cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሀይማኖቴን ልወቅ (የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርት)

አንድ ጌታ አንድ ሀይማኖት አንዲት ጥምቀት ወደ ኤፌሶን ሰዎች ምዕ4:-5

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
250
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

18. የአጥቢያ ኮከብ የአጥቢያ ኮከብ የብርሃን ፋና ቅዱስ ጊዮርጊስ ፈጥነህ ቶሎ ና እኛን አሰማን 2 የሰላም ዜና አዝ.............. ለዘረንጦስ ለቲዮብስታ የሆንክላቸው መከታ ምድራዊ ንግስናን ንቀህ ሰማያዊ ክብር አገኘህ ሰዐለነ ጊዮርጊስ 2 ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ አዝ................. በሚያመልኳቸው ጣዖታት ያፈሩ ሰባው ነገስታት ድል ያረካቸው ጊዮርጊስ አማልደን ከኢየሱስ ሰዐለነ ጊዮርጊስ 2 ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ አዝ................ ስጋህ አመድ ሆኖ ቢዘራ በደብረ ይድራስ ተራራ የአመለከው አድኖሃል ሰባት አክሊላት ደፍተሀል ሰዐለነ ጊዮርጊስ 2 ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ አዝ................ ለዘረንጦስ ለቲዮብስታ የሆንክላቸው መከታ ምድራዊ ንግስናን ንቀህ ሰማያዊ ክብር አገኘህ ሰዐለነ ጊዮርጊስ 2 ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ @hayemanotenlewek @hayemanotenlewek
نمایش همه...
[_ከምን ዓይነት ነገር መላቀቅ እንዳለብህ ታዉቃለህ ?_] ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ ምድራዊ ምኞት ምን ያህል አስከፊ እንደሆነና እንዴት ከዚህ ነገር ነፃ መውጣት እንዳለብን እንዲህ በማለት ይመክሩናል፦ "ወዳጄ ከምድራዊ ምኞትህ ተላቀቅ ከምን አይነት ነገር መራቅ እንዳለብህ ታውቃለህ? ከምድራዊ ፍላጎት ከመሳሰሉት ራቅ ፍፁም የመንፈስ ነፃነት እንዲኖርህ ከፈለክ ከምድራዊ ምኞቶችህ ተላቀቅ። በእርጋታና በግልጽነት ላውጋህ እጅግ አብዝተህ የምትጨነቅባቸው ልብህን የተቆጣጠሩት ታላላቅ ምድራዊ ተስፋዎች አሉህ። እነኚህም ሃሳብህን ሁሉ ይቆጣጠሩታል ብቻህን በምቶንበት ጊዜ በምናብ ይመጡብሃል በምትተኛ ጊዜ ህልምህ ሁሉ ይህ ይሆናል ልትክዳቸው የማትችለው ነገር ግን የምታውቃቸው ምድራዊ አላማዎች አሉህ። ተፈላጊነት እንዲኖርህ ትመኛለህ፣ ስልጣን እንዲኖርህና፣ ኃያል እንድትሆን፣ ዕውቅና እንዲኖርህና ስምህ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ እንዲናኝ ትፈልጋለህ። በሀብት፣ በምድራዊ ስልጣን፣ በዕውቀት በማዕረግና በመልክ ዝነኛ የመሆን ተስፋ አለህ ፣ በመኖሪያ ቤት፣ በምግብ፣ በልብስና በሰውነት ደስታን በሚሰጡ ነገሮችም ተስፋ አለህ። ዓለም በአንተ እንጂ አንተ በዓለም እየኖርክ አይደለም። ስለዚህ አንተነትህ በዚህ ምድራዊ ተስፋ የታጠረ ነው። መንፈስህም ከስጋ ፍላጎቶች መራቅን ትመኛለች ሥጋ በመንፈስ ላይ መንፈስ በሥጋ ላይ ይመኛልና። (ገላ.5፥17) እነዚህ ሥጋዊ ተስፋዎችና ፍላጎቶች ስኬታማ ስለማይሆኑ ግራ ትጋባለህ። ይህን በእርግጥ ቅሬታን ያመጣብሃል። እነዚህን ነገሮች ሁሉ ትናፍቃለህ ነገር ግን ናፍቆትህ አያስደስትህም። ስለዚህ ለምኞትህ ሁሉ ማስተካከያ ታበጅለት ይሆናል ምናልባትም ይጠቅሙኛል የምትላቸውን ሰዎች ማግኘት፣ በምኞትህ ዙሪያ የተጻፈ መዛግብት ማገላበጥ ትፈልግ ይሆናል በዚህም ላይ ታች ስትል ምኞትህን ለማሳካት ትታገላለህ እንዲሆን ሌላ ዘዴ ልትፈጥር ትችላለህ ይሁን እንጂ ሳይሳካልህ ቀርቶ በሃሳብና በጥረት ትታክታለህ ከዚያም ትበሳጫለህ። ከዚህ የከፋው ነገር በእነዚህ ምኞቶችና ተስፋዎች ስኬታማ አለመሆን ምክንያት ለከፋ ሕይወት መዳረግህ ነው። እንደምትሰለች አውቃለሁ አዘንኩልህ እስከመቼ ድርስ በምኞት ማዕበል ውስጥ ትኖራለህ? የምትመኘውን ባገኘህ ጊዜ ደስተኛ ትሆናለህ ይህ ደስታ ስለማያረካህ ሌላ አዲስ ደስታን እንድትመኝ ያደርግሃል። ልክ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ "ከዚህ ውሃ የሚጠጣ ሁሉ እንደገና ይጠማል" (ዮሐ.4፥13 ) እንዳለው እርካታ አይኖርህም። ስለዚህ ውድ ወንድሜ ነገሩን በእርጋታ ከአንተ ጋር ለመነጋገር እፈልጋለሁ። "አለሙም ምኞቱም ያልፋል" (1ኛ ዮሐ.2፥17) ታዲያ ይህን ቃል ካወክ ለምን አለማዊ ፍላጎቶችን ለማግኘት ትታክታለህ? አንተ ልክ እንደ እኔ ለመሬት እንግዳ ነህ። ዓለም የሚያልፍበት አንተም የምትጠፋበት ጊዜ ይመጣል ልክ ከእናትህ ማህጸን ራቁትህን እንደመጣህ እንደዚሁ ራቁትህን ትመለሳለህ።(ኢዮ. 1፥21) ዓለምን ከነክብሯ ከነሀብቷና ከነስሟ ለቀሃት እንድትሄድ በመገደድ እንደ ማንኛውም ሰው ወደ መሬት ትወርዳለህ። ከዚያም ከዓለም ያገኘኽውን ደስታ ታወቂነት ወይም ምንም ይሁን ምን ሥጋህን ከሞት ሊከላከልልህ አልያም ሥጋን ከሚበሉት ትል ሊከላከልልህ አይችልም። በፍርድ ቀን ከዓለም ሀብትና ንብረት ውጭ በእግዚአብሔር ፊት ትቆማለህ። መልካም ይሁን ክፉ የሰራኸው ሥራ እንጂ የዓለም ቁሳዊ ነገር አይከተልህም። ስለዚህ ውድ ወንድሜ ምኞትህንና ተስፋህን በዓለም ላይ በማድረግ መታወክህ ለአንተ ጥሩ አይደለም ይህችን ምድር እሾህንና አሜኬላን እንዳበቀለችልህ ትዘነጋለህን!!! ከእኛ በፊት የነበሩና ምድርን ሊረግጧት የማይገባት የቅዳሳን አባቶችና እናቶች አሠራርና ፈለግ ተከተል ቅድስናቸውን ያገኙት ይህችን ዓለም በመውደድ ሳይሆን በመናቅ ነበር ሁኔታዎች ሁሉ ተመቻችተውላቸው ሳለ በዓለም ስላሉ ነገሮች ለማንኛውም ጉጉት አልነበራቸውም ። ውድ ወንድሜ አሁንም ምኞት አሉህ መዝገብህ ባለበት ልብህ ደግሞ በዚያ ይሆናልና (ማቴ.6፥21) የሥጋን ምኞቶችን