cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Thomas Jejaw Molla - ቶማስ ጀጃው ሞላ

I didn't bit the land that feeds you!

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
5 107
مشترکین
-224 ساعت
-267 روز
-11530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ኔትወርክ መለቀቁን ተከትሎ ያለፈውን ላይክ እያደረጋችሁ ለምትገኙ የአማራ ክልል ሰዎችና ለሌሎቻችሁ ዛሬን በተመለከተ ትናንት በሙሐዘ ጥበባት Daniel Kibret "ሥራው ሂሳቡን" ጽሑፍ ጋበዝኳችሁ። እውቀት ነፃ እንደሚያወጣና ከአላስፈላጊ መስዋዕትነት እንደሚታደግ ስጋ ለብሶ ነብስ ዘርቶ ያረጋግጥላችኋል። ሥራው ሂሳቡን ጢሱ የማይነካቸው የአሜሪካ ቀበጤዎችን ትተህ አንተ ሂሳቡን ሥራው። አትጠራጠር ውጊያውን መከላከያ በሆነ መንገድ ይጨርሰዋል። ሲያልቅ ግን ገበሬው፣ ነጋዴው፣ ተማሪው፣ የመንግሥት ሠራተኛው፣ አስጎብኚው፣ ሼሁና ቄሱ ምን ያገኛሉ? ሂሳቡን ሥራው። ፨ ወረዳና ዞኖች ከሌላው ወደ ኋላ ይቀራሉ፤ ፨ ያቋረጡ ተማሪዎች 'ሀ' ብለው ትምህርት ይጀምራሉ፤ ፨ ብሔራዊ ፈተና እንዳለፋቸው ሰምተው የሚደነግጡ ተማሪዎች ይበዛሉ፤ ፨ ነጋዴዎች የተዘረፈ መጋዘንና የወላለቀ ፋብሪካ ያተርፋሉ፤ ፨ የመንግሥት ሠራተኞች ስላለፋቸው ዕድገት እያሰቡ ይቆዝማሉ፤ ፨ አስጎብኚዎች ቱሪስት አልባ ቅርስ ታቅፈው ይተክዛሉ፤ ፨ ለተቸገሩ አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶች የገቢ ማሰባሰቢያ ይበዛል፤ ፨ ጊዜ ያለፈባቸው ሞባይሎችን የያዙ ሰዎች ይበዛሉ፤ ፨ ብዙ የክልሉ ሰዎች የእሥራኤል እና የሐማስን ጦርነት እንደ አዲስ ይሰማሉ፤ ፨ ማንቸስተር ዩናይትድ በሲቲ መሸነፉን ያልሰሙ ብዙ ደጋፊዎች እንደ አዲስ ይበሳጫሉ፤ ፨ አርሴናል ሼፊልድን 5ለ0 ማሸነፉን ሰምተው ደጋፊዎች እንደ አዲስ ይጨፍራሉ፤ ፨ ብዙዎቹ የጃውሳ መሪዎች በስማቸው የሚጠሩ ሌሎች ሰዎች መኖራቸውን ሰምተው ይናደዳሉ፤ ፨ በስማቸው የመጣው ገንዘብ የት ገባ? ብለው መጠየቅና መቃጠል ይጀምራሉ፤ ፨ ምናልባትም 2016 ዓም መግባቱን ያልሰሙ ሰዎች ይፈጠራሉ፤ ፨ ጥቂት የግጭት ነጋዴዎች ግን ሞጃ ሆነው ይንፈላሰሳሉ። ወገን ብዙ ከመክሠርህ በፊት ሂሳቡን ሥራው።
نمایش همه...
