Nikodimos Christian center
رفتن به کانال در Telegram
Nikodimos Show is a unique program which is hosted by the famous Ethiopian Gospel Singer Tigist Ejigu, https://www.facebook.com/tigist.ejigu.5 This show is working on creating awareness on sensitive Christian issues inside the Church of Ethiopia.
نمایش بیشتر6 565
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+47 روز
-3130 روز
آرشیو پست ها
276ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ አብድዩ ምዕራፍ 1
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
275ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ ኢዩኤል ምዕራፍ 1-3
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
274ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ ሚክያስ ምዕራፍ 4-7
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
273ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ ሚኪያስ ምዕራፍ 1-3
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
272ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ አሞጽ ምዕራፍ 5-9
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
271ኛ ቀን
በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ዘወትር ከምሽቱ 3:00 ሰዓት ቲክቶክ live እና ቴሌግራም ላይ ኑ የእግዚአብሔርን ቃል እናጥና::
ዛሬ የምናነበው ክፍል ትንቢተ አሞጽ ምዕራፍ 1-4
የዩቱብ የቲክቶክ እና የቴሌግራም ሊንኮችን ከታች ታገኛላችሁ👇
YOUTUBE#1:- www.youtube.com/NikodimosShow
YOUTUBE#2:- www.youtube.com/@thewordwithtg316
TIKTOK#1:- tiktok.com/tigistejiguwondmu
TIKTOK#2:- tiktok.com/nikodimoschrstiancenter
TELEGRAM:- https://t.me/nikodimosshow
በየትኛውም የኃላፊነት ስፍራ ላይ ብንሆን ሊሸልምን ወይንም ሊያባርረን የሚችል አለቃ እንዳለን አንዘንጋ
ከቁጥር 20-22 ኤልያቄምና እግዚአብሔር የሚሰጠው ቁልፍ
ኤልያቄምን አስነሳዋለሁ !
"[22] የዳዊትን ቤት የቊልፍ መክፈቻ እሰጠዋለሁ፤ እርሱ የሚከፍተውን መዝጋት፥ የሚዘጋውንም መክፈት የሚችል አይኖርም።" (አ.ት)
ኤልያቄም የኢየሱስ ክርስቶስ ጥላ ነው : ነቢዩ ኢሳያስ መልእክቱን በጊዜው ስለነበረው ኤልያቄም ስለተባለው ሰው ቢናገርም መልእክቱን ግን መሲሀዊም ጭምር ነው
የዮሐንስ ራእይ 3
7 በፊልድልፍያም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ። የዳዊት መክፈቻ ያለው፤ የሚከፍት፥ የሚዘጋም የሌለ፤ የሚዘጋ፥ የሚከፍትም የሌለ፤ ቅዱስና እውነተኛ የሆነው እርሱ እንዲህ ይላል።
".....ለህዝቦች እንደ እባት ይሆናል!"
እንደ ሼብና እራሱን የሚያስቀደምና በህዝቡ የሚጠቀም ሳይሆን እንደ አባት ለህዝቡ የሚራራ የሚንከባከባቸው ይሆናል "
የዮሐንስ ወንጌል 10
11 መልካም እረኛ እኔ ነኝ። መልካም እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል።
እውነትኛ መሪዎች ህዝቡን የሚንከባከቡና የሚጠበቁ ናቸው
1 የጴጥሮስ መልእክት 5
[2] በዐደራ የተሰጣችሁን የእግዚአብሔርን መንጋ ጠብቁ፤ መንጋውን የምትጠብቁትም በግድ ሳይሆን እግዚአብሔር በሚፈልገው ዐይነት፥ በፈቃደኛነት ይሁን፤ ለገንዘብ በመስገብገብ ሳይሆን ለማገልገል ባላችሁ ፍላጎት ይሁን። (አ.ት)
23-25 ኤልያቄም ምንም እንኳን ኩላብ ተብሎ እንደሚጠራው ዕቃ መስቀያ ጠንካራና አስተማማኝ ቢሆንም ሰው ነውና አንድ ቀን ተሰብሮ ይወድቃል!
ምንም ያህል መልካምና ጠንካራ ቢሆን የሰው አገዛዝ ፍፃሜ (ማብቂያ) አለው : አስተማማኝና ለዘላለም የማይናወጥ መሰረት ክርስቶስ ብቻ ነው
ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2
20 በሐዋርያትና በነቢያት መሠረት ላይ ታንጻችኋል፤ የማእዘኑ ራስ ድንጋይም ክርስቶስ ኢየሱስ ራሱ ነው፤(አ.መ.ት)
ምን እንማር?
1. ችግሮችን ለመፍታት ከመነሳታችን በፊት የእግዚአብሔርን ፊት እንፈልግ
2. አካላችን ለመንፈሳዊ እንቅስቃሴዎች ቀርቦ ልባችን ከእግዚአብሔር እንዳይርቅ እንጠንቀቅ
3. እግዚአብሔር ባስቀመጠን በየትኛውም ስፍራ እንደ ባለአደራና አለቃ እንዳለው ሰው ኃላፊነታችንን እንወጣ
4. ቁልፉን በእጁ የያዘውን እንመነው
ትንቢተ ኢሳያስ ምእራፍ 21-22
ስለ ባቢሎን አወዳዳቅ የተነገረ ትንቢት
በዋናነት ስለባቢሎን ቢናገርም ስለኤዶም እና ስለ አረብም ትንቢት ይናገራል
" ሂድ ጉበኛ አቁም "
ከቁጥር 2-3 አስጨናቂ ራእይ አየሁ ይላል : ነቢዩ ኢሳያስ መልእክቱን በግብር ይውጣ አይደለም የሚያስተላልፈው "በምጥ ላይ እንዳለች ሴት ጭንቅ ያዘኝ" ይላል
እግዚአብሔር መልእክትን ሲሰጥ ከሸክም ጋር ነው እውነተኛ አገልጋዮች ሸክምን ይጋራሉ እንጂ መልዕክቱን ብቻ በግዴለሽነት አያስተላልፉም
የማንራራለትን ህዝብ ማገልገል ትርጉም የለውም
የማቴዎስ ወንጌል 9
35 ኢየሱስም በምኩራቦቻቸው እያስተማረ፥ የመንግሥትንም ወንጌል እየሰበከ፥ በሕዝብም ያለውን ደዌና ሕማም ሁሉ እየፈወሰ፥ በከተማዎችና በመንደሮች ሁሉ ይዞር ነበር።
36 ብዙ ሕዝብም ባየ ጊዜ፥ እረኛ እንደ ሌላቸው በጎች ተጨንቀው ተጥለውም ነበርና አዘነላቸው።
ቁ 5 ፍርድ እየመጣ እነሱ ግብዣ ያዘጋጁ ነበር
"[5] ባየሁትም ራእይ ግብዣ ተዘጋጅቶ ለእንግዶች መቀመጫ ስጋጃዎች ተነጥፈዋል፤ እነርሱም ገና በመብላትና በመጠጣት ላይ ሳሉ፥ “እናንተ የጦር መኰንኖች! ጋሻችሁን ወልውላችሁ አዘጋጁ!” የሚል ድንገተኛ ትእዛዝ ተላለፈላቸው።"(አ.ት)
"ድንገተኛ ትእዛዝ "
የማቴዎስ ወንጌል 24
38 በዚያች ወራት ከጥፋት ውኃ በፊት፥ ኖኅ ወደ መርከብ እስከገባበት ቀን ድረስ፥ ሲበሉና ሲጠጡ ሲያገቡና ሲጋቡም እንደ ነበሩ፥
ምቾት መንፈሳዊ ንቃታችንን እንዳይሰርቀን እንጠንቀቅ
ከቁጥር 6-9 ሂድ ጠባቂ አቁም ያየውን ይናገር!
የጉበኛው (ጠባቂው) ስራ ነቅቶ የሚሆነውን መጠባበቅና ፈጥኖ መናገር ነው
አማኞች በመንፈስ ንቁዎች እንድንሆን የእግዚአብሔር ቃል በተደጋጋሚ ያሳስበናል
የማቴዎስ ወንጌል 26
41 ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ፤ መንፈስስ ተዘጋጅታለች ሥጋ ግን ደካማ ነው አለው።
ዛሬም በቤትክርስትያን ጉበኞች ያስፈልጋሉ
- ነቅተው የሚፀልዩ
- ወቅቱንና በመንፈሳዊው ዓለም የሚሆነውን የሚረዱ
- ሌሎችን በፍቅር እና በሸክም የሚያስጠነቅቁ
- የክርስቶስን ዳግም ምፃት ነቅተው እየጠበቁ ሌሎችንም የሚያነቁ ጉበኞች ያስፈልጉናል
በመንፈስ መንቃት ለተወሰኑ ሰዎች የሚተው አገልግሎት ሳይሆን የሁሉም አማኝ ቁመና ሊሆን ስለሚገባ ሁላችንም ወደዚያ ማደግ አለብን
"ባቢሎን ወደቀች"
ባቢሎን በአንድ ወቅት የነበረች ሀገር ብቻ ሳትሆን በእግዚአብሔር ላይ የማመፅና የትእቢት ምሳሌ ስለሆነች በአዲስ ኪዳንም ይህ ቃል በተደጋጋሚ ተነግሯል
የዮሐንስ ራእይ 14
8 ሌላም ሁለተኛ መልአክ። አሕዛብን ሁሉ የዝሙትዋን ቍጣ ወይን ጠጅ ያጠጣች ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች እያለ ተከተለው።
የዮሐንስ ራእይ 18
2 በብርቱም ድምፅ። ታላቂቱ ባቢሎን ወደቀች፥ ወደቀች፥ የአጋንንትም ማደሪያ ሆነች፥ የርኵሳንም መናፍስት ሁሉ መጠጊያ የርኵሳንና የተጠሉም ወፎች ሁሉ መጠጊያ ሆነች፤
በእግዚአብሔር ላይ ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ ማንኛውም ሲስተም ፍፃሜው ውድቀት ነው
ከቁጥር 11-12 በኤዶም ላይ የተነገረ ትንቢት ነው
"ጠባቂ ሆይ ሊነጋ ምን ያህል ቀረው?"