ስለተቆራኘ መንፈሳዊ ነገሮች በአንተ አመለካከት ዋጋቸውን ያጣሉ ይህ የክብር ጌታ እንደተፈተነው ዓይነት ፈተና ነው። (ማቴ.4፥8-9) አሁን አስተውል እነዚህን ነገሮችን ብትይዝ በጥሩ ምኞት ያላሰርካት ነፍስህን ብታጣ ጥቅሙ ምንድን ነው? ነፍስህ ነጻነትን ትሻለች። ከስጋ ምኞት ተላቀን የመንፈስ ፍሬ የሆኑትን " የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፣ ደስታ፣ ሰላም፣ ትዕግሥት፣ ቸርነት፣ በጎነት፣ እምነት፣ የውሃት፣ ራስን መግዛት ነው።"(ገላ.5፥22) እንዳለው ብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ እነዚህን ገንዘብ አድርገን እንድንኖር እግዚአብሔር አምላክ ይርዳን!! [_ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሳልሳዊ ]
نمایش همه...
Music
نمایش همه...
ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሚ ሰማእት.mp34.47 MB
ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሚ ሰማዕት ይቅርታን ለመነ እሱን ለወገሩት ለአይሁድ አማፅያን የጠየቀ ምህረት ቅዱስ እስጢፋኖስ ቀዳሚ ሰማዕት 2 የስምዖን የሀና የእምነታቸው ፍሬ በአኖስ ከተማ ተወለደ ዛሬ ኦሪትን ተማረ ከገማልያል እውነት ሊመሰክር ሊሆነን መምህር አዝ ሊቀ ዳቆን ሆኖ ጉባዬ ሲመራ መልኩ እንደ መላዕክት እጅግ የሚያበራ ምግባርና እምነቱ ተመስክሮለታል ወልድን በመንበሩ በክብር አይቶታል አዝ አገር ለአገር ዞሮ ወንጌል አስተማረ ስለ ክርስቶስ ፍቅር እውነት መሰከረ ከአይሁድ ወገኖች ማንንም ሳይፈራ በክብር ተሰዋ ለስጋው ሳይራራ አዝ ቅድስና ሞልቶ እያየ ፈጣሪን እውነት ቢነግራቸው የፅራርያሙን ሁሉም አንድ ሆነና ቄዳርላይ ወገሩት ቁጥሩ ማይለካ ድንጋይ ከመሩበት  @hayemanotenleweke
نمایش همه...
Music
نمایش همه...
ኦ እስጢፋኖስ ሰማእት.mp32.17 MB
ኦ እስጢፋኖስ ሰማዕት 2 አክሊልን አገኘህ ከጌታ በእውነት የወንጌልን ትምህርት ቀዳሚ ሰማዕት ስለመገብካቸው " " አይሁዶች ወገሩህ ጨክኖ ልባቸው በድንጋይ ሲወግሩህ ቀዳሚ ሰማዕት በጣም ተጨነቀ " " ለሚወግሩት ሰዎች ይቅርታን ጠየቀ 2 አዝ የወንጌል በር ከፋች ቀዳሚ ሰማዕት የተባልከው ቅዱስ " " ተመሰከረልህ ከእውነተኛው ንጉስ ስራ ያስደንቃል ቀዳሚ ሰማዕት እጅግ ድንቅ ስራ " " በአንተ ተበተነ የወንጌል አዝመራ 2 አዝ የድቁናን ስራ ቀዳሚ ሰማዕት በክብር የፈፀምክ " " የስላሴ ዙፋን ተከፍቶ ያየህ የድንጋይ ሩምታ ቀዳሚ ሰማዕት ያላዘናጋህ " " ቀዳሚ ሰማዕት እስጢፋኖስ ነህ አዝ ዙፋኑ ተከፍቶ ቀዳሚ ሰማዕት ቀና ብሎ አየ " " ነፍሴን ተቀበላት በማለት ፀለየ ጌታም ተቀበለው ቀዳሚ ሰማዕት ቃሉንም ሰማለት " " ሰማያዊ አክሊል ወደ እርሱ ላከለት 2  @hayemanotenleweke
نمایش همه...
✞በዙሪያችን ካሉ✞ በዙሪያችን ካሉ ድንቅ ምሥክሮች በዕምነት በምግባር ከጸኑት እናቶች ከፍ ብላ ታየች በገድሏ ብዛት ንዕድ ክብርት ነች አርሴማ ቅድስት(፪) ሐብት እና ንብረቷን ውበቷን የናቀች ንግሥት መባልን በእምነት የተወች የኢየሱስ ክርስቶስ የስሙ ምስክር የቅድስት አርሴማ እጹብ ነው የእርሷ ክብር(፪) አዝ= = = = = እግዚአብሔር ጽናቷን የመሰከረላት በቤቱ በቅጽሩ መታሰቢያ አላት የወንጌሉን ብርሃን ለዓለም ያበራች ሠማዕቷ አርሴማ ለእኛም አማላጅ ነች(፪) አዝ= = = = = ይኸው በዚህ ዘመን እግዚአብሔር ገለጻት ለረድኤት በረከት ምክንያት አደረጋት አክሊል ተጎናጽፋ ታይታለች በክብር ዛሬም በልጆቿ በረከቷ ይደር (፪) አዝ= = = = = እንደተናገረው ጌታችን በቃሉ በእኔ የሚያምኑ ድንቅን ይሰራሉ ደዌ እንዲርቅለት ፈውስን የተጠማ ከደጇ ላይ ይውደቅ ይበላት አርሴማ(፪) ሊቀ መዘምራን ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ "በቤቴና በቅጥሬ ውስጥ ከወንዶችና ከሴቶች ልጆች ይልቅ የሚበልጥ መታሰቢያና ስም እሰጣቸዋለሁ፤ የማይጠፋም የዘላለም ስም እሰጣቸዋለሁ።" ኢሳ፶፮፥፭ @hayemanotenleweke
نمایش همه...
በዙሪያችን ካሉ.mp34.23 MB
ገደ ወዲያውም ዐረፈ አባ ሳሙኤልም ቀበረው ገድሉንም ጻፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሙሴ ጸሎት ይማረን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የመስከረም 2 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለሙሴ ዘረሰየ እምዓለም ተፈልጦ። ቈጽለ ሆሣዕና አራዘ ወፍሬ ዘይቶን ሥብጦ። በብዙኅ መከራ አምድኅረ ሰይጣን አስፈጦ። እግዚአብሔር መሐሪ መንገደ ገዳም ሜጦ። ኀበ ሥጋሁ የዓርፍ ወነፍሶ ይትሜጦ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የመስከረም 3። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ አድኀንካ ለነፍስየ እሞት። ወለአዕይንትየኒ እምአንብዕ። ወለእገርየኒ እምዳኅዕ"። መዝ 55፥13-14። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ተሰ 3፥13-ፍ.ም፣ 2ኛ ዮሐ 1፥8-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥28-31። የሚነበበው ወንጌል 18፥18-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ አንበስ የዕረፍት በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። @hayemanotenleweke
نمایش همه...
