cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ቅልቅል😂😍🤨😥😴🤔🙄😜😇🧒👧👵👴

በኔ channel ግጥም፣እውነተኛና ልቦለድ ፅሁፎች👩‍❤️‍💋‍👩፣ እንደፍላጎቶ ሁሉም አለ በchanneሉ፣ 😂በቅልቅል ዘና ፈታ ይበሉ፣ 😍😘ስወዶት leave አይበሉ። Creator at any comment @WithIhsan @qilqladmixture

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
209
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

አምላክ አለ! የትኛውም የዚህ አለም ችግር በአምላክህ ፊት እንደ ቁጫጭ ነው፤ ለምን ብቻህን ትታገላለህ? ያንተ ስራ እኮ ፈጣሪህን አጥብቀህ መጠየቅ እና የጠየከውን ለማግኘት በሙሉ አቅም መጣር ነው እንጂ መጨነቅ አይደለም እኮ። ወዳጄ ካንተ በላይ የሚያስብልህ አምላክ አለ! ሁሉንም ለርሱ አደራ ስጥ! ግሩም ዕለተ ሰንበት ተመኘንላችሁ🙏 @Inspire_Ethiopia የእናንተው ምርጥ ጓደኛ!
نمایش همه...
የዑመር ኢብኑልኸጣብ (ረዐ) 20ምርጥ ምክሮች፤ . 1. ‹የምትጠላውን ሰው ተጠንቀቅ፤› 2. ‹ብልጥ ሰው የእለት ስራዎቹን ከራሱ ጋር ይተሳሰባል፡፡ 3. ‹የዛሬን ስራ ለነገ አታሳድር፡፡› 4. ‹ከሰዎች ጥያቄ ተነስተህ አስተሳሰባቸውን መለካት ይቻላል፡፡› 5. ‹ለሌሎች ዳዕዋ በምታደርግበት ወቅት እራስህን አትርሳ፡፡› . 6. ‹ከዱንያ ትንሽን ብቻ ስትፈልግ ይበልጥ ነፃነትን እያገኘህ ትሄዳለህ፡፡› 7. ‹ወንጀል አለመስራት ከፀፀት ይሻላል፡፡› 8. ‹ታጋሽ ሁን፤ ትዕግስት የእምነት ምሶሶ ነችና፡፡› 9. ‹አሏህን ፈሪ መሆን እድለኛነት ነው፤ ከዚህ ውጭ ያለው እድለቢስ መሆን ነው፤› 10. ‹ወደ አኺራ የሄዱ ሰዎችን ንግግር ጠብቁ፤ እነርሱ የተናገሩት አሏህ እንዲናገሩ ያገራላቸውን ብቻ ነውና፡፡ . 11. ‹አሏህን ፍራ፤ እርሱ ሁሌም ህያው፤ ከርሱ ውጭ ያሉ ሁሉ ጠፊ እና አላቂ ናቸውና፡፡ 12. ‹ጥፋቴን በነገረኝ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡ 13. ‹እውቀትን ገብያት፤ ከዚያም ለሰዎች አስተምር፡፡› 14. ‹የተከበርክ፣ ታማኝ እና እውነተኛ ሁን፡፡› 15. ‹ትምክህተኛ ምሁር አትሁን፤ ትምክህተኛነት እና እውቀት አንድ ላይ አይሄዱምና፡፡ . 16. ‹ለዚህች አለም ፍቅር ያለው አዋቂ ባየህ ግዜ እውቀቱ አጠራጣሪ መሆኑን ተረዳ፡፡› 17. ‹ትንሽ አውርቶ ብዙ በሚሰራ ሰው ላይ የአሏህ እዝነት ይውረድ፡፡› 18. ‹ታማኝነት ማለት በምትሰራው፣ በተናገርከው እና በምታስበው ነገሮች ልዩነት አለመኖር ማለት ነው፡፡ 19. ‹የሰው ልጅ ምንም እንኳ እንደ ቀስት ቀጥ ያለ ስራ ቢሰራ ተቃውሞ አያጣውም፡፡› 20. ‹አዕምሮህ እንዲሰፋ ከፈለግክ፤ ከፈሪሀ አሏሆች ጋር ተቀመጥ፤› T.me/Alqasas_islamic
نمایش همه...
 😢 #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ #የመጨረሻዉ #ክፍል    ፊርዶስ ደወለች ስልኩን አነሳሁት ...ምንም አልተፈጠረም ለወሬ አቸኩሉ 😊   .....ፊርዶስ ጋር ሰላምታ ከተለዋወጥን ቡሀላ  አንድ ነገር ልጠይቅሽ ነበር አለችኝ ......እኔም ምን ነበር ፊርዱ አልኳት ........እሷም ምሳ የጠራችሁን ሁለታችን ነበር ግን አንድ ሰዉ አብሬ እናንተ ጋር ካልሄድኩ አለን ምን ትያለሽ ሂኩ .....እኔም ችግር የለም እሄዳለሁ ያለዉን አብራችሁ ኑ አልኳት ....ፊርዱም የዛሬዉ ቀን እኮ ለ ዙበይር  ታላቅ ቀን ነዉ ትናንት ቅዳሜ አዳር እንቅልፍ ሳይወስደዉ ነዉ ያደረዉ በደስታ ተባብለን ተሳስቀን ፊርዶስ አሁን ከቤት እየመጣን ነዉ ብላ ነገረችኝ፡፡ እኛም ተዘጋጅተን ነዉ እየጠበቅናቸዉ ያለነዉ...       ከ30 ደቂቃ ቡሀላ እቤት ደረሱ ፡፡ ወደ ቤት ሲገቡ ያየሁትን ማመን አቃተኝ የፊርዶስ እናት አብረዉ መጥተዋል ቅድም ደዉላ አንድ ሰዉ ይዤ ልምጣ ያለችዉ እናታቸዉን እንደሆነ ተገለፀልኝ ፡፡ የእኔ እናት እና አባት ብድግ ብለዉ ተቀበሉ ፊርዶስ የእኔን እናት ከእሷ እናት አስተዋወቀች አባቴንም ..የፊርዶስ እናት  እና የእኔ ቤተሰቦች ሲያወሩ ዛሬ አዲስ የተገናኙ አይመስሉም ነበር በጣም ደስ አለኝ ፡፡      ዙበይር ግን ፈርቶ ዝም ብሏን አባቴ አብሽር ተጨዋት አትፍራ እንጂ እያለዉ ነዉ፡፡  ከዛም ምሳችንን በልተን ጨረስን ቡናዉ ተፈልቶ ተመራርቀዉ ቡናዉን ተጠጥቶ ከጨረሱ ቡሀላ የዙበይር እናት እስኪ የመጀመሪያ ስለሆነ ማስታወሻ  ብለዉ የተጠቀለለ ስጦታ ሰጡን ስጦታዉ ለእናቴ የሚያምር ድርኢና ጎጎራ እና የሚያምር ጫማ ሲሆን ለአባቴ ደግሞ ሽቶ የዙበይር እናት አበረክተዉ ለምሳዉ ፕሮግራም አመስግነዉ ተመራርቀዉ ተለያዩ  እናቴም አባቴም በጣም ተደስተዉ ከአሁን ቡሀላ ምን ቀረ እንግዲህ ልጄ ያሰብሽዉን አላህ ያሳካልሽ ብለዉ አባቴም እናቴም መረቁኝ፡፡     ማታ ላይ ዙበይር ደወለልኝ ብዙ ነገሮችን አዉርተን ሂኩ መኖሪያ ቤቴን ያከራየሁትን ሰዎቹን ቤት እንዲፈልጉ ደዉየ ነግሪያቸዉ እሺ በቅርብ ቀን ለቀዉ እንደሚወጡ ነግረዉኛል ስለሆነም ተዘጋጂ ብሎ ነገረኝ፡፡ እኔም እሺ  አልኩት ዙበይርም ሂክማ እወድሻለሁ አላህ ሀላሌ ስላረገኝ የአንቺ በጣም ደስተኛ ነኝ አለኝ፡፡ እኔም እወድሀለሁ ዙበይር አንተ ማለት የሂወቴ ብሩህ ተስፋየ ነህ ጥሩ ልጅ ወልደን በዲነል ኢስላም ገንብተን እንደምናሳድግ ይታየኛል ኢንሻ አላህ አልኩት፡፡ ብዙ ደቂቃዎች አዉርተን ተሰነባብተን ወደ መኝታየ አመራሁ፡፡ የእኔ እናት እና የዙበይር እናት በስልክ ማዉራት መቀራረብ ጀምረዋል በጣም ደስተኛ ነኝ    ፊርዶስም እቤት መቼ ሽምግልና እንላክ ብላ ጠየቀችኝ ...