cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

አልማዝየ ሰንቦ

በቀጥታ መረጃ መስጠት ለምትፈልጉ @almazyesenbo ብላችሁ ላኩልን‼

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
519
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ከኮሚንቱ Reply ኮሜንቱ 😂😂😂😂😂😂😂 መድፍ፣ ዙ_23፣ ሮኬት ቀላቅሎ የተኮሰ Reply ነው። እንግድህ ሴትዮዋ የወሎን ህዝብ እንዲህ ነው የምትንቀው እሷን ተከትላችሁ እንዘጭ እንዘጭ፣ እጧ እጢ፣ ጲሪሪሪሪ የምትሉ የ4ተኛ «ጨ» ክፍል ተማሪዎች የፖለቲካ ሳይንስ ትምህርት 8ተኛ «ቀ» ላይ ስለሆነ የሚጀመረው ተረጋጉ ለማለት እንወዳለን‼
نمایش همه...
#የአድሱ_ዞን_ጉዳይ❗ 🖊🖊🖍🖍🖍🖍 ለግዜው ምዕራብ ወሎ (ሊባል የታሰበው ምስራቅ ግዮን ነው) የተባለው ከደቡብ ወሎ ዞን ተቆርሶ ይመሰረታል የተባለው አድሱ ዞንን በተመለከተ የተደበቁ ነገሮችን ማጥራትና መጋፈጥ ያስፈልጋል። የተወሰኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ወረዳዎች ተወላጆች ተመካክረን አድሱ ዞን ስለሚያስከትለው መዘዝ ለመንግስትና ለህዝብ ማስገንዘብ ያስፈልጋል ብለን አምነናል። በዚሁ መሰረት ሀሳባችንና ስጋታችን እንደሚከተለው አቅርበናል። አድሱ ዞን ለመመሰረት ሀሳቡ መንሸራሸር ከጀመረ ቢያንስ 10 አመት አልፎታል። ጅምሩ ላይ ደቡብ ወሎ ዞን ስለሰፋ የአስተዳደርና የልማት ጥያቄዎችን በቀላሉ ለመፍታት እንድቻል ደቡብ ወሎ ዞን ለሁለት ይከፈል ከሚል ቅንነት የመነጨ ሀሳብ ነበር። ከለውጡ በህዋላ ግን ይህ ሀሳብ በተወሰኑ የቦረና ሊህቃን እና በክልሉ የሚሰሩ የጎጃም ባስልጣናት ተጠልፎ አለማውን 100% በሚባል መልኩ ስቷል። ይህን ዞን እነሱ በፈለጉት መልኩ ለማስፈፅ የአንድ ወይም የሁለት ወረዳዎች ሊህቃን በአካል እየተገኙ፣ በማህበራዊ ሚድያው ግሩፕ እየፈጠሩ በህቡዕ ማሴር ከጀመሩ ቆይተዋል። የነዚህ ሊህቃን ግቦች የሚከተሉት ናቸው። አደንኛ የአድሱ ዞን መቀመጫ መንደራቸው መውሰድና የዞን መዋቅርን ለግለሰባዊ ልማት መጠቀሚያና በመንግስታዊ ስልጣን ሽፋን የግል ፍላጎት ማስፈፀሚያ ማድረግ። ሁለትም አድሱ ዞን ሲፈጠር የምትገኝን ስልጣን መለቃቀም። ሶስተኛ አድስ የሚፈጠረውን ዞን በጎጃም ስነ ልቦና ቀርፆ ከወሎ እንዲፋታ ማድረግ ቀስ በቀስ ደግሞ ወሎየነትን ማክሰም ወሎን ማጥፋት ነው። በተለይም ይህ ሶስተኛው ሃሳባቸው አሁን አሁን እያበበ የመጣውን የወሎየነት ስነ ልቦና እንደ ማክሰሚያና ፀረ ወሎየነትን በወሎ አካባቢ መፍጠር የሚለውን ትልቅ ፕሮጀክት የክልሉ መንግስት ድጋፍ በማግኘቱ ከጀርባ ሁኖ የሚያግዘውና ለእውናዊነቱ በትልቁ የሚቋምጥለት ሁኗል። ይህ ቡድን መካነ-ሰላም፣ ሳይንትና ወግዲን ሙሉ በሙሉ ወስዶ ሌሎች ወረዳዎችን ደግሞ ለሱ በሚመቸው መልኩ እያፈረሰ አድስ ወረዳ እየፈጠረ የቋመጠላትን ዞን መፍጠር ነው። ለምሳሌ እንድፈርሱና እንድቆረሱ ከተፈረዳዎች ወረዳዎች መካከል ለጋንቦ፣ መቅደላ፣ ተንታና ከላላ ይገኙበታል (ከታች ያለውን የቡድኑን ካርታ ተመልከቱ)። በመሰረቱ በዚህ ሀገሪቱ ማጥ ውስጥ በገባችበት ወቅት አድስ ዞን (ያውም ለአንድ ወረዳ ሊህቃንን ብቻ ሲባል) መመስረት እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው ብለን እናምናለን። ይህ ጉዳይ ደቡብ ወሎ ዞንን ብቻ ሳይሆን አማራ ክልልን ጭምር ወደ ለየለት ትርምስ የሚወስድ ነው። የቦረና ሊህቃን ያልገባቸው ነገር እነሱ ጥቅማቸውን ለማስከበር በህቡዕ ከ5 አመት በላይ ሲመክሩ የሌላው ወረዳ ተወላጅ ቁጭ ብሎ ይጠብቀናል ብለው ማሰባቸው ነው። መቅደላ አንባ ዩኒቨርሲቲን በጉልበትና ባለስልጣናትን በማማለልና በማስፈራራት ለመውሰድ ሲሞክሩ የተፈጠረውን ነገር የረሱት ይመስላሉ። ለማንኛውም የቦረና ሊህቃን በህቡዕ በሚመክሩት መልኩ አድሱን ዞን ለመመስረት መሞከር በአካባቢው የለየለት ደም መፋሰስ እንድመጣ መፍቀድ ነው። ይህን ጉዳይ የሚመለከታቸው ወረዳዎች፣ የደቡብ ወሎ ዞን፣ አማራ ክልል እና የፌደራል መንግስቱ በደንብ ሊያስቡበት በአንክሮ ሊከታተሉት ይገባል። ስለዚህ የመጀርያው ነገር በዚህ ሰዓት አድስ ዞን አያስፈልግም። ህዝቡ ያለው የልማት ጥያቄ እንጅ አድስ ዞን ይመስረትልን የሚል ጥያቄ አይደለም። ሁለተኛ የዞኑ መመስረት አስፈላጊ ሆኖ ከተገኘ የዞኑ መቀመጫ መወሰን ያለበት በሚመለከታቸው በሁሉም ወረዳዎች ህዝብ ምርጫ (referendum) እንጅ ከ10 የማይበልጡ የአንድ ወረዳ ሊህቃን በፈለጉት ወይም በወሰኑት አይደለም። በመሰረቱ የአድሱ ዞን መቀመጫ ካልሆነች የተባለችው መካነሰላም ለአድሱ ዞን መቀጫነት ቀርቶ ለምርጫ እንኳ መታጨት የለባትም። ምክናየቱም: 1ኛ ጅኦግራፊያዊ አቀማመጧ ከምዕራብ ወረዳዎች ጠርዝ ላይ ነው። ስለዚህ ለየትኛውም ወረዳ አመች አይደለችም። 2ኛ) ከተማዋ ከፍተኛ የውሃ ችግር አለባት። እንኳን ዞን ከተማ ሁና ተጨማሪ ሰው ተጨምሮባት አሁን ኗሪዎቿ ውሃ የሚያገኙት በ15 ቀን አንድ ቀን ነው። ከዚህም በተጨማሪ በተፈጥሮ ሃብትና በቆዳ ስፋት ወረዳዋን ብዙ ወረዳዎች ይበልጧታል። ስለዚህ ከተማዋ ያለምንም ውድድርና ምርጫ ዋና ከተማ ልትሆን ቀርቶ ምርጫ ውስጥም መግባት የለባትም። እነሱ የሚሉት ድሮም አውራጃ ስለነበረች ብሎ ከተማዋ የተሻለ መሰረተ ልማት ስላላት ወዘተ የሚል ነው። ይህ ደግሞ እንደት እንደማይሰራ እናስረዳ። አውራጃነትን በተመለከተ ወረዒሉ፣ ተንታም አውራጃ ነበሩ። ስለዚህ አውራጃ በሚለው አመንክዮ እነዚህ ከተሞችም የአድሱ ዞን መቀመጫ መሆን አለባቸው ማለት ነው። ከተማዋ የለማች ነው የሚለው አመንክዮ ዞንነትን መሸከም የሚችሉ ብዙ ከተሞች አሉ። በተጫማሪም ዞን ከሆኑ በህዋላ መልማት ይችላሉ። ስለዚህ አድሱ ዞን ምስረታ በጥቂት ሊህቃን ተጠልፎ የብጥብጥ አጀንዳ ሊሆን ስለሆነ አራቱም የመንግስት እርከኖች ማለትም የሚመለከታቸው ወረዳዎች፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ አማራ ክልልና የፌደራሉ መንግስት ደም ከመፋሰሱ በፊት ነገሩን ትኩረት ሰጥተው ሊያዩትና መፍትሄ ሊሰጡት ይገባል። አልማዝየ ሰንቦ #ጉዳዩን_ትኩረት_ብትሰጡበት Office of the Prime Minister-Ethiopia Ministry of Peace የሰላም ሚኒስቴር Amhara National Regional council Amhara securityaffairs House of Peoples Representatives of FDRE Taye Dendea Aredo
نمایش همه...
