cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ የመዝናኛ ዝግጅት ነው። የfacebook አድራሻችን👇👇👇 https://www.facebook.com/habeshatae/ https://www.facebook.com/groups/220848820108415/ @DjFortink @Daniyenatu

نمایش بیشتر
کشور مشخص نشده استزبان مشخص نشده استدسته بندی مشخص نشده است
پست‌های تبلیغاتی
189
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ። አዲሱ አመት የሰላም እና የጤና እንዲሆንላችሁ ፍርቱና ይመኛል። (የሐበሻ ጣዕም ፕሮግራም አዘጋጆች ዳኒ እና ዲጄ ፎርቲን ኬ) #share #like #follow
نمایش همه...
ተስፋ ኮንሰርት በአዲስዓመት ዋዜማ (ጻጉሜ 5 ቀን 2014 ዓ.ም) በሚልኒየም አዳራሽ እንደሚካኼድ አዘጋጆቹ አስታወቁ። በኮንሰርቱ ላይ ዳዊት ፅጌ፣ አብዱ ኪያር፣ ልጅ ሚካኤል፣ አዲስ ሙላት፣ ሀመልማል አባተ እና ታደለ ገመቹ እንዲሁም በዲጄ የተቀናበረ ሙዚቃ የኘሮግራሙ አካል ይሆናል ተብሏል። የመግቢያ ዋጋ መደበኛ 800 ብር፣ ቪአይፒ 5000ብር መሆኑን አዘጋጆቹ አስታውቀዋል። ኮንሰርቱ ተስፋ የተባለበት ዋና ምክንያት ሀገራችን ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ ወደፊት መሻገር እንደሚቻል፣ የተስፋ ጭላንጭል መኖሩን ለማጉላት ነው ብለዋል። በዛሬው ዕለት በሸራተን አዲስ ሆቴል በተሰጠው መግለጫ ላይ አቶ ናሁሰናይ አያሌው ኢቨንት ማኔጀር፣ የሸራተን ሆቴል ስራ አስኪያጅ ሚስተር አንቶኒዮ ከሙዚቀኞች አበጋዝ እና ያሬድ ተገኝተዋል ሐበሻ ጣዕም
نمایش همه...
"አፍሪካ ለአፍሪካውያን"አህጉራዊ ትላቅ ሁነት በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነው። አቢሲኒያ ቢዝነስ ኔትወርክ ከአጋሮቹ ጋር በመሆን ያዘጋጀው " "አፍሪካ ለአፍሪካውያን " የተሰኘ ግዙፍ አህጉራዊ ዝግጅት ከጥቅምት 11- 13 2014 ዓ.ም በወዳጅነት አደባባይ ይካሄዳል። ይህንን ሁነት አስመልክቶ አዘጋጆቹ ዛሬ ቦሌ በሚገኘው አንባሳደር ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥተዋል። "አፍሪካን ለአፍሪካውያን" በተሰኘው በዚህ ዝግጅት ላይ የአፍሪካን በአፍሪካ ምርቶች ፣የባህል ፣ኪነጥበብ ፣ኢንቨስትመንት የንግድ እሴቶች የሚያጎላና በዓይነቱ እና በይዘቱ ለየት ያለ አህጉራዊ ሁነት ነው ተብሏል። "አፍሪካ ለአፍሪካውያን " በመላው አፍሪካ በሚገኙ ማህበረሰቦች ውስጥ ያሉትን የቢዝነስ ፣ የባህል ፣ የኪነጥበብ ፣ የንግድ እና ኢንቨስትመንት ልዩነቶችን በማቀራረብ እና አንድነትን ለማምጣት የተወጠነ ዝግጅት ሲሆን ይህም የአፍሪካ ሀብትን በጋራ ለመጠቀም ያለመ ዓመታዊ ዝግጅት እንደሆነ ተገልጿል። በዚህም ግዙፍ ሁነት ላይ የተለያዩ ዝግጅቶች የሚኖሩ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ባህሎቻቸውን እና ሀገራዊ እሴቶቻቸውን የሚያንጸባርቁበት የእያንዳንዱ ተሳታፊ ሀገር በተዘጋጀ የኤግዚቢሽን ጎጆዎች የሚካሄድ ይሆናል። በተጨማሪም የፋሽን ሾው ፣ የአውቶ ሾው ፣ የዳንስ እና ሙዚቃ ኮንሰርት ይኖራል ተብሏል። በዚህ ሁነት ላይ ከሚጠበቁ ልዩ ዝግጅቶች መካከል የተለያዩ የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችን ያሳተፈ የዳንስና ስፖርታዊና አካል ብቃት ያጣመረ የዳንስ ፊትነስ ኮንሰርት ይኖራል የተባለ ሲሆን ይህም በርካታ የሰው ቁጥር የተሳተፈበትን የዳንስ ፊትነስ ኮንሰርት የጊነስ የዓለም ድንቃድንቅ መዝገብ ላይ ለማስመዝገብ ጥረት እንደሚደረግ ተገልጿል። ሐበሻ ጣዕም
نمایش همه...
አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ አዲስ የአቅርቦትና የሎጅስቲክ አገልግሎት መጀመሩን አስታወቀ ለአዲሱ ዓመት ዶሮና በግን ጨምሮ የተለያዩ የበዓል ግብአቶችን በአሸዋ የሞባይል መተግበሪያ መገበያየት እንደሚቻልም ተገልጿል ማክሰኞ ነሐሴ 24 /12/ 2014 አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ አክሲዮን ማህበር የአለምን ምጣኔ ሀብት እያንቀሳቀሰ በሚገኘው የዲጅታል ኢኮኖሚ ዘርፍ ላይ በመሰማራት እየሰራ የሚገኝ ተቋም ሲሆን፤ በዛሬው ዕለት አዲስ የአቅርቦትና የሎጅስቲክ አገልግሎት ይፉ አድርጓል። ድርጅቱ “በቀልጣፋ፣ አስተማማኝ አቅርቦትና ሎጀስቲክስ ከልዩ ዋስትና ጋር የአገራችንን የግብይት ሥርዓት በአሸዋ ዶት ኮም /Ashewa.com/ እናዘምን!" በሚል መሪ-ቃል በአዲስ አበባ፤ ቀነኒሳ ሆቴል ባከናወነው በዚህ ይፋዊ የአገልግሎቱ ማስጀመሪያና ማስተዋወቂያ መርሃግብር ላይ ከፍተኛ የመንግስት ሀላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተውበታል። በመድረኩ የአሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ አ.ማ መስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ዳንኤል በቀለ፤ ድርጅቱ የኢትዮጵያ መንግስት በ2025 ዲጅታል ኢትዮጵያን በመገንባት እየሰራ ያለውን ሥራ በመደገፍ፤ በኢ-ኮሜርስ፣ ኢ-ለርኒንግ እና በሌሎች 11 የቴክኖሎጂ ዘርፎች ውስጥ በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ገልጸው፤ የኢ-ኮሜርስ አንዱ አካል በሆነው አሸዋ ዶት ኮም (Ashewa.com) በኩል ደግሞ ይህን ራዕይ ለማሳካት በሙሉ አቅም በሥራ ላይ እንደሚገኝ ተናግረዋል። አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ የአገራችንን ወግ፣ ባህል እና ሥነ ልቦና መሠረት በማድረግ መሬት ላይ ያለውን ችግር የሚፈቱ፣ የማህበረሰቡን ህይወት የሚያሻሽሉ ብቁ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎች ይዞ ወደ ሥራ መግባቱን የገለጹት ዳንኤል፤ በዚህም ምክንያት ድርጅቱን ለማቋቋም ከሚያስፈልገው 200 ሚሊየን ብር ውስጥ 70 ሚሊየኑን በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመሸጥ መቻሉን ተናግረዋል። አሸዋ ዶት ኮም ይዞት የመጣው ሲስተም የኑሮ ውድነትን የሚፈታ፣ የገበያ መረጋጋትን የሚፈጥር እንዲሁም ቀላል እና አስተማማኝ በሆነ መልኩ ገጠሩን ከከተማው በንግድ ማስተሳሰር የሚያስችል ነው ያሉት ዋና ሥራ አስኪያጁ፤ ድርጅቱ በአሁኑ ሰዓት ከ1 ሺሕ 500 በላይ ሻጮችን፣ ከ10 ሺሕ በላይ ምርቶችን ይዞ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸው፤ 5 ሺሕ ምርቶችንም በወር ዉስጥ በማድረስ “በቀልፋ፣ አስተማማኝ አቅርቦትና እና ሎጀስቲክስ ከተሟላ የዌርሀውስ ጋር አጣምሮ በመሥራት ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል። በዛሬው ዕለት በይፉ ሥራ በጀመረው የአቅርቦትና የሎጅስቲክ አገልግሎትም፤ አምራቾች ምርቶቻቸውን በቀላሉ እና በፍጥነት ለተጠቃሚ እንዲያደርሱ የሚያስችል ሲሆን፤ ድርጅቱ ምርቶቹን በቀጥታ ከዋና አምራቹ መጋዘን ወደ ተጠቃሚዎች፣ ወይንም ወደ አሸዋ ቴክኖሎጂ መጋዘኖች በማድረስ፤ ከዛም ወደተጠቃሚዎች የማድረስን አገልግሎት እንደሚያካትት ተገልጿል። አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ በአዲስአበባ ይጀመራል የተባለ ሲሆን፤ በቀጣይ በኹሉም የኢትዮጽያ ክፍሎች የአቅርቦትና የሎጅስቲክ አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል አቅምን በመገንባት ላይ እንደሚገኝም አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ አስታውቋል፡፡ በተጨማሪም ሸማቾች ባሉበት ቦታ ሆነው አሸዋ ዶት ኮም የሞባይል መተገበሪያን በመጠቀም ለበዓል የሚሆኑ ምግብ ነክ የሆኑ ግብአቶችንም ሆነ ዳሮ፣ በግ፣ ፍየል በሬ የመሳሰሉ እንስሳቶች በኦን ላይን መግዛት እንደሚችሉም አሸዋ ቴክኖሎጂ ሶሉሽንስ አስታውቋል። ሐበሻ ጣዕም
نمایش همه...
ፈረስ ትራንስፖርት ሁለተኛ ዙር የፈረስ ማይልስ ለበጎ አድራጎት ተቋማት እና ግለሰቦች አስረከበ (ነሐሴ 21/2014 አዲስ አበባ) የከተማችን ተጠቃሽ የትራንስፖርት ቴክኖሎጂ አቅራቢይ የሆነው ፈረስ ትራንስፖርት ከቅን እና መልካም አሳቢ ቤተሰቦቹ እንዲሁም ከትጉህ አሽከርካሪዎች በበጎ ፈቃደኝነት የሰበሰበውን ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የፈረስ ማይሎችን ለተለያዩ የልማት እና የበጎ አድራጎት ስራዎች እንዲውሉ በማቀድ በራድሰን ብሉ ባዘጋጀው የስጦታ መርሐ ግብር ለሚመለከታቸው አካላት አስረክቧል። በዚሁ መሰረት ለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ(100ሺህ ብር)፣ለአርቲስት ዘነበች ገሠሠ ቤተሰቦች(106ሺህ ብር)፣ለቢላሉል ሃበሺ የልማት እና የመረዳጃ እድር(100ሺህ ብር)፣ለጊርጌሴኖን የአእምሮ የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማእከል(142ሺህ ብር)፣ለኢትዮጵያ የልብ ህሙማን ማእከል(369ሺህ ብር) በእያንዳንዳቸው ስም በማይልስ መልክ የተሰበሰበው ስጦታ በብር ተቀይሮ በልገሳ ፕሮግራሙ ተላልፏል ። አንድ ማይልስ የአንድ ብር ዋጋ አለው።በልገሳ ፕሮግራሙ ላይ እያሉ ለህልፈት ህይወት የተዳረጉ ቤተሰቦቹ ለአቤል አማርከኝ፣ለይበልጣል አለበል እና ለሳላሃዲን አማን ቤተሰቦች ለእያንዳንዳቸው የ50,000 ብር ተበርክቷል። ድርጅቱም ለለጋስ ፣ቅን እና በጎ አሳቢ ቤተሰቦቹ ላቅ ያለ አክብሮትና ምስጋና በማቅረብ ይህ መልካምና አርአያነትያለው ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል እና በቀጣይ ለሶስተኛ ዙር #ለኢትዮጵያ ካንሰር ህሙማን አሶሴሽን #ለኢትዮጵያ ዳይለሲስ ሴንተር #ለዘውዲቱ መሸሻ የሕፃናትና ቤተሰብ በጎ አድራጎት ማህበር እና #ለመቄዶንያ የበጎ አድራጎት ማህበር በተመሳሳይ መልኩ ከመልካም ቤተሰቦቹ ጋር በመተባበር ማይልሶችን እንደሚያሰባስብ በመርሃ ግብሩ ይፋ አድርጓል ። ፈረስ ትራንስፖርት ለአገልግሎቱ ተጠቃሚዎች ከእያንዳንዱ ጉዞ የ5% የፈረስ ማይልስ ተመላሽ አድርጎ የሚሰጥ ሲሆን ደንበኞቹም ያገኙትን የፈረስ ማይላቸውን የሞባይል ካርድ ሊገዙበት ፣ወደ ፈረስ ጉዞ ሊቀይሩት ፣ለወዳጅ ለዘመድ ሊያስተላልፉት፣እንዲሁም ለበጎ አድራጎት ተቋማትና ግለሰቦች ሊለግሱት ይችላሉ ። ፈረስ የአገልግሎት አቅራቢዎችንና ተጠቃሚዎች በቴክኖሎጂ አማካኝነት በማገናኘት ዘመናዊ፣ቀልጣፋ፣አስተማማኝና ደህንነቱ የተጠበቀ የትራንስፖርት አገልግሎትን በተመጣጣኝ ዋጋ በማቅረብ ዘርፉን በማዘመን ረገድ የራሱን ድርሻ እየተወጣ የሚገኝ ድርጅት ነው። ያበለፀገውን ቴክኖሎጂ የአሽከርካሪዎችንና የደንበኞች ዝርዝር መረጃ ፣ያደረጓቸውን ጉዞዎችና የክፍያ መረጃዎችን የያዘና በተፈለገ ጊዜ መረጃዎቹን ከመረጃ ቋት ማግኘት የሚቻልበት መንገድ ነው። ደንበኞች አገልግሎቱን ለማግኘት 3 አማራጭ ያላቸው ሲሆን አንዱ አማራጭ የፈረስ ደንበኞች መተግበሪያን ከአፕ ስቶር ወይም ከፕሌይ ስቶር በማውረድ በስልካቸው አማካኝነት በመመዝገብ ነው።ሌላኛው አማራጭ በጥሪ ማእከል አማካይኝነት በ6090 ላይ በመደወል የሚገኝ አገልግሎትነው።ሶስተኛው አማራጭ ደግሞ በፖርታል አማካኝነት ማግኘት የሚቻለው ሲሆን ይሄኛው አማራጭ ለተቋም ደንበኞች የሚሰጥ ነው። ፈረስ በብዙ አማራጮች አገልግሎቱን 24 ሰአት በማቅረብ አስተማማኝነቱና ደህንነቱ የተረጋገጠ አለም አቀፍ ደረጃ ያለው አገልግሎት በመሥጠት ላይ ይገኛል ። በቀጣይም ከአዲስ አበባ ውጭ በሌሎች የሃገሪቱ ከተሞች እንዲሁም ከኢትዮጵያ ውጭ በጎረቤት ሃገራት አገልግሎቱን በቅርቡ የሚጀምር እና በተጨማሪም ፈረሰኛ በሚል የዴሊቨሪ አገልግሎት በአዲስ አመት እንደሚጀመሩ ታውቋል። ፈረስ ያደርሳል! ፈረስ ይደርሳል ! (ሐይማኖት ወንድምነህ)
نمایش همه...
Photo unavailableShow in Telegram
እንኳን ለቡሄ በዓል አደረሳችሁ!
نمایش همه...