ቤተሰቦቼን ጠይቄ የሚመችባቸዉን ቀን ቤተሰቦቼን ጠይቄ ለፊርዶስ ነገርኳት ዙበይርም መኖሪያ ቤቱ አስለቅቆ የቤት እቃ እያሟላ ነዉ ፡፡ በስልክ ቀን በቀን እያወራን ነዉ አልፎ አልፎ በአካል እንገናኛለን ግን ተሳስመን አናቅም የወደፊት መሆን ያለባቸዉን ተወያይተን እንለያያለን....    ሸምግልና የሚልኩበትን ቀን ቤተሰብ የሚመችባቸዉን ጠይቄ ለዙበይር ነገርኩት..... አስታዉሳለሁ ቅዳሜ ቀን የዙበይር አባትን አብሮ በመምጣት እስከ 10 የሚደርሱ ሽማግሌዎች መጥተዉ ልጅህን ለልጄ ተባብለዉ ለዙበይር ታጨሁ ...በዛዉም የሰርጉን ቀን ተቆርጦ ሽማግሌዎቹ ተመለሱ ....በጣም በሂወቴ ደስተኛ እየሆንኩ ነዉ የዙበይር የሰራዉ የመኖሪያ ቤት ሸጎሌ መንገድ 7 አካባቢ  ነዉ፡፡ ምን የራሱ ለወደፊት አብረን ልጅ ወልደን የምናሳድግበት ቤት ነዉ እንጂ    የሰርጉ ቀን ደረሰ ሰርጋችንንም .. ሁለታችንም ተነጋግረን ጦር ሀይሎች አካባቢ በሚገኘዉ  በኡማ ሆቴል ነበር ፡፡ ፊርዶስ ለኔ የመጀመሪያ ሚዜ ሆነች ሁለቱ ሚዜዎቼ ደሴ ከተማ ካሉት የአጎቴ ልጆች አረኩኝ  ..ፊርዶስ ለዙበይር መጀመሪያ የሱን ደስታ ያስቀደመች እህቱ ለእኔ ደግሞ የዲን እህቴም ጓደኛየም ..የወንድሟ ባለቤት(አይቷ)  ነኝ፡፡ ሰርጉ በሚያምር ዘመድ ጓደኛቼ በተገኙበት በአማረ ሁኔታ በኡማ ሆቴል ተፈፀመ፡፡ ፊርዶስ ጋር ከበፊቱ በበለጠ ከአገባሁም ቡሀላ ተቀራርበናል ደስ የሚል ሂወት እየመራሁ ነዉ፡፡  አንተን ያወቅኩ ለታ የዛን እለት ማታ ትዝ ይልሀል ያኔ ያወራሀኝ አንተ የወደድኩህ እኔ ያን ምገዛውን ፈጣሪዬን ትቼ ህጉን ተላልፌ ራሴን ሰዉቼ       ትዝ ይልሀል ያኔ🤔 መዉደድህ ሲያሰክረኝ ፍቅርህ እንዲያ ሲያንገላታኝ መውደድህ የእውነት ማፍቀርህ የእውነት ማውራትህ የእውነት ሁሉም ነገር እውነት መስሎ ያዘናጋኝ ትዝ ይልሀል ያኔ ከቤት  ተደብቄ ምክንያት ፈጥሬ የውሸት  ጋጋታ  አውርቼ ደርድሬ አንተ ጋር ለመምጣት ብዙ ቀባጥሬ   ትዝ ይልሃል ያኔ አሁን  አስብና ያን ሁሉ መሆኔ ፈገግ  እላለሁ አወይ ስልጣኔ   ለካ ፍቅር የሚሠምረው ፈክቶ  የሚጠነክረው ከአላህ  ጋር ሁኖ የተመሠረተ ነው በትላንቴ አፍራለሁ በዛኛው ዘመኔ      ግና መሀሪው ጌታዬ እስኪ ተቀበለኝ ፀፀት  ፍራቻዬን አዲሱን ህይወቴን ካንተ ጋ ልጀምር አንተ የገባህበት አያውቅም  ድንግርግር     ፊርዶስ ከእኛ ሰርግ አራት ወር ቡሀላ ስለታጨች  የምታገባበት ቀን ደርሷል ......እኔም ዙበይር ጋር ጥሩ የትዳር ሂወት መኖር ጀመርኩ፡፡ ሁሉም ወንድ አንድ አይደለም ለምን ሁሉም ሴት አንድ ስላላይደል...አንድ ሰዉ የምንቀርበዉ የምንወደዉ ሰዉ ሲሸዉደን መጥፎ ስራ ሲሰራብን ጥሩ ሰዉን ማመን ስለሚያቅተን ሂወታችን ህልማችን ዳግም  አይሳካም በሚል እኔ ዙበይርን ላጣዉ ነበር፡፡ የሰዉ ልጅ ነን እና እንሸወዳለን ግን ከተሸወድን ቡሀላ በዛ ነገር ላይ ቋሚ ወንጀለኛ መሆን የለብንም ወደ አላህ መመለስ መቻል አለብን፡፡ ዙበይር ጋር በደስታ በፍቅር እየኖርኩ ነዉ .. በቅርብ ቀን ደግሞ ፊርዶስ ልታገባ ነዉ እኔም የመጀመሪያ ሚዜየ አንቺ ነሽ ተዘጋጂ ብላኝ ዝግጅት ላይ ነኝ፡፡ እህቶቼ  ብዙ ሴቶች በቻት የሚያወሩ አሉ ቻት እና የተለያዩ group እንደ እኔ እንደሚጎዱ ከመቶ አንድ የሚቆጠሩ እንደዙበይር ያሉ ወንዶችን ለማግኘት በቻት ሳይሆን በዱአ ነዉ እንጂ በቻት አይደለም ቻት የዚና መስመር ነዉ እንጂ የትዳር መስመር የሚጀመረዉ በኒካህ ነዉ፡፡ አንዴ በራስሽ ፍቃድ ሂወትሽን አበላሽተሽ ፈጣሪሽን አታማሪ ወንድንም አታማሪ መጀመሪያ ብልጥ መሆን ያለብሽ አንቺ ነሽ ሴት ልጅ ክብር ነሽ ..ክብርሽን በማያቁ ወንዶች ክብርሽን አትነፈጊ   ታሪኬን እዚህ ላይ ጨረስኩኝ፡፡ #ተ........ #ፈ....... #ፀ....... #መ
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  đŸ˜˘ #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 2⃣4⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ     እኔም እናት እና አባቴ በዚህ ጉዳይ ሲጣሉ ሲቸካቸኩ አባቴ አይሆንም እያለ ሲጮህ ይህ ችክችክ ወደ ሌላ ወደ ቤተሰብ ፀብ እንዳይዞር እኔዉ እራሴ መፍታት ማስታረቅ አለብኝ ብየ ወሰንኩ ግን አባቴን ማሳመኑ አደራዉ እኔ ጋር እንደሆነ ተገነዘብኩኝ ...በራስ መተማመን ይዤ አባቴ የተናገረኝን ቢናገረኝ ላልቀየም ላላለቅስ የአላህ ቀድር ከሆነ በእኔ ምንም መለወጥ አልችልም ብየ አስቤ.. እራሴን አሳምኜ በሩን ስከፍተዉ እናት እና አባቴ መቸካቸካቸዉን አቁመዉ ሁለቱም ወደ እኔ ትኩረታቸዉን አደረጉ፡፡ ቤቱ ፀጥ አለ ማን ወሬ እንደሚጀምር አስፈራኝ ግን እኔ መጀመር እንዳለብኝ ተረዳሁ ...ወደ አባቴ ጎን ሂጄ ቁጭ አልኩኝ     አባቴ ምነዉ እናቴ ጋር አለመግባባት ምን ተፈጠረ አልኩት ነገሮችን እንዳልሰማሁ ሁኜ .....እሱም የምሰማዉ ነገር እዉነት ነዉ እንዴ??? አለኝ .....እኔም እዉነት ቢሆን ለአንተ ደስ አይልህም እንዴ?? አልኩት .....