cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Fantahun wakie ፋንታሁን ዋቄ

ወሳኝ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን የሚነኩ አገራዊ ጉዳዮችን የውይይት አጀንዳ እንዲሆኑ በማቅረብ አስተያየትና የመፍትሔ ምክረ ዐሳብ ይቀርቡበታል። የሚያወያዩ የቤተክርስቲያንና ስለአገር የሚቆረቆሩ ወገኖች የሚያቀርቡትን ሀሳብ እንጋራታለን። https://www.facebook.com/fwakie Join me also here https://www.youtube.com/@Orthodox_Secular_Fant

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
10 270
مشترکین
+1924 ساعت
+637 روز
+4430 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ሰራቄ ነፍሳት ሠረቀ እም ግበ ጓሣ ወአተግሃ ከመ ያፅልም ብርሃነ ክርስቶስ ዘኢይተከሃል። https://www.facebook.com/share/v/43uGfC5codHjBhrp/?mibextid=w8EBqM
نمایش همه...
Log in or sign up to view

See posts, photos and more on Facebook.

የነፈንታሁን ዋቄ አቋም ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያናችን ባሸከመቻቸው በ151ኛ በተመዘገበው ዳዊት በተናገረው መርሆ ላይ የተመሠረተ ሆኖ ከፋኖ መፈክር ጋራ ተቀራራቢ ቢመስልም፦ እነ ፈንታሁን ይዘው የተነሱት ከፋኖው ለየት ያለ ቅዱስ ጳውሎስ የመንፈስ ሰይፍ ብሎ የገለጸው ረቂቅ ትጥቅ ነው፡፡ ይህ ረቂቅ ትጥቅ በ149 ነኛው መዝሙረ ዳዊት ላይ እንደሚከተለው የሰፈረው ነው፡፡ “ወከመ ይእሥሮሙ ለነግስቶሙ በመዋቅህት ፡፡ ወለክብራኒሆሙኒ በእደ ሰናስለ ሐጺን፡፡ ከመ ይግበር ኩነኔ ዘጽሑፍ ላዕሌሆሙ፡፡ ክብር ይእቲ ዛቲ ለኩሉ ጻድቃኑ” የሚለው ቃል ነው፡፡ ይህም ማለት፦ “መሪወቻቸው ሞራለ ቢሶች ሲሆኑ እግሮቻቸውን በእግር ብረት እጆቻቸውን በዛንጅር አስረው በተጻፈው ሕጋቸው ይቀጧቸው ዘንድ ለተመረጡት እድል ተሰጣቸው” ይህን የዳዊትን ሀሳብ ክርስቶስ ለዮሐንስ በራእይ “ወዘሰ በመጥባሕት ይቀትል ሀለዎ ይሙት በመጥባህት፡ ወዘሂ ውእቱ ትዕግስቶሙ ወብጽዕት ሃማኖቶሙ ለቅዱሳን፡ ወኢአንክሮቱ ለሰይጣን” ብሎ ገለጸው ፡፡ (ራእየ ዮሐንስ 13፡ 10)፡፡ እነ ፈንታሁን ብዙወቹ ከሚከሰሱበት ከሰይጣን ወጥመዶች ከዝሙት ከስለት ገንዘብ ከዘረፋና ከመወላወል ገለል ያሉ እንደ ቀዳሜ ሰማእቱ ቅዱስ እስጢፋኖስ “እናንት አንገተ ደንዳኖች ልባችሁና ጆሯችሁ ያልተገረዘ እውነቱን የምትቃወሙ” (የሐዋ 7፡51) እያሉ ከቀኖናው ከነገረ መለኮቱ ርቀው ያሉትን ለመገሰጽ እግዚአብሔር ያደላቸው በልዕለ አእሞሮ ላይ ያሉ ናቸው፡፡ 4ኛ ዶክተር ዮናስ ለሲኖዶሱ የሰጡትን ከንቱ ውዳሴ የቤተ ክርስቲያንችን አስተምህሮ አንኮታኩቶ ሲጥለው ከዚህ በታች የሰፈረውን እንመልከት፡፡ “ወኤጲስ ቆጶስሰ ዘነሥአ ክህነተ እምእግዚአብሔር ከመ የዐቀብ ሥጋ ውሰነፍስ እምኀጉል በከመ ነፍስ ትከብር እምሥጋ ከማሁ ክህነትኒ ትትሌዓል በክብር እመንግሥት ወይእቲ ተ አሥሮ ለዘይደልዎ ኩነኔ ወትፈትሖ ለዘይደልወ ፋትሐ፡፡ ወበከመ ክህነት ትትሌዐል እመንግሥት ወከማሁኬ ትትሌዐል ኩነኔሁ ለዘይትቃረና ለክህነት ይፈደፍድ እምኩነኔሁ ለዘይትቃወሞ ለንጉሥ”(ፍ አ 9፡289_290) ፡፡ ማለትም፦በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ የተመሠረተ ክህነት በምዳራዊ ፈቃድ ጉስቁላና በቅድስና ተዐቅቦ የተለየ ስልሆነ በምድራዊ ፈቅድ ላይ ከተጻፈው ሕግ በላይ ነው፡፡ በብጽዕናውና በቅድስናው ከምድራዊው መንግሥት በላይ ስለሆነ ከምድራዊውም ሕግ በላይ ነው፡፡ ምድራዊውንም ሰማያዊውንም ሕግ በምሳሌነት አክብሮ በማስከበር ከመንግሥት የላቀ ከፍተኛ ልዕለ አእምሮ አለው፡፡ ሲኖዶሱ በዚህ ሁሉ ድርብርብ ተቀብዖቱ ከመንግሥት የላቀ ሥልጣንና ሀላፊነት አለበት፡፡ ምድራዊው መንግሥት በሥጋዊ ፍላጎት ተፈትኖ ሀላፊነቱን ረስቶ ራሱ ከሰራውና አስፈጽመዋለሁ ብሎ ከማለለት ህግ በታች ሲወድቅ ፦ ሲኖዶሱ የመገሰጽ ብሎም ህዝብ የካደው መንግስት የተሰነዘረበትን የአመጽ ዱላ ሰባብሮ እንዲጥለው የማስተማር ግዴታ አለበት፡፡ ህዝብ የተሰነዘረበትን የአመጽ ብትር ሰባብሮ እንዲጥለው የተቀደሰው ሲኖዶስ በሚያደርገው ቅስቀሳ፡ ከሀዲው መንግሥት ከሚሰነዘረበት የአመጽ በትር ሲኖዶሱ ሳያፈገፍግ ከህዝብ በፊት ድብደባውን የመቀበል ግዴታ አለበት፡፡ ዶክተር ዮናስ ለዘመናችን ሲኖዶስ የሰጡት ከንቱ ውዳሴ ተንኮታኩቶ እንደወደቀና እነ ፈንታሁን ዋቄ በቀኖናችን ላይ መቆማቸውን ከዚህ በላይ ክ 1 እስከ 4 በዘረዘርኳቸው አንቀጾች ካሳየሁ በኋላ ለዶክተር ዮናስና ለመሰሎቻቸው ከዚህ በታች በማቀርባት በ5ኛዋ አንቀጽ የተማኅጽኖ ጥሪ በማቅረብ ሀሳቤን እቋጫለሁ፡፡ 5ኛ ለዶክተር ዮናስና ለመሰሎቻቸው የቀረበ የተማሕጽኖ ጥሪ፦ ዶክተር ዮናስ ብሩ ሆይ! ለጽሑፈዎ መነሻ አድርገው ለፋኖና ለነ መመምህር ፋንታሁን ለሰጡት ምክር ራሰዎ “The Imperative Comparative: Lessons from the EOTC and Fano” ያሏትን እኔም ሐሳበዎን ለመቃወም “The Imperative Comparative: Lessons from the EOTC and Fano” ያሏትን እንደመግቢያ አድርጌ ተጠቅሜአታለሁ፡፡ የተቃውሞ ጽሑፌን በገባሁባት ለመውጣት ብቻ ሳይሆን ለማቀርብለዎ ጥሪ መገቢያ ካደረኳት ሌላ የተሻለ ሀሳብ ስላላገኘሁ ጭምር እንደ መግቢያ ያደረኩትን ለመጥሪያነት ተጠቅሜ መደምደሚያ ባደርጋት ስነጽሑፍ ነውር አያደርግብኝምና በመግቢያየ የጀመርከበትን የተቃውሞ ሐሳብ የጥሪየ ተማኅጽኖ አድርጌ ሳቀርብለዎ በደጊመ ቃልነት እንዳይሰለቹ አደራየ ጥብቅ ነው ፡፡ የዘመናችንን ሲኖዶስ ከፋኖ ጋራ ፖለቲከኞችን ከነፈንታሁን ዋቄ ጋራ በማነጻጸር ሲኖዶሱን እያደነቁ፦ ፋኖንና የፋኖ ደጋፊወችን ከፈንታሁን ዋቄ ጋራ ደምረው የነቀፉበት ሀሳብ እንድንማርበት ያቀረቡልንና በመቀጠለም “The same screwed up culture is what has allowed መምህር Fantahun Waqe to jump out of the woods of the 18 th century and cacophonize the 21 st century” ብለው ያቀረቡትን ከቤተ ክርስቲያናችን መርሆ ጋራ መጋጨቱን አሳይቻለሁ፡፡ የገለጹበት መንገድ ከቤተ ክርስቲያናችን ቀኖናዊ መርሆ ጋራ የተቃረነ ቢሆንም፡ ባነጋጋሪነቱና በቀስቃሽነቱ አእምሮየን ቀስቅሶ የሲኖዶሱን ዝቅጠት በትኩረት እንድመለከተው አድርጎኛል፡፡ ይዝለቁበት አይዘለቁበት እርግጠኛ ባልሆንም የዘመናችን ዲያቆናት እነ ፈንታሁን ዋቄ አሁን የሚመሩበት መንገድ ቀዳሜ ሰማእት የምንለው ቅዱስ እስጢፋኖስ የሄደበትን ሐዋርያዊ ትውፊት እንዳይ አድርጎኛልና አመሰግነወታለሁ፡፡ ይሁን እንጅ እንደ መልካም ምሳሌ አድርገው ያቀረቡት ሲኖዶስ በቀኖናችን ሲመዘን መወገዝ መወገድ የሚገባው እንጅ ለመልካም ምሳሌነት መጠቀስ እንደማይገባው ራሱ ሲኖዶሱ በራሱ ይመስክራል፡፡ እርሰዎ የሲኖዶሱን ስህተት እንደ መልካም ምሳሌ አርገው ማቅረበዎ እኔ አይደለሁም ቀኖናችን ይቃወመወታል፡፡ ታዲያ ይህን ቀኖናዊ ተቃውሞ በአኮቴት ተቀብለው አመለካከተወን አስተካክለው፡ ለቤተ ክርስቲይናችንም የሚጠቅመው ቀኖናውን መከተል መሆኑን ተገንዝበው ፡ ሲኖዶሱ ብልጽግናን መከተሉን እርግፍ አርጎ ትቶ ቀኖናችንና ዶክትሪናችንን በመከተል እነ ፋንታሁን ጸንተው የቆሙበትን የቅዱስ እስጢፋኖስን ምሳሌ ይከተል ዘንድ በነካ እጀዎ በጽሑፍ የጥሪ መልእክት እንዲያቀርቡለት በትህትና እጠይቀወታለሁ ፡፡ ይህን ቢያደርጉ ለቆሙላት አገረዎም ለቤተ ክርስቲያናችንም እንደሚበጅ እርግጠኛ ሆኜ ልገልጽለወ እወዳለሁ፡፡ እግዚአብሔር መልካም መሪወችን ለኢትዮጵያ ይፍጠር !
نمایش همه...
💯 4
00:57
Video unavailableShow in Telegram
ሰረቀ ስለ አማራ 1.mp4
نمایش همه...
2.15 MB
2
አምስቱ የጎሣ ጳጴሳት አዕማደ ምሥጢራት:- የሕወሃት እና የኦነግ-ኦሮሙማ/ብሎጽግና ጳጳስ ለመሆን ማሟላት ከሚገባህ መስፈርት መካከል 1) በጥምቀት ሰው ሁሉ ከሥላሴ በመወለድ አንድ አዲስ ዘር መሆኑን በመካድ ሰዎችን በነገድና በቋንቋ የሚለያዩና የሚበላለጡ መሆናቸውን ማመን እናጰየሐዋርያት ቀኖናን መኔድ 2) አማራ የተባለ ነገድ መጥላት 3) የኢትዮጵያን ረዥምና አዎንታዊ ታሪክ በጎሣ ርእዮተ ዓለም አንጻር በሐሰት ትርክት መቀየርን መቀበል 4) ክብረ-ሰብእ ተጨፍሎቆ በበክብረ ጎሣ/ብሔረሰብእ መቀየሩን ማመን 5) ታላቋቋን አገር በትኖ በአገር ውስጥ አገራት ለመፍጠር አማራና ኦርቶዶክስ ክርስትናን ማጥቃት ናቸው
نمایش همه...
💯 5
00:57
Video unavailableShow in Telegram
ሰረቀ ስለ አማራ.mp4
نمایش همه...
2.15 MB
🤣 5 2💯 1
የሕዝብ መከራ መሠረታዊ መንስዔና መድኀኒቱ - የግል አስተያየት (ፋንታሁን ዋቄ_ Fantahun Wakie) https://youtube.com/watch?v=6KxGag2m09k&si=gahIHYBI906fHSJE
نمایش همه...