"ራዳር አይዶል ሾው“ በ'ቲክቶክ' |ራዳር– ከዮሃና ጋር (Radar with Yohana) በመላ ሃገራችን የሚገኙ አቅምና ችሎታ ያላቸውን ምርጥ ወጣት ድምጻውያንን ለማግኘት ጨየሚካሄድ የተሰጥዖ ፍለጋ ውድድር ነው ይህ ውድድር በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ በሶሻል ሚዲያ ብቻ የሚካሄድ የድምጽ ተሰጥዖ ውድድር (Idol Show) ነው። በ ሎም በዕውቀትና ልምድ የተገነባ የአዘፋፈን ክህሎትን እንዲያገኙ የሚያስችል ልዩ ፕሮግራም ነው ራዳር ወጣት ድምጻውያን ችሎታ ውን የሚያሳዩበት ዕድል በመፍጠር በሙያው መድረክ ራሳ ውን እንዲያስተዋውቁ “ራዳር አይዶል ሾው“ በሶሻል ሚዲያ በተለይም በ'ቲክቶክ' የሚቀርበ የውድድር ዓይነት ነው። ወጣትና ጀማሪ ድምጻውያን በራሳቸው ዘፈናቸውን ቀርጸው ለራዳር የውድድር ዝግጅት ቲም ይልካሉ፥ የተቀረጹት ዘፈኖች በ'ራዳር ቲክቶክ” ለአድማጭና ለተመልካች ይተላለፋሉ። ከተመልካቾች በሚሰበሰብ ነጥብ ና ከራዳር የውድድር ዳኞች በሚሰጥ ውጤት ባለልዩ ተሰጥዖ ድምጻውያን ይመረጣሉ። በዚህ ሂደት ችሎታ ያላቸው ድምጻውያን ወደ ሙያው የሚገቡበትን መንገድና መድረክ ያገኛሉ፥ ብቁ ድምጻዊ የመሆን አቅምና ተሰጥዖ እንዳላቸውም ያምናሉ። ይህ፡ ራዳር– የሶሻል ሚዲያ የተሰጥዖ ውድድር፡ አገልግል ሬከርድስ እና ገሃድ ኢንተርቴይንመንት በሚባሉ ሁለት ድርጅቶች ከሐበሻ ቢራ ፋብሪካ አ.ማ. ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ወርቃማ ዕድል ነው። የቲክቶክ ውድድሩም ከአርቲስት/ድምጻዊ ዮሃና ጋር የሚቀርበ ይሆናል። ስያሜውም፡ ራዳር– ከዮሃና ጋር (Radar with Yohana) ይሰኛል። ዮሃና በተለይ ለወጣቶች በቀረቡ ዘመናዊና ምርጥ ዘፈኖች እየታወቀ የመጣ ድንቅ ወጣት ድምጻዊ ነው። አገልግል ሬከርድስ እና ገሃድ ኢንተርቴይንመንት፡ በመዝናኛ ኢንዳስትሪው ውስጥ ትርጉም ያለው ለውጥ ለማምጣት የሚተጉ፣ ወጣት አርቲስቶች ተሰጥዖና ችሎታቸው የሚያሳዩበት እንዲሁም ሙያዊ ክህሎት የሚያገኙበት ልዩ ዕድል ለመፍጠር የተቀናጁ ድርጅቶች ናቸው። ሐበሻ ቢራም በሁሉም የሙያ መስክ ወጣቱ በጣም የተሻለ ትውልድ እንዲሆን ባለው ፅኑ ፍላጎት መሰረት፡ በኪነ ጥበቡ ዘርፍም ተሰጥዖ ያላቸው ወጣቶች ችሎታቸውን የሚያሳዩበትና በ ቁ ባለሙያ የሚሆኑበትን መድረክ ማገዝ ይገባል በሎ ስለሚያምን ይህን የተሰጥዖ ውድድር ከሁለቱ ድርጅቶች ጋር በመተባበር አቅርቧል። ልዩ ችሎታ ያላቸው ድምጻውያን ራሳቸውን የሚያሳዩበትና የሚወዳደሩበት ቀላልና ምቹ መድረክ መፍጠር፡ ያደገ እናየዘመነ የሙዚቃ ኢንዳስትሪ በሃገራችን እንዲኖር ያስችላልና፡ ይህን ፕሮግራም በማየት፣ አስተያዬትና ድምጽ በመስጠት ማበረታታትና ማገዝ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ኃላፊነት ነው በለን እናምናለን። 0913585200 0920953221 [email protected] ሐበሻ ጣዕም ©
نمایش همه...
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.