እሱም የጠየኩልሽን አጭር መልስ ንገሪኝ ከአፍሽ ልስማዉ አለኝ ...እኔም ከእኔ መነገሩ ጥቅም የለዉም እናቴም ነግረሀለች አዎ እዉነት ባቢ ዙበይርን ነገ እናንተን ላስተዋዉቅ ምሳ ጠርተነዋል ከነ እህቱ አልኩት ....አባቴም እኔ አባትሽ አይደለሁ እስከ አሁን እንዴት ሳትነግሪኝ እኔ የልጄን ሂወት መወሰን አልችልም ማለት ነዉ?? ቢሆንም ባይሆን እንዴት አንድ ቀን ሲቀረዉ ትነግሪኛለሽ ?? እኔ ከእናተ እርቄ የመንግስት መስሪያ ቤት የምሰራዉ አስተካክየ ቁርስ በልቼ ምሳ በቅጡ የማልበላዉ ለማን ብየ መሰለሽ ለአንድ ፍሬ ልጄ ለአንቺ ብየ እኮ ነዉ፡፡ በጣም ጥፋተኞች ናችሁ አዝናለሁ አለኝ፡፡  áŠ á‰Łá‰´ እዉነቱን ነዉ የቤተሰብ ፍቅር እርቆ  በአገኘዉ የወር ደመወዝ ነዉ የሚያስተዳድረን ግን ዙበይር ጋር እዚህ ደረጃ ለትዳር እንደርሳለን ብየ ትዝም ብሎኝ አያቅም..... ደግሞ ቀድሜ ብነግራቸዉ ይሆናል ብየ ባይሳካ ቤተሰቦቼ እኔን ምን ይጠረጥሩኛል ?? አጃጅሎ ተዋት ብለዉ ወይ እኔን አያምኑኝም ወይ እሱ ጋር ፀብ እንደሚኖር መዘንጋት የለብኝም፡፡    አሁን ያለኝ አማራጭ አባቴ ያለኝን የጠየቀኝን ከመመለስ እኔ ይቅርታ ብለዉ የተሻለ መሰለኝ፡፡ ከአባቴ ጎን ተነስቼ  ከእግሩ ሾር ተደፍቼ አባቴ ጥፋተኛ ነኝ ይቅር በለኝ እኔ እንደዚህ ይከፋሀል ብየ ትዝም አላለኝ ሰርፕራይዝ ላረግህ ነበር ሀሳቤ ይቅር በለኝ እኔ ይሄ ትዳር ይሆናል ብየ አላሰብኩትም ለእናቴ እንኳ የነገርኳት ከሶስት ቀን በፊት ነዉ እኔ ዙበይር የሂወት አጋሬ ይሆናል ብየ አስቤዉም አላቅ አዉፍ በለኝ ብየ አለቀስኩኝ አባቴ እግር ላይ ተደፍቼ፡፡     አረ ልጄዋ አታልቅሺ እኔ የአንቺን ለቅሶ አልፈልግም ሀገር ለሀገር የምዞረዉ አንቺ ደስተኛ እንድትሆኝ ነዉ አዉፍ ብየሻለሁ ብሎ ግንባሬን ሳመኝ እኔም በደስታ እሺ የነገዉን ምሳ ፕሮግራም እዚሁ ልትገኝ ተስማማህ?? አልኩት    አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ አለኝ ለእሱ ብዙ ነገር ጠየቀኝ መለስኩለት የጓደኛየ ወንድምም እንደሆነ..እናቴ እንደጠየቀችኝ ሀብቱን አይተሽ እንዳይሆን አለኝ፡፡ እኔም በጭራሽ ይሄ እንዳለዉ ያወኩት ቅርብ ቀን ነዉ እኔ መስፈርቴ ብር አይደለም ነበር እኔ ማንነቴን አዉቆ ስለተቀበለ ነዉ የመረጥኩት አልኩት     አባቴም ግን ልጄ እኔ የጠየቁኝ አሉ እሺ ከህመሟ ይሻላት እያልኩ መልሻለሁ  የነገዉን ምሳ ችግር የለም እንተዋወቃለን ፡፡ ግን ብትረጋጊ እና እኔ የጠየቁኝን ሰዎች አጥንተሽ ለምን መርጠሽ አታገቢም አለኝ እኔም ሳቅ እያልኩ አባቴ የመጡልኝ እኮ ማንነታቸዉን አላዉቅም ፀባያቸዉን ከኔ ምን እንደሚፈልጉ የማቀዉ የለኝም ዙበይር እኮ ከኔ የሚፈልገዉ ፍቅሩን እና የትዳር አጋሩ እንድሆን ነዉ፡፡ አንተን የጠየቁህ ለክብራቸዉ ለዘራቸዉ ሊጨነቁ ይችላሉ ደግሞ መቀራረብ እንጠናና በሚለዉ እኔም የእሱን ፀባይ ልወቅ ስል እሱም የኔን ፀባይ ልወቅ ሲል መቀራረብ አላህ ብዙ የከለከሉ ወንጀሎችን ልንሰራ እንችላለን ፡፡አንተ አስተዋወከን  ቀርባችሁ ተዋወቁ ነዉ የምትለን ..ቀርባችሁ ተዋወቁ  ማለት ከዚህ የባሰ ምን ይፈጠራል አባቴ አልኩት    እሱም ይሄ ቂርአት ብዙ አስተምሮሻል ብሎ እየሳቀ እሺ ይሁና ልጄ እኔ የምፈልገዉ አግብተሽም ደስታሽን ነዉ አለኝ ቤቱ በደስታ አባቴም እናቴም እኔም ተቃቀፍን የቅድሙ ጭቅጭቅ በጠረንቤዛ ዙሪያ ዉይይት በመሰለ አጀንዳ በሰላም በፍቅር ተፈታ ቤታችን በአንዴ ወደ ቤተሰብ ፍቅር ዞረ ፡፡     ቤተሰብም ጋር ሳያለቅሱ ተረጋግቶ ማዉራት ጥቅም አለዉ፡፡ ግን አንዳንድ እህቶቼ ይዘሀኝ ጥፋ...እሱን ካልዳራችሁኝ እታነቃለሁ በሂወት አታገኙኝም የሚሉ አሉ ይሄ አግባብ አይደለም ማንኛዉም ቤተሰብ ለልጆቹ ክፉ አይደለም ብቻ የትዳር ሂወት ማለት ሁለተኛ ሂወት ስለሆነ ቤተሰብም በትንሹም ቢሆን ጣልቃ መግባቱ አይቀሬ ነዉ፡፡ ትዳር ጋር አለመስማማት ቢኖር ተመልሰን የምንመጣዉ ወደ ቤተሰብ ነዉ፡፡     እሷ እና ጠቢቡ #እሷ👇 አምላክ ልጠይቅህ ፍቅር ግን ምንድነው ያኛውም ይሄኛውም ወደድኩሽ የሚለው የቱ ነው የወደደኝ የቱ ነው ያፈቀረኝ አንተው መልስልኝ እኔስ ግራ ገባኝ #ጠቢቡ👇 ልጄ ተባረኪ ጥሩ ጥያቄ ነው መውደድ በጣም ብዙ ማፍቀር ግን 1 ነው አንቺን የሚወዱሽ ተቆጥረው አያልቁም ያፈቀረሽ ሰው ግን ከ 1 እንኳን አይበልጥም #እሷ👇 እንዲ ከሆነማ አፈቀርኩሽ ያሉኝ ከ 1 እኮ ይበልጣሉ መጥተው የጠየቁኝ ከነዛ ሰው ሁሉ ተድያ እንዴት ልለየው የእውነት እፍቃሪ ምልክት ምንድነው #ጠቢቡ👇 በማስመሠል ዘመን ማመኑ ቢከብድም የእውነት ፍቅርን ግን መለየት አያቅትም ተወኝ ብትይውም ሊተውሽ ቢፈልግ ልቡ ግን አይፈቅድም ይሄንን ለማድረግ አንቺን እንዲተውሽ ፊት አንኳን ብትነሺው ፊትሽን ይተውና ልብሽን ነው የሚያየው አፈቀርኩሽ ብሎ ፅናቱ ካልታየ የውሸት ፍቅር ነው እለፊው ባላየ #ምንጭ_anu  á‰…á‹łáˆœ ተሻግረን እሁድን የወፎች ጫጫታ አስተጋባ ትናንት ጀምሮ እናቴ ጋር አብሬ ደፋ ቀና እያልን ነዉ ስድስት ሰአት ላይ ስራዉን አጠቃለልን ስድስት ተኩል ሲል ከፊርዶስ ስልክ ተደወለ.... ስልኩን አነሳሁት ..ፊርዶስም ማመን የማልችለዉን በስልክ ነገረችኝ..... ምን ተፈጥሮ ይሆን ?? የሂክማ ነገር አንዱን ፈተና ስጨርስ ሌላ የማትወጣዉ ፈተና ይመጣባታል ...    á‹¨áˆ‚ክማ ታሪክ በመጨረሻዉ ክፍል እና በማጠቃለያ ፁሁፋችን ይጠብቁን ... #Share_it👇 @AmruIslamic @AmruIslamic