ሆ ሆ የዛሬዉ ቀን ከምሳ በኋላ ከአንድ ጓደኛየ ከምሳ በኋላ የስልክ ጥሪ መጣልኝ፤ ብዙ ጊዜ ሰዉየዉ (ጓዴኛየ) ምሳ በልቶ ቡና እየጠጣ እኔን መልከፍ በኔ መዝናናት ደስ ይለዋልና ሊዝናናብኝ ፈልጎ እንደሆ ስለገባኝ የመጀመሪያ ጥሪዉን አላነሳሁለትም፡፡ ደገመ (አረ ጉድ ይሄ ሰዉየ አልተፋታኝም) ላጥ አድርጌ አነሳሁት፤ “ስሚ” አለኝ ወይየ አልኩት ቀዝቀዝ እንዲል ብየ “ዉታፍ ነቃይ ማለት ምን ማለት ነዉ?” አለኝ ቀብረር ብየ ድምፄን ካስተካከልኩ በኋላ “ዉታፍ ነቃይ ማለት ለገዥ መንግስት አመራሮች ማሽቋለጥ ዘይት ካልጠበስኩ የሚል ሁልጊዜ ስለነሱ ድጋፍ ብቻ የሚከራከር ማለት ነዉ” አልኩት “አታዉቂማ” አለኝ እንግድህ ጀመርከኝ አልኩት/ “ እዉነቴን ነዉ አታዉቂማ ዉታፍ ነቃይ ማለት በድሮ ጊዜ የሚለበስ መነፋንፍ ሱሪ ነበር እና ባለስልጣኖች እሱን ሱሪ ያለ ዉስጥ ሱሪ ይለበስ ስለነበር እና ሱሪዉ በመቀመጫቸዉ በኩል ስለሚወተፍ እሱን እየተከተለ የሚነቅል ማለት ነዉ” ብሎ ቀኔን በሳቅ ጀመረዉ ይሄዉ እስከ አሁን እየሳቅኩ ነዉ፡፡
نمایش همه...
ከአበርገሌና አካባቢዉ የተፈናቀሉ ህዝቦች በሰቆጣ ከተማ አሰቃቂ ህይወት እየገፉ ይገኛሉ፤ በትግራይ ወራሪ ሃይሎች ስጋት ከየአካባቢዉ የተፈናቀሉ የሰቆጣና ዋግኸምራ አካባቢ ዜጎች በሰቆጣ ከተማ የከተሙ ቢሆንም ህዝቡ በረሃብ መሞት ጀምሯል፡፡ መንግስት እስከ አሁን ድረስ ምንም ድጋፍ ያላደረገ ሲሆን ህይወታቸዉን እያቆዩ ያሉት አልፎ አልፎ ከተራድኦ ድርጅቶች በሚሰጥ ፕላምፕሌት ነዉ፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብን የሰበሰበዉ የአማራ ክልል መንግስትም ሆነ የፌድራል መንግስቱ ሰቆጣ ከተማ ለተፈናቀሉ ወገኖች ረሃብና ሞት አይመለከተኝም በሚል ዝም ጭጭ ብለዋል፡፡ በሌላ በኩል የትግራይ ወራሪ ሃይሎች ወደ ሰቆጣ ከተማ መጠጋታቸዉን ከነጋ ሰምተናል፤ በአካባቢዉ ያሉ የአማራ ልዩ ሃይልም ሆነ የመከላከያ ሰራዊት ትዕዛዝ አልተሰጠኝም በሚል ዝምታን መምረጣቸዉን እንደመልካም አጋጣሚ በመጠቀም ወደ ሰቆጣ ከተማ እየጠጠጉ ይገኛል፤ የሰቆጣ ከተማም ሰጋቱ ያንጃበባት በመሆኑ በአካባቢዉ ያለዉ ድባብ ደስ የማይል መሆኑን አረጋግጠናል፡፡
نمایش همه...
