ آمِنَةً مُّطْمَئِنَّةً يَأْتِيهَا رِزْقُهَا رَغَدًا مِّن كُلِّ مَكَانٍ فَكَفَرَتْ بِأَنْعُمِ اللَّهِ فَأَذَاقَهَا اللَّهُ لِبَاسَ الْجُوعِ وَالْخَوْفِ بِمَا كَانُوا يَصْنَعُونَ አላህ ጸጥተኛ፣ የረካች፣ ሲሳይዋ ሰፊ ኾኖ ከየስፍራው ይመጣላት የነበረችውንና በአላህ ጸጋዎች የካደችውን አላህም ይሠሩት በነበሩት ኃጢኣት የረኃብንና የፍርሃትን ቅጣቶች ያቀመሳትን ከተማ (መካን) ምሳሌ አደረገ፡፡ An Nahl 111-128
نمایش همه...
An Nahl 111-128.mp33.27 MB
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.