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  đŸ˜˘ #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 2⃣3⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ     እኔም እናቴ ጎን ቁጭ ኡልኩኝ...ሁሉንም ልነግራት ጀመርኩ ሾለ ዙበይር እናቴ ዙበይር ማለት .......የፊርዶስ ታላቅ ወንድም ሾለ ፀባዩ እና እስከሚሰራዉ ሾል መርካቶ ሱቅ እንዳለዉ መኖሪያ ቤትም እንዳለዉ አከራይቶት እሱ ቤተሰብ ጋር እንደሚኖር ነገርኳት፡፡      እናቴም ጥሩ ግን ፊርዶስ በጣም ጥሩ ልጅ ናት ማሻ አላህ የነ እሱ ዘር ጋር አንቺ መጋብትሽ ደስ ይለኛል፡፡ ግን ልጄዋ አለችኝ በስስት እያየችኝ የወደድሽዉ ብር ስላለዉ ሱቅ ስላለዉ መኖሪያ ቤት ስላለዉ ነዉ ወይ ? .... አንቺ በብር አስበሽ ከሆነ አላህ ያይሻል አንቺ በብር የምትገዢ ሸቀጥ አይደለሽም እኔ የምፈልገዉ ኢማን ያለዉ አንቺን ወዶሽ በፍቅር ተሳስራችሁ ልጅ ወልዳችሁ የአንቺን ደስታ ማየት ነዉ እንጂ ገና እሱ ብር አለዉ ብለሽ አስበሽ የትዳር አጋር የመረጥሽዉ ከሆነ ልጄዋ ይቅርብሽ እኔ ዲን ያላቸዉ አብራችሁ ማደግ የምትችሉ ሁለት ሰዉ ቅርብ ቀን ልጅሽን ዳሪኝ ያሉኝ አሉ ልጄ እኔ የምፈልገዉ የአንቺን ደስታ እንጂ ወንድ ልጅ በብር ሀይል አግብቶሽ የሀብታም እስረኛ እንድትሆኝ አልፈልግም አለችኝ፡፡ .....እኔም እናቴን ምንም አላልኳት ወሬዋን አስጨረስኳት እዉነቷን ነዉ ትዳር ማለት ሁለተኛ ሂወት ማለት ነዉ እንጂ እንደ ሆቴል ገብቶ ተጠቅሞ የሚወጣበት ሂወት አይደለም፡፡ እናቴ ልክ ነሽ ግን ዙበይርን በብዙ ነገር ፈትኘዋለሁ እናቴ ብዙ ለአንቺ መንገሩ ጥሩ መስሎ ያልታዩኝ ሂወቶች ነበሩኝ..... ዙበይር ነዉ የተረዳኝ እሱ በብሩ የማይተማመን እኔ ለልሹ ይሄ ሁሉ እንዳለዉ የሰማሁት ቅርብ ቀን ነዉ ...የቀረበኝ ፍቅሩን ይዞ ትዳርን አስቦ እንጂ ይሄ ቤት አለኝ መርካቶ ሱቅ አለኝ ብሎ አንድ ቀን አዉርቶኝ አያቅም ማሚ በዲኑም ጎበዝ ነዉ ፡፡ የሚገርምሺ እንደ አንዳንድ ወንዶች አይደለም እናቱ ምሳ አዘጋጅተዉ ጠርተዉኝ አስተዋዉቆኛል፡፡ ለእናቱ የወደፊት ሚስቴ ናት ብሎ አሳዉቋል ማሚ እናቱም ወደዉኝ ስጦታ ሰጥተዉኛል ..ዙበይር የሚፈልገዉ እኔን ማጃጃል ሳይሆን ወደ በሀላል ወደ ትዳር ለመግባት ነዉ፡፡ እኔ ወድጀዋለሁ አንቺም ዉደጅልኝ ማሚ አልኳት፡፡   ....እናቴም እኔ አንቺን እወድሻለሁ የወደድሽዉንም እወዳለሁ የምጠይዉንም እጠላለሁ ግን አንድ ፍሬ ልጄ ነሽ ጥሩ ትዳር እንዲኖርሽ እፈልጋለሁ ድል ባለ ሰርግ ነዉ የምድርሽ ዙበይርን አምነሽበታል አለችኝ ...እኔም አዎ እናቴ ዙበይር ነዉ ምርጫየ ብየ ብዙ ነገሮችን አጫወትኳት ያዉ የሚደበቀዉ ያለ ሁኖ መቼም እናቴ ናት እና ሀይደር ጋር ያሳለፍኩትን እና በዛ ነገር ሀኪም ቤት የተኛሁበትን ሂወት እኔም እናቴም እንድታስታዉሰዉ አልፈልግም........ በመጨረሻም እናቴ እሺ አለችኝ ..እኔም ደስ አለኝ ደግሞ ደስታየን እናቴ እንዲህ ብላ ጨመረችልኝ፡፡ ዙበይር አንቺን ለእናቱ ካስተዋወቀሽ በጣም ጎበዝ አስተዋይ ልጅ ነዉ እኔንም እሁድ ምሳ አዘጋጅተን ዙበይርን አስተዋዉቂኝ እሁድ ንገሪዉና ምሳ እንጋብዘዉ   እህቱ ፊርዶስም አብረዉ ይምጡ  ...እኔም ነገ ጠዋት ደዉየ ለአባትሽ እቤት እንደመጣ እነግረዋለሁ .. አባትሽም ይወቀዉ ነገ ከሰአት መጥቶ ከአባትሽ ጋር እንመካከርበታለን  ብላ እናቴ አስደሰተችኝ እኔም እናቴ ጋር ተቃቅፈን ሁለታችንም በጣም ደስ አለን ፡፡ እሁድ ለመድረስ ገና አራት ቀናቶች አሉ፡፡ እናቴ ለአባቴ ደወለችለት መምጣት የሚመቸዉ ቅዳሜ እንደሆነ ነገራት፡፡ ቅዳሜ አደራ እንዳቀር ለአስቸኳይ ጉዳይ ነዉ የምትፈለገዉ አለችዉ እናቴ... .....አባቴም ለመስማት ጓጉቶ አሁን በስልክ ንገሪኝ ቢላት አይሆንም በስልክ ተነግሮ አያልቅም በአካል ስንገናኝ ነዉ የምነግርህ አለችዉ...    ወዳዉ መኝታ ቤት በመግባት ለዙበይር ደወልኩለት ሁሉንም ነገር ነገርኩት እና እናቴ እሁድ ምሳ ትዉዉቅ እናድርግ  ብላኛለች እሁድ ይመቸሀል ከነእህትህ አልኩት ......እሱም በደስታ እንዴት አይመቸኝ ቤተቦችሽን ለመተዋወቅ ዝግጁ ነኝ አለኝ፡፡ .......ከዛ ለፊርዶስ ደወልኩላት ብዙ አዉርተን ...እሁድ ስላት ወሬየን አቋርጣ ሂኩ ታዘብኩሽ አለችኝ ምን ሆንሽ ፊርዱ አልኳት እሷም የምሳ ግብዣዉን መጀመሪያ ለኔ ሳትነግሪ ለወንድሜ ነግረሽ ነዋ ከእኔ እና እሱ መጀመሪያ ያወቅሽዉ እኔን አይደል ብላኝ ተሳሳቅን፡፡ የማይደርስ የለም ነገ እሁድ ነዉ ዛሬ ቅዳሜ ላይ ነን ቅዳሜ ሙሉቀን ጀምረን እኔ እና እናቴ ለእሁዱ ባሌን የማስተዋዉቅበት የምሳ ፕሮግራም ደፋ ቀና እያልን ነዉ ..አባቴንም ሸዋ ሮቢት ስለሚኖር እሁድ እቤት ምሳ ተዘጋጅቷል ምክንያቱ ስትመጣ ይነገረሀል ብለን ቅድሚያ ስለነገርነዉ ቅዳሜ ማታ እቤት ገባ፡፡      እቤት እንደገባም ሾለ ነገዉ እሁዱ የምሳ ፕሮግራም እናቴ ነገረችዉ ግን አባቴ እና እናቴ በነገዉ ምሳ ላይ የተስማሙ አልመሰለኝም ፡፡ አባቴ ጮክ ብሎ ይሄማ መቼም አይሆንም እኔ ፈቅጄ ልጄን አልሰጥም አንቺ እኔ ሳልፈቅድ ትድሪያት እንደሆነ አያላሁ...