cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ከብራናው

@ከብራናው ቁም ነገር የምንይዝበት ግሩፕ ነው። 👉ታሪክን በሰፊው ✅ 👉ስለ ፍቅር ታሪክ ✅ 👉ጅንጀና ✅ 👉ጨዋታ እና ወሬ✅ እንደልባቹ ነፃ ግሩፕ 👉ስድቡ ❌ 👉ትረካ ✅ 👉ስለ መፅኃፍ @kebranaw 🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
375
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-47 روز
-1030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ጳጉሜን ጳጉሜን የሚለው ስያሜዋ “ሄፓጉሜኔ” ከሚለው የግሪክ ቃል የመጣ መሆኑን አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ተነግሯል፡፡ “ኤፓጉሜኔ” ማለት ጭማሪ ማለት ነው፡፡ በግእዝ ቋንቋችን ተውሳክ ማለት ነው፡፡ ተውሳክ ማለት ተጨማሪ ማለት ነው፡፡ “ወሰከ - ጨመረ” ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ነው፡፡ (ምንጭ መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ ወመዝገበ ቃላት ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ገጽ ፱፻፭)፡፡ ምዕራባዊያኑ ጳጉሜን ተጨማሪ ቀን አድርገዋታል፡፡ እኛ ግን የወር ተጨማሪ አድርገናታል፡፡ በጽርዕ ኤፓጉሜኔ ትባል እንጂ ሊቃውንት ግን ተረፍ ይሏታል፡፡ ጳጒሜን የአሮጌው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መንደርደሪያ ዕለት እንደሆነች የክርስቶስ ልደትም የዓመተ ፍዳ ማቆሚያ የዓመተ ምሕረት መጀመሪያ በመሆኑ ዕለታቸው ራሱ በተመሳሳይ ቀን ተቀምሮ ይውላል፡፡ የጳጉሜን ወር ‹‹የምሕረት ወር›› ስለመባሏ፡- ኢትዮጵያ በዓለም ብቸኛዋ የ፲፫ ወራት ጸጋ ባለቤት ስትሆን የጳጉሜን ወርም በኢትዮጵያውያን ዘንድ የምሕረት ወር ተብሎ ይታመናል። በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ጸሎት የሚያደርግበት ዕለተ ምጽአት የሚታሰብበት የምሕረት ወር መሆኑን ታስተምራለች፡፡ በተለይም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት መሠረት ምእመናኑ በጳጉሜን ጸበል በመጠመቅ ድኅነት በማግኘታቸው የምሕረት ወር መሆኑን ምእመናን ያብራራሉ፡፡
نمایش همه...
