cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Addis Mereja

እንኳን ወደ ቻናላችን በሰላም መጡ። ይህ ፈጣን መረጃዎችን የምታገኙበት ቻናል ነው። ➡አዳዲስ ዜናዎች ና መረጃዎች ➡ድንቃድንቅ ወሬዎች ➡ስፖርታዊ ዘገባዎች ➡የመዝናኛ ዜናዎች ➡News & Media Channel

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
341
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የዩኒቨርሲቲዎችን የቅበላ ዝግጅት የሚያረጋግጡ 11 ተቆጣጣሪ ኮሚቴዎች ሥራቸውን ጀምረዋል! የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የቅበላ ዝግጅት የሚያረጋግጥ 11 ተቆጣጣሪ ኮሚቴዎች የዩኒቨርሲቲዎችን ዝግጅት ለማረጋገጥ ከትላንት ጀምሮ መሰማራቱን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ። ተቋማቱ የኮቪድ-19 ወረርሽኝን ከግምት ያስገባ ዝግጅት አድርገው በቀጣዩ ወር ተማሪዎችን የሚጠሩበትን ቀን ያሳውቃሉ ሲሉ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ደቻሳ ጉርሙ ለኢዜአ ገልጸዋል። የተቋማቱ የኮሮና ቫይረስን እየተከላከሉ የሚያስተምሩበትን ሁኔታ መፍጠራቸውን ኮሚቴዎቹ ካረጋገጡ በኋላ ሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተማሪዎች ቅበላ ፕሮግራማቸውን ይፋ ያደርጋሉ ብለዋል። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ወደ ትምህርት የሚመለሱበት ቀን እስካሁን እንዳልተወሰነ የገለጹት ዳይሬክተሩ፣ ከተቋማቱ የተማሪዎች ቅበላ ጋር ተያይዞ በማህበራዊ ሚዲያና በሌሎች ምንጮች የሚሰራጨው መረጃ ስህተት እንደሆነ ገልጸዋል። @tikvahethmagazine @tikvahmagbot
نمایش همه...
ትምህርት ሚኒስቴር ለ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች 450 ሺህ ታብሌቶችን ሊሰጥ ነው፡፡ ት/ት ሚኒስቴር ለመጀመሪያ ጊዜ በኦንላይን የሚሰጠውን የ2012 ዓ.ም የ12ተኛ ክፍል ዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተናን ለማከናወን ለተፈታኞቹ ታብሌት ኮምፒውተሮችን እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ ፈተናው የሚሰጠው ከህዳር 28 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ ሲሆን የተፈታኞቹም ብዛት 450 ሺ ገደማ ነው፡፡ ነገር ግን በርካታ ሰዎች በአገሪቱ ካለው የኢንተርኔት ግንኙነት ደካማ መሆንና የዲጂታል መሳሪያዎች እጥረት አኳያ ተማሪዎች ሊቸገሩ እንደሚችሉ ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡ ይህንን በተመለከተ ከካፒታል ጋዜጣ ጥያቄ የቀረበላቸው የት/ት ሚኒስቴር ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተሯ ወ/ሮ ሀረጓ ማሞ ለእያንዳንዱ ተፈታኝ ተማሪ ታብሌት ኮምፒውተር እንደሚሰጠው አስታውቀዋል፡፡ ት/ት ሚኒስቴር በአገሪቱ ያለውን የኢንተርኔት ችግር ከግምት ውስጥ በማስገባትም በራሱ ሳተላይት በተመረጡ ት/ት ቤቶች ኢንተርኔት ግንኙነት ለመፍጠር መዘጋጀቱን ገልፀዋል፡፡ እንደ ት/ት ሚኒስትር ውሳኔ ከሆነ ማንኛውም 11ኛ ክፍልን ያጠናቀቀና የ12ተኛ ክፍልን ያለፈውን አመት የመጀመሪያ ሴሚስተር የተማረ ተማሪ ለፈተናው መቀመጥ የሚችል ሲሆን፣ ምዝገባው የሚደረገውም በኦንላይን ነው፡፡ ይሁንና ከፈተናው በፊት ተፈታኞቹ የ45 ቀናት ት/ትና የቴክኖሎጂ መመሪያ እንዲወስዱ ይደረጋል፡፡በተጨማሪም እንደ ሚኒስትር መስሪያ ቤቱ ውሳኔ የስምንተኛ ክፍል ፈተና ህዳር 22 እና 23 የሚሰጥ ሲሆን በአጠቃላይ በአገሪቱ በሚቀጥሉት ሶስት ሳምንታት ጊዜ ትምህርት ቤቶች በሙሉ ይከፈታሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ት/ት ቤቶች ሲከፈቱ የተማሪዎችን አካላዊ ርቀት ለመጠበቅ በአንድ ክፍል ውስጥ 25 ተማሪዎች ብቻ በ1ዴስክ ላይ 1 ተማሪ ብቻ እንዲሆን ተወስኑል፡፡ #Capital @ethio_mereja_news @ethio_mereja_news
نمایش همه...
የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና እና ምዝገባ በኦንላይን እንደሚካሄድ እና ተማሪዎች የ45 ቀን የማካካሻ እና የቴክኖሎጂ መለማመጃ ጊዜም እንደሚሰጣቸው የት/ት ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ወ/ሮ ሐረጓ ማሞ ተናግረዋል። የ12ኛ እና የ8ኛ ክፍል ፈተና በተያዘለት የጊዜ ገደብ እንዲሰጥ በቅድሚያ ትምህርት ቤቶች ኮቪድ-19 መከላከልን መርህ ባደረገ መልኩ ዝግጅት ሙሉ በሙሉ ማጠናቀቅ ይጠበቅባቸዋል ብለዋል። ከፈተናው አስቀድሞም የትምህርት ቤቶችን ዝግጁነት የማረጋገጥ ስራ በትምህርት ሚኒስቴር እንደሚሰራም ተገልጿል። ትምህርት ቤቶች የሚከፈቱት እና ፈተናዎችም የሚሰጡት ትምህርት ቤቶች አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ ማሟላት ሲችሉ ብቻ መሆኑም ተገልጿል። ትምህርት ሚኒስቴር ትምህርት ቤቶች እንዲከፈቱ ያቅስመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች ሳይሸራረፉ እንዲተገበሩ ለሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥሪ አቅርቧል። ምንጭ : ት/ት ሚኒስትር @addiss_mereja @addiss_mereja
نمایش همه...
የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ተቋማትን መልሶ ለመክፈት እየተደረጉ ያሉ ዝግጅቶች እና ኮቪድ 19ን ከመከላከል አኳያ የነበሩ ተግባራዊ ምላሶች ላይ ያተኮረ የሁለት ቀን ምክክር በአዲስ አበባ ተጀምሯል፡፡ በመድረኩ ላይ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት ዶክተር ሙሉ ነጋ የተቋረጠውን ስልጠና ለማስቀጠል መደረግ ስለሚገባቸው ጥንቃቄዎች እና ስልጠናውን ለማስጀመር መደረግ ስላለባቸው ዝግጅቶች በመመካከር ስልጠናው የሚጀምርበት አቅጣጫ ይቀመጣል ብለዋል። (MoSHE) @amharictutorialclass @amharictutorialclassbot
نمایش همه...
ዩኒቨርስቲዎችና ኮሌጆች እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ተማሪዎቻቸውን ለመቀበል ያላቸውን ዝግጁነት ሪፖርት እንዲያደርጉ ተጠየቁ፡፡ ©ሸገር ራዲዮ @amharictutorialclass @amharictutorialclassbot
نمایش همه...
መስከረም_14፣_2013_ዩኒቨርስቲዎችና_ኮሌጆች_እስከ_መስከረም_መጨረሻ_ድረስ_ተማሪዎቻቸውን_ለመቀበል.MP33.74 MB
ተጨማሪ ፦ #የ8ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ሕዳር 22 እና 23 ቀን 2013 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ፈተና ላይ መቀመጥ የሚችሉት 7ኛ ክፍልን ተምረው ያጠናቀቁና የ8ኛ ክፍልን የአንደኛ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው። በተመሳሳይ #የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና መውሰድ የሚችሉት የ11ኛ ክፍል ትምህርት ያጠናቀቀቁና የ12ኛ ክፍልን የመጀመሪያ ሴሚስተር ትምህርት የተከታተሉ ብቻ ናቸው ተብሏል። የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከሕዳር 28 እስከ ታህሳስ 1 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሚሰጥም በምክረ ሀሳቡ ላይ ተጠቅሷል@amharictutorialclass @amharictutorialclassbot
نمایش همه...
የትምህርት ቤት አከፋፈት ሂደቱ በሶስት ዙር እንደሚከናወን ውሳኔ ሃሳብ ቀርቧል። በዚህም መሰረት: 💥በመጀመሪያው ዙር ማለትም ጥቅምት 9 ቀን 2013 ዓ.ም: በገጠር ወረዳና ቀበሌ ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሃሳብ ቀርቧል። 💥በ2ኛ ዙር ጥቅምት 16 ቀን 2013 ደግሞ በሁሉም የዞንና የክልል ከተሞች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ትምህርት እንዲጀምሩ ነው ምክረ ሃሳብ የቀረበው። 💥ጥቅምት 30 ቀን 2013 ዓ.ም በአዲስ አበባና በፊንፊኔ ዙሪያ የሚገኙ ትምህርት ቤቶችም ትምህርት እንዲጀምሩ የውሳኔ ምክረ ሀሳብ ቀርቧል። @amharictutorialclass @amharictutorialclassbot
نمایش همه...