👍 31
ባለፈው ክረምት ላይ የፃፍኩት ፅሑፍ ላይ ሪአክት የሚያደርጉ ሰዎችን ተመለከትኩና እንዴት ብዬ ስጠይቅ ለካ በአማራ ክልል ኢንተርኔት ስለተለቀቀ ለእነሱ ፖስቱ እንደ አዲስ ነው። "እነዬ እነዬ " ማለት አሁን ነው😂 በሉ ለማንኛውም ቋንቋችን እንዳይደበላለቅ እንደምንም ብላችሁ ወራቶቹን በመዝለል ብትችሉ አሁን ካለንበት ካልሆነ ግን ቢያንስ ከሰኔ አካባቢ ጀምሩልን። ይህን ጉዳይ የሚገልፅ ለአዲስ ተቀላቃዮችም ሆነ ሶሻል ሚዲያው ላይ ቢቆዩም ትናንት በስሜት ፈረስ እየጋለቡ ከቀልባቸው ላላነበቡት እንዲያነቡት "ሥራው ሂሳቡን" በሚል የግጭቱ ሰሞን ሙሐዘ ጥበባት ዳንኤል ክብረት አስቀድሞ ዛሬን የፃፈው ፅሑፍ ጋበዝኳችሁ። እውቀት ነፃ እንደሚያወጣና ከአላስፈላጊ መስዋዕትነት እንደሚታደግም ፅሑፉ ስጋ ለብሶ ነብስ ዘርቶ ያረጋግጥላችኋል። የሚከተለው ነው ፅሑፉ። ሥራው ሂሳቡን ጢሱ የማይነካቸው የአሜሪካ ቀበጤዎችን ትተህ አንተ ሂሳቡን ሥራው። አትጠራጠር ውጊያውን መከላከያ በሆነ መንገድ ይጨርሰዋል። ሲያልቅ ግን ገበሬው፣ ነጋዴው፣ ተማሪው፣ የመንግሥት ሠራተኛው፣ አስጎብኚው፣ ሼሁና ቄሱ ምን ያገኛሉ? ሂሳቡን ሥራው። ፨ ወረዳና ዞኖች ከሌላው ወደ ኋላ ይቀራሉ፤ ፨ ያቋረጡ ተማሪዎች 'ሀ' ብለው ትምህርት ይጀምራሉ፤ ፨ ብሔራዊ ፈተና እንዳለፋቸው ሰምተው የሚደነግጡ ተማሪዎች ይበዛሉ፤ ፨ ነጋዴዎች የተዘረፈ መጋዘንና የወላለቀ ፋብሪካ ያተርፋሉ፤ ፨ የመንግሥት ሠራተኞች ስላለፋቸው ዕድገት እያሰቡ ይቆዝማሉ፤ ፨ አስጎብኚዎች ቱሪስት አልባ ቅርስ ታቅፈው ይተክዛሉ፤ ፨ ለተቸገሩ አብያተ ክርስቲያናትና መስጊዶች የገቢ ማሰባሰቢያ ይበዛል፤ ፨ ጊዜ ያለፈባቸው ሞባይሎችን የያዙ ሰዎች ይበዛሉ፤ ፨ ብዙ የክልሉ ሰዎች የእሥራኤል እና የሐማስን ጦርነት እንደ አዲስ ይሰማሉ፤ ፨ ማንቸስተር ዩናይትድ በሲቲ መሸነፉን ያልሰሙ ብዙ ደጋፊዎች እንደ አዲስ ይበሳጫሉ፤ ፨ አርሴናል ሼፊልድን 5ለ0 ማሸነፉን ሰምተው ደጋፊዎች እንደ አዲስ ይጨፍራሉ፤ ፨ ብዙዎቹ የጃውሳ መሪዎች በስማቸው የሚጠሩ ሌሎች ሰዎች መኖራቸውን ሰምተው ይናደዳሉ፤ ፨ በስማቸው የመጣው ገንዘብ የት ገባ? ብለው መጠየቅና መቃጠል ይጀምራሉ፤ ፨ ምናልባትም 2016 ዓም መግባቱን ያልሰሙ ሰዎች ይፈጠራሉ፤ ፨ ጥቂት የግጭት ነጋዴዎች ግን ሞጃ ሆነው ይንፈላሰሳሉ። ወገን ብዙ ከመክሠርህ በፊት ሂሳቡን ሥራው።
نمایش همه...
👍 14
Photo unavailableShow in Telegram
በጎርጎራ ፕሮጀከት መጠናቀቅ ደስታቸውን ከገለፁት መካከል!
نمایش همه...