💯 4
نمایش همه...
ፋንታሁን ዋቄ Fantahun Wakie ገጽ

https://youtu.be/D4vt0bh_pDs?si=f9q6AHQryKuVr2kv

💯 3
نمایش همه...
ኑ ከመከራችን ስለምንወጣበት እንማከር (የፋንታሁን ዋቄ የግል አስተያየት)

ኑ! ከዚህ ከምንገኝበት ሁለገብ አገራዊ መከራ እንዴት እንውጣ ብለን እንመካከር፡፡ የግለሰብ፣ የማኅበረሰብ እና የአገር መከራ የሚፀናው በየደረጃው በግለሰብ፣ በማኅበረሰብ እና በአገርደረጃ በመንግሥት ሥርዓትን በሚመሩ ሃይማኖትን በሚያስተምሩ፣ ባህልን በሚያስጠብቁ ሰዎች ደረጃ ሁሉ ጥመት፣ ክፋት፣ ኃጢአት፣ ርኵሰት እየበዛ በተቃራኒው ደግሞ ርቱዕነት፣ መልካምነት፣ ቅድስና፣ እምነት ሲያንስ ነው። እንደ መፍትሔ፡- 1) ንስሐ መግባት፣ 2) መከራ ለሚቀበሉት ድምጽ መሆን፤ 3) ክፉ ሰዎችን ከቤታችን ጀምረን ማስተካከል፤ 4) የንዑስ-ማንነት ፖለቲካ የሚፈጥረው የዘረኝነት ