162
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
ስሚኝ!!
መውደዴን ለመግለፅ
ቃላቶች ቢያጥሩኝ
አይቼሽ ለማውራት
ፊትሽ ቢያስፈራኝ
አሁን ፍቅር ጥሎኝ
እግርሽ ላይ ብወድቅም
የዛሬን አያርገውና
እንዲህ አልነበርኩም
ውዴ ስሚኝ ልንገርሽ...
ቃላት ከሚደረድር ከሸንጋዩ ሰው
ፍቅር ፍቅር እያለ ከሚለፈልፈው
እያየ የሚወድሽ ድፍረት ለነፈገው
እሱ ይበልጣል ከሁሉም በልቡ የያዘው
✍ ተፃፈ በእዮብ ተሾመ©
02/09/2013 E.c
07:33A.m
@poemday
ስሚኝ!!
መውደዴን ለመግለፅ
ቃላቶች ቢያጥሩኝ
አይቼሽ ለማውራት
ፊትሽ ቢያስፈራኝ
አሁን ፍቅር ጥሎኝ
እግርሽ ላይ ብወድቅም
የዛሬን አያርገውና
እንዲህ አልነበርኩም
ውዴ ስሚኝ ልንገርሽ...
ቃላት ከሚደረድር ከሸንጋዩ ሰው
ፍቅር ፍቅር እያለ ከሚለፈልፈው
እያየ የሚወድሽ ድፍረት ለነፈገው
እሱ ይበልጣል ከሁሉም በልቡ የያዘው
✍ ተፃፈ በእዮብ ተሾመ©
እኔ ምልሽ ውዴ
አንቺን በመውደዴ
ባውቶብስ ፌርማታ
ባቡር ተጠበቀ
ሌባው እየኮራ
ፖሊስ ተደበቀ
ጥርስ ያለው አይስቅም
ድዳሙ እየሳቀ
ለነገሩ ይሁን
ቀን ነግቶ ይመሻል
እንኳን ሌላው ቀርቶ
አንቺም የኔዋ ጉድ
የኔን ልብ ሠርቀሻል።
እመስላለሁ አይደል ?
(አብርሀም ሙሉ ሰው)
እመስላለው አይደል? ፣ደስ እንደተሰኘ
አጥቶ እንዳገኘ
ህልሙን እንደነካ
በልቶ እንደጠገበ፣ ጠጥቶ እንደረካ…
"ተስማምተው ይመስል፣ ነፍስና ስጋየ"
ድብቁን እንደሰማ፣ ሚስጥሩን እንዳየ
የመኖር ብዥታ፣ እንደሆነለት ግልፅ
የሀሳቡ ሞልቶ፣ እንደያዘለት ቅርፅ…
እመስላለሁ አይደል ?
የጨበጠው መልካም፣ የረገጠው ቀና
ለምለም የሆነለት፣ የህይወት ጎዳና
ውሀው ወይን ሆኖ፣ ያሰከረው አይነት
እርካታን እረክቷት፣ ያቆመ መመኘት
ፍቅር ያሰጠመው፣ መውደድን የሚጠልቅ
ሁሉንም የሚያውቅ ፣በሁሉም ሚታወቅ
እመስላለሁ አይደል ?
እመስላለሁ አይደል ? ፣ያማረበት ለብሶ
ጆሮው መርዶ ያልሰማ፣ አይኑ ያላየ ለቅሶ
እስኪ መልሱልኝ ፣እመስላለሁ አይደል ?
መታገል ያልጣለው፣ ያቆመው መታደል!
.
እንኳን አደረሳችሁ 🙏❤🙏
📖📖📖
የገነት በሬነህ
_______
ለኔ ለደካማ ክፋት ለወረረኝ
በሰው ደም ለቆሸሽኩ ምህረት ማይገባኝ
በዝሙት በርኩሰት ገላዬ ላደፈው
ቅንጣት ሀዘኔታ በውስጤ ለሌላው
ተንኮል ለማሴረው ለጨኳኟ ነብሴ
ሁሌም ኗሪ ለሆንኩ ለሟይሞላው ኪሴ
አንተ ግን ተሰቀልክ ደምክን አፈሰስክ
የኔን በደል ትተህ ለእኔ ተከሰስክ
እኔ ድኜ ባንተ
እኔ ድኜ ባንተ
ዳግመኛ ተነሳህ ሞትህ ድል አድርገህ
ከቶ ምን ሊሳንህ የገነት በሬነህ
በዳዳ coffee
✟✞ ትንሳኤ ለኔ ነሽ ✟✞
አዳም ቢበድልም በምኞት ስህቱ ለምድር ቢሰጥም
ሔዋን ብትስትም እምነቷን ለስህተት ፈቅዳ ብትሰጥም
ቆይ ግን
እንደምን ባለ መልክ
ምን በሆነ ሁኔታ
እንዴት የሰው ፍጡር ማሰብ የተሰጠው ማወቅን ያወቀው፣
እባብ ያስተዋል የማወቅን እውቀት ጥበብ ያልተሰጠው።
መሳቱንስ ይሳት
ይህን ስህተት ሊያርም ቢወርድ ከመንበሩ፣
እጅጉን ይከፋል
በርን እያንኳኳ ግባ እሚለው አቶ ከደጃፍ ማደሩ።
በጥፊ ሲመታ
በባርያ መዳፍ ላይ በደም መልክን መሳል፣
የተካደው እውነት
ለካደው ሐሰት ሲል ከመስቀል ላይ መዋል፣
ምን አይነት ፍቅር ነው ምን የሚሉት መንደድ
ምን ይሉት ስቃይ ነው ምን የሚሉት መውደድ
ወዳጅ መስሎ ቀርቦ ስሞ ላሸመተው
አላውቀውም ብሎ ሶስት ጊዜ ለካደው
የዶሮዋን ጩኀት ሰምቶ ላለቀሰው
ወንጀለኛን ፈቶ ንፁሁን ላሰረው
እስኪ ልጠይቅሽ
ምን አስገድዶት ነው፦
መራራን የጠጣው?
ሀሞት የቀመሰው?
አንቺ የይሁዳ ምስል
ዲናር ብታስበልጭ ፍቅሬን ችላ ብለሽ፣
ልረሳሽ አልችልም አላውቃትም ልልሽ።
አንቺን በማለቴ
ቁጥሩ ማይታወቅ ጅራፍ ቢያርፍብኝም
የመረረን ሀሞት ምላሴ ቤቀምስም
የረሳሽው ጅራፍ ስንዝር የመረረው ሀሞት ስፍር
ቢያስክደኝም እኔነቴን ላያከስመው ያንቺን ፍቅር
ከክናፍርሽ ስር ያለውን ውብ ጠለል ቢጠማም ከንፈሬ
ደጅሽ ሲመላለስ ሚስማር ቢወጋውም ቢንሻፈፍም እግሬ
ከድንግሏ እናቱ ከስጋዋ ስጋን ነስቶ ተዋህዶ
ሊያድነኝ ከመጣ ህመም መከራዬን ሊቀበለኝ ወዶ
እኔን ከመሰለ ስጋን ከለበሰ ለፍቅር ተዋርዶ
እኔ እርሱን ልመስለው ይገባል ልገልጠው
ያያ የእውነት ፍቅሩን የእውነት ልኖረው
አንቺ እኔን ብጠይኝ ምራቅ ብተፊብኝ
በጥላቻሽ ጅራፍ እጥፍ ብትገርፊኝ
ግራዬ እያልኩሽ ጎኔን ብትወጊው
በደሜ ማህተም ቃሌን ሰጥሻለው
እኔን የመሰለኝ ለወጉት ጥላቻን ሲሰጥ ስላላየው፣
ዕፅፍ ወድሻለሁ ፍቅር ለፍቅርሽ ስል ነፍሲን እሰጣለው።
ትንሳኤ ለኔ ነሽ ፦
ካለሁበት ፅልመት ሳይሽ እምመለስ፣
መግነዝ ሳላስፈታ ከደጅሽ ላይ ምደርስ፣
በር ሳልቀበቅብ ልብሽ ላይ ምገለጥ፣
ሳጣሽ ግን አንቺ ልጅ ሲኦል ነው ምቀመጥ።
✍ ዮላ
ቀን 23:08:2013 ዓ/ም
ሰዓት 04:15
አጣጥለህ አትነሳ
(አብርሃም ሙሉ ሰው)
አጣጥለህ አትነሳ
ያንዱን ውድቀት፣ አትደገፍ
ጥረህ ፣ግረህ ፣ሰርተህ እለፍ
አሊያ አንደኛ ብትወጣ...
አያጠግብህ የሚበላ፣ አያረካህ የሚጠጣ
አያምርብህ የሚለበስ
በሰው ልፋት፣ አንተ ስትደርስ
ያለ ቦታህ ስትሰየም፣ ያለ ጊዜህ ስትገኝ
ያለእውቀትህ ስትሞገስ፣ ያለ ሞያህ ስትቀኝ
ውጭህ ሙላት፣ ውስጥህ ባዶ
ስኬት አይባልም
የራስን መካብ፣ የሌላውን ንዶ!፡፡
ከወደዱት ለወዳጆ ያጋሩ
#የጠቢብ ቃል!
(ሚካኤል አስጨናቂ)
.
#ባህር ዳር ተኝቼ ሳልሞቅ ጠሀይቷን
አየር ላይ በርሬ ሳልጎበኝ ምድሪቷን
ቁርሴን አዲሳ ' ባ ምሳዬን ፓሪስ ላይ
እንዲህ ተዝናንቼ ድሎት ተድላ ሳላይ
በቆንጆዎች ጉያ ስራቸው ሰምጬ
ብኖር ነው ደስታዬ ዓለሜን ቀጭቼ
እያልሁ አስብ ነበር !
አቤት የኔ ነገር ...
ዳምኖ ይሄ ቀኔ ... ሰፍኖበት ፅሞና
ከሎሬቱ ቅኔ.. . አንዷን እመዝና
ምነው እመብርሀን
ኢትዮጵያን ዘነጋሻት?
ቀኝሽን ረሳሻት ... ?
እያልሁ ሳልዘምር ...
ስንኙን ሸምድጄ በቃል ሳልደረድር
በዝናብ ሳልተኛ በሬን ዘጋግቼ
ብልጭልጭ መኪና ሳልሾፍር ገዝቼ
ድንጋይ በድንጋይ ላይ ህንጣ ሳልገነባ
እልፍ ሎሌ ኖሮኝ ታጅቤ ሳልገባ
ይሄ ህይወት ነው ወይ... አሁን የኔ ኑሮ ?
እያልኩ አስብ ነበር ያ...ኔ በፊት ድሮ
ይሄ ታሪኬ ነው ሌላ ነው ዘንድሮ !
ዛሬ ...
ከመጥሀፍ ትንቢት አንዲቷን ቆንጥሬ
ገላልጬ ባየው ...
ይሄ ስንዝር ገላ ድሎት አበጃጅቶት
ወዘና ቢያጠምቀው
ዝናው ባህር አልፎ የአዳም ዘር ቢያውቀው
በስልጣን በውበት ሁሉ ቢያዳንቀው
አሸርጋጅ አጎንባሽ ዙሪያውን ቢያጅበው
ጠቢቡ ሰለሞን አበክሮ እንዳለው
ሁሉም ከንቱ ... ከንቱ ...
የከንቱ ከንቱ ነው !
የሚወድ ይጽናና!
-
በገበያ ዓለም ውስጥ...
ብርቱ በመፃጉዕ በሚታዘልበት
ነፍስ ባሞሌ ጨው በሚለወጥበት፤
ያጸና አንድ ሲገኝ መንፈሱን እንዳ'ለት
ተመስገን ነው ማለት!
ፍትህና ሰላም
በደኅና አይጠላም - ብሎ
ከኅሊናው መክሮ...
የራሔልን ዋይታ
ከሚፈጥሩት ተርታ፤
ከበደለኞች ሰልፍ መራቅ የመረጠ
ክፋትን በለጠ።
ፍትሕ ናት ገናና
ሰላም ናት ገናና
የሚወድ ይፅናና!
ለተከታይ መንጋ - ሰው ጀርባ ለቆመ
ውበት ወደዚህ ናት - ብሎ የጠቆመ
እምነት ወደዚህ ናት - ብሎ የጠቆመ፤
ገሚሱ ጣቱ ላይ - ወጥቶ ቢንጠለጠል
በገሚሱ ደግሞ - ግብሩ ቢብጠለጠል፤
ከሰልፍ ባሻገር - ዐይኑን ገልጦ ያየ
ልቡን ከፍቶ ያየ
ከነፍሱ ተስማማ- ከመንጋ ተለየ!
ውበት ናት ገናና
እምነት ናት ገናና
የሚወድ ይፅናና!
የኖረ እንኳ ቢኾን - ገድሎ፣ ዘርፎ፣ ዋሽቶ
ሞት ጽድቅን እንዳይቀድም - ሥርየትን ሽቶ፤
ልቡን ወደ ምህረት - ካለ የመለሰ
ራሱን ፈወሰ!
ምሕረት ናት ገናና
የሚወድ ይጽናና!
ያግኝም ይጣትም
ሽልማት ቅጣትም፤
ታግኘው ትጣውም
ክስረቱም ዕጣውም፤
ከማግኘት ከማጣት- ከርሱም ከርሷም ይልቅ
(ከእኔም ካንቺም ይልቅ)
(ከኹላችን ይልቅ)
ፍቅር ነው ገናና
የሚወድ ይፅናና!
በገበያ ዓለም ውስጥ...
ብርቱ በመፃጉዕ በሚታዘልበት
ነፍስ ባሞሌ ጨው በሚለወጥበት፤
ያጸና አንድ ሲገኝ መንፈሱን እንዳ'ለት
ተመስገን ነው ማለት!
ጭቁን መች ይዝላል?
ያነሳል ይጥላል፤
ድሮ ቀረ ይላል
አዲስ ዘመን ይላል፤
ትዝታ ያኝካል
ተስፋ ያመነዥካል፤
ጨቋኝ መች ይዝላል?
ያነሳል ይጥላል፤
በትግል ይነግሣል
በትግል ይፈርሳል፤
እንትን ኹለት ይላል
እንትን ኻያ ይላል፤
የሻገተ ልቡን በምላሱ ያጥባል
የነጠፈ አንጎሉን በሽንገላ ያልባል።
ለመንፈስ መታወክ - ተስፋ እንደሚቸረችር፣ ታሪክ የሚሸቅጥ
ሐርነት ምን እንደኹ፣ መታደስ ምን እንደኹ- አልተረዳም በቅጥ።
የየግለሰቡ የየነፍሱ እውነት
የየራሱ ጥበብ፣ የየራሱ ኪነት፤
ሐርነት ገናና
ነጻነት ገናና
የሚወድ ይጽናና!
በአምልኮ አደባባይ - በትምህርት ገበታ
ጥላቻ እየፀናች - በርዕዮት ተፈትፍታ፤
በራዲዮን ልሳን - በቴሌቪዥን መስኮት
ቂም እየተዘራ - በቀል ሲኮተኮት
ቀጥፎ ሞት ለማትረፍ - አዳሜ ሲራኮት፤
በገበያ ዓለም ውስጥ...
በገበያ ዓለም ውስጥ...
ብርቱ በመፃጉዕ በሚታዘልበት
ነፍስ ባሞሌ ጨው በሚለወጥበት፤
ያጸና አንድ ሲገኝ መንፈሱን እንዳ'ለት
ተመስገን ነው ማለት!
እንዲህ ዐይነቱ ሰው - ስም ቢቀርበትም - ስም ቢወጣለትም
እውነት ነፍሱ አትሞትም!
እውነት ናት ገናና!
የሚወድ ይጽናና!
-------------------------
መስፍን ወልደተንሳይ
ሰኞ- መስከረም 1- 2004
(ክብ ልፋት መድብል)
یک طرح متفاوت انتخاب کنید
طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.