ሌሊት : የመከራ : የፍርሃት : እርግጠኝነት የማጣትና ንጋትን ብቻ ተስፋ የማደረግ ተምሳሌት ነው
ሊነጋ (ይህ ሁሉ ሊያበቃ) ምን ያህል ቀረው?
የጠባቂው መልስ
"12 ፤ ጕበኛውም። ይነጋል ድግሞም ይመሻል፤ ትጠይቁ ዘንድ ብትወድዱ ጠይቁ፤ ተመልሳችሁም ኑ አለ።"
በዚህ ምድር እስካለን ድረስ ጥቂት እፎይታ ብናገኝም ደግሞ መምሽቱ የማይቀር ነው
ላይመሽ የሚነጋው ጌታችን ዳግም ተመልሶ ሲመጣ ብቻ ነው!
ወደ ሮሜ ሰዎች 13
12 ሌሊቱ አልፎአል፥ ቀኑም ቀርቦአል። እንግዲህ የጨለማውን ሥራ አውጥተን የብርሃንን ጋሻ ጦር እንልበስ።
ከቁጥር 13-17 በአረብ ላይ የተነገረ ትንቢት ነው
" የቄዳር ክብር በአንድ አመት ያበቃለታል!"
1ኛ የዮሐንስ መልእክት 2
17 ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል።
ምን እንማር ?
1. እንደ ጉበኛ እንኑር
2. መንፈሳዊ ንቃታችንን ከሚሰርቅ ነገር እንጠበቅ
3. ይህ ሌሊት ይነጋል " ለቅሶ ማታ ቢሆን ጠዋት ግን ደስታ ይሆናል " አንድ ቀን ግን.. ደግሞ ላይመሽ ይነጋል
4. በኃላፊው ዓለም ሳይሆን በሰማይ መዝገብ ሃብታችንን እናኑር
ትንቢተ ኢሳያስ ምእራፍ 22
ስለኢየሩሳሌም የተነገረ ትንቢት
ከቁጥር 1-4 ስለራእይ ሸለቆ የተነገረ ንግር (ትንቢት)
የራእይ ሸለቆ እግዚአብሔር ፍቃዱን የሚገልጥበትን ኢየሩሳሌምን የሚወክል መጠሪያ ነው
ነገር ግን እግዚአብሔር ፍቃዱን በሚገልጥበት በዚያ ስፍራ መንፈሳዊ እውርነት ነግሷል : እግዚአብሔር የንስሐ ጥሪ እያደረገ ከተማይቱ ግን በፌሽታና በፈንጠዝያ ተሞልታለች
መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ለሚደረግባቸው ስፍራዎች እጅግ ቅርብ ሆነን ከእግዚአብሔር ሀሳብ ጋር ልንተላለፍ እንችላለን
ሰዎች ልባቸው ከእግዚአብሔር ጋር ተቆራርጦ በአምልኮ ስፍራዎች ሊገኙ ብሎም ሊያገለግሉ ይችላሉ : እግዚአብሔር ሲናገር እየሰሙ አይሰሙም
የማቴዎስ ወንጌል 13
13 ስለዚህ እንዲህ በማለት በምሳሌ የምነግራቸው ለዚህ ነው፤
“እያዩ ስለማያዩ፣
እየሰሙ ስለማይሰሙ ወይም ስለማያስተውሉ ነው።(አ.መ.ት)
"4 ስለዚህ፣ “ከእኔ ራቁ፤
አምርሬ ላልቅስበት፣
ስለ ሕዝቤ ጥፋት፣
ልታጽናኑኝ አትሞክሩ” አልሁ።"(አ.መ.ት )
ኢሳያስ መፅናናትን ከፌሽታና ከፈንጠዝያ ማግኘት አልወደደም
እውነተኛ መፅናናት ሁኔታውን በመካድና በምድራዊ ነገር ደስታን ለመፍጠር በመሞከር ሳይሆን ከእግዚአብሔር ብቻ ይገኛል
8-11 "ችግሩን ስታዩ ምንጩን ሳትጠይቁ መፍትሄ ለማግኘት ተጣደፋችሁ"
- የጦር መሳሪያ ሰበሰባችሁ
- ቅጥሩን አደሳችሁ
- ውሃ አጠራቀማችሁ
ይህ ሁሉ በራሱ ችግር የለበትም : ችግሩ ግን "ይህን ሁሉ በመጀመሪያ አቅዶ ያደረገው እግዚአብሔር መሆኑ ትዝ አላላችሁም "
መንፈሳዊ እርምጃ ሳይወስዱ ቁሳዊ ነገሮችን ለማስተካከል እየሞከሩ ነበር
ከእግዚአብሔር ጋር ሳንስማማና እግዚአብሔርን ሳናስቀድም የምናቅደው እቅድ ከንቱ ነው
የማቴዎስ ወንጌል 6
33 ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል።
እቅድ ያለፀሎት የማይጨበጥ ምኞት ነው!
ቁጥር 12-13 የእግዚአብሔር ጥሪና የህዝቡ ተቃራኒ ምላሽ
እግዚአብሔር :-ኑ እዘኑ : አልቅሱ : ንስሐ ግቡ!
ህዝቡ :- ነገ እንሞታለን : እንብላ እንጠጣ!
1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15
32 እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ።
የትንሣኤ ተስፋ ያላቸውን አማኞች ተስፋቸው በዚህች ሕይወት ብቻ ከሆኑ ሰዎች ጋር እንዳይመሳሰሉ ይገስፃል
ከቁጥር 15-19 ለሼብና የተሰጠ ማስጠንቀቂያ
ሼብና በሕዝቅያስ ዘመነ መንግስት የነበረ ታላቅ ባለስልጣን ነበረ : ህዝቡን ከማገልገል ይልቅ ለራሱ ስምና ዝና የሚሮጥ : የህዝቡ መኖሪያ እየፈረሰ እርሱ መቃብሩን የሚገነባ ትእቢተኛና እራስ ወዳድ ሰው ነበር
የማርቆስ ወንጌል 10
43 በእናንተስ እንዲህ አይደለም፤ ነገር ግን ማንም ከእናንተ ታላቅ ሊሆን የሚወድ የእናንተ አገልጋይ ይሁን፥
መሪነት ባለአደራነትና አገልጋይነት ነው እንጂ ልዩ ጥቅም የሚያስገኝ ዕድልና የበላይነት አይደለም
"[19] እግዚአብሔር አንተን ከደረጃህ ዝቅ ያደርግሃል፤ ከሥራህም ያባርርሃል።"(አ.ት)
ሻሎም ቅዱሳን: የሰኔ ወር ንባብ ፕሮግራም ይህ ነው:: ፀጋ ይብዛላችሁ!
ሰኔ 1 አሞፅ 1-4
ሰኔ 2 አሞፅ 5-9
ሰኔ 3 ሚክያስ 1-3
ሰኔ 4 ሚክያስ 4-7
ሰኔ 5 ኢዩኤል 1-3
ሰኔ 6 አብድዩ
ሰኔ 7 ዮናስ 1-3
ሰኔ 8 ናሆም 1-3
ሰኔ 9 ዕንባቆም 1-3
ሰኔ 10 ሶፎንያስ
ሰኔ 11 ሐጌ 1-2
ሰኔ 12 ዘካርያስ 1-5
ሰኔ 13 ዘካርያስ 6-10
ሰኔ 14 ዘካርያስ 11-14
ሰኔ 15 ሚልክያስ 1-4
ሰኔ 16 ማቴዎስ 1-3
ሰኔ 17 ማቴዎስ 4-6
ሰኔ 18 ማቴዎስ 7-10
ሰኔ 19 ማቴዎስ 11-14
ሰኔ 20 ማቴዎስ 15-18
ሰኔ 21 ማቴዎስ 18-20
ሰኔ 22 ማቴዎስ 21-23
ሰኔ 23 ማቴዎስ 24-28
ሰኔ 24 ማርቆስ 1-4
ሰኔ 25 ማርቆስ 5-7
ሰኔ 26 ማርቆስ 8-10
ሰኔ 27 ማርቆስ 11-13
ሰኔ 28 ማርቆስ 14-16
ሰኔ 29 ሉቃስ 1-4
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
