MediLab Info.
የዚህ ቻናል ዋናው አላማ፣ ለህብረተሰቡ አስፈላጊውን የህክምና አስተምሮት እና መልእክት እንዲሁም ለስራ ፈላጊዎች የቅጥር ማስታወቂያ በቀላሉ እንዲደርሳቸው ማድረግ ነው።
نمایش بیشتر439
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1130 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል (CPD Center) አቋቋመ።
**********
ሐምሌ 26/2015 ዓ፣ም፤ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ
የእንጅባራ ዩኒቨርስቲ ህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ለማቋቋም አስፈላጊ ግብዓቶችን በማሟላት ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቷል፡፡
በመሆኑም የጤና ሚኒስቴር ባወጣው መመሪያ መሰረት በደብረታቦር ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ እውቅና ሰጪ አማካኝነት ተገምግሞ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማቅረብ የሚያስችለዉን የእዉቅና ፈቃድ አግኝቷል።
የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የህክምና እና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ዲን ዶ/ር አብርሐም አማረ የማዕከሉ መቋቋም እንደ እንጅባራ ዩኒቨርሲቲ ብቻ ሳይሆን የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር እና አጎራባች ዞኖች ያለውን የሙያ ማጎልበቻ ችግር መቅረፍ የሚችል እና በአግባቡ የተደራጀ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
የእንጅባራ ዩንቨርስቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተከታታይ ሙያ ማጎልበቻ ማዕከል አስተባባሪ የሆኑት ወ/ሮ የውበምርት ሻረው በበኩላቸው ከዚህ ቀደም መሰል የሙያ ማጎልበቻ ማዕከል ባለመኖሩ ባለሞያዎች ወደተለያዩ አካባቢዎች ሄደው ይሰለጥኑ እንደነበር ጠቅሰው አሁን ላይ እዚህ በመከፈቱ አላስፈላጊ እንግልትን ከመቀነስ ባሻገር ለባለሙያዉ በሚፈልገው ጊዜ እና ቦታ ተደራሽ እንደሚሆን ተናግረዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር ፤ የሬሜዲያል ፈተና ያልወሰዱ ተማሪዎች ፈተናቸውን ከነሐሴ 23 – 26 ቀን 2015 ዓ.ም በኦንላይን እንደሚወስዱ አሳውቋል።
@healthinovation
የእንጅባራና አካባቢው የማህበረሰብ ሬዲዮ ጣቢያ (እንጅባራ ኤፍ ኤም 104.1) በዋና አዘጋጅነት፣ በከፍተኛ ሪፓርተርነት እና በቴክኒሻን የቅጥር ማስታወቂያ አውጥተቀል።
ለሬሜዲያል ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ ይፋ ሆነ‼️
=============================
በ2015 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲያችን የሬሚዲያል ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የቆያችሁ ተማሪዎች ማለፊያ ነጥብ:-
1ኛ.ለተፈጥሮ ሳይንስ የማለፊያ ነጥብ 200 መቶ እና በላይ
2ኛ. ለማህበራዊ ሳይንስ የማፊያ ነጥብ 150 እና በላይ
3ኛ. እንዲሁም ለአይነ ስውራን ደግሞ 100 እና በላይ መሆኑን እናሳስባለን።
#ObsinetGaruma👏
በሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና 99 ከ 100 ያስመዘገበችው የነቀምቴዋ የሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ተማሪ ለሁለተኛ ዲግሪዋ ሙሉ ስኮላርሺፕ እና በመረጠችው ካምፓስ እንድትቀጠር የስራ እድል ተመቻቸላት።
የሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ የወለጋ፣ ነቀምቴ ካምፓስ የነርሲንግ ዲፓርትመንት ተማሪ የሆነችው ኦብሲነት ገሩማ በሀገር አቀፉ የመውጫ ፈተና ከ100 ጥያቄ 99 ጥያቄዎችን በመመለስ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግባለች።
የሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዜዳንት ዶ/ር አበበ ገመቹ ፤ ተማሪዋ ባስመዘገበችው በሀገር ደረጃ ከፍተኛ ውጤት #ለነቀምቴ ካምፓስ እንዲሁም ለመላው የዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ የደስታ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ከዚህ በተጨማሪ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ለኦብሲነት ገሩማ ሁለተኛ ዲግሪዋን እንድትሰራ ሙሉ ስኮላርሺፕ እንዲሁም በመረጠችው ካምፓስ የስራ እድል እንደተመቻቸላት በይፋ አሳውቀዋል።
ማሳሰቢያ
“ከጥር 1/2015 ዓ.ም ምደባ ተሠጥቷቸው በተለያየ ምክንያት ወደተመደባችሁበት ሆስፒታል ያልሔዳችሁና የለቀቃችሁ ሠራተኞች አሁን ምደባ የተሠጠው በቀደመው ዝርዝር ስለሆነ የትራንስፖርት እና ለመሠል ወጭዎች እንዳትዳረጉ እናሳስባለን። የለቀቁ ሠራተኞች ዝርዝራቸውን እየተቀበልን ሲኾን ማንኛውም ሠራተኛም ወደተመደበበት ተቋም ሲሔድም በሐምሌ ወር የተጻፈ ክሊራንስ እንደሚያስፈልግ እናሳስባለን።”
- ጤና ቢሮ
ክልሉ ቋሚ ምደባ በሰጠው መሰረት በሜዲካል ላቦራቶሪ ቴክንሺያን ሰሜን ጎንደር የተመደብኩ ስሆን መቀየር የምትፈልጉ (አዊ ዞን ፣ ም/ጎጃም ) በውስጥ አናግሩኝ
❤ 1