👍 18
Photo unavailableShow in Telegram
የዓለም ዐይንና ጆሮ የትራምፕ የግድያ ሙከራ ላይ ነው። የበርካታ ሐገራት መሪዎችም ዶናልድ ትራምፕ ከጉዳቱ በተሎ እንዲያገግም በፀሎት ጭምር እንደሚያስቡት መልካም ምኞታቸውንም አየገለፁ ይገኛሉ። የትዊተር መንደር ከትናንት ጀምሮ እስካሁን የተጥለቀለቀው በትራምፕ አጀንዳ ነው። ኤለን መስክም የግድያ ሙከራ በተደረገበት ቅፅበት ነበር I fully endorse President Trump and hope for his rapid recovery ብሎ የተናገረው። ከላይ ከላይ ትዊት ማድረጉንም ቀጥሏል። መሃል ላይ የነበሩ የሚመስሉ ወይም ድምጻቸው ተሰምቶ የማያውቁ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችም ሁሉ ድርጊቱን ወጥተው ከማውገዝ ባሻገር ድምጻቸውን ለትራምፕ እየሰጡ ነው። በጥሩ ጤንነት ከተመለሰ ምርጫውን ትራምፕ ከወዲሁ ያሸነፈ ይመስላል(ከመጀመሪያውም እኔ ጥርጥር አልነበረኝም)። በትራምፕ የግድያ መኩራ ላይ የታዘብኩትና በእኛም ሐገር ላይ ባህል ሊሆን የሚገባው ብዬ የማስበው በሁሉም ወገን ማለትም በተቃዋሚውና በደጋፊው ወገን በኩል ያሉ ትላልቆቹ ተፅዕኖ ፈጣሪ ግለሰቦች ፖለቲከኞች አክቲቪስቶች የግድያ ሙከራውን ወዲያው ወደሴራ ትንተና ከመውሰድ ይልቅ ሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ በአንድ ድምፅ ድርጊቱን እየኮነኑ ለእሱና ለቤተሰቡ መልካም ምኞታቸውን የተመኙበት፣ለሐገራችን መጻዒ ዕድል እንፀልይ ያሉበት እና የሴኪዩሪቲ ሰርቪሱን ወደማብጠልጠል ያልገቡበት የሰውነትና የስልጡንነት ልክ እጅጉን የሚያስደንቅ ነበር። እየቆየ እየዋለ እያደረ ያው እንደሚወጡ መረዎችና አሰላለፎች ሁሉም የራሱን አቋምና ስሜት እየገለፀ መሄዱ ግን የሚጠበቅ ነው። ትራምፕ ደህና መሆናቸው ከተነገረ በኋላ ወደ ትራምፕ ተፎካካሪ ባይደንም ምፀቶች ተጀምረዋል። ልክ እንደስክሪን ሾቱ! ሰላም ለሐገራችን! ትልማ ኢትዮጵያችን!
نمایش همه...
👍 8
ምክር ወተግሳጽ ከታናሽ ወንድማችሁ በድፍረት! ቆሞ-ቀር ላልሆናችሁትና ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ ወደ መደመር መሸጋገር ለቻላችሁ በብልጽግና ፓርቲ እና በመንግሥት የስራ ኋላፊነት ላይ የምትገኙ አመራሮች የአማራን ሕዝብ አሁን ካለበት ድባቴ ለማውጣት ታሪካዊ ኋላፊነት አለባችሁ። ምንም እንኳን ቁጥራችሁ ጥቂትና ጠላት ማንነታችሁን ቀድሞ ያውቅ ስለነበረ በተቀናጀ መንገድ ለማጥፋት የሞከረና እናንተም ራሳችሁን ለመከላከል የሰራችሁት ስራ ባለመኖሩ አንዳንድ ክፍተቶች የተፈጠሩ ቢሆንም አሁንም ግን ራሳችሁን ለማብዛትና የአማራን ሕዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያዊያን በወንድማማችነት አብሮ እንዲዘልቅ የሚያስችል ትልቅ ዕድል እጃችሁ ላይ አለና እሱን ተጠቀሙበት። የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መቃብር ጠባቂዎች