fa
Feedback
Grace Commission

Grace Commission

رفتن به کانال در Telegram

የታረቀ ማኅበረ ሰብ _ 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥20

نمایش بیشتر
2 539
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
-630 روز
آرشیو پست ها
"ነገረ መለኮታዊ ጭቅጭቆችና ውዝግቦች ለጥንቁቅ ክርስቲያናዊ መንፈስ የሚያስጠሉ ናቸው። እንዲህ ያለውን ነገር ደስ ልንሰኝበት ብንሞክር፥ ወዮልን!" _ ጆን ስቶት ትርጉም፦ የአምላክ-ቸርነት በዛብህ

በዚህ የመላእክት ምስክርነት ውስጥ ሦስት ነገር እናስተውላለን፡፡ በዚህ ምስክርነት ውስጥ በመጀመሪያ የምናስተውለው የተወለደው መድኀኒት ነው የሚለውን ነው፡፡ የዕብራውያን ጽሐፊ “ኀጢአታችንን በራሱ ካነጻ በኋላ” እንዲል የተወለደው ከኀጢአት የሚያጥብ ነው፡፡ ኹለተኛው በምስክርነቱ ውስጥ የምናስተውለው ቁም ነገር የተወለደው ክርስቶስ ነው የሚለውን ነው፡፡ ክርስቶስ የሚለዉ የግሪክ ቃል ሲሆን “የተቀባ” ማለት ነዉ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስም የተቀባ መኾኑን ሐዋርያት ሥራ 10÷38 እንዲህ ይላል “እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅደስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔርም ከእርሱ ጋር ነበረና፤” በማለት ኢየሱስ የተቀባ አገልጋይ መኾኑን ይገልጻል፡፡ ኢየሱስን ክርስቶስ ነው ብሎ ማመን አንድ የእምነታችን መሠረት ነውና (1ዮሐ. 5÷1)፡፡ ሦስተኛውና የመጨረሻው የዚህ ምስክርነት መልእክት፣ የተወለደው ጌታ ነው የሚል ይኾናል፡፡ ኩሪዮስ (kurios koo’-ree-os) የሚለው የግሪክ ቃል ሲኾን ገዥ፣ አለቃ፣ የበላይ ማለት ሲኾን አዶን ወይም አዶናይ እንዲኹም ኤሎሂይም ከሚለው የእግዚአብሔር ስም ጋራ አቻ ትርጉም አለው፡፡ የሰማይ ደስታ እና የምድር ሰላም (ቁ. 13–14): የእግዚአብሔር ተልእኮ ማስታረቅ ነው በድንገት፣ ሰማዩ እግዚአብሔርን በሚያመሰግኑ መላእክት ተሞላ፡፡ ሰማይ ዝም ብሎ መቆየት አልቻለም፡፡ የሰማይ ሠራዊት ሁሉ ከተገለጠው መልአክ ጋር በአንድነት “ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ይሁን ሰላምም በምድር ለሰውም በጎ ፈቃድ አሉ።”፡፡ የመላእክት መዝሙር “ሰላምም በምድር” ስሜታዊ ግጥም አይደለም፤ የእግዚአብሔርን የማስታረቅ ተልእኮ መግለጫ ነው፡፡ ሰላም (ሻሎም) ማለት ሙሉነት፣ መልሶ ማቋቋም እና ከእግዚአብሔር እና ከሌሎች ጋር ትክክለኛ ግንኙነት ማለት ነው፡፡ እግዚአብሔር ከአሁን በኋላ ሩቅ አይደለም፡፡ እግዚአብሔር ከአኛ ጋር ሁኗል(አማኑኤል)፣ ዓለምን ቀውስ ውስጥ የከተተው ኀጢአት መድኀኒቱ መጥቷል፡፡ ተስፋ ወደ ጨለማው ዓለም ውስጥ ገብቷል፡፡ እግዚአብሔር ያደረገውን ስንረዳ ዝም ማለት አንችልም፡፡ የተገለጠላቸው ለእግዚአብሔር የሰጡትን “ምላሽ”(ቁ. 15-17) “እንሂድ” (ቁ. 15-16): መገናኘት ወደ እንቅስቃሴ ይመራል ቤተ ክርስቲያን ተልእኮን አትፈጥርም፤ በእግዚአብሔር ተልእኮ ውስጥ ትሳተፋለች፡፡ አብ ወልድን እንደላከው ሁሉ፣ ወልድም ቤተ ክርስቲያንን ይልካል (ዮሐ. 20፥21)፡፡ የኢየሱስ ልደት የቤተ ክርስቲያን ሕይወትና ምስክርነት ምሳሌ ይሆናል፡፡ እረኞች የመጀመሪያዎቹ ሚስዮናውያን ናቸው፡፡ ክርስቶስን ካገኙ በኋላ ስለ ሕጻኑ የተወራላቸውን ገልጠው አወሩ (ሉቃስ 2፥17) አ.መ.ት፡፡ ልክ እንደ እረኞቹ፣ ልጁን በእውነት የምታይ ቤተ ክርስቲያን ዝም አትልም፡፡ እረኞች አልተከራከሩም፡፡ አልዘገዩም፡፡ “ወደ ቤተልሔም እንሂድ” አሉ(አ.መ.ት)፡፡ ተልእኮ ሁልጊዜ የሚጀምረው ለመሄድ በመወሰን ነው፡፡ ይህንን ልብ እንበል፣ እረኞቹ በጎቻቸውን ትተው ነበር፡፡ ያ አደገኛ ነበር፡፡ ነገር ግን ክርስቶስን መገናኘት ሁልጊዜ የምንተወውን ነገር በእግዚአብሔር እንድንታመን ይጠይቀናል፡፡ ዛሬም፣ ተልእኮ እንቅስቃሴ ይጠይቃል፡፡ ከምቾት ወደ ታዛዥነት፣ ከፍርሃት ወደ እምነት፣ ከማወቅ ወደ መሄድ፡፡ “አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።”(ቁ. 17): ካዩም በኋላ ስለ ሕፃኑ የተነገራቸውን ግለጠው አወሩ(አ.መ.ት) እረኞቹ ኢየሱስን ካዩ በኋላ በሴሚናር ላይ አልተገኙም፡፡ መደበኛ ስልጠና አልወሰዱም፡፡ እረጆቹ ያዩትንና የሰሙትን ብቻ ተናገሩ፡፡ ተልእኮ ሁሉንም መልሶች ስለማግኘት አይደለም፡፡ ክርስቶስ ለእኛ ያደረገውን ስለማካፈል ነው፡፡ እረኞቹ ምስራቹን ሰምተዋል፣ የሰማይን መላእክት ዝማሬ ሰምተዋል፣ የጌታን ክብር አይተዋል፣ ወደ ቤተልሔም ሄደውም ሕፃኑን ተመልክተዋል፡፡ ነገር ግን ታሪኩ እዚያ ላይ አላበቃም። ሉቃስ 2፥17 እረኞቹ “አይተውም ስለዚህ ሕፃን የተነገረላቸውን ነገር ገለጡ።” ይለናል፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለን ትልቁ ችግር "አይተን ዝም ማለታችን" ነው፡፡ ብርሃኑን አይተናል ግን ጨለማ ውስጥ ላሉት አልበራንም፤ መድኀኒቱን አግኝተናል ግን ለታመመው ዓለም አልሰጠንም፡፡ እረኞቹ ግን የታያቸውንና የተነገራቸውን ነገር ምስክር ሳይሆኑ ሊቀሩ አልቻሉም፡፡ እረኞቹ መልእክቱን በሰሙ ጊዜ "እስቲ እንሂድና እንይ" አሉ። ምሥራቹን ለማብሰር መጀመሪያ ወደ ክርስቶስ መቅረብና እርሱን ማየት ያስፈልጋል፡፡ ለአሁኗ ቤተ ክርስቲያን፦ ተልእኮ የሚጀምረው በምቾት ወንበር ላይ ተቀምጦ ፕሮግራም በማድነቅ አይደለም፡፡ ተልእኮ የሚጀምረው የክርስቶስን