❤ "በስመ አብ ወወልደ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ መስከረም ፫ (3) ቀን። ❤ እንኳን ለገዳመ ሲሐቱ ለአባ ሙሴ ለዕረፍት በዓል፣ የከበረ አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ ከተሾመ በሁለተኛው ዓመት በእስክንድርያ ከተማ ነፍስ ከሥጋዋ ጋር ትሞታለች በዕለተ ትንሣኤም ከሥጋዋ ጋር አብራ ትነሣለች ስለሚሉ ክፉዎች የኤጲስቆጶሳት የአንድነት ጉባዔ ለተደረገበት ቀን በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰማዕት ከአባ ዲዮስቆሮስ፣ ሰማዕት ከሆነ ከሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ፣ ከዲያቆን በትንከል፣ ከብዙዎች የፋርስ ሰማዕታት ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ በዚች ቀን የከበረ አባት ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮናስዮስ ከተሾመ በሁለተኛው ዓመት በእስክንድርያ ከተማ የኤጲስቆጶሳት የአንድነት ጉባዔ ተደረገ። ❤ ይህም ጉባዔ የሆነው ነፍስ ከሥጋዋ ጋር ትሞታለች በዕለተ ትንሣኤም ከሥጋዋ ጋር አብራ ትነሣለች ስለሚሉ ክፉዎች በዐረቢያ አገር ስለ ተነሡ ሰዎች ነው። እነርሱም ለከፋችና ብልሹ ለሆነች ሃይማኖታቸው የፈጠራ ድርሰትን ደርሰው በእስክንድርያ ከተማ ወደሚኖሩ ሰዎች ላኩ። ❤ አባታችን ሊቀ ጳጳሳት አባ ዲዮስናስዮስም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ከዚህ ከክፉ ሥራም እንዲመለሱ አስተማራቸው ገሠጻቸውም እነርሱ ግን አልሰሙትም አልተመለሱም። ስለዚህም በእነርሱ ላይ ይህን ጉባዔ ሰብሰቦ ተከራከራቸው ስሕተታቸውንም ገልጾ አስረዳቸው እነርሱ ግን ሰይጣን አሳውሮአቸዋልና ተጸጽተው አልተመለሱም ይህም ጉባኤ ረግሞ ከቤተ ክርስቲያን አንድነት ለይቶ አሳደዳቸው። ❤ ይህም አባት ዲዮናስዮስ ስለርሳቸው ድርሳናትን ደረሰ በውስጣቸውም እንዲህ የሚል "በዚህ በቸርነቱ ስጦታ ውስጥ የእግዚአብሔር ፍቅር የጎላ የተረዳ ሆነ ነፍስ ረቂቅ ስለሆነች እንደ መላእክት በሕይወት እንድትኖር እንጂ እንዳትሞት እንዳትጠፋ ማድረጉ ነው። ❤ ከሥጋዋም በምትወጣ ጊዜ ስለ በጎ ሥራዋ እንደሚገባት መጠን ወደ ሕይወት ቦታዋ ይወስዷታል ወይም እንደ ሥራዋ ክፉነት ወደ ሥቃይ ይወስዷታል። በትንሣኤ ቀንም ንቃሕ መዋቲ ተብሎ ዓዋጅ ሲነገር በፈጣሪያቸው ትእዛዝ የሙታን በድኖች ሲነሡ ነፍሳት እንዲህ ይሆናሉ እያንዳንዲቱ ነፍስ ከሥጋዋ ተዋሕዳ አብራ ትነሣለች"። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን አባቶቻችን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ የገዳመ ሲሐት አባ ሙሴ፦ ይህም ቅዱስ ከመነኰሰ ጀምሮ ዓለምን ትቶ ከበረሀ ገብቶ በጾም በጸሎት በመጠመድ ተጋደለ። እግዚአብሔር ዘይቶንና የተምር አትክልት ያለባትን የአትክልት ቦታ በማየት ልቡን ብሩህ እስከ አደረገለት ድረስ በወሩ መባቻም ከዘንባባ ዕንጨትና ከዘይቶን የወደቀውን ፍሬ ወስዶ ይበላል። ምግቡም ታናሽ ወፍ በሚመገበው መጠን ልክ ነው ልብሱም ከዘንባባ ቅጠል የተሠራ ሰሌን ነው። ስለዚህ ለሚያስጨንቅ ለክረምት ቅዝቃዜና ለበጋ ቃጠሎ የተጋለጠ ከዚህም ጋር በጾምና በጸሎት የተጠመደ ነው ። ❤ ነገር ግን መጻሕፍትን የሚያውቅ አይደለም የዱር አራዊትም በየወገናቸው ወደርሱ ይመጡ ነበር እርሱም ያረጋጋቸዋል። የጸሎት ጊዜም ሲደርስ በእጁ ሲጠቅሳቸው ይሔዳሉ። ድርቅ የሆነ እንደሆነም ሊያነጋግሩት እንደሚሹ ሁነው መጥተው በፊቱ ይቆማሉ እርሱም የሚሹትን በመንፈስ ቅዱስ አውቆ በጸሎቱ ዝናብን ያወርድላቸዋል። እንዲሁም እያደረገ ከእርሳቸው ጋር አርባ አምስት ዓመት ኖረ ። ❤ ሰይጣንም ቀናበት ዘመኑ በአለፈና እጅግ በአረጀ ሽማግሌ አምሳል በጥቂት በጥቂት ሲያዘግም ከበዓቱ ውስጥ ሁኖ አየው ለዚህ ቅዱስ አባ ሙሴም ገዳማዊ መናኒ መስሎት ወደርሱ ሒዶ አምጥቶ ወደ በዓቱ አስገባው አራዊት ግን በሽማግሌ የተመሰለውን ሰይጣን በአዩት ጊዜ ከእርሱ ሸሹ። ❤ ከዚህ በኋላ አባ ሙሴን አገሩንና ሃይማኖቱን ጠየቀው እርሱም ሁሉን ነገረው ደግሞ አባ ሙሴ ኑሮው እንዴት እንደሆነ ሽማግሌውን ጠየቀው ። በሽማግሌ የተመለሰ ሰይጣንም እንዲህ ብሎ መለሰለት "እኔ በዓለም ኃጢአት በመሥራት ብዙ ዘመናት ኖርኩ አንዲት ሴት ልጅንም ወለድኩ ። ከዚያም የዓለምን ኃላፊነትና ጠፊነት አሰብኩ ከዓለምም ወጥቼ በበረሀ ውስጥ አርባ ዓመት ኖርኩ። ልጄን ያገባት እንደሌለ በአሰብኩ ጊዜ በዚህ ነገር ምክንያት ወዳንተ መጣሁ ከአንተ በቀር የሚያገባት የለምና በሞትኩም ጊዜ የምትቀብረኝ አንተ ነህ ብዙ ስፍራዎችና የአታክልት ቦታዎችም ስላሉኝ ሁሉንም እንተ ትወርሳለህ"። ❤ አባ ሙሴም ሰምቶ ደነገጠ "እኔ መነኲሴ ስሆን ይህን እንዴት አደርጋለሁ" አለ የተመረጡ ጻድቃን ሲሆኑ ሚስቶች የነበሩአቸው አብርሃምን ሙሴን ዳዊትን ከብሉያት መጻሕፍት ምስክር ማስረጃ አድርጎ አመጣለት በዚህም ወደ ተንኰሉ ልቡን አዘነበለው። በውስጡ ያጌጠች ሴት ልጅ ያለችበትን የተሸለመ አዳራሽ አሳየውና ከዚያም በኋላ እንደሞተ ሆነ አባ ሙሴም አይቶ በለዩ አለቀሰ ገንዞም ቀበረው። ❤ ልጅቷ ወዳለችበት ለመግባት በፈለገ ጊዜ ጥቅል ነፋስ ነፍሶ የኋሊት ጣለው ከዚህ በኋላ ልቡ ሲመለስለት አዳራሹንም ልጅቷንም የአትክልት ቦታዎችንም አጣ ፈጽሞ እያደነቀ ወደ ማደሪያው ተመለሰ ከዕንጨቱም ፍሬ ምግቡን ሊመገብ ፈለገ በአፉም ውስጥ መራራ ሆነበት በረኃብም ስለ ተጨነቀ ወደ ዱር ወጥቶ ሔደ። ❤ ከዚህም በኋላ በአህያው ላይ ተቀምጦ ወደ እስክንድርያ በሚሔድ በሽማግሌ ነጋዴ አምሳል ሰይጣን ተገናኝው መብልና መጠጥም ይዞ ነበር አባ ሙሴንም ከርሱ ጋር ወሰደው ወዳንድ አገርም አድርሶ በዚያ ተወው ። ❤ ዳግመኛም በገዳማዊት በመናኒነት በምትኖር አምሳል ሰይጣን ታየው እርሷም ውኃ የምትቀዳ መስላ ነው ሥራውን ጠየቀችው ሰይጣን እንደ ፈተነው ሁሉን ነገራት በልቧም ሳቀችበት ወደ ቤቷም ወስዳው አብልታ አጠጥታ ከዚያ በኋላ የጋብቻን ነገር አሳሰበችው ብዙ ገንዘብም እንዳላት እርሷም የሟች ንጉሥ እንደሆነት ነገረችው። ልቡም እንደአዘነበለ አይታ "እኔ አይሁዳዊት ነኝ እኛም ብዙዎች ነን" ሃይማኖቱንም እስከካደ ድረስ በብዙ ተንኰል ተስፍ አስደረገችው ። ❤ ዳግመኛም እንዲህ አለችው "ና ወደ በረሀ እንውጣና ያኖርኩትን ገንዘብ እንውሰድ" ብላ ውኃ ወደሌለበት በረሀ ወሰደችው ከተራራ በላይም ወጥታ ተለወጠችበት እንዲህም አለችው "እኔ ብዙዎችን ያሳትኩ ሰይጣን አንተነንም ከገዳምህ አስመጣሁህ ሃይማኖትህንም አስካድኩህ እነሆ በዚህ በረሀም ሙተህ ነፍስህ ወደገሃነም ትወርዳለች" ይህንንም ብሎ ሰይጣን ከርሱ ተሠወረ። በተመለሰም ጊዜ በቀኝም በግራም መንገድ አጣ የሚጠጣውም ውኃን አላገኘም ምድር ጠበበችው በምድር ላይም ወድቆ በፊቱ ውስጥም አፈርን በተነ ነፍሱም ከሥጋው ለመለየት እስከደረሰች ደረስ ተንከባለለ ጭኸ መሐሪና ይቅር ባይ ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር ራራለት ያጽናናው ዘንድ መልአኩን ላከለት እርሱም "ኃጢአትህ ተሠረየልህ እስከ ሰባት ቀንም ታርፍለህ የእግዚአብሔር አገልጋይ ሳሙኤልም ይቀብርሃል" ብሎ አጽናናው ሰላምታም ሰጥቶት ዐረገ ። ❤ ያን ጊዜም ሳሙኤል መጣ ንጉሥ ኢጋቦም በበረሃ ውስጥ ወደአነፃት ቤተ ክርስታያን ወሰደው እርሷም ገዳማውያን የሚሰበሰቡባት ተሰውራ የምትትኖር ናት ወደርሷም በደረሱ ጊዜ ቅዱሳን ተሰብስበው መሥዋዕትን ሲያሳርጉ አገኙና በአንድነት ሥጋውንና ደሙን ተቀበሉ ሰንብትም ከሆን በኋላ ከቅዱሳን መቃብር በረከትን ሊቀበሉ ከአባ ሳሙኤል ጋራ አብረው ሔዱ ከዚያም ደርሶ አባ ሙሴ ሰ
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.