እዚህ ቤት ወንዱ ወይ አንቺ ወይ እኔ እንሆናለን አትሰቢዉ እኔን የጠየቁኝ ሰዎች አሉ እንደዉም ለአንዱ ቃል ገብቸለታለሁ ትምህርቷን ስጨርስ ብየ አሁን ከህመሟ ከሻረች እኔም አንቺን አማክርሻለሁ እያልኩ ነበር በስራ ተወጣጥሬ ነዉ እንጂ ዛሬ ላማክርሽም ነበር ለአስቸኳይ ስትይኝ ጭራሽ ልጄ ታገባለች ብየ ትዝም አላለኝ፡፡ ወደድሽም ጠላሽም እኔ መቼም አልስማማም እኔ ለመረጥኩት ሰዉ ነዉ ልጄን የምድረዉ ...የነገዉም ምሳ ፕሮግራም እኔ አልኖርም እንደፈለጋችሁ ማረግ ትችላላችሁ...ተስማምቼ እሱን እኔ አልተዋወቅም፡፡ እናተ እሱ እቤት መጥቶ ብትተዋወቁ እኔ እና አንቺ ፍች ነዉ የሚለየን...እኔ ከሀገር ሌላ ሀገር በመንግስት ሾል የቤተሰብ ፍቅር ሳላይ በግዥ በሁቴል ምግብ የምኖረዉ አንቺ እና ልጄ እንድትደሰቱ እንዳትከፉ እንጂ ለልሴ መኖር መች አቃተኝ...ስለሆነም ይሄ የትዳር ነገር መቼም የማይሆን ነዉ ሲል እዉጭ ሁኜ ሰማሁት፡፡ የኔ ፈተና ብዙ ነዉ እኔም ከቤት ዉጭ ሁኜ ደንግጬ ቆምኩኝ...የማወራዉ ጠፋኝ ነገ ምሳ ዙበይርን ጠርቸዋለሁ....ትዳር ቤተሰብ ስቆ መርቆ ሲሰጥ ነዉ አለመግባባት ቢኖር ተመልሰን የምንመጣዉ ወደ ቤተሰብ ነዉ፡፡ ቤተሰብ ለወደደዉ ስቆ ደስተኛ ሁኖ ካልሰጠ ቡሀላ የሆነ ነገር ቢፈጠር ሌላ የቤተሰብ ጫና ይፈጠራል፡፡ ....የሂክማ ፈተና በዛ አሁን ደግሞ አባቷ እኔ ያልኩት ካልሆነ አታገባም አለ..ዙበይርም ምሳ ተጠርቷል ምን ይፈጠር ይሆን በቀጣዩ ክፍል እናየዋለን #Part 2⃣4⃣ ይ...........ቀ........... .........ጥ..........ላ................ል #Share_it👇 T..➳ @AmruIslamic   T..➳ @AmruIslamic
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  đŸ˜˘ #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 2⃣2⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ         እምባሺን ጥረጊ ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ በእጁ እምባየን ጠረገልኝ......አይን አይኔን እያየ ሂኩ ብቻ ዉደጅኝ አንቺን ማጣት አልፈልግም ..እኔ እስከማንነትሽ አንቺ ጋር ጥሩ የፍቅርሽ ተካፋይ የትዳር አጋሪ ልትሆኝ ዝግጁ ነሽ አለኝ...... ዙበይር እኔ እኮ ....እንዳጨርሺዉ ጨረስን እኮ እኔ የምፈልገዉ ፍቅርሽን ዲንሺን እንጂ ደምሽን አይደለም ሸይጧን አሳስቶሽ የሰራሽዉ ወንጀል ተዉበት አርገሻል...... ኢነሏሀ ዩሂቡ ተዋቢነ ወዩሂቡ ሙተጦሂሪን ተብሎ የለ አንድ ሰዉ ወንጀል ይሰራል ይሳሳታል ነብዩሏህ አደም ዐ.ሰ ተዉ ይሄን ፍሬ አትብላ ተብሎ በልቶ አይደል ከጀነት የተባረሩት....ሸይጧን በፊት ስሙ አብዱረህማን አልነበር አርሽን ሁሉንም ሰግዶበታል ስንዝር ያልሰገደበት አይገኝም ግን ኩራት ይዞት ከጌታዉ ተጣልቶ ሰዎችን ለማሳሳት ተነስቷል፡፡        ስለሆነም ሂክማ ወንጀል እንደሆነ እያወቅሽዉ ትሸወጃለሽ ስንት ሰዉ በአለበት ወንጀል ሳይቶብት በሰራዉ ወንጀል ሲመፃደቅ እየኖረ አይደል?? ስለሆነም አንቺ ቶብተሽ ወደ አላህ ተመልሰሻል ማታ ማታ ስታለቅሺ ዱአሽ እኔም ዱአ ሳደርግ የዱአ ዉጤት አላህ እኔ እና አንቺን አገናኘን ስለሆነም እኔ አንቺን በማሰብ መርካቶ በቅጥረኛ ሰራተኞች ነዉ ልብሱ ሲሸጥ የሚዉለዉ እሺ በይኝ እና እኔም ወደ ስራየ ጥቅልል ብየ ገብቼ ስራየን ልስራ አለኝ፡፡ ......እኔም የደስታ እምባ እያነባሁ እሺ ዙበይር እኔም እወድሀለሁ አፈቅርሀለሁ የወደፊት ሚስትህ ከአላህ ጋር እሆናለሁ አልኩት ...አላቅፈዉ አልስመዉ ገና ነዉ የእኔ እና እሱ ነገር ለመተቃቀፍ ለመሳሳም ኒካህ ያስፈልገናል፡፡ ዙበይር በጣም ደስ አለዉ የሚሆነዉ ጠፋዉ በደስታ ከእኔ ፈጠን እያለ መሄድ ጀመረ እንደገና ከሄደ ቡሀላ ቁሞ ጠበቀኝ ፡፡ እሱም አይስመኝ አያቅፈኝ ገና ነዉ ግድ ኒካህ ማረግ አለብን... ዙበይርም ይሄን ደስታየን ለፊርዶስ ልደዉልልላት አለኝ፡፡ እኔም አዎ ደዉልላት አልኩት ለፊርዶስ ደዉሎ ዛሬ ደስተኛ ነኝ ተሳካ እኮ አላት.... ፡ፊርዶስም ዙበይርም በጣም ተደሰቱ የሚያስቀኑ እህት እና ወንድም በጣም ደስ ሲሉ.... በአንቺ ክሶኛል በ ዘ አዶኒ ባርኮት ‹………………..….......…› አሁን ደስ ብሎኛል ተደስቻለሁ የልፋቴን ዋጋ ምላሽ አጊቻለሁ ከከበረው ሁሉ ትበልጭብኛለሽ ከቶ አልችልም ተመን ላወጣልሽ ወጥቴ ወርጃለሁ ብዬ ፍቅርሽን ግን አልተቻለኝም ማሸነፍ ልብሽን ቢደከምልሽ የሚገባሽ ፍጥረት ፀባዬ ሰናይ  ነሽ በእውነት ስሜቴን አክብሬ ሳልጎዳ ስሜትሽን ፍቅርን ፍለጋ ጠንቻለሁ ደጅሽን ሃሳቤ ነጉዶ ልቤ ብሎ አንቺን ዓይኖቼ ናፍቀው ለማየት ዓይንሽን ተስፋ አድርጌ አምኜው ፍቅርሽን ስጠብቅ ነበረ መምጫ ቀንሽን ዛሬ ግን ተሳካ ቀን ወጣልኝ በሩን ከፈተና ልብሽ ልቤን ታደገልኝ አሁን ደስ ብሎኛል ተደስቻለው ያ ሁሉ አለፈና ሰላም አጊቻለው ፍፁም የነፃ በደል ያልቆጠረ ከወርቅ ከአልማዝ እጂግ የከበረ ቸርነትን የሚያደርግ የማይሰስት የማያስመስል የሚጠላ ወረት የልቤን አይቶ ጥማት ረሃቤን አንቺን አመጣሽ አዝኖ ሃዘኔን እውነተኛ ፍቅር ፅናት ይጠይቃል በለሷን የጠበቀ ፍሬዋን ይበላል እድለኛ ነኝ እኔ አምላክ የረዳኝ ጥማቴን አይቶ አንቺን የሰጠኝ ተደስቻለሁ ፍቅሬ አሁን ደስ ብሎኛል ያከበርኩት ፍቅር ባንቺ ክሶኛል፡፡ ሂኩ ከአሁን ቡሀላ ጊዜ መስጠት አያስፈልግም እኔ እቤት ላሳዉቅ ነዉ አንቺምለቤተሰቦችሽ  አሳወቂ አለኝ ፡፡ እኔም እሺ አሳዉቃለሁ መቼ እናሳዉቅ?? አልኩት ...