የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት
رفتن به کانال در Telegram
✝️ በኢ/ኦ/ተ/ቤ የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ገጽ ነው። • መረጃዎችን • ማስተዋወቂያዎችን • ትምህርቶችን እንዲሁም ሌሎች ዝግጅቶችን እንዲያገኙ #Join በመንካት ይከታተሉ። 📩 ለጥያቄ እና አስተያየትዎ @SSUBdr ያግኙን 👥 መወያያ 'ግሩፕ' ➯ @SSUBdrDiscussion ✅ SUBSCRIBE YouTube.com/andnetmedia
نمایش بیشتر1 210
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
📚''ከእግዚአብሔር ቤት መረቅናችሁ መዝ 117: 66 '' የምርቃት ጥሪ
✝️የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2015 በጀት ዓመት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትግበራ ሲያካሂዱ የነበሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶች
👉የአንደኛ ክፍል
👉ሁለተኛ ክፍል
👉አራተኛ ክፍል
👉ሰባተኛ ክፍል ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ 3100 በላይ ተማሪዎችን ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተገኙበት ያስመርቃል።
👉የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እና፣
👉 የየመምሪያ ኃላፊዎች፣
👉የገዳማት እና የአድባራት አስተዳዳሪዎች ፣
👉 የሰበካ ጉባኤ አባላት ፣
👉የማኅበረ ቅዱሳን ባሕር ዳር ማዕከል
👉የጽዋ ማኃበራት እና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አመራር ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት
👉ቀን የፊታችን እሑድ ሀምሌ 23/15 ዓ/ም
👉 ሰዓት: ከቀኑ 7:00
👉 ቦታ በደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ማርያም ሰ/ቤት ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ያስመርቃል።
🌐 በባሕረዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
SUBSCRIBE @AndnetMedia 👇 https://www.youtube.com/c/AndnetMedia 💠 የማኅበራዊ ሚዲያ ገጾቻችንን @EOTCBDSSU በመቀላቀል መረጃዎችን ይከታተሉ ለሌሎች ኦርቶዶክሳዊያንም ያዳርሱ... #Share
†
[ እንደ ቁራ ጠቁረው አየኋቸው ! ]
አባ እንጦንስ አባ ጳውሊን ሊጠይቀው በሔደ ጊዜ አባ ጳውሊን ፦ "እስኪ ይህ ሥርዓተ ምንኩስና ከእኔ በኋላ ይቀራል ወይስ ይቀጥላል የሚለውን ከእግዚአብሔር ጠይቅልኝ?" አለው።
አባ ጳውሊም በጸሎት እግዚአብሔርን ጠየቀለት፡ ከጸሎቱ በኋላ የአባ ጳውሊ ገጽ በደስታ ተመላ። አባ እንጦንስም ፦ "ምን አየህ?" ብሎ ጠየቀው:: አባ ጳውሊም "ነጫጭ ርግቦች አንተ እየመራኻቸው በጠፈር ላይ ሲሔዱ አየሁ" አለው። አባ እንጦንስም ፦ "ምንድን ናቸው? ሲል ጠየቀው። "በቆብ የምትወልዳቸው ንጹሐን ጻድቃን መነኮሳት ናቸው" አለው።
አባ እንጦንስም ፦ "እስኪ ደግመህ አመልክትልኝ" ብሎ ለመነው በድጋሚ ሲጸልይ የአባ ጳውሊ ፊቱ በሐዘን ተመላ። "ምነው?" ሲል አባ እንጦንስ አባ ጳውሊን ጠየቀው:: "በክንፋቸው ላይ ጥቁር መልክ የተቀላቀለባቸውን ርግቦች አየሁ" አለው። "እነዚህ ደግሞ ምንድን ናቸው?" ሲል አባ እንጦንስ ጠየቀ። "ጽድቅና ኃጢኣት እየቀላቀሉ የሚሠሩ መነኮስት ናቸው" አለው::
"እስኪ ለሦስተኛ ጊዜ አመልክትልኝ" አለና ለመነው:: አባ ጳውሊም ጸለየለት። በዚህ ጊዜ አባ ጳውሊ ድምፁን ከፍ አድርጐ ጮኾ አለቀሰ፡፡
አባ እንጦንስም ፦ "ምነው ምን ሆንክ?" አለው። "እንደ ቁራ ጠቁረው አየኋቸው" ሲል መለሰለት። "ምንድን ናቸው?" ቢለው "ሹመት ፈላጊዎች ፣ ገንዘብ ወዳጆች ፣ በጠዋቱ ከመኳንንቱ ጋር ለማዕድ የሚቀመጡ ፣ በፍጻሜ ዘመን የሚነሡ ኃጥኣን መነኮሳት ናቸው።" አለው። አባ እንጦንስም ፦ "ንስሐ ሳይገቡ በሞት እንዳይወስዳቸው እስኪ እግዚአብሔርን ለምንልኝ" አለው። የዚህ መልስ ግን ከአባ ጳውሊ አልመጣለትም።
† † †
በትግራይ ክልል የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቀኖና እና ሥርዓት ውጪ ሕገ ወጥ የኤጲስ ቆጶሳት ሹመት ዛሬ ሐምሌ 16 ቀን 2015 ዓ.ም አከናወኑ።
ትግራይ ባሉ አባቶች "መንበረ ሰላማ" ከመሰየም ጀምሮ ከሕገ ቤተ ክርስቲያን ያፈነገጡ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ በተደጋጋሚ የሰላምና የውይይት ጥሪ ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል።
በትግራይ የሚገኙ "ጳጳሳት" ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ በርዕሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ገዳም የሕገ ወጥ ሢመት "የአስኬማ ጸሎት" እያደረጉ መሆኑ ተዘገበ !
ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም አንድነት ሚዲያ ( ባሕር ዳር - ኢትዮጵያ)
በብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ ፣ በብፁዕ አቡነ መርሐክርስቶስ ፣ በብፁዕ አቡነ መቃርዮስ እና በብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሚመራው እና በቅዱስ ፍሬምናጦስ ስም የሚነግደው ሕገ ወጥ ቡድን በዛሬው ዕለት በድፍረት ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን በመጣስ መረጥኳቸው ላላቸው መነኮሳት "የአስኬማ ጸሎት እያካሄደ እንደሚገኝ የትግራይ ቲቪ ካሰራጨው መረጃ ለመረዳት ተችሏል።
የ"አስኬማ ጸሎት" በሚል እያከናወኑት በሚገኘው ሥርዓት ላይ መንግስታዊው የትግራይ ቲቪ የቀጥታ ሥርጭት ሽፋን እየሰጠው የሚገኝ ሲሆን በቡድኑ መሪ በብፁዕ አቡነ ኢሳይያስ አማካይነት እና በሌሎች ሊቃነ ጳጳሳት ተባባሪነት ሕገ ወጥ ሢመቱ እየተከናወነ መሆኑ ታይቷል።
በትግራይ የሚገኙ ሊቃነ ጳጳሳት ፖለቲከኞች እንኳ ምርጫቸው ያደረጉት የሰላም እና የይቅርታ መንገድ በመርገጥ ፍቅረ ሢመት ያደረባቸው መነኮሳትን በመሰብሰብ የጨረቃ ሢመት ለማድረግ እያደረጉት ያለው ጥድፍያ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን መከፋፈል በላይ አደጋው የከፋ ነው፡፡ የትግራይ ቲቪን ዋቢ አድርጎ የዘገበው ተሚማ ነው፡፡
አንድነት ሚዲያ ( ባሕር ዳር - ኢትዮጵያ)
ሐምሌ 15/2015 ዓ.ም
✝የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሰረት እያስተገበሩ የሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በዛሬው ዕለት ማጠቃለያ ምዘና አሰጠ።
✝የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበራችሁ ያላችሁ በሙሉ የሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ምዘና የፊታችን ሀምሌ 9/2015 ዓ/ም ይሰጣል።
✅ለአንደኛ ክፍል ጥዋት 2:00 እስከ 3:30
✅ሁለተኛ ክፍል 3:30 እስከ 5 ሰዓት
✅ሰባተኛ ክፍል ከቀኑ 7:30 እስከ 9:00
✅ አራተኛ ክፍል በተመሳሳይ ከሰባተኛ ክፍል ሰዓት ጋር ይሰጣል።
በእዚህ መሰረት ምዘናው የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ከዎዲሁ እንድትዘጋጁ ስንል እናሳዉቃለን።
ለምዘና ወደ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የተመደባችሁ መዛኞች በሰዓት በመገኘት ምዘናውን እድትሰጡ እና የምዘናውን ሪፖርት ለየምድብ አንድነቶች እንድታሳውቁ።
የፈተና ወረቀት የተላከ በመሆኑ ከምድብ አንድነቶች ከወዲሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
.................................................