የጳጉሜን ወር በጸሎት በንስሓ ተወስነን ወደ አዲሱ ዓመት የምንሸጋገርባት ድልድይ ናት፡፡ ከዚህም የተነሳ እግዚአብሔር የፈቀደላቸው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ጸሎት በመጸለይ ጸበል በመጠመቅ ያስቧታል፡፡ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ካሉት ሁለት የፈቃድ አጽዋማት መካከል አንዱ በዚህ በጳጉሜን ወር የምንጾመው ሲሆን መሠረት የሚደረገውም ጾመ ዮዲት ነው፡፡ የዮዲት ጾም የሚባለውም እርሷ ስለ ጾመችው ነው፡፡ ይህን መሠረት አድርገው ሕዝቡ ሳይቀር “ጳጉሜን ዕድሜ ትሰጠናለች፤ በኋላም ታድነናለች” ብለው ጾም ይጾሙባታል፡፡ (ምንጭ-ቅዱስ መልከ ጸዴቅ ድርሳን)፤ በሀገራችንም ንግሥት ዘውዲቱ እና ምኒልክ የጾም ሥርዐት ይፈጽሙባት ነበር፡፡ ሌሎችም ሽማግሌዎችና ባልቴቶች አክብረው ይጾሙባታል፡፡ የጳጉሜንን አቆጣጠር አንዱ ከቀን ጋራ ሲደርገው፣ ሌለኛው ደግሞ ከወር ጋራ ቢያደርገውም በሁሉም አቆጣጠር ውስጥ ሕያዊት ሆና መገኘቷ የታወቀ ነው፡፡ የዐውደ ዓመት መሸጋገሪያ ናት፡፡ ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ መሸጋገሪያ ናት፡፡ ጳጉሜን የዓመቱ መጨረሻ ወር ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ ናት፡፡ ስለሆነም አዲሱ ዘመን የሰላም፣ የፍቅር፣ የአንድነት፣ የልማት፣ የመተሳሰብ ዘመን እንዲሆንልን በጾምና በጸሎት ማሰብ እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ነገረ ምጽ አት የሚታሰብባት ናት፡፡ የጳጉሜን ወር የነገረ ምጽአት የሚታሰብባት ስትሆን ምጽአት ማለት የጌታን መምጣት የሚያስረዳ በመሆኑም ቤተ ክርስቲያን የጌታን ምጽአት በዓመት ሁለት ጊዜ ታስታውሳለች፤ ይኸውም በጳጉሜን ወርና በጌታ ጾም እኩሌታ (በደብረ ዘይት) ነው። ቅዱስ ዳዊት ”እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል፤ ዝም አይልም፤ እሳት በፊቱ ይነዳል፤” እንዲል፤(መዝሙረ ዳዊት ፵፱ ፣ ፪-፬)፡፡ ይህ ስለ ነገረ ምጽአት ያስረዳል፡፡ ይህም ጳጉሜን ከአሮጌው ዓመት ወደ አዲሱ ዓመት፣ ከክረምት ወቅት ወደ ጸደይ ወቅት መሸጋገሪያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ከጊዜያዊው ወደ ዘላለማዊ፣ ከምድራዊ ወደ ሰማያዊ፣ ከዚህ ዓለም ወደ ወዲያኛው መሸጋገሪያ ናትና ነው፡፡ ጳጉሜን የክረምቱ ማብቂያ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም በመጨረሻው ዘመን መከራ የሚበዛበት የዚህ ዓለም ማብቂያ ናት፡፡ ወርኃ ጳጉሜን አዲሱን ዓመት ለመቀበል የዝግጅት ጊዜ እንደሆነች ሁሉ ምጽአትም ጻድቃን አዲሲቷን ምድር (መንግሥተ ሰማያትን) ለመውረስ ተዘጋጅተው “ኑ የአባቴ ብሩካን ዓለም ሳይፈጠር የተዘጋጀላችሁን የእግዚአብሔር መንግሥት ውረሱ” የሚባሉባት ቀን ናት፡፡ የጌታ አመጣጥ ሳይታሰብ ነውና በተሰጠን ጸጋ ቅዱስ አምላካችንን እያመሰገንን ተዘጋጅተን እንድንጠብቀው የድንግል ማርያም ልጅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ይርዳን፤ ቀጣዩ ዘመንም ቃሉን ፈጽመን መልካም ፍሬ የምናፈራበት ዓመት ይሁንልን፤ አሜን !!!
نمایش همه...
አዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሣሥ 6 ቀን 1978 ዓ.ም የወጣ አፄ ምኒልክን አንድ እንግሊዛዊ " ከጥቁርና ከነጭ ማን ይበልጣል ?" ሲል ይጠይቃቸዋል:: ምኒልክም " አስበህ እንደጠየቅከኝ አስቤ መልስ እሰጥሃለው " ብለው በቀጠሮ ይለያያሉ፡፡ ከዛም ሊቃውንቶቻቸውን ሰብስበው ለተጠየቀው ጥያቄ መልስ እንዲሰጡ ይጋብዟቸዋል፡፡ ለጊዜው ምንም መልስ አልተገኘም፡፡ በኃላ አለቃ ድንቄ የተባሉ ብልህና አዋቂ ሰው " አይቸገሩ ጃንሆይ ! መልሱን እኔ እሰጥዎታለሁ " አሏቸው፡፡ ምኒልክም በፅሞና ይጠብቋቸው ጀመር፡፡ አለቃ ድንቄም " ፈረንጁ ከጥቁርና ከነጭ ማን ይበልጣል አይደል ያለው ? ፍላጎቱ ይገባናል፡፡ እርስዎም በፈንታዎ " ከአይንህ ነጩ ነው ጥቁሩ የሚያይልህ ? " ብለው ይጠይቁት መልሱን ከዛ ያገኘዋል " አሏቸው፡፡ እውነትም ምኒልክ ለፈረንጁ ይህን ሲሉት በነገሩ ተደንቆ ዝም አለ፡፡ ምንጭ ፡ አዲስ ዘመን ጋዜጣ ታህሣሥ 6 ቀን 1978 ዓ.ም _ @kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
'ኡቡንቱ" አንድ የስነ ቅሪት ተመራማሪ ወደ ደቡብ አፍሪካ ገጠራማ መንደር ለስራ ባቀናበት ወቅት በአካባቢው ከሚኖሩ ህጻናት ጋር ወዳጅነት ይመሠርታል። አንድ ቀን ሕጻናቱን ለማስደሰት ሽልማት ያለው ጨዋታ ያዘጋጃል። በማንጎ የተሞላ አንድ ቅርጫት ከዛፍ ስር በማስቀመጥ ህጻናቶቹን ከዛፉ አንድ መቶ ሜትር እንዲርቁ አደረገ። ከዚያም እንዲህ አላቸው "እኔ ጀምሩ ስል ቀድሞ ከቅርጫቱ የደረሰ ሙሉውን ማንጎ ይበላል። " ህጻናቶቹም ጨዋታው ሲጀመር  ከጨዋታው ህግ ውጪ ያልተጠበቀ ነገር አደረጉ። ሁሉም እጅ ለእጅ ተያይዘው እኩል ወደ ቅርጫቱ ሮጡ። ዚያም አንድ ላይ በቅርጫቱ ውስጥ ያለውን ማንጎ በአሸናፊነት መንፈስ ተካፍለው መብላት ጀመሩ። የስነ ቅሪት ተመራማሪውም በመገረም "ለምን እንዲህ አደረጋቹ?" ሲል ጠየቃቸው። ሁሉም በአንድነት "ኡቡንቱ! " አሉት። በመቀጠል አንዱ ልጅ እንዲህ አለው "እንዴት ሌላው ሁሉ ልጅ ተከፍቶ አንድ ልጅ ብቻውን ይደሰታል? ይሄ ባህላችን አይደለም::" "ኡቡንቱ" የሚለው ቃል መሠረት የደቡብ አፍሪካው የዙሉ ማሕበረሰብ ሲሆን፤ ትርጓሜውም “ለመኖሬ ምክኒያቱ አንተ ነህ፤ ላንተም መኖር እኔ” የሚል ሰብዓዊነትን ያዘለ ፍልስፍና ነው። 👇👇👇 @kebranaw 📗📒📕 @kenranaw 📗📒📕
نمایش همه...
የዚህ ቤት ባለቤት ፥ ጥሩነሽ ዲባባ (በእውቀቱ ስዩም) የጠዋት እቅልፍን  ከነፍሴ በላይ እወዳለሁ፤ጫጫታ እጠየፋለሁ፤ አንዳንዴ  መላ ከተማውን “ ሳይለንት ሞድ “ ላይ ማድረግ ቢቻል እንዴት አሪፍ ነበር ብየ እመኛለሁ፤  የጥንት የጎጃም ደብተራዎች የነጋሪት ድምጽ የሚዘጋ ድግምት ነበራቸው ይባላል፤ በሚቀጥለው አገር ቤት ስሄድ የዚህን ምስጢር ማጣራት አለብኝ ፤ ዛሬ ጠዋት ፥ ከበድ ያለ የትርምስና የጫጫታ ደምጽ ቀሰቀሰኝ፤ ካልጋየ ላይ እየተቅመደመድሁ ተነስቼ ፤ እየተራገምኩ በሩን ከፈትኩት: : አምስት ጩጨዎች ናቸው፤ ከቁመታቸው እሚበላልጥ ዱላ ይዘዋል፤ እያንዳንዱ ዱላ ጫፉ ሁለት ሶስት ቆርኪ  ስለተንጠለጠለለት፥ በረንዳየን በወቀረው  ቁጥር  ባንዴ የከበሮና የጽናጽል ድምጽ ያወጣል ፤ ዋናው አስጨፋሪ ልጅ  ከሌሎች ልጆች በውፍረትም በቁመትም የሚብልጥ መዛጊያ የሚያክል ዱላ ይዟል፡: የዱላ አያያዛቸው ፥ከጭፈራው ጎን ለጎን  ህብረተሰቡን የማስቦካት አላማ እንዳላቸው ያሳብቃል፤ “ መጠናል ባመቱ አረ እንደምን ሰነበቱ” ሲል ጀመረ ባለመዛጊያው፥ አቡሽ! የዛሬ አመት እዚህ አገር አልነበርኩም፤ ጭፈራውን ለምን በቀደዳ ትጀምረዋለህ? ነውር አይደለም እንዴ? ጩጨዎቹ ግሳጼየን ከመ-ጤፍ ሳይቆጥሩ ሆታውን ተያያዙት ፤  ፤ አንደኛው ልጅ አይናፋር ብጤ ነው ፤  ሆታውን አይቀበልም፤ ዝምታውን  ለማካካስ በረንዳየን በዱላው በሀይል ይወቅጠዋል፤ “እዚያ ማዶ ! ሆ ! አንድ አበባ ! ሆ ! እዚህ ማዶ አንድ አበባ! ሆ የዚህ ቤት ጌታ ሆ! ጥሩነሽ ዲባባ” አለ  አስጨፋሪው፤ “ እኔ የቤቱ ተከራይ ነኝ ፤ ቢሆንም፤ ሙገሳውን ለባለቤቱ አስተላልፋለሁ” አልኩ፤ አስጨፋሪው በቃሉ የያዘው ጭፈራ ሲያልቅበት ፤ ከኪሱ  ቢልቦርድ እሚያክል ወረቀት አወጣ፤ “ በቃ! በቃ! እንኩዋን አደረሳችሁ፤ ዛሬ ኪሴ ውስጥ ገንዘብ ስለሌለ በሚቀጥለው አመት ተመለሱ “ ብየ ልገባ ስል፤ አስጨፋሪው ፤ “ በሞባይል ባንክ ትራንስፈር ልታረግልን ትችላለህ” አለኝ   ትውልዱን እየተራገምኩ፥ ወደ ቤት ገባሁና ተመልሼ   ወጣሁ፤ አስጨፋሪው የሰጠሁትን አስር ብር አገላብጦ በቅሬታ አይቶ ወደ ኪሱ ከጨመረ በሁዋላ ተከታዮቹን እየነዳ መውረድ ሲጀምር   “ እግረመንገዳችሁን ይቺን ይዛችሁልኝ ውረዱ “ አልሁና በረንዳየ ጥግ ላይ በግብዳ ብጫ ፌስታል ቁዋጥሬ ያስቀመጥኩትን ቆሻሻ ብድግ አድርጌ አቀበልኩዋቸው ፤ ሁለተኛውን ደረጃ ከወረዱ በሁዋላ አስጨፋሪው ቀና ብሎ እያየኝ እንዲህ ሲል ሰማሁት “ “ የወፍ ፋፋ የወፍ ፋፋ አንተ ሶየ ተነፋ “ ወደ ምኝታቤት ተመልሼ አልጋየ ላይ ስወጣ ፤ ሁለተኛው ዙር የጩጨ ባንድ  በረንዳየን መውቀጥ ጀምሯል፤ @kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
ስልክ ጢርርር 📱"አቤት" ☎️"አንተ ምናባህ ሆነህ ነው እንደዚህ የጠፋኸው!?"🙄 |ቃ ቃ ቃ ሽንኩርት ስትከትፍ| 📱"ምን ባክሽ ስራ እያሯሯጠኝ..." ☎️"ስልክ መደወል እስኪያቅትህ ድረስ ስራ በዝቶብህ?" 📱"ያው ታውቂው የለ የአዲስ ስራን ነገር...ዛሬ ግን በምን ትዝ ብዬሽ ደወልሽ?" ☎️"እእእ...ቅድም ሶደሬ ላይ የሆነ ፊልም እያየሁ እኮ... ልክ እንዳንተ ለፍላፊ የሆነ ካራክተር ሲመጣ ትዝ አልከኝና የታባቱ ጠፍቶ ይሆን ብዬ ደወልኩልህ..." |ትሽሽሽሽ የምታቁላላው ሽንኩርት ላይ ውሃ ጠብ ስታደርግ| 📱"እእእ እንደዛ ነው?" ☎️"አዎ" 📱"አለሁ ምን እሆናለሁ... የት ሆነሽ ነው አንቺ? አሁንም እዛው ቤት ነሽ አ?" ☎️"አዎ እዛው ነኝ...