ፍቅር ቀምሶ፣ ያንን ፍቅር ለሌላው ለማካፈል ካለ ጉልበት ነው፡፡ ዓለም በኀጢአትና በጭንቀት እየተቃጠለች ባለችበት በዚህ ዘመን፣ ቤተ ክርስቲያን ቅጥር ግቢዋ ውስጥ ብቻ መሸሸግ የለባትም፡፡ እረኞቹ መንጋቸውን(ጊዜያዊ ማደሪያ በረት) ጥለው እንደወጡ፣ እኛም ከሃይማኖታዊ ልማዳችን ወጥተን ወደ ሰው ልብ መጓዝ አለብን። እረኞቹ የተናገሩት የራሳቸውን ፍልስፍና ሳይሆን ስለ ሕፃኑ የተነገረላቸውን ነው፡፡ ዛሬ ዓለም የሚያስፈልጋት የሰውን ንግግር ሳይሆን ስለ ክርስቶስ የሚነገር ምስክርነትን ነው። የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ (የእኛ ተልእኮ) የክርስቶስን ማንነትና ሥራ ለሰዎች ማሳወቅ ነው፡፡ ሰዎችን ወደ ሃይማኖት ሳይሆን ወደ ሕያው ጌታ ማገናኘት ነው፡፡ አንድ የታመመ ሰው መድኀኒት አግኝቶ ከዳ በኋላ፣ መድኀኒቱን ለሌሎች ታማሚዎች ሳይናገር ዝም ቢል ይህ ጭካኔ ነው። እኛም የዘላለም ሕይወት አግኝተን ለሚጠፋው ዓለም ዝም ካልን ትልቅ ዕዳ አለብን፡፡ ዝምታችን የብዙዎችን ሕይወት ሊያስከፍል ይችላል! እነዚያ እረኞች በዚያች ሌሊት የቤተልሔም አውራ ጎዳናዎችን በደስታ ጩኸት ሞሉት! "አገኘነው! መድኃኒቱ መጥቷል! ሰላሙን አየነው!" እያሉ ሲጮኹ፣ ዓለም በመደነቅ ተሞላች(ቁ.18)፡፡ ዛሬ ቤተ ክርስቲያን የሚያስፈልጋት ይህንን ነው፡፡ ያየችውንና የቀመሰችውን እውነት ለሚጠፋው ዓለም በኀይል የምታውጅ ምስክር መሆን፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ዛሬም ጌታ እንዲህ ይላታል፡- ባየሽው ብርሃን ጨለማውን ውጊ፤ በሰማሽው ቃል የተጠሙትን አርኪ፤ በጨበጥሽው እውነት የታሰሩትን ፍቺ፡፡ ማጠቃለያ፡ ግርግሙ ከእግዚአብሔር ወደ ቤተ ክርስቲያን የቀረበ ግብዣ ነው፡፡ ወደ ዝቅተኛ ቦታዎች መሄድ፣ ለተራ ሰዎች መናገር፡፡ እረኞቹ ሕፃኑን ሲያዩ ዝም ማለት አልቻሉም፡፡ ያዩትንና የተነገራቸውን ነገር ወዲያውኑ ማውራት (መመስከር) ጀመሩ፡፡ ማየት ወደ ማውራት ይመራል፡፡ ክርስቶስን በትክክል ያየ ሰው ዝም ሊል አይችልም፡፡ የእግዚአብሔር መገለጥ ዛሬም በቃሉ በኩል ለእኛ ደርሷል፡፡ ጥያቄው ግን፦ የእኛ ምላሽ ምንድነው? እንደ እረኞቹ ሮጠን ወደ እርሱ እንቀርባለን? ወይስ ሰምተን እንዳላየን እናልፋለን? በግርግም የጀመረው የእግዚአብሔር ተልእኮ እያንዳንዱ ነገድ፣ ቋንቋ እና ሕዝብ ምሥራቹን እስኪሰማ ድረስ በታክ ውስጥ ቀጥሏል፤ አኹንም በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ይቀጥላል፡፡ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ነው፡፡ (ዓለማየሁ አየለ፣ ታህሳስ፣ 2018 ዓ.ም) የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን!