እሱም እኔ እንኳ እናቴ ታቃለች እናቴን በፊት አማክሪያታለሁ በህልሜ ሂክማ ስል አይደል የማድረዉ አለኝ ...ሁለታችንንም ተሳሳቅን.... አንቺ አሳዉቂ ለኔ ቀላሌ ነዉ ተባብለን ወደ ገርጂ የሚሄድ ታክሲ አስይዞኝ ተለያየን፡፡ በሒወቴ እንደዛሬዉ ቀን ተደስቼ አላቅም ዙበይር በጣም ወደድኩት ለካ ሁሉም ወንድ አንድ አይደለም...እያልኩ፡ሁሉንም ወንድ አንድ ነዉ እያልኩ ተስፋ ቆርጬ ነበር ግን እንደነዙበይር አይነት ወንዶች እንዳናገኝ እንደ ሀይደር ያሉ ወንዶች ግርዶ ሽፋን ይሆንብናል..እኔ ሂወቴ የሚስተካከል አይመስለኝም ነበር..ግን በዙበይር እንደገና ህልሜ ሊሳካ ሆነ አልሀምዱሊላህ... ታክሲ ላይ ሁኜ ሀሳብ ገባሁ የዛሬዋ ቀን ለኔ ተስፋ የሰነቀች ቀን ናት፡፡    መቅሪብ አካባቢ እቤቴ  ደርስኩ ስገባ እናቴን ሞቅ ያለ ሰላምታ ሰጥቼ ገብቼ ግንባሯን ሳምኳት፡፡ መቼም እናቶች በኛ ፊት ላይ ደስታን እና ሀዘንን ማንበብ ይችላሉ ........እንዴ ልጄ ዛሬ ምን ተገኘ ደስተኛ ትመስሊያለሽ አለችኝ  .....እኔም እናቴ መንገድ ላይ ዙበይር ጋር ያየችኝ መሰለኝ ፍርሀት ተሰማኝ ፊቴ በደስታ አብርቷል ገና እናቴን ሳልነግራት በፊቴ አወቀችዉ......   እኔም እንዴት አወቅሽ??? አልኳት .....እናቴም ዛሬ ልጄ የተገኘ ነገር አለ ማለት ነዉ ቀርበሽ እንደ እናት አዉርተሽኝ አታቂም እኮ ስገቢም ግንባሬን ከሳምሽኝ ቆየሽ ከመታመምሽ በፊት ነበር እኮ ግንባሬን የምስሚኝ ..... እስኪ ዛሬ የተገኘዉን ታጫዉችኛለሽ እርግጠኛ ነኝ አዲስ ነገር አለ ማለት ነዉ አለችኝ፡፡ ለነገሩ ዛሬ እቤት አገባቤ በጣም በደስታ ስለሆነ እናቴ ፊቴን አንብበዋለች ግን ዛሬ የደስታ ቀኔ ነዉ ዙበይርም ጋር ዛሬ እቤት እናሳዉቅ ተባብለን ነዉ የተለያየነዉ፡፡ .....እናቴን እሺ መቅሪቢን ሰግጄ አንድ የማማክርሽ ጉዳይ አለ እናወራለን ብየ መኝታ ክፍሌ ገብቼ መቅሪቢንሰግጄ ወደእናቴ ጋር ሳሎን ተመልሼ እናቴ ጎን ቁጭ አልኩኝ፡፡ ....እናቴም ፀጉሬን እየሻሸች ዛሬ ምን ተገኘ ልጄ??? አለችኝ .....እኔም ዝም ብየ ቀረሁ አፌ ላይ ወሬዉ እያለ መተንፈስ ተሳነኝ ....እናቴም አይዞሽ ወይ እኔ ልጀምርልሽ እንዴ አለችኝ እኔም ......... እሺ ጀምሪዉ አልኳት ......የትዳር ጥያቄ የመጣልሽ መሰለኝ ባልሳሳት አለችኝ ....እኔም እንዴ ማን ነገረሽ አልኳት .....እናቴ ሳቀች  ማንም አልነገኝ ግን ስመጪ ፊትሽ የደስ ደስ ይዞ ነበር የገባዉ ፡፡ ደግሞ ባለፈዉ በተከታታይ  አዳሬን ጥሩ ህልም አይቸልሻለሁ... ዛሬ  አዳሬንም ጥሩ ህልም አየሁ ህልሙ ተደጋገመብኝ....ያየሁትን ህልም  ዛሬ ማታ እነግርሻለሁ እያልኩ የእናትሽ ህልም አንቺዉ መጥተሽ ሳልነግርሽ ህልሙን ፈታሽዉ አለችኝ፡፡ እኔም እናቴን እቅፍ አርጌ ሳምኳት ...እናቴ በደንብ አዳምጪ ሁሉንም ልነግራት ጀመርኩ ሾለ ዙበይር እናቴ ዙበይር የሚባል ልጅ እንድንጋባ ጥያቄ አቅርቦልኛል ....... ዙበይር ማለት ....... #part 2⃣3⃣ #ይ.............#ቀ............... .........#ጥ...............#ላ.......................#ል #Share_it👇              T..➳ @AmruIslamic   T..➳ @AmruIslamic
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  đŸ˜˘ #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 2⃣1⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ   ወደ አምስት ሰአት አካባቢ ከቤት ልብሴን ቀያይሬ ፊርዶስ ጋር አብረን ጉዟችንን ቀጠልን ..ፊርዶስም ዛሬ ምሳ እኔ ነኝ የምጋብዝሽ ብላኝ መገናኛ አካባቢ የሚገኝ  ኢስላም ሬስቶራንት(ምግብ ቤት ) ገባን ስንገባ ግን ያየሁትን ማመን አቃተኝ አሁንም ዙበይርን ነበር ያገኘሁት፡፡ ፊርዶስም ዛሬ እስኪ ምሳ አንድ ላይ ሁነን ልጋብዛችሁ ብየ ነዉ አለችን፡፡ ...... ምሳችን አዘን በላን....ከዛም ምሳ በልተን ከምግብ ቤቱ ወጣን ፡፡ ሶስታችን ከመገናኛ ተነስተን እግራችን ወደ አመራን እየተጓዝን ነዉ...ትንሸ እንደሄድን ዙበይርም  ፊርዶስን እስኪ ሁለታችን የምናወራዉ ወሬ አለን አየር ትለቂልናለሽ አላት ...ፊርዱም ከእኔ ደብቀህ የምታወራዉ አለ ዙበይር እሺ ካልክ እገነጠላለሁ ብቻ የህዝብ ተወካዮች የፓርላማ ዉይይት እንዳታረጉት ብላ ገንጠል አለች     እኔ እና ዙበይር ብቻ ቀረን ሁለታችንም ተፋፈርን በዝምታ ብዙ መንገዶች ተጓዝን ማን ወሬ ይጀምር የተባባልን ይመስል አንዳችን የወሬን መጀመሪያ መክፈቻ ዙበይር ተነፈሰ .. ....... የዛሬዉ ምሳ እንዴት ነበር አለኝ .......እኔም አሪፍ ነዉ አላህ ይስጣት እህትህ ጋበዘችን አልኩት .....እሱም ግን እኔ መኖሬን ብታቂ  ፊርዶስ ብነግርሽ ትመጪ ነበር???? ብሎ ጠየቀኝ ....እኔም እንጃ ግን እህትህ የምትለኝን እሰማለሁ ፊርዶስን የማያት እንደ እህቴ ነዉ፡፡ ስለሆነም ፊርዶስን ያለችን እንቢ የምልበት ድፍረት የለኝም አልኩት፡፡ .......ማሻ አላህ እህቴን እኔም አንቺም እንወዳታለን ፊርዶስ á‰ á‰¤á‰°áˆ°á‰Ľ የመጣ ትዳር አለ ግን ሁሌ የምትለዉ እኔ ከማግባቴ በፊት ወንድሜን ዙበይርን ደግሼ ድሬዉ ነዉ የማገባዉ ትላለች የእኔ እና እሷ አስተዳደግ የተለየ ነዉ ተከታታይ ስለሆን ተዋደን ነዉ ያደግነዉ ..አሁንም ድረስ ወንድሞቼን ሁሉንም በአንድ አይን ብታይም እሷ ግን እኔ ጋር አስተዳደጋችን የተለየ ስለሆነ በጣም ነዉ የምንዋደደዉ ሚስጥር አደብቀኝም እኔም አልደብቃትም አለኝ፡፡ ......እኔም ፊርዶስን እንደ እህቴ ነዉ የማያት የምደብቃት የለኝም አልኩት፡፡ አሁን መፈራራት የለም ሁላችንም ግልፅ ሁነን እያወራን ነዉ፡፡ ዙበይርም ግን ይሄን  ጥሩ ፀባይ  ይዘሽ እስከአሁን እንዴት ነዉ እንደ እኔ በፍቅር የወደቀ አላስቸገረሽም እንዴ አለኝ እየቀለደ ....       እኔም ለዙበይር ምንም ላልደደብቀዉ ወስኛለሁ፡፡ እኔም የፈነዳ የመኪና ጎማ ይመስል ኡፍፍፍ ብየ #የት #ይደርሳል #የተባለዉን #ዛፍ #ቀበሌ #ቆረጠዉ፡፡ አልኩት፡፡ ዙበይርም ማለት አልገባኝም አለኝ .....እስከ አሁን የት እደርስ ነበር ግን በመሀል ዛፍም ያድጋል ብለሀዉ ሲቆረጥ ማደጉ ያቆማል ይደርቃል  የኔም ሂወት እንደዛ በለዉ አልኩት ..ዙበይርም እንዴ እንደ እሱ አይደለም ዛፍ ሲቆረጥ ሌላ ያወጣል ያቆጠቁጣል አለኝ ...እኔም የኔ አቆራረጥ እንዳያቆጠቁጥ ነዉ ብቻ በሂደት ያንን ማስረሻ እህትህን ሰጠኝ አልሀምዱሊላህ አልኩት ...እሱም በአላህ ተወኩል ነዉ አላህ ያለዉ ነዉ የሚሆነዉ ደግሞ ያሰብሽበት ግብ ለመድረስ የትናንት ትናንት ነዉ አሁን ያለሽዉ አሁን ላይ ነዉ ያለፈ ትዝታ ትርፉ ቁጭት ነዉ፡፡ የወደፊት ራዐይ ግን ተስፋ ነዉ አለኝ፡፡ .....እኔም ኢንሻ አላህ ግን እስከ አሁን አንተ ለምን አላገባህም ???? ማስተዳደሪያ ብርም አለህ ነጋዴ ነህ መኖሪ ቤትም አለህ አከራይተህ ነዉ የምትኖረዉ ለምን እስከ አሁን አላገባህም??? አልኩት     እሱም እኔ የምመኘዉ ዱአየ አላህ የምወዳትን ልጅ መጀመሪያ የወደድኳትን የትዳር አጋሬ አርግልኝ ነበር የምለዉ .....ግን ብዙ አመታት ማንም ሴት ልቤ ዉስጥ ገብቶ አያቅም ነበር....ግን ከትንሽ ወራት በፊት አንዲት ልጅ ወደድኩኝ ግን ምን ዋጋ አለዉ ፍቅሩ እኔ ጋር ብቻ ሆነ የአንድ ሰዉ መዉደድ ማለት በአንድ እጅ እንደማጨብጨብ ነዉ ዱአ አርጊልኝ ልጅቱ እንደምወዳት እንድትረዳኝ አለኝ፡፡ ......እኔም እንደዚህ ሲለኝ እንዴ እኔን ነዉ ወይስ ሌላ ናት ብየ ተወዛገብኩ ለምን እንደሚወደኝ አቃለሁ ደግሞ እኔ ጋር ሁኖ ሾለ ሌላ ሴት ያወራኝ መሰለኝ ....እኔም እስከ አሁን ስትወድ የመጀመሪያህ የሆነችዉን ለማግባት ወስነሀል ማለት ነዉ?? አልኩት እሱም አዎ ወስኛለሁ ልጅቱን እኮ ታቂያታለሽ አለኝ፡፡ ...እኔም ማን ናት አልኩኝ ፈጠን ብየ እሱም ገሞች አለኝ እኔም መገመት አልችልም አንተዉ ንገረኝ አልኩት ....እሱም ሂኩ አንቺ ነሽ ለምን አትረጂኝም አንቺ በፍልጥ ካልሆነ በፈሊጥ አይገባሽም ማለት ነዉ?? አለኝ ፈገግ እያለ.....      ግን አንተ እኔን የወደድክብኝ ምክንያት መስፈርቱ ምንድን ነዉ ዙበይር እንዴት የትዳር አጋርህ እንድሆን መረከኝ አልኩት... እሱም ሂኩ እኔ ከሆነሉም የወደድኩሽ ግልፅነትሽ እና ዲን ስላለሽ የዛሬወን ሳይሆን የነገዉን ሂወት የምታስቢ ፊርዶስ በጣም ትወድሻለች ታከብርሻለች ፊርዶስ የወደደችዉ ለኔ የወደፊት ትዳሬ ከሆነ ደስተኛ ነኝ ፍቅር መቼ የት እንዴት ከየት ወደ የት የማይባል ግዑዝ ነገር ነዉ አላህ ፍቅሬን በሀላሉ አድርጎ የትዳር አጋሬ ብትሆኝ እድለኛ ነኝ ሂኩ ......እኔም የደስታም የሀዘንም እንባ ከየት መጣ ሳይባል በአይኔ እንደምንጭ ዉሀ ኩልል እያለ ወረደ .... ሳለቅስ ዙበይር ደነገጠ ምን ሆንሽ መናገር የለብኝም ነበር እንዴ ምን ላርግ ተቸግሬ ነዉ ሂኩ አለኝ፡፡ ያለቀስኩት በእሱ መወደዴ የደስታ እምባ ሲሆን በተዘዋዋሪም እኔ ደግሞ ለትዳር ብቁ አይደለሁም ዙበይርን እኔም እወደዋለሁ ግን የኔ እንደማይሆን በማሰብ በዉሸት መዉደድ ጉድ የሰራኝ ሀይደር እዉነተኛ እኔን የሚወድ ሳገኝ  የተደበላለቀ ሁለት ስሜት ያለዉ እምባ ነዉ፡፡     ግን ዙበይርን ልዋሸዉ አልፈለኩም፡፡ ልነግረዉ ወሰንኩ እሱም አረ በፈጠረሽ አታልቅሺ አታስጨንቂኝ ይለኛል ዙበይር፡፡ .....እኔም እምባየን በክሪሜ አበስ አድርጌ ዙበይር እኔ ለአንተ አልሆንህም ሌላ ፈልግ እኔ አንተን ባገባህ ደስ ይለኝ ነበር ግን ....ብየ ልቀጥል ስል ...ሂክማ አሁን ያለነዉ ዛሬ ጋር ነዉ ሁሉንም ፊርዱ አስረድታኛለች ......እምባሺን ጥረጊ ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ በእጁ እምባየን ጠረገልኝ......አይን አይኔን እያየ ሂኩ ብቻ ዉደጅኝ አንቺን ማጣት አልፈልግም ዛሬ ቁርጤን ንገሪኝ ሂክማ እኔ እወድሻለሁ..እኔ እስከማንነትሽ ተቀብየ አንቺ ጋር ጥሩ የፍቅርሽ ተካፋይ የትዳር አጋሪ ልትሆኝ ዝግጁ ነሽ ...የአንቺን ልብሽ ዉስጥ ያለዉን ስሜት ንገሪኝ ...ዛሬ ዉሳኔሽን አሳዉቂኝ አለኝ.... ሂክማ የመጨረሻ ዉሳኔ ትሰጣለች ምን ትወስን ይሆን ?? በሚቀጥለዉ ክፍል እናያለን #part 2⃣2⃣ #ይ.............#ቀ............... .........#ጥ.............#ላ...................#ል #Share_it 👇         T..➳ @AmruIslamic   T..➳ @AmruIslamic
نمایش همه...
እዉነተኛ ታሪክ  đŸ˜˘ #አስለቃሽ #የቴሌግራም               #ፕሮፋይል       🌀 #Part 2⃣0⃣ ✍ ፀሀፊ #አሚር #ሰይድ         እኔም ቀጥታ ወደ ቤት ሄድኩኝ.......እቤቴም ደረስኩኝ ዙበይር ሲደዉልልኝ ስልክ አላነሳሁም ነበር....መልሳ ፊርዶስም ደወለች ግን ለእሷም ማንሳት አልፈለኩም መረጋጋት ስላለብኝ እንባየን ጠረኩኝ እና እቤቴ ቁርአኔን ቀርቼ ኢሻን ሰግጄ ተኛሁኝ፡፡  ከሱብሂ ቡሀላ ትንሽ ጋደም እንዳልኩኝ ጠዋት ላይ የፊርዶስ ስልክ ተደወለ ግን ማንሳቱን ፈራሁ ለምን ማታ ወንድሟን አስቀይሜዋለሁ.......ከአሁን ቡሀላ ከእኔ ተስፋ ቁረጥ ብየዋለሁ ግን እኔ ዙበይር ጠልቸዉ አይደለም በፊት የሰራሁት ሾል እኔን የበታች አርጌ ስለማይ እንጂ......    ለፊርዶስ ደግሞ እንደነገራት እርግጠኛ ነኝ ለምን ለእሷ ምንም ነገር አይደብቃትም እና....ፊርዶስ ደግማ ስደዉል ...አላስችለኝ አለ ለምን ፊርዶስ የኔ ምርጥ ጓደኛየ ባለዉለታየ ሀሳቤን ያካፈልኳት የሀሳቤ ተካፋየ ነች...ከዛም ስልኩን አነሳሁት ሰላማታ ከተለዋወጥን ቡሀላ ፊርዶስ እየቀለደች አሁን ስልክ አላነሳም ያልሽኝ እቤትሽ አካባቢ መሆኔን አይተሽኝ ነዉ እንዴ አለችኝ እኔም ወላሂ በይ ሰፈራችን መጥተሻል እንዴ አልኳት ....እሷም እኔ ግቢያችሁ በር ላይ ነኝ መቆርቆሩ ደብሮኝ ነዉ መጥተሽ ክፈችልኝ አለችኝ ...እኔም ምንም ጊዜ ሳልፈጅ ሂጄ የግቢዉን በር ስከፍተዉ ፊርዶስ ቁማለች ...ከዛ የተራራቁ ዘመዶች ይመስል ተቃቀፍን  ወደ ቤት ገባን እናቴ ጋር ሰላም ከተባባሉ ቡሀላ  ቁርስ አልበላሁም ነበር እናቴ ቁርስ አዘጋጅታ አብረን በላን... ቁርስ በልተን ከጨረስን ቡሀላ እናቴ ወደ ዉጭ ስትወጣ  ፊርዱም እየቀለደች ትናንት የት ለመድረስ ነዉ ያን ያህል እሩጫ እኔ ደግሞ ሂክማ የመቶ ሜትር ሩጫ አለባት እንዴ  እስከምል ድረስ የት ለመድረስ ነዉ እኔ መቼም አንደኛ ወጥተሽ ተሸልመሽ እንደሆነ ሽልማቱን ለማየት ነዉ የመጣሁት አለችኝ እየቀለደች፡፡ ወይ ፊርዶስ ቀልዷ በጣም አሳቀኝ እኔ የጠበኩት ለምን ዙበይርን እንደዛ ጥለሽዉ ተናግረሽዉ ትሄጃለሽ ብላ የምትቆጣኝ መስሎኝ አይኗን ለማየት እየፈራሁ ነበር፡፡ እኔም ሳቅ ብየ ዝም አልኳት ጥሩም ክፉም አልተናገርኩም.....መቼም ዙበይር እንደሚነግራት አልጠራጠርም... ፊርዶስም ሂክማ አንቺም እህቴ ነሽ ክፉሽን አልወድም ጥሩሽን ነዉ የምወደዉ...ዙበይር ወንድሜ ነዉ የእሱንም ክፉንም አልወድም ስለሆነም ትናንት የተፈጠረዉን ነገር ነግሮኛል ...የአንቺን ጉዳት አቃለሁ እሱ ደግሞ አንቺን ወዶሻል በዚህ የሚቀጥል ከሆነ  ከአንቺ በላይ እንደሚጎዳ ነዉ የሚታየኝ  ወንድሜ ደግሞ በፍቅር ሲንገላታ ሲያለቅስ ማየት አልፈልግም ....አንቺን መዉደዱን እንኳን  እናቴ ታቃለች ዙበይር በህልሙም ሂክማ ሲል ነዉ የሚያድረዉ፡፡ እናቴ ለምን አታገባም ብላ ጠይቀዋለች .. ....መሾመር ላይ ነኝ ዱአ አድርጊልኝ ነዉ ሁሌ መልሱ  ፡፡ እናቴም ቀን በቀን ስትጠይቀዉ አንቺን እንደሚወድ እና አንቺን ማግባት እንደሚፈልግ ነግሯታል፡፡ የትናንትናዉ የምሳ ግብዣ እናቴ ሂክማን ማወቅ አለብኝ አንቺን ለማወቅ ጓጉታ ሂክማን አስተዋዉቂኝ የወደፊት የልጄን ሚስት ብላኝነዉ..ስለሆነም አንቺም ወንድሜን ተረጂዉ እየወደደሽ አንቺን ቢያጣ አሁን ባለበት ሁኔታ ወንድሜ ሰዉ አይሆንም፡፡ ለወንድሜ እኔ እመሰክርለታለሁ ሴትን ልጅ ቀጥ ብሎ የማያይ ዲን ያለዉ ሰዉ አክባሪ ነዉ ..ስለሆነም ሁለታችሁም ተግባቡ ሂክማ ...አላህ ፅፎላችሁ ይሆናል ስለሆነም ወንድሜ ጋር አብራችሁ ብትኖሩ ደስ ይለኛል አንቺ ለኔ የልብ ጓደኛየ ለወንድሜ ደግሞ የትዳር አጋሩ ስትሆኝ ደስ አይልም እንዴ አለችኝ፡፡ ደግሞ ስለአለፈዉ ማንነትሽ ያቃል ስነግረዉ አዝኖ የብስ ፍቁሩ ጨመረበት ሂክማ አለችኝ.......       ካልደበረሽ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ ሂኩ አለችኝ.. .....እኔም እሺ ጠይቂኝ አልኳት ...በእስከአሁኑ ቆይታችሁ ዙበይርን ትወጅዋለሽ አትወጅዉም አለችኝ ......እኔም የምመልሰዉ አጣሁ በእርግጥ ዙበይርን ወድጀዋለሁ ግን ለወደፊት አብረን የምንሆን ስለማይመስለኝ እሱን ልርቅ ወስኛለሁ ለምን በሀይደር የሴትነቴን ክብር አጥቻለሁ በዙበይር ደግሞ ሁለተኛ ፍቅር በሚባል መጎዳት አልፈልግም ብየ ወስኛለሁ፡፡ .....ፊርዶስም መልሽልኝ እንጂ አለችኝ ........እኔም አዎ እወድዋለሁ ግን....ስል ወሬየን አቋረጠችኝ ሰባራ ነው ልቤ~ በፍጹም ቅንነት ከልብህ ቀርበኸኝ የ ሃሳብ ተካፋይ እህትህ አድርገኸኝ የሆዴን ብሶት በዝርዝር ስነግርህ ቁስልህ ስለሆነ ቁስሌ አመመህ ብዙ አይነት ፈተና ቢፈራረቅብኝም ያን ሁሉ መከራ ችየ አሳልፌም ግማሹን ታሪኬን በአፌ ስነግርህ ያለፍኩትን ዘመን ዳስሼ ሳወራህ ድንገት ሳላስበው ብሶት አስለቀሰኝ መሆኑ ሳይገባህ በአንተ ህይወት ውስጥ እራሴን አጊቼ አብሽሪ አልከኝ ማልቀሴ ቢመስልህ ላንተ ተከፍቼ በጥርሴ ደብቄ የያስኩት ሚስጥር ታሪኬ ሰፊ ነዉ ገብቶ ሲመዘብር ያለፍኩትን ህይወት ብነግርህ በዝርዝር እንዴት እንደሆነ ሰውን አምኖ ማጣት ቁልጭ ብሎ ታየኝ የልቤ ስብራት የኔ ነገር ብዙ ነው አንዴ ላጫውትህ ያንጀቴን የሆዴን ውስጤን ልንገርህ እናትና እህትህ ባለቤት ልሁንህ ሰባራውን ልቤን ከሰባራው ልብህ ልገጣጥመውና አንተም በኔ ድነህ እኔም ልሁን ደህና ሃሳቤን ዘርዝሬ ልነግርህ አልኩና ተመልሼ ተውኩት ደግሞ ፈራሁና ምን አልባት ምን አልባት ህልሜ ይከሽፍና ማገገሚያ ባጣስ በሰባራው ልቤ ዳግም እጎዳና .......እኔ የምፈልገዉ እሱን መዉደድሽን ብቻ ነዉ ..ሌላ ምክንያት አልፈልግም አለችኝ... ከተመቸሽ ዛሬ የምንሄድበት ቦታ አለኝ ፍቃደኛ ከሆንሽ እቤት ሾል ከሌለሽ እንሄድ አለችኝ....እኔም እሺ አልኳት ፊርዶስ የት ትወስደኝ ይሆን ??? አብረን በቀጣዩ ክፍል እናያለን #part 2⃣1⃣ ይ.............ቀ............... .........ጥ...............ላ.......................ል #Share👇 T..➳ @AmruIslamic   T..➳ @AmruIslamic
نمایش همه...