ምናባህ አንተ እኮ ልምጣ ልትል ይሆናል አታፍርም!" |ስታማስል...ሽሮ እየሰራች ነው| 📱"ኧረ አይደለም... ጨዋታውን ካመጣሺው ግን መጥቼ ባይሽ ደስ ይለኛል"🤷🏽‍♂️ ☎️"አ አ...አይቻልም" 📱"ለነገሩ ተዪው ... ልምጣ ብልም መንገዱ ራሱ ትዝ አይለኝም" ☎️"ወገኛ...በእንትና ሱቅ ጋር ታጥፈክ የእንትናን ፀጉርቤት እልፍ ብለክ ያለው ት/ቤት ጎን እንደሆነ ጠፍቶክ ነው?"🙄 📱"አሃ አሁን መጣልኝ... ከመጣሁ ስለቆየሁ ጠፍቶብኝ ነበር... እና በቃ ልምጣ አ?" ☎️"ኖ ኖ አይቻልም አልኩህ እኮ" 📱"ለነገሩ ተዪው...ይሄኔ ባልሽ ሶፋ ላይ ተከምሮ ኢሳት እያየ ነው" ☎️"ውይ የመቼህን?? ተፋታን እኮ... እሱም እዛው ሞያሌ ገባ እኔም ልጆቼን ለእናቴ ሰጥቼ ብቻዬን ፈልሰስ እልልሃለሁ" 📱"የምርሽን ነው?? በስማም የሚገርም ነው!.... እና በቃ ልከሰታ?" ☎️"አይቻልም አልኩህ እኮ ሰውዬ!" 📱"እሺ ገባኝ" ☎️"ምኑ ነው ሚገባህ??"🙄 📱"ደህንነቴን ለማረጋገጥ ብቻ እንደደወልሽ" ☎️"እና ሌላ ምንህን ፈልጌ እደውላለሁ!?ናፍቀኸኝ??" |ወጥ በማማሰያ ስትቀምስ አፏ ላይ ይሰማል| 📱"አልናፈቅኩሽም?" ☎️"እና ብትናፍቀኝስ??"🙄 📱"ከሰይጣን ፈጥኜ ልምጣ አ??" ☎️"ኦኦኦ ሰውዬ አይቻልም አልኩልህ እኮ!" 📱"እሺ" °°° ••• ☎️"ስማማ" 📱"ወዬ" ☎️"ያቺን የምትወዳትን ሽሮ እኮ እየቀመምኩ ነው" 📱"ጎበዝ" ☎️"ከሰብለ ባልትና እንጀራ ገዝቼ መጥቼ አቅርቤ እስክበላ ከደረስክ ትበላለህ" 📱"እና ልምጣ???"🧐 ☎️"...አዎ ግን ማደር አይቻልም...መጥተህ መመለስ ነው! በዛ ላይ ከብየዳ ቤት ቀጥታ ፍየል ፍየል እያልክ እንዳትመጣ... እዚህ ውሃ ስለጠፋች እዛው ታጥበህ ና!" 📱"እህህ... ሽሮ ልበላ ብቻ አይደል የምመጣው... በብብቴ አልጎርስ ወጥ አልጨልፍ " ☎️"አፈር ብላ!!🤬🤬🤬...ከፊቴ እንጀራ ልትቆርስ ስትዘረጋ አፍንጫዬ ብብትህን ማሽተቱ ይቀራል??" 📱"እእእ...እሺ በቃ ለቅለቅ ብዬ ስምዘገዘግ ነው ምመጣው" ☎️"ደግሞ ሽሮ መብያህን እንዳትረሳ!" 📱"እሱን ብረሳ ቀኜ ትርሳኝ" ☎️"ኧረ ሽሮ ያለቃሪያ ስለማትወድ ቃሪያውን ነው ያልኩህ አንተ ከውካዋ"🤦🏽‍♀️ 📱"ቃሪያውን ነው እንዴ? እሺ መንገድ ላይ ከሚመድቡት ገዝቼ ይዤ እመጣለሁ"🤦🏾‍♂️ ☎️ "ደግሞ የሚያቃጥለውን መርጠህ ግዛ... ጎመን ጎመን የሚል ይዘህ እንዳትመጣ!" 📱"እሺ" ☎️"ስማኝ ደግሞ" 📱"እ?" ☎️"ኮንዶ'ምም እንዳትረሳ!" *ስልክ ንግግሩን ሲያዳምጡ የነበሩ የቴሌ(ሳፋሪኮም) ኦፕሬተሮች*: @kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