📹 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
🔸የክብረ በዓል ጥሪ ለህዝበ ክርስቲያን በሙሉ
እነሆ ሐምሌ 5 ፥ በቀበሌ 10 በደብረ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ወቅድስት አርሴማ አብያተ ክርስቲያን ፥ የቅዱሳን ሐዋርያት ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት በደመቀ ሁኔታ ይከበራል።
እርስዎም ቤተሰቦችዎ ጋር በመገኘት በዓሉን አክብረው በረከት እንዲያገኙ መንፈሳዊ ጥሪያችንን በአክብሮት እናስተላልፋለን።
✍ የደብሩ ሰበካ አስተዳደር ጽ/ቤት
........................................................
🔴LIVE በዓሉን በዩቲዩብ ገጻችን በቀጥታ ሥርጭት አምናስተላልፍ በመሆኑ ቤተሰብ ሆነው ይከታተሉን።
https://www.youtube.com/c/AndnetMedia
📹 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
✝የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በአዲሱ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበራችሁ ያላችሁ በሙሉ የሁለተኛው ወሰነ ትምህርት ማጠቃለያ ምዘና የፊታችን ሀምሌ 9/2015 ዓ/ም ይሰጣል።
✅ለአንደኛ ክፍል ጥዋት 2:00 እስከ 3:30
✅ሁለተኛ ክፍል 3:30 እስከ 5 ሰዓት
✅ሰባተኛ ክፍል ከቀኑ 7:30 እስከ 9:00
✅ አራተኛ ክፍል በተመሳሳይ ከሰባተኛ ክፍል ሰዓት ጋር ይሰጣል።
በእዚህ መሰረት ምዘናው የሚሰጥ መሆኑን አውቃችሁ ከዎዲሁ እንድትዘጋጁ ስንል እናሳዉቃለን።
ለምዘና ወደ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የተመደባችሁ መዛኞች በሰዓት በመገኘት ምዘናውን እድትሰጡ እና የምዘናውን ሪፖርት ለየምድብ አንድነቶች እንድታሳውቁ።
የፈተና ወረቀት የተላከ በመሆኑ ከምድብ አንድነቶች ከወዲሁ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
.................................................
📹 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ጉባኤ ቤት 33 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።
ሰኔ 24 ቀን 2015 ዓ.ም
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ጉባኤ ቤት 33 ደቀ መዛሙርትን አስመረቀ።
በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ አቡነ አብርሃም
የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ስራ አስኪያጅ ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የስብከተ ወንጌልና እና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ ተገኝተዋል።
በሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በብፁዕ አቡነ አብርሃም በ2010 ዓም እንደተመሠረተ የሚነገርለት የ፬ቱ ጉባኤያት ምስክር ጉባኤ በ2014 ዓም 23 ደቀመዛሙርት አስመርቋል።
ጉባኤው በዘንድሮ 2015 ዓ.ም ዓም በሐዲስ ኪዳን ትርጓሜ፣በብሉይ ኪዳይ ትርጓሜ እና በመጽሐፈ ሊቃውንት ያስተማራቸውን ደቀመዛሙርት ነው ያስመረቀው።
በዕለቱም ለተመራቂ ደቀመዛሙርት በብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ስራ አስኪያጅና የባህር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ እንዲሁም በብፁዕ አቡነ ማርቆስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሐዋርያዊ ተልዕኮ መምሪያ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ አባታዊ መመሪያ ሰጥተዋል።
.................................................
📹 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/የባሕርዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