ምሥራቹ እና ለምስራቹ የተሰጠው ምላሽ (ሉቃስ 2፥7-17) በክርስቶስ የተወደዳችሁ ወንድሞችና እህቶች፣ እንኳን ለጌታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ፡፡ በሕይወታችን ብዙ ምሥራች ሰምተናል፡፡ የሥራ ዕድል ማግኘት፣ የታመመ መፈወስ፣ ጦርነት አብቅቶ ሰላም መውረድ፣ ወይንም የሕፃን ልጅ መወለድ... ወዘተ. እነዚህ ኹሉ ያስደስታሉ፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ምሥራቾች ሁሉ "ውስንነት" አለባቸው፡፡ የሰው ምሥራች አድሎአዊ ነው፤ የአንዱ ድል የሌላው ሽንፈት ነው፡፡ የሰው ምሥራች ጊዜያዊ ነው፤ የዛሬው ደስታ በነገው ጭንቀት ይዋጣል፡፡ የሰው ምሥራች ውድ ነው፤ ለማግኘት ድካምና መከፈል ያለበት ዋጋ ይጠይቃል፡፡ በዚህ ጽሑፍ ከሰው ምሥራች ሁሉ የሚበልጥ፣ ሰማይ ለምድር የላከውን፣ ታሪክን ለሁለት የከፈለውንና የሰው ልጅን ዕጣ ፈንታ የለወጠውን ታላቅ ምሥራች እናያለን፡፡ እርሱም የኢየሱስ መወለድ ነው፡፡ በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ብዙ ድንቅ ክስተቶች ተከስተዋል፡፡ ነገር ግን የሰማይ ጌታ ሥጋ ለብሶ(ሰው ኹኖ) ወደ ምድር የመጣበትን ያህል ታላቅ ዜና የለም። በምንመለከተው በዚህ ክፍል ውስጥ ኹለት ትልልቅ እውነታዎች ላይ እናተኩታለን፡፡ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ያደረገው “መገለጥ” እና የተገለጠላቸው ለእግዚአብሔር የሰጡትን “ምላሽ” ነው፡፡ የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት በየዓመቱ የሚታወስ ታሪካዊ ክስተት ብቻ አይደለም፤ ዓለምን የመቤዠት የእግዚአብሔር ተልእኮ ወሳኝ ተግባር ነው፡፡ በተልእኮ ሥነ መለኮት ውስጥ፣ ተልእኮ የሚጀምረው በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ እንደሆነ ያስተምራል፡፡ አብ ወልድን ይልካል፤ አብና ወልድ መንፈስ ቅዱስን ይልካሉ፤ ሥሉስ አሐዱ አምላክ ወይም እግዚአብሔር ቤተ ክርስቲያንን ወደ ዓለም ይልካል፡፡ ስለዚህ፣ ግርግሙ እግዚአብሔር ለሕዝብ ኹሉ የሚያደርገው የቤዛነት እንቅስቃሴ መጀመሪያ ነው፡፡ የማቴዎስ ወንጌል ተዛማጅ ክፍል የጌታን ልደት መለኮታዊ ዐላማ መግለጫ ይሰጣል፡፡ ኢየሱስ የተወለደው “ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ለማዳን” ነው(ማቴ. 1፥21)፡፡ ስለዚህ ሥጋዌው በራሱ ፍጻሜ ሳይሆን ቤዛነት የሚከናወንበት አስፈላጊ መንገድ ነው። በርግጥ መጽሐፍ ቅዱሳችን ቃል ሥጋ የመሆኑ ዝርዝር ዓላማዎች በብዙ መንገድ ይገልጻል፡፡ መለኮታዊውን ባሕርይ ለሰው ልጅ ለመግለጥ(ዮሐ. 14፥9፣ ዮሐ. 1፥18)፣ የኀጢአትን ዕዳ ለመክፈል፣ የሰይጣንን ሥራ ለማፍረስ((ዕብ. 2፥14፣ 1ዮሐ. 3፥9)፣ ሊቀ ካህናት ለመሆን ሰው ኾነ(ዕብ. 5፥1)፡፡ ስለ መወለዱ ስናወራ ከሞቱና ከትንሣኤው ነጥለን ሊሆን አይችልም፡፡ የክርስቶስ ልደትና ሞት የአንድ ሳንቲም ኹለት ገጽታዎች ናቸው፡፡ አንዱ ያለ አንዱ ትርጉም አይሰጥም፡፡ አምላክ በባሕርዩ ዘላለማዊ ነው፤ ሊሞት አይችልም፡፡ ነገር ግን እኛን ለማዳን የግድ መሞት ነበረበት፡፡ ስለዚህ ሥነ-መለኮታዊው ምስጢር እዚህ ጋር ነው፡፡ ክርስቶስ ሰው የሆነው ለመሞት የሚያስችለውን ሰውነት ለማግኘት ጭምር ነው፡፡ በቤተልሔም በረት ውስጥ ድንግል ማርያም ያቀፈችው ያ ሕፃን፣ ለሞት የተዘጋጀ መሥዋዕት ነበር፡፡ ሥጋዌ እግዚአብሔርን ከእኛ ጋር መሆኑን ያሳያል፡፡ መስቀሉ ደግሞ እግዚአብሔርን ለእኛ ይገልጣል፡፡ ትንሣኤ እግዚአብሔርን በእኛ መካከል ድል አድራጊ አድርጎ ያሳያል፡፡ ስለዚህ የማይነጣጠሉ ነገሮች ናቸው፡፡ የምሥራቹ መገለጥ፦ ሰማይ ምድርን ሲጎበኝ (ቁ. 7-14) በግርግም የተወለደ አዳኝ (ቁ. 7)፡ የእግዚአብሔር ተልእኮ መጀመሪያ ወደ ሉቃስ ክፍል ስንመጣ፣ ሉቃስ እንደሚነግረን ማርያም “የበኵር ልጅዋንም ወለደች፥ በመጠቅለያም ጠቀለለችው፤ በእንግዶችም ማደሪያ ስፍራ ስላልነበራቸው በግርግም አስተኛችው።” ቁ.7 ለአፍታ አስቡት፡፡ የዓለም አዳኝ እንስሳት የሚያድሩበት ግርግም ተወለደ፡፡ የክብር ንጉሥ ያለ ጭብጨባ፣ ያለ ምቾት፣ ያለ እውቅና ወደ ዓለም ገባ፡፡ እግዚአብሔር ተልእኮውን የሚጀምረው በዚህ መንገድ ነው፡፡ አጽናፈ ዓለሙን የሚይዘው እርሱ በእናቱ እቅፍ ተያዘ፡፡ ግርግሙ ስለ እግዚአብሔር ልብ ጥልቅ ስሜት የሚፈጥር ነገር ይነግረናል፡፡ እግዚአብሔር የሰው ልጅ ንፁህ፣ ብቁ ወይም ዝግጁ እስኪሆን አልጠበቀም፡፡ ወደ ቆሻሻ ማንነቱ መጣ፡፡ ምስራቹ የተገለጠላቸው ሰዎች እግዚአብሔር ታላቁን ምስጢር (ቃል ሥጋ መሆኑን) ለመግለጥ የመረጠው የቤተ መንግሥት መኳንንትን ሳይሆን፣ በሌሊት መንጋቸውን የሚጠብቁ ተራ እረኞችን ነው፡፡ ወንጌልን የሰሙት የመጀመሪያዎቹ ካህናት አይደሉም፡፡ ነገሥታት አይደሉም፡፡ ምሁራን አይደሉም፡፡ እረኞች፡፡ እግዚአብሔር ለተናቁት እረኞች ታላቁን ምስጢር(ቃል ሥጋ መሆኑን) መግለጡ ያስደንቃል፡፡ እረኞች ድሆች፣ ቆሻሻዎች እና በኅብረተ ሰቡ ችላ የተባሉ ነበሩ፡፡ ሆኖም እግዚአብሔር በታሪክ ውስጥ እጅግ ታላቅ የሆነውን አዋጅ በዐደራ ሰጣቸው፡፡ የምስራቹ ይዘት “እነሆ፥ ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ” ቁ.10 “ለሕዝብ ሁሉ” የሚለው ሐረግ የምሥራቹን ስፋት ወይም የእግዚአብሔርን ተልእኮ ዓለም አቀፋዊ ስፋት ያሳያል፡፡ ትስጉት(የአምላክ ሰው መሆን) እግዚአብሔር በአብርሃም ዘር አማካኝነት ሁሉንም አሕዛብ እንደሚባርክ የሰጠውን የብሉይ ኪዳንን ተስፋዎች ፍጻሜ ነው (ዘፍ. 12፥3)፡፡ ኢየሱስ የእስራኤል መሲሕ ብቻ ሳይሆን የዓለም አዳኝ ሆኖ ተወለደ (ዮሐ. 4፥42)፡፡ የዓለም ዜናዎች "ለተመረጡት" ናቸው፡፡ የኢየሱስ ምሥራች ግን የድንበር አጥር የለውም፡፡ ለእረኞች (ለተናቁት) ተበሰረ፤ ለሰብአ ሰገል (ለጥበበኞች) ተገለጠ፤ ለአይሁድም ለአሕዛብም ሆነ፡፡ ይህ የምሥራች እንደ ሰማይ ዝናብ ነው፡፡ ዝናብ በሀብታም እርሻ ላይ ብቻ አይዘንብም፤ ድሃውም ጋ ይደርሳል፡፡ ነፍሳችን የጠማትን ዕረፍት፣ ልባችን የናፈቀውን ፍቅር ያገኘነው በቤተልሔሙ ሕፃን ውስጥ ነው፡፡ ዓለም ሊሰጠን የማይችለውንና ሊነጥቀን የማይችለውን ሰላም ይዞልን መጣ፡፡ የደስታው ዓይነት “ታላቅ ደስታ” ተብሎ ተገለጸ፡፡ ይህ ደስታ "ታላቅ" የተባለው ከመጠን በላይ ስለሆነና በምድር ስለማይገኝ ነው፡፡ ምድራዊ ደስታ በኪሳችን ሁኔታ፣ በጤናችን ወይንም በሰዎች አመለካከት ላይ ይወሰናል፡፡ የኢየሱስ ደስታ በሞት ሸለቆ ውስጥ ስናልፍ እንኳ የማይጠፋ፣ በችግር እሳት ውስጥ የማይቃጠል፣ በክርስቶስ ማንነት ላይ የተመሠረተ የውስጥ ሰላም ነው፡፡ የሰማይ መልስ ለምድር ፍርሃት ("አትፍሩ!") መልአኩ "አትፍሩ" አለ፡፡ ዓለም በጨለማ፣ በኃጢአትና በሞት ጥላ ተውጣ በነበረችበት ወቅት ሰው እግዚአብሔርን መፍራት ብቻ ሳይሆን መቅረብም ይፈራ ነበር፡፡ የኢየሱስ መምጣት የፍርሃትን ሰንሰለት ሰባበረ፡፡ እግዚአብሔር ከሰው ጋር ሊጣላ ሳይሆን ሊታረቅ፣ ሊፈርድ ሳይሆን ሊያድን ወደ ምድር ወረደ፡፡ እርሱ ሲመጣ ፍርሃት ቦታውን ለፍቅር፣ ጭንቀት ደግሞ ቦታውን ለሰላም ለቀቀ፡፡ ዛሬም ይህ ምሥራች ለልባችሁ የሚለው፦ "አትፍሩ፤ አዳኝ ተወልዶላችኋል!" የሚል ነው፡፡ መልአኩ “ለሕዝቡ ሁሉ የሚሆን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁና” አለ፡፡ ይህ ስለ ተልእኮ አንድ አስፈላጊ ነገር ይነግረናል፡፡ የእግዚአብሔር መልእክት ለአስፈላጊዎች ብቻ አይደለም፣ ለተረሱት ኹሉ ነው፡፡ በዚያች ሌሊት፣ እረኞች በሰማይ ተመርጠዋል፡፡ የምስራቹ ማንነት “ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።” ቁ.11

photo content
+1

Track 04 ክብሬ ነህ.mp312.68 MB

እኛ ያለን አንድ ነው፤ እሱም ኢየሱስ። በሁሉም ስፍራ (በሰማይም በምድርም) እርሱን እየመነዘርን እንኖራለን! እርሱ ሁሉን ሆነልን!

ከመጽሐፍ ቅዱስ ጠቅሶ ከመስበክ፥ ጠቅሶ መኖር ይከብዳል! በዚህ ዘመን ግን በትክክል ጠቅሶ መስበክም ዳገት ሆኗል!

photo content

እግዚአብሔር ኀጢአትን የሚጠላ መሆኑን መጠራጠር ስንጀምር፣ መስቀሉን ማሰብ ይኖርብናል፡፡  ልጁ የተቀለደበት፣ የተፌዘበት እና የተገረፈበት ምክንያት ኀጢአት ነው! _ ፍራንሲስ ቻን

ልጆቻችንን ወደ ቄሳር ትምህርት ቤት እየላክን፥ ሮማውያን ሆነው ሲመጡ መደነቅ የለብንም! _ቮዲ ቦካም

photo content

photo content
+1

አንድ ሕዝብ በወንጌል አልተደረሰም ማለት ምን ማለት ነው? በወንጌል አልተደረሰም የሚለው ጽንሰ-ሐሳብ በተልእኮ ሥነ መለኮት ውስጥ ማእከላዊ ቦታን ይይዛል። የሚያመለክተውም በአንድ ሕዝብ ክፍል ውስጥ ወንጌልን የማግኘት ዕድል የሌላቸው ወይም በእነርሱ ውስጥ ራሳቸውን የሚደግፉ፣ የአገሬው ተወላጆች ክርስቲያናዊ እንቅስቃሴ የሌለባቸውን አባላትን ነው። በመጽሐፍ ቅዱሳዊው መሠረት፣ ያልተደረሰው ምድብ እግዚአብሔር ለሁሉም ሕዝቦች ባዘጋጀው ማዳን ውስጥ ገና አልተካተተም ማለት ነው። እናም ወደዚህ ማዳን የሚገባው ክርስቶስ ለቤተ ክርስቲያኑ በሰጠው ተልእኮ ነው። የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት ከመጀመሪያው፣ ቅዱሳት መጻሕፍት እግዚአብሔርን እንደ የተልእኮ አምላክ ያቀርቡታል። ዐላማው በመረጠው ሕዝብ በኩል ሁሉንም አገሮች(ሕዝብ) ለመባረክ ነው። የአብርሃም ቃል ኪዳን ይህንን አጽናፈ ዓለማዊ ሐሳብ ይመሠረታል፡- “የምድር ነገዶች ሁሉ በአንተ ይባረካሉ” (ዘፍ. 12፥3)። ይህ መለኮታዊ የተስፋ ቃል ከእስራኤል አልፎ ወደ ህዝቦች ሁሉ ይዘልቃል፣ ይህም የእግዚአብሔር የማዳን እቅድ በባህሪው ዓለም አቀፋዊ መሆኑን ያሳያል። ነቢያት ጌታን ለማምለክ የሚመጡትን አሕዛብ አስቀድሞ ሲያዩ ይህን ዓለም አቀፋዊ ስፋት ያስተጋባሉ (ኢሳ. 49፥6፤ መዝ. 67፥1-4)። በዐዲስ ኪዳን ውስጥ፣ ኹለንተናዊ ተልእኮ በክርስቶስ ሞት እና ትንሣኤ የመጨረሻው ደረጃ ላይ ደርሷል። ኢየሱስ ወንጌልን “ለአሕዛብ ሁሉ” እንደሆነ ተናግሯል (ማቴ. 28፥19፤ ሉቃስ 24፥47)። ስለዚህ ታላቁ ተልእኮ የቤተ ክርስቲያንን ማንነት እና ኀላፊነት እስከ ምድር ዳርቻ የተላከ የተልእኮ ማኅበረ ሰብ አድርጎ ይገልጻል። የሐዋርያት ሥራ መጽሐፍ የዚህን ትእዛዝ ደረጃ በደረጃ መፈጸሙን ይተርካል። ከኢየሩሳሌም እስከ ይሁዳ፣ ሰማርያ፣ እና በመጨረሻም ወደ አሕዛብ ዓለም (ሐዋ. 1፥8)። በራእይ 7፥9 ላይ ያለው ራእይ ደግሞ እግዚአብሔር  በዙፋኑ ፊት “ከሕዝብ፣ ከነገድ፣ ከወገን፣ ከቋንቋም ሁሉ” የተዋጁ ሲመልኩት የተልእኮውን ፍጻሜ ያሳያል። ከሥነ-መለኮት አንጻር፣ ያልተደረሰው ሕዝብ የማያምኑት ስብስብ ብቻ ሳይሆን፣ በራሱ የባህልና የቋንቋ ማእቀፍ ውስጥ በቂ የወንጌል መዳረሻ የሌለው ማኅበረ ሰብ ነው። ሚሲዮሎጂስት ዴቪድ ቦሽ አፅንዖት እንደሰጠው፣ ተልእኮ የግለሰብን መለወጥ ብቻ ሳይሆን በእያንዳንዱ ህዝብ ቡድን ውስጥ የሚታይና የሚመሰክር የእምነት ማኅበረ ሰብ መመስረት ነው።