ጠያቂ፦ ላምህ በቀን ምን ያህል ወተት ታመርታለች? ገበሬ፦ የቷን ነው ጥቁሯ ወይንስ ነጯ? ጠያቂ፦ ጥቁሯ ገበሬ፦ በቀን 2 ሊትር ጠያቂ፡-  ነጯስ? ገበሬ፦ በቀን 2 ሊትር ጠያቂ፦ የት ነው የሚተኙት? ገበሬ፦ ጥቁሯ ወይስ ነጯ? ጠያቂ፦ ጥቁሯ ገበሬ፦ በጋጣው ውስጥ ጠያቂ፦ እና ነጯንስ? ገበሬ፦ በጋጣው ውስጥ ጠያቂ፡ ላሞችህ ጤናማ ሆነው ይታያሉ ምን ትመግባቸዋለህ? ገበሬ፦ የቷን ጥቁሯ ወይንስ ነጯ? ጠያቂ፡ ጥቁሯ ገበሬ፦ ሳር ጠያቂ፡ እና ነጯስ? ገበሬ፦ ሳር ጠያቂ፦ (ተናደደ) ግን መልሱ አንድ ሆኖ ሳለ ጥቁሯ ወይ ነጯ እያልክ ለምን ትጠይቀኛለህ?? ገበሬ፦ ጥቁሯ የኔ ስለሆነች ነው። ጠያቂ፡- እና ነጯስ? ገበሬ፦ እሷም የኔ ናት ነው። 😂 @kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
ሮበርት ሙጋቤ በ1ድ ወቅት አውሮፓውያን በዚምባብዌ ግብረሰዶማዊነት አትፈቅድም ለምንድነው ሲሉት። "እኛ አፍሪካውያን ጋ እንደዛ አይነት ነገር አይሰራም ከፈለጋችሁ እዚ እንደፈለጋችሁ መሆን ትችላላችሁ እኛ ጋ ግን ይህን ግብረሰዶማዊነት ሲፈፅሙ ብናገኝ በሞት ነው ምንቀጣው አሳማ እንኳን ተቃራኒ ፆታ እንዳለ ያቃል እናንተ እንዴት አታቁም።" @kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
@kebranaw 📗📔📕
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
አንበሳ ራበው አሉ ቀበሮን ጠርቷት "የምበላው ነገር አምጪልኝ አለበለዚያ አንቺን እበላሻለሁ" አላት ቀበሮም አህያ ጋር ሄዳ "አንበሳ ሊያነግስህ ይፈልጋልና እንሂድ" አለችው አህያም አንበሳው ፊት ዘውዱን ሊደፋ ቆመ አንበሳው አፈፍ አድርጎ ሊይዘው ሲል የአህያውን ጆሮ ቆረጠለት:: አህያውም እንደምንም ብሎ አመለጠ "ቀበሮ ሆይ! ለምን ዋሸሺኝ ? አስበልተሺኝ ነበር እኮ" ብሎ ሲጠይቃት "ተው እንጂ አትሳሳት! አንበሳው እኮ ጆሮህን የቆረጠልህ ዘውዱን ሲደፋልህ ጆሮህ እንዳይከለክለው ሊያመቻችልህ ብሎ ነው:: በል አሁን ተነስ እንሂድ" ብላ አስማማችው አህያ በቀበሮዋ ሀሳብ ተስማምቶ ወደ አንበሳው ተመለሱ አንበሳው ግን አህያውን በድጋሚ ሊይዘው ሲሞክር ጭራውን ቆረጠለት ግን እንደምንም አመለጠው "በድጋሚ ሸወድሺኝ! አንበሳው እኮ ጭራዬን ቆረጠኝ" ሲል ጮኸባት "ተው እንጂ አትሳሳት! አንበሳው እኮ ጭራህን የቆረጠልህ የንግስና ወንበርህ ላይ ስትቀመጥ እንዳይቆረቁርህ ነው:: በል ተመልሰን እንሂድ" ብላው አግባባችው አሁን ግን አህያው አላመለጠም:: አንበሳው አፈፍ አድርጎ ያዘው አንበሳውም ቀበሮዋን "ጥሩ ስራ ነው የሰራሺው:: በይ እንግዲህ ከሆድ እቃው: ከአንጎሉ: ከጉበቱ: ከሳንባው: ከልቡ እየመተርሽ አጉርሺኝ! " ሲል አዘዛት ቀበሮውም እንደታዘዘችው አድርጋ ነገር ግን ልቡን እና አእምሮውን ራሷ ሰልቅጣ አጣጣመችው አንበሳውም "ልቡ እና አእምሮውስ የታለ?" ሲላት "ጌታዬ አንበሳ! አህያው ልብ እና አእምሮ ቢኖረው ኖሮ ጆሮው እና ጭራውን ቆርጠኸው ተመልሶ አይመጣም ነበር እኮ" ስትል መለሰችለት አንበሳውም "እሱን እንኳ ልክ ነሽ" በዘመላዕክ እንድሪያስ የቀረበ!!
نمایش همه...