#ውድ_ተከታዮቼ‼ ፌስቡክን በብዙ የኢሜል ምልልስ ምንም አይነት Community Standardን የሚጥስ ፁሁፍ አለመፃፌንና የታገድኩትም በማስ ሪቦርት እንጂ ፁሁፌን ባለመገምገም መሆኑን ለማስረዳት ሞክሬያለሁ፤ እውነት ለመናገር ፅፈሃል የተባልኩት hat speach በፍፁም የጥላቻ ንግግር ሳይሆን ምክርና ሃሳብ የተንፀባረቀበት አስተያየት ነበር። የሆነው ሁኖ የማርክ ዙከምበርክ ካምፓኒ ቅሬታየን ተመልክቶ #ለ75_ቀን_የታገድኩትን እገዳ ከሰዓታት በኋላ እንደሚነሳልኝ ገልጦልኛል። በመሆኑም ወዳጆቼ/የኔዎቹ አፈሳሶዩዎቼ ሁሉ ዋናዋን መስኮት አልማዝየ ሰንቦ ን በመክፈት እግር በእግር እንድትከታተሉኝ ይሁን ብያለሁ። መሞንጨር ለፈለጋችሁም ሊንኩን ከፍታችሁ ኑና እንፈሳፈስማ አቦ፣ ወርቆቼዋ https://www.facebook.com/profile.php?id=100027822683707
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

#ወሎየው_ተሰብሰብ‼ 🎤📣📣 ✴✳✴✳✴✳ በአሁኑ ሰዓት ደስታችን ሙሉ ነው❓ በርግጥ ከነበርንበት የሰቆቃና የጨለማ ጊዜያ፣ ከተፈጠረብንና ከሚፈፀምብን የትግራይ ወራሪ ቡድን ዘረፋና ደፈራ እንዲሁም በህይወት የመኖር ዋስትና ማጣት፣ የመሰረተ ፍላጎት መብት መነጠቅ አንፃር ሲታይ በርግጥ ወሎየውን በሙሉ እንኳን ደስ ያለን ማለት እፈልጋለሁ። ከዚያስ? በጦርነቱ የደረሰብንን 🎯የፖለቲካ ቀውስ 🎯 የኢኮኖሚ ቀውስ 🎯 የማህበራዊና የስነ ልቦናዊ ቀውሶች እንዴት እናክማቼው? በሰላም የመኖር፣ እንደማንኛውም ኢትዮጲያዊ ሃብት የማፍራትና ለሃብታችን ዋስትና የማግኘት መብት እንጂ ልዩ ስጦታ አይደለም። መንግስት የሚገባንን ነጥቆ አሁን ሁሉም ነገር ከወደመ በኋላ ነፃነት እንዲናገኝ ትብብር አድርጓል፣ ከዚያስ በቂ ነው? ወሎ ለደረሰበት ውድመት ሁሉ በከፍተኛ ትኩረት ካሳ ያስፈልገዋል‼ በሁሉም መስክ በተደራጄ መንገድ ህዝባችን ወደ ነበረበት የተረጋጋ ህይወት የመመለስ ግዴታ አለበት ለዚህ ግልፅ የሆነ ምላሽ ከመንግስት እንዲሰጥና የተዘረፉ አንጡራ ሃብቶችን ማስመለስ፣ የወደሙ የብዙ የስራ እድል መፍጠሪያ ፍብሪካዎችን ስራ ማስጀመርና ለትግሉ አጋርና ተፋላሚ አካላቶች በግልፅ እውቅና መስጠትና የህዝባችንን የስነ ልቦና ቀውስ ማከም ከመንግስት ይጠበቃል‼ #ሌላው_ነገር_ይህ_ጊዜ_የወሎየው_መነጋገሪያ_ነው‼ ወሎየው ትልቅ የቤት ስራ ይኖረዋል፣ ይህ ሁሉ ግፍና መከራ፣ ይህ ሁሉ ሰቆቃ፣ ይህ ሁሉ ዝርፊያ ሰብዓዊ መብት ጥሰትና ግዲያ ወሎ ላይ ሲፈፀም 1) ከመንግስት ጋር አንገት ለአንገት ተናንቆ ህዝቡን አስቆጥቶ የሚመራ፣ ወያኔ ደ/ብርሃን ሲደርስና የፌድራል መንግስቱን ዙፋን ሲገዳደር ብቻ ሳይሆን ወልዲያ ስትያዝ የሚደራደር የፖለቲካ ኤሊት፣ ታዋቂ ሰው፣ ወሎየ የማህበረሰብ ክፍሉን የሚያስተባብር አክቲቪስት መንግስትን የሚያስፈራራና የሚገዳደር ሰው ለምን አጣን? 2) ወያኔ ከራያ እስከ ደሴ ለመድረስ ከ4 ወር በላይ የፈጀባትና ብዙ መስዋትነት የከፈለችው ወልዲያና ቦሩ ሜዳ ሁኖ ሳለ በመንግስት እንዝላልነትና ትኩረት ማጣት ደሴና ኮቻ ሲያዙና ሲዘረፉ የወሎ ህዝብ በተፈናቀለበትና ወደሚሸሽበት አካባቢ የወሎን መታወቂያ ይዞ መንቀሳቀስ እንደ ነውር በመቁጠር ወሎየው እንዳልታገለና መርቶ እንዳስገባ ሲቆጠር ሲንገላታ ነበር። ለምሳሌ ባ/ዳር፣ ደ/ብርሃን፣ የአዲስ አባባ ለመግባት በኦሮሚያ ክልል ዘንድ ወሎየውን ለማሸማቀቅና የተፈናቀሉ ሰዎችን አሰቃቂ በሆነ መንገድ ለመያዝ ሲሞከር ነበር። ለምን? ምን ጎድሎን ነው? 3) የወሎን ህዝብ ለመከፋፈልና ወሎ #የሚገባውን_የህዝብ_ጥቅም የሚጠይቁ #የማህበረሰብ_አንቂዎችና የሲቪክ ማህበራትን በወሎ ህዝብ ዘንድ ጥርጣሬ እንዲፈጠርና የኦነግ ክንፍ በሚል በግለሰብም በማህበራትም ላይ ፈረጃ እየተሰጠ ወሎየው በአንድ እንዳይቆም አንድ ላይ እንዳይመክርና ወሎየ ሙስሊም ክርስቲያኑ በወሎ ባህልና አኗኗር መንፈስ ውስጥ ሁኖ እንዳይወያይ በከፍተኛ ሁኔታ ሲሰራ ነበር፤ እየተሰራም ነው፣ ከገዥው መንግስት ጀምሮ እስከ ፅንፈኛና ጫፈኛ አክቲቪስቶች “ወሎ” የሚለውን መጠሪያ የወራሪ ስም እያሉ የዲሞግራፊ ለውጥ ለማድረግና ይህንን የሚቃወሙና በግልፅ የሚናገሩ አካላት እስከ ግዲያ ዛቻ የደረሱ ቡድኖች ነበሩ፣ አሉ። ግን ችግሩ ሲመጣ መከራውና ማሳደዱ ሲመጣ በግልፅ የወሎ ህዝብና ወሎየው ነው ሰለባ የሆነው‼ ዛሬስ ወሎየው እስላም ክርሰቲያኑ፣ ፕሮቴስታንት፣ ካቶሊኩ፣ አማኙም ኢ–አማኙም፣ ብልፅግናውም አብኑም፣ ቅንጂቱም፣ ኢዜማውም  በወሎየነት ጥላ ስር ተሰባስበህ ተደራጅተህ በአንዲነት ጥቅምህን ታስከብራለህ? ወይስ በነበረው መንገድ አጀንዳ እየሰጡህ ያተራምሱሃል? በግልፅ ተነጋግረህ ተቀራርበህ ልዩነትህን ደፍነህ ተባብረህ የደረሰብህን ስብራት ትጠግናለህ? ወይስ ሌላ ታማትራለህ? በአጠቃላይ ይህንን ጦርነት ከፍተኛ የሆነ ስብራት ቢያደርስብንም ክፍተታችንን ለመዝጋትና ለመመካከር እድል ፈጥሮልናል፣ የግድ የመጣብንን ችግር ወደ መልካም አጋጣሚ መቀየርና በጋራ መቆም አማራጭ የሌለው ተመራጭ ሁኖ ተገኝቷል‼ ስለሆነም የግታታ ዜማህን ትተህ ምንም የሌለ የማይገናኝ የአንተን መደራጀት የማይፈልግና በስልት ሊያዳክምህ የሚፈልግን ሴራ (እንትና የሚባለው ድርጅት፣ ማህበር፣ ግለሰብ ኦሮሞ ነው፣ የኦነግ ተላላኪ ነው፣ ዶ/ር አብይ የላከው ነው፣ የአማራን አንዲነት ሊከፋፍል የመጣ ነው) የሚል የተንኮል ወሬ ሲነሳልህ ሆይ ሆይ ማለት ሳይሆን ሰው ነህና እንዴት? እሱ ማን ነው? በየት በኩል ኦሮሞ፣ በየት በኩል ኦነግ ነው? ብለህ ጠይቅ? ጠላትህ በደካማ ጎንህ ገብቶ እንደ ጋሪ ለጉሞ እንዲነዳህ ሳትፈቅድ ወደፊት ወደ ኋላ፣ ወደ ታች ወደ ላይ ጠይቅ ተመልከት መርምር በራስህ አረጋግጥ፣ የላስታ ሰው ላስታ ነው‼ የራያ ሰው ራያ ነው‼ የመከና ሰላም ሰው የመካነ ሰላም ነው‼ የደሴ ሰው የደሴ ነው‼ የቃሉውም የቃሉ ሰው ነው‼ የአርጎባውም የአርጎባ ሰው ነው‼ የላሊበላም የላሊበላ ሰው ነው‼ ይህ ሁሉ ሲደመር ወሎየ እንጂ ኦሮሞ አይደለም፤ ወሎየውን የሚያፈናቅለው የሚገድለው ጫፈኛና ፅንፈኛ አማራዎች በሚናገሩት ቃላት አማራ ነህ በማለት እንጂ ኦሮሞ ነህ ተብሎ አይደለም። ስለሆነም የሚበጅህ ጉተታውን ትተህ ተሰባስበህ ምከር የሚጠቅምህ መቀራረቡ ነው። የጠላትን ወሬ፣ ወሎየ መስሎ/በወሎ ስሞች ሰርጎ በገባ የፌክ አካውንት መናወጥህን አቁም ቀጥ ትል ከሆነ ቀጥ በል፣ ደግነትህና የዋህነትህ የባህልህ እሴት መገለጫ እንጂ የመጎዳትና የመበተኛህ ምክናየት እንደ ጅልና ሞኝ ተታላይነት መቆጠሪያ ምልክት መሆን የለበትም‼ THIS IS THE TIME FOR CHANGE‼ © አልማዝየ ሰንቦ ለፈጣን መረጃ 👇👇👇 ▶የቴሌግራም ቻናል (Join) https://t.me/almazyesenbo ▶የፌስቡክ ፔጅ (Like & follow) https://www.facebook.com/wollofree/
نمایش همه...
አልማዝየ ሰንቦ

በቀጥታ መረጃ መስጠት ለምትፈልጉ @almazyesenbo ብላችሁ ላኩልን‼

#የሰብዓዊ_ድጋፍ_ጥሪ‼ የከለላ ልማት ማህበር በወረዳው ተዎላጆች የተቋቋመና የማህበረሰባችንን ማህበራዊ ችግር ለመፍታትና እንደተወላጅም ላስተማራቼው የማህበረሰብ ክፍል ድጋፍ ለማድረግ በአሁኑ ሰዓትም በወረዳችን ላይ ህዋሃት ወራሪ ቡድን በተለይም በልጓማና ቲርቲራ አካባቢ ህዋሃት ገብቶ ከፍተኛ የሆነ ሰብዓዊና ቁሳዊ ውድመት አድርሷል፣ ጤና ጣቢያዎች ተዘርፈዋል፣ የትምህርት ተቋማት ወድመዋል፤ በትግል ላይ ብዙ የወረዳችን ተዎላጅ ሚሊሻዎች ህዝባቸውን ለመጠበቅ ብለው ከወራሪ ቡድኑ ጋር ሲፋለሙ ተሰውተዋል። ጉዳት ለደረሰባቼው 1ኛ) የሰማዕታት ሚሊሻ ቤተሰቦችን ማቋቋምና ማገዝ፣ ልጆቻቼው በቋሚነትም ይሁን በጊዜያዊነት ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ፣ 2ኛ) ለጤና ተቋማት የመጀመሪያ ደረጃ ህክምና ርዳታ የሚያገለግሉ የህክምና ቁሳቁሶችን በቲርቲራ፣ ልጓማ፣ ጎርና ባከት ጤና ተቋማት ላይ በተቻለው መጠን ድጋፍ ለማድረግ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። በመሆኑም የሰማዕት ሚሊሻ ወገኖችን ለመደገፍና እንዲማሩ ለማድረግ ከታቻለም የጤና ተቋማትን አነስተኛ የሆኑ የመጀመሪያ ህክምና ርዳታን ለማድረግ ማንኛውም ሰብዓዊነት የሚሰማው በተለይም ደግሞ የአካባቢ ተወላጆች ርብርብና ድጋፋችሁ እጅግ አስፈላጊ ሁኗል። ሞራላዊና ዜግነታዊ ሃላፊነታችሁን ዋጋ ለከፈሉልን ወገኖች ድጋፍ ለማድረግ ትወጡ ዘንድ በከለላ ልማት ማህበር አመራሮች 1) በዶ/ር በላይ ደምሴ 2) በዶ/ር ሰሚር ካሳ 3) በአቶ ሞገስ አምደስላሴ ስም በጥምር በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000446583143 ተከፍቶ ወደ ስራ ተገብቷል። ሁሉም ሰው ካለበት ሁኖ ድጋፉን እንድታደርጉ ማህበሩ ጥሪውን ያስተላልፋል። #በውጭ_ሃገር_የምትኖሩ_ወገኖቻችን_በቀጥታ በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ Sofit Cod CBETETAA ብላችሁ መላክ ትችላላችሁ።
نمایش همه...
https://strawpoll.com/qc8hqg51s በፌስቡክ ፔጄ በምሰጠው መረጃ ምን አስተያየት አለዎት??
نمایش همه...
በፌስቡክ ፔጄ በምሰጠው መረጃ ምን አስተያየት አለዎት?? | StrawPoll.com

What's your opinion? Vote now: ትክክለኛና ጠቃሚ ስለሆነ ቀጥይበት, ፌስቡክ ዘግተሽ ብትጠፊ ይሻላል, የምትፅፊውም የምትይውም አይገባኝም...

የትግራይ ወራሪ ቡድን ከደሴና ኮቻ የዘረፈው ሃብት የትግራይ ክልል የ10 ዓመት በጀት አይመልስውም‼ መንግስት የሁኔታ ትንተና ሰርቶ፣ ወይም ከተሞቹ እንደሚያዙ ሲያውቅ/ወይም እንድያዙ ስለፈቀደ የህዝብንና የመንግስትን ሃብትና ንብረት ማሸሽ እየተቻለ በዝምታ ተዝረክርኮ በከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚገዙ የህዝብ መገልገያ ንብረቶች ሁሉ ሳይቀሩ ተጭነዋል፤ 👉 ከኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ ከ251 በላይ ኮንቴኔሮችን ጭኗል፤ 👉 ከጉና ትሬድንግ ኃ/የተ/የንግድ ማህበር ከ35 በላይ ተሳቢ ጤፍ ጭነዋል፣ 👉 ከኢንትዮጲያ ንግድ ባንክ ደሴ ዲስትሪክት ከየባንኮቹ የተሰበሰበ 1.4 billion ብር በካሽ ተቀምጦላቸው ነው የተዎጣው በጣም በሚገርም ሁኔታ ባገኘሁት መረጃ ወያኔ ደሴ ስትጠጋ ለደመወዝ በሚል ከ500 ሚሊየን በላይ ካሽ ንግድ ባንክ ጠይቆ ከአዲስ አበባ እንደመጣለት ሹክሹክታዎቼ ሹክ ብለውኛል። 👉 ደሴ ሆስፒታል እስከ 100ሚሊየን ብር የሚያወጣ መድሃኒት ተቀምጦ እንዲቆያቸው አይገቡም በሚል ነው። 👉 ኮቻ ሆስፒታል በመንግስት የግዥ አቅም የማይቻሉና በብዙ ሚሊየን ብር የሚያወጡ ማሽኖችን በልመና ከተለያዩ ተራድኦ ድርጅቶች ኬሻ አሸርጠው የለመኑትን የህዝብ ሃብትና ንብረት የተዘረፈው በመንግስት እዝላለነት ነው። ዛሬ ላይ ይህን ሁሉ የፖለቲካ ጥመትና ሽርሙጥና ረስተን ማግኘት ያለብንን መብትን ተነጥቆ ስለተሠጠን እየቦረቅን ነው። እኔ ጨንቆኛል ህዝቡ በራሱ ሃብትና ንብረቱን በትንሹም