[1] እንደዚህ ያለ ቤተ ክርስቲያን አለመኖሩ ወንጌል ገና ከውጪ ድጋፍ ሊሰጥ በሚችል መልኩ ሥር እንዳልሰደደ ያሳያል። እንደ ጆሹዋ ፕሮጀክት እና የላውዛን ንቅናቄ ያሉ የወንጌላውያን ተልእኮ ኤጀንሲዎች፣ ያልተደረሰውን የህዝብ ክፍል ከሁለት በመቶ ያነሱት ወንጌላውያን ክርስቲያኖች እንደሆኑ እና ከአምስት በመቶ በታች የሚሆኑት በስም ክርስትናን የሚከተሉ እንደሆኑ ይገልፃሉ። [2][3] ጳውሎስ “እንዴት ያምናሉ? ያለ ሰባኪስ እንዴት ይሰማሉ?” ሲል ተናግሯል( ሮሜ. 10፥14)። ያልተደረሱት በመንፈሳዊ ጨለማ ውስጥ የቀሩት ወንጌልን ስለናቁ ሳይሆን ገና ትርጉም ባለው መልኩ የሚያደርሳቸው ስላላገኙ ነው። ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል እንደመሆኗ መጠን በሁሉም የባህል እና የቋንቋ ድንበሮች ወንጌልን በመስበክ ይህንን ክፍተት የማስተካከል ኀላፊነት አለባት። ስለዚህም እያንዳንዱ ሕዝብ በራሱ ቋንቋና ባህል ወንጌልን እስኪያገኝ ድረስ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ የተሟላ አይደለም። ያልተደረሱ ህዝቦች መኖራቸው የራእይ 7፡9 የፍጻሜ ራእይ አሁንም በሂደት ላይ እንደሆነ ሥነ-መለኮታዊ ማሳሰቢያ ነው። ቤተ ክርስቲያን ይህንን መለኮታዊ ዐላማ እስክትፈፅም ድረስ፣ የተልእኮው ሥራ ሳይጠናቀቅ ይቀራል። “Missions exists because worship doesn't” John Piper, Let the Nations Be Glad! The Supremacy of God in Missions (Grand Rapids, MI: Baker Academic, 1993), (30TH ANNIVERSARY EDITION),p.1 ሰዎች በክርስቶስ በኩል እግዚአብሔርን እንዲያመልኩት ለተልእኮ (ለወንጌል) እንትጋ። የጌታ ጸጋ ይብዛልን! #በዓለማየሁ #አየለ ተጻፈ ሕዳግ 1. David J. Bosch, Transforming Mission: Paradigm Shifts in Theology of Mission (Maryknoll, NY: Orbis Books, 1991), 389. 2. Joshua Project, “Unreached People Groups,” accessed November 13, 2025, https://joshuaproject.net. 3. Lausanne Committee for World Evangelization, The Lausanne Covenant (Lausanne, 1974), 56. ዋቢ መጻሕፍት Bosch, David J. Transforming Mission: Paradigm Shifts in Theology of Mission. Maryknoll, NY: Orbis Books, 1991. Joshua Project. “Unreached People Groups.” Accessed November 13, 2025. https://joshuaproject.net. Lausanne Committee for World Evangelization. The Lausanne Covenant. Lausanne, 1974.

photo content

https://vm.tiktok.com/ZMHcE4RqGk9oc-2aUbk/ This post is shared via TikTok Lite. Download TikTok Lite to enjoy more posts: https://www.tiktok.com/tiktoklite

photo content

photo content

2:45_3:20