✏️የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ትምህርት የማስጀምር ውሳኔ❗️ ➡️ ለስድስት ወራት ተቋርጦ የቆየው የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ትምህርት ዳግም እንዲጀመር መወሰኑን የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ደቻሳ ጉርሙ ተናግረዋል። ➡️ በዚህም ለመማር ማስተማር ሂደቱ ዝግጁነት ያላቸው ዩኒቨርሲቲዎች እስከ ተያዘው ወርሃ መስከረም መጨረሻ ዝግጁነታቸውን አጠናቀው ለተማሪዎች ጥሪ እንዲደረግ ውጥን ተይዟል። ➡️በርካታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የኮቪድ-19 ለይቶ ማቆያና ምርመራ ማዕከላት ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ለትምህርቱ ፈጥኖ መጀመር እንደ ስጋት ተነስቷል። ➡️በመሆኑም በአማራጭ ጉዳይ ላይ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመምከር ለጊዜው በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚገኙት 700 ሺህ ተማሪዎች ገደማ ቁጥራቸው ከ100 ሺህ የሚለቀውን ተመራቂዎች ቅድሚያ ሰጥቶ ወደ ትምህርት ገበታው እንዲመለሱ ነው የተወሰነው። ➡️በቀጣይነትም ከኮሮና ወረርሽኝ ሁኔታ ጋር በሚስማማ መልኩ ተለዋዋጭ እቅዶችን በመያዝ ቀሪዎቹ ተማሪዎች ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ እንደሚሠራም ተገልጿል። ➡️ በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ ወጥነትን ሳይጠብቁ ቀድመው ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ዩኒቨርሲቲዎች ከመስከረም 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ ለተመራቂ ተማሪዎች ጥሪ በማድረግ ወደ መማር ማስተማር ሥራው እንዲገቡ ጉባኤው ወስኗል። ➡️ ለተማሪዎች ጥሪ ከተደረገ በኋላ ከመጓጓዣ ሂደት ጀምሮ በየዩንቨርሲቲዎቹ በሚኖራቸው ቆይታ ወረርሽኙ እንዳይዛመት ከፍተኛ ዝግጅት መደረግ አለበትም ተብሏል። ➡️ከኮቪድ-19 ዓለም አቀፍ ወረርሽኝ ባልተናነሰ አምና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ የመማር ማስተማር ሂደቱ ላይ ፈተና ሆኖ የከረመው የፀጥታ መደፍረስ እንዳያጋጥም ከአምና ልምድ መወሰዱን ጉባኤው የመከረበት ሲሆን፤ ጉዳዩ አሁን ለጊዜው ስጋት ባይሆንም መዘናጋት ሳይፈጠር ዩንቨርሲቲዎች ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እንዲሠሩበት እቅድ መያዙ ተገልጿል።  @addiss_mereja @addiss_mereja
نمایش همه...
የድምፃዊ ግርማ ተፈራ ካሳ ልጅ የሆነችው ኤፍራታ ተፈራ ዛሬ በወሊድ ምክንያት ህይወቷ አልፏል!! የልጁን ሞት ተከትሎ ድምፃዊው ይሄን በፌስ ቡክ ገፁ አስፍሯል "ልጄ እህቴ ልጄ ጓደኛዬ ልጄ መካሪዬ ልጄ አስተማሪዬ ሁሌም እወድሻለሁ በልቤም ትኖሪያለሽ። አይንሽን ለማየት እኔም አያት አደረግሽኝ ብዬ ልጅሽን ለማቀፍ ነበር ምኞቴ።እግዚአብሔር የፈቀደዉን አደረገ።ነፍስሽን በአፀደ ገነት" ያኑርልኝ።የነገሮች ሁሉ ባለቤት የሆንከው አምላክ ሆይ አሁንም ክበር ተመስገን።አሜን ። @amharictutorialclass @amharictutorialclassbot
نمایش همه...
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ #ለድኅረምረቃ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን አውጥቷል፡፡ በዚህም የመደበኛ ድኅረ ምረቃ( ከመጀመሪያ ድግሪ በላይ) ምዝገባ መስከረም 11 እና 12 የሚደረግ ይሆናል፡፡ #ማስታወሻ፡- የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች ይህ ማስታወቂያ እናንተን አይመለከትም፡፡ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የተቋረጠውን ትምህርት የሚጀመርበትን ጊዜ እንደሚያሳውቅ እስከዛው ግን ተማሪዎች በዝግጅት እንዲቆዩ ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.