ቢሆን ከመጠበቅ ይልቅ አብሮ ሲዘርፍና ሲያዘረፍ ነበር። መንግስት እንዚህ ክስተቶች የተከሰቱት አውቆና ሆም ብሎ ወራሪ ቡድኑ ሃብት እንዲያገኝ ፈልጎ፣ ወይም ደግሞ የወራሪ ቡድኑን ጨካኝነትና አረመኔነት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለማሳየትና የወራሪ ቡድኑን ጭካኔ ለማሳየት ብሎ፣ ወይም ደግሞ ወራሪ ቡድኑን ወደ መሃል ሃገር አስገብቶ በደጀን መሃል የወሎን ህዝብ እያሰቃየ ሃብትና ንብቱን እየዘረፈ ስትራቴጂካል አካሄድን ለመጠቀም፣ ወይም ደግሞ የወራሪ ቡድኑ ታጣቂዎች የሃይል የበላይነቱን አግኝተው አሸንፈው ደሴና ኮቻን ተቆጣጠሩ በሚል በተለያዩ እይታዎች እንኳን ብናየው ሁሉንም ሴናሪዎች የዶ/ር አብይ መንግስት አብጠርጥሮ ያውቀዋል። እና በዚህ ልክ መዘላዘሉና መዝረክረኩ ችግሩ የማን ነበር ቢያስ ቀላል የሆኑ ካሽ ብሮችንና ትልልቅና ውድ የሆኑ ሃብቶችን ማሸሽ እየተቻለ ይህ ሁሉ ሃብትና ንብረት የሰው ነፍስ ለምን ፊዳ ሆነ? ጥያቄው ከባድ ነው፣ ከባዱን ጊዜ ጀምረነዋል‼ ደፍሮ የሚጠይቅም ያለ አይመስልም፣ መንግስትም ወራሪ ቡድኑ ያደረሰውን ውድመት ደረቱን ነፍቶ ዘገባ እየሰራ ነው፣ ሰምሮለሃል¡ ጠ/ሚ/ሩ በአስቸኳይ ግልፅ የሆነ ማብራሪያ ቢሰጡ፣ የደረሰውን ጉዳት የሚያጠና ከሁሉም አካላት የተካተቱበት ግብረ ሃይል ቢዋቀር፣ የተለቀቁ ከተሞችን የፀጥታ ሁኔታውን በአግባቡና በህግና ስነ ስርዓት እንዲመራ ቢደረግ ብዙ ጊዜ አለግባብ የሆኑ መስዋትነቶች ከወታደራዊው ፍልሚያው በኋላ በሴረኞችና በድል አጥቢያ አርበኞች ከተሞች ስርዓት አልባኛ እየሆኑ ሌላ ቀውስ ስለሚያስከትል፣ እስከ አሁን ያልተመደበው የትግራይ ክልል በጀት ጉዳት ለደረሰበት ለወሎና አካባቢ መመደብና በጀቱን በትክክል መሬት ላይ ቆጥሮ በመልሶ ግንባታ የወደመውን ጥፋት ሁሉ እንዲሟል ቢደረግ (ይህ በጥንቃቄ መመራት ያለበት የፌድራል መንግስቱ የሚመራው የመልሶ መቋቋም ግበረ ሃይል በየ ጊዜው ሪፖርት እያቀረበ የሚገመገም ቢቋቋም)፣ ነፃ የወጡ ከተሞችን የፀጥታ ሁኔታ የሚየስከብር በአካባቢው ያሉ ሚሊሻዎችና የፖሊስ አካላት እንዲያስከብሩት ቢደረግ መልካም ይሆናል። በአጠቃላይ ግን ወሎን በዚህ ልክ ውድመትን ጥፋት ያደረሰበት የትግራይ ወራሪ ቡድን በተግባርና የፌድራል የክልል ኘንግስቱ ደግሞ አውቀውም ይሁና ሳያውቁ በተወሳሰበ የፖለቲካ ግትልትልነት የተፈጠረ እዝላልነት ይመስለኛል። © አልማዝየ ሰንቦ ለፈጣን መረጃ ▶የቴሌግራም ቻናል (Join) https://t.me/almazyesenbo ▶የፌስቡክ ፔጅ (Like & follow) https://www.facebook.com/wollofree/
نمایش همه...
አልማዝየ ሰንቦ

በቀጥታ መረጃ መስጠት ለምትፈልጉ @almazyesenbo ብላችሁ ላኩልን‼