ቢያንስ በድርጅታችሁ ውስጥ ሆነው መዋቅራዊ ጉልበት ይዘው እናንተን እንዳያጠቁ የአማራን ሕዝብ ማህበራዊ እረፍት እየነሱ እንዳይቀጥሉ በየደረጃው ያለውን ለደሞዝ የተቀመጠውን እያራገፋችሁ(እያጠቃችሁ አላልኩም) በምትኩ ለሕብረ-ብሔራዊነት ለሰውነት ቦታ ያላቸውንና የአማራ ችግር በኢትዮጵያዊነት ማዕቀፍ ይፈታል ብለው የሚያምኑትን ከውጭም ቢሆን እያመጣችሁ ቀላቅሉ። ከውስጥ ተስፋ የሚጣልባቸውን እያጠናከራችሁ እያሳደጋችሁ ራሳችሁንም ድርጅቱንም አጠናክሩ። ቢያንስ ቁጥር ሁለት ኢህአዴግን መፍጠር ፈልገው ብልፅግናን ብአዴን የሚሉ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ መቃብር ጠባቂ ብኤዴናዊያንን ብልፅግና ስፖንሰር ሆኖ እንዳይቀጥል ከጉያችሁ አራግፋችሁ ጣሉ። ቤታችሁ ላይ በቁማችሁ እንዲጫወቱባችሁ አትፍቀዱ። ማን ምንድነው የሚለውን ለመለየት ስራ ስሩ። ለዚህ ደግሞ እስካሁን የመጣንባቸው መንገዶች ከበቂ በላይ ማስረጃ ይሰጣሉ። በይቅርታና በመደመር ጥፋታቸው እንዲታለፍላቸው ለሚፈልጉና አሁንናዊ የኢትዮጵያን ተጨባጭ ሁኔታ ለተረዱት ደግሞ ዕድል መስጠት ይቻላል ነገር ግን አይታወቅብንም ወይም ራሳቸውን እንደ ጀግና እንደ አዋቂ ብልጥ ቆጥረው በተለመደው መንገድ ሊራመዱ የሚፈልጉትን ግን ገለል እንዲሉ ማድረግ ነው። እንደዛ አለማድረግ የሆደ ሰፊነት ምልክት ወይም የዲሞክራሲ ልምምድ ነው ብዬም አላምንም። ሌላው ሶሻል ሚዲያ ላይ ብቻ ሳይሆን በአካልም ቢሆን በአማራ በኦርቶዶክስ ስም ተቆርቋሪ መስለው ነገር ግን የዘወትር አጀንዳቸው ከሁከትና ከጥላቻ ከግጭት ቀስቃሽ ከአፍራሽ አጀንዳ ውጭ ስለ ሰላምና ልማት ስለ ሕዝብ ጥቅም አጀንዳ የሌላቸውን በተለይ ደግሞ የልማት ፕሮጀክቶችን ለማደናቀፍ የሚሰሩትን(በየትኛውም አካባቢ ወደፊት እንዲመጡ የተደረጉትን) ሰዎችን እንደ ቀደመው በስመ አማራ ወይም ኦርቶዶክስ በማመን መረጃ ማጋራት ወይም መረጃ ለመቀበል ከመፍቀዳችሁ በፊት የሁሉንም ማንነት እንደ አዲስ ለመመርመር ብትሞክሩ። እርግጠኛ ሆኜ እናገራለሁ ውጤቱ እስካሁን እንደምታስቡት አይደለም። ይህን የምለው ያለ ምክንያት አይደለም። 1001% ትጠቀማላችሁ እንጅ አትጎዱበትምና ሂዱበት። በመጨረሻም ብልፅግና ለአማራ ሕዝብ ማህበራዊ እረፍት ማምጣት በሚያስችል ገቢራዊ የመፍትሄ መንገድን መራመድ ባይችል እንኳ የቀደመውን አማራን ሕዝብ እረፍት የመንሻ መንገድን ሊከተልና አቀንቃኞቹን ስፖንሰር ሊሆን አይገባም። አመሰግናለሁ!! ሰላም ለሐገራችን! ትልማ ኢትዮጵያችን! ፎቶው እመቤቲቱ በጎርጎራ ምን ጎደለ እያለች
نمایش همه...
👍 17
አበቅየለሽ አሏት ስም ሲያወጡላት አይናሚት ጎንደሬ የደም ገምቦ ናት
نمایش همه...
👍 27
Photo unavailableShow in Telegram
ዳግማዊት ጣይቱ በጎንደር ጎርጎራ!
نمایش همه...
👍 24👎 2
👍 10
በፈተናዎች የመፅናት አቅማችን የተገለጠበት ውጤት ጎርጎራ!
نمایش همه...
👍 13
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.