Abdurahim Ahmed
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
📈 تحلیل کانال تلگرام Abdurahim Ahmed
کانال Abdurahim Ahmed (@abdure99) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 773 مشترک است و جایگاه 8 356 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 3 084 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 773 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 30 اوت, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -62 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 0 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 0% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً N/A% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 0 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 0 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
توضیحی برای کانال ارائه نشده است.
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 31 اوت, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کردهاند.
10 773
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-137 روز
-6230 روز
آرشیو پست ها
10 773
ረመዷን የቁርዓንን የሶላትን ጥፍጥና ለማግኘት ከሶሻል ሚዲያ ስክሮል ሱስ እንውጣ ሶሻል ሚዲያ ሱስ እንዲይዘን ምንድን ነው የተደረገብን እጅግ ወሳኝ ማስታወሻ
10 773
ረመዷን የቁርዓንን የሶላትን ጥፍጥና ለማግኘት ከሶሻል ሚዲያ ስክሮል ሱስ እንውጣ ሶሻል ሚዲያ ሱስ እንዲይዘን ምንድን ነው የተደረገብን እጅግ ወሳኝ ማስታወሻ
10 773
*የአፋልጉኝ ማስታወቂያ*
እዚህ ፎቶ ላይ የምትመለከቱት ወንድማችን *ዘይኑ ሸረፉ ተማም* ይባላል ተወልዶ ያደገው በስልጤ ዞን አልቾ ውሪሮ ወረዳ ሲሆን የ አምስት /5 ልጆች አባት ነዉ ከሁለት አመት በፊት ከቤት እንደወጣ ስላልተመለሰ ልጆቹ አባታችን የት ነዉ እያሉ ሌት ተቃን ሀዘን ላይ ናቸዉ ወንድማችንን የለበት የሚያውቅ ወይም ያየው ካለ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች ደውሎ ላሳወቀን ወረታውን እንከፋላለን
09 55 99 28 35
09 11 89 33 86
10 773
የኢማሞች በግፍ መገደል የሙስሊሞች በደል ያሳስበኛል የምትል ከሆነ አጀንዳህ አትልቀቅ !
መጀመሪያ በግፍ ይገድላሉ ለምን ብለህ ስትጠይቅ እኛ ክልል ኮሽ ባለቁጥር ይላሉ :: ከዚያም ስልጤ አህመዲን ሙጂብ እያሉ የጥላቻ የሀሰት ትርክታቸውን ይቀጥላሉ :: አንተም እኔም ስልጤ ነኝ እኔም አህመዲን ነኝ እኔም ሙጂብ ነኝ እያልክ አጀንዳህን ትጥላለህ ! ብሽሽቅህን ትቀጥላለህ ! ከዚያ ደግሞ ሌላ አጀንዳ ይመጣና አጀንዳህን ትረሳለህ !
ከዚያም አዙሪቱ ይቀጥላል !
በነ ፋንታሁን ዋቆ በነ ዘመድኩን በቀለ የጥላቻ አዝማቾችን እንዲሁም የግፍ ገዳዮችህን ረስተህ ያው ትቀጥላለህ !
ብቻ የምናሳዝን ነን ! በየቦታው ተወሽቀን ጭራ መሆናችን መቀለጃ መሆናችን ያሳዝነኛል ! በዚህ ጊዜ ምንም ባልል ደስ ይለኛል ! ግን ደግሞ የሚሰራው ግፍ የኛም በራሳችን መቀለዳችን ያበግነኛል !
ደስ የሚለኝ ነገር ! ተበዳይንጅ በዳይ አይደለንምና በዳዮች የእጃቸውን ማግኘታቸው የማይቀር መሆኑ ያበረታኛል !
10 773
''የእናት አደራ '' በሚል ርእስ የሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን አል አሙዲን የህይዎት ጉዞን በማስመልከት የተሰራውን ዶክመንተሪ አየሁት። ከዚህ ቀደም ስለ ሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን አል አሙዲ ሰምተናቸው የማናውቀውን ልብ የሚነኩ ታሪኮች የሚድሮክ ዋና አስፈጻሚ በሆኑት ጀማል አህመድ በኩል ሰምተናል ።
ከሁሉ ልቤን የነካኝ ሼይኽ ሙሐመድ ሁሴን አል አሙዲ ያን ሁሉ ልማት ለሀገር እየሰሩ በወቅቱ ያሳለፏቸው ፈተናዎች እጅግ የሚያሙ ልብንም የሚያደሙ ነበሩ ። ከሳኡዲ አረቢያ በመምጣታቸው ''ውህብያን ሊያስፋፉ ነው ። ሸራተንም መስጅድ ነው ''ተብሎ ተዘግቶ ፍተሻ እንደተደረገበት ሁሉ ሰማን ።
በኢህአዴግ አፍላነት ወቅት ተቃዋሚ ለነበሩት ታዋቂ ሰዎች በአውሮፓ ህክምና እንዲያደርጉ በማድረጋቸው፣በአሜሪካ ቤት በመግዛታቸው በጥርጣሬ ይታዩ እንደነበር በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ያሳዩት አጋርነት እንደሆነ እምነት እንዲጣልባቸው ያደረገው የሚለውም ሌላኛው አስገራሚ ነገር ነው ።
ከመንግስት ቀጥሎ ከ70 ሺ በላይ ሰራተኞችን የሚያስተዳድረው ሚድሮክ ሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን አል አሙዲን እናታቸውን ሊያሳትምሙ በመጡበት የሀገርህን ነገር አደራ በማለቱ ስለ ሀገር ሲሉ የከፈሉት ሁሉ የሚደንቅ ነው ።
ሚድሮክ ለሀገር በሚል በሚሊኒየም አዳራሽ ቀን፡ ከነሐሴ 26 – 30፣ 2017 ኤግዚብዢን እየተካሄደ ነው ።
ሼይኽ ሙሀመድ ሁሴን አል አሙዲን ይህን ሁሉ ስራ ሰርተው በአሁኑ ጊዜ ደግሞ በሳኡዲ አረቢያ መንቀሳቀስ የማይችሉ የቁም እስረኛ ሁነዋል። ዱንያ ለትንሹም ለትልቁም ፈተናዋ ብዙ ነው ።
አላህ ከቁም እስር ነጃ ብሏቸው ለሚወዷት ሀገራቸው ብዙ እንዲሰሩ በሁለቱም ሀገር መልካሙ እንዲገጥማቸው ዱዓችን ነው ። ዶክመንተሪውን ማየት ለምትፈልጉ ከስር ሊንኩን አስቀምጨዋለሁ ።
(አብዱረሂም አህመድ)
10 773
መጪው ትውልድ ላይ ስራ መስራት እጅግ አስፈላጊም አስደሳችም ነው :: በዚህ ተግባር ላይ ለተሳተፋችሁ ሁሉ አክብሮቴ ይድረስ
ሀሩን ሚዲያ፣ ቢዋይድ ቴክኖሎጂስና መወዳ እስኩል ጋር በመተባበር ያዘጋጁት በቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት ላይ ያተኮረ ልዩ የክረምት ስልጠና በአዲስ አበባ ካራ ቆሬ በሚገኘው መወዳ ትምህርት ቤት እየተሰጠ ይገኛል።
የስልጠናው ዓላማ ሙስሊም ተማሪዎች የክረምት ጊዚያቸው በቴክኖሎጂ እና በኢስላማዊ ስነምግባር እንዲያሳለፉ ለማድረግ ያለመ ነው።
ስልጠናው ትኩረቱን ያደረገው፦ ድረ ገፅ ማበልፀግ (Web Development) የሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ (App Development)፣ የማንነት እነፃ (Personal Development) ፣የእምነትና የእሴት መሰረታውያን(Foundations of Islamic Truth and Values)ልምድ ማጋራት (Mentorship) ፣እስልምናንና እስላማዊ ታሪክን መረዳት (Understanding Islam and Islamic History)እና ሌሎችም ኮርሶችን ያካተተ የክረምት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል።
ስልጠናውን እየወሰዱ ያሉ ተማሪዎች ስልጠናውን አስመልክቶ ለሀሩን ሚዲያ በሰጡት አስተያየት እንደገፁት በርካታ ቁምነገር ያገኙበት ስልጠና መሆኑን አንስተው ከዋናው ትምህርታቸው ጎን ለጎን ይህን መሰል ስልጠናዎችን መውሰዳቸው ለወደፊቱ ለሚኖራቸው ራዕይ መንደርደሪያ እንደሚሆናቸው ተናግረዋል።
ይህ ስልጠና መጪው ትውልድ ከታች ጀምሮ ከቴክኖሎጂ ጋር በማስተዋወቅ በቀጠይ በትክኖሎጂው ዘርፍ ላይ ቀዳሚ ትውልድ ለመፍጠር እጅግ ከፍተኛ ሚና ይኖረዋል ያለው ደግሞ የሀሩን ሚዲያ የሀገር ውስጥ ስቱዲዮዎች ስራ አስኪያጅ አቶ ባህሩ አባስ ነው።
©ሀሩን ሚዲያ
10 773
ፕሮጀክት ዜሮ
የኢትዮጲያ ወንጌላዊያን አብያተ ክርስቲያን ካውንስል እስከ 2030 ወንጌል ላልደረሳቸው አካባቢዎች ተደራሽ ለማድረግ በሚል ይፋ ያደረገው አዲስ ፕሮጀከት ነው። ከመላው የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያናት የመጡ መሪዎች በተገኙበት በይፋ አስጀምሯል፡፡ ወንጌል ያልደረሳቸው ብሎ እቅዱ ውስጥ ካካተታቸው መካከል ሙስሊሞች ናቸው።
ከኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጋር በአንድ ቀን በፓርላማ በአዋጅ የተቋቋመው ካውንስሉ ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ መጠነ ሰፊ የሆኑ ስራዎችን ሰርቷል።
ታዋቂው አሜሪካዊ ሚሽነሪ ፍራንክሊን ቢሊግርሃም ኢቫንጀሊካል አሶሴሽን በማቋቋም አዲስ አበባ እና ሸገር ላይ ብቻ ከ26ሺ በላይ አገልጋዮችን አሰልጥኗል። መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጲያ የሚለውን ፕሮግራም የተካሄደው ይህ ሁሉ ከተሰራ በኋላ ነው።
ይህ አንዱ ማሳያ ነውንጅ በየዘርፉ በቢዝነሱ፣ በቴክኖሎጂው፣ በዲጂታል ሚሽነሪ፣ በዩንቨርስቲ ተማሪዎች፣ በሜንቶርሺፕ በሊደርሺፕ መጠነ ሰፊ ስራዎች እየሰሩ ነው። ይህ መብታቸው ነው።
እኛስ የት ነን? ብሎ ራስን መጠየቅ ብልህነት ነው። የኔ ድርሻ ሚና ምንድን ነው ብሎ ለይቶ መንቀሳቀስ በሁላችንም ላይ የተጣለ ሃላፊነት ነው።
እንደ አስፈላጊነቱ መማሪያም ስለሚሆኑ በዚህ ጉዳይ ላይ ያጠናናቸውን ጥናቶች በፕሮግራም መልክ ለማቅረብ እንሞክራለን፣ ኢንሻአላህ
ግን በማየው እና በማስተውለው ካለንበት ማንቀላፋት መንቃት ካልቻልን ራሳችንም ኡማውም ላይ ትልቅ ጥፋት እናስተከትላለን !
አላህ ያስተካክለን አላህ ያግዘን !
መልካም ጊዜ !
10 773
ልዩ የክረምት ስልጠና
በቴክኖሎጂና ኢስላማዊ ማንነት
ልጆቻችሁ ክረምቱን የትና በምን ሁኔታ ማሳለፍ እንዳለባቸው ላሳሰባቹህ ቤተሰቦች በሙሉ፦
ሀሩን ሚዲያ፣ ቢዋይድ ቴክኖሎጂስና መወዳ እስኩል ጋር በመተባበር ውስን ተማሪዎችን ለመቀበልና ለማሰልጠን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ሲገልፅ በታላቅ ደስታ ነው።
በስልጠናው የሚካተቱ ርዕሶች፦
- Web Development (ድረ ገፅ ማበልፀግ)
- App Development (የሞባይል መተግበሪያ ማበልፀግ)
- Personal Development (ማንነት እነፃ)
- Foundations of Islamic Truth and Values (የእምነትና የእሴት መሰረታውያን)
- Mentorship (ልምድ ማጋራት)
- Underastanding Islam and Islamic History (እስልምናንና እስላማዊ ታሪክን መረዳት) እና ሌሎችም
የስልጠና ቦታ መወዳ እስኩል (ካራቆሬ)
ከ6ኛ ክፍል እስከ 12ኛ ክፍል ላሉ ተማሪዎች
ለመመዝገብ ኮሜንት ስር በሚገኘው ሊንክ አልያም በሚከተሉት ቁጥሮች ይደውሉ፦
+251941417431
+251995477358
10 773
We're Hiring: Web & App Development Trainers (2 Positions)
📍 Duration: 2 Months | 🕒 Application Deadline: June 30, 2025
📌 Organization: Bewide Technologies
We are looking for passionate and skilled Web & App Trainers to join our team. The ideal candidates will deliver engaging and hands-on training sessions in web and mobile app development, empowering learners with practical tech skills for real-world projects.
🔹 Responsibilities:
Design and deliver training programs on web and mobile app development
Provide hands-on mentorship and guidance to students
Create and update training materials based on industry trends
🔹 Requirements:
Proven experience in web/app development (HTML, CSS, JavaScript, React, Flutter, etc.)
Strong communication & presentation skills
Prior teaching/training experience is a plus
📨 Apply Now:
Submit your CV/Resume, Portfolio, and GitHub link through this form:
👉 https://lnkd.in/eAGFGRnZ
10 773
ዒድ ሙባረክ !
ሁሉ ነገራችን ከሀገራችን ጋር የተሳሰረ ነው !
ኢትዮጲያ ያላችሁ እንቅልፋችንን ትተን ኢዳችሁን ይህን ያህል ካደመቅንላችሁ አረፍ እንበል ! እኛ ጋር አሁን ሌሊት ስምንት ሰዓት እየሆነ ነው ! ኢትዮጲያ ደግሞ ዒዱ እየተሰገደ ነው ::
ኢትዮጲያም በሌሎችም ሀገራት ለምትገኙ በሙሉ ዒድ ሙባረክ ተቀበለሏሁ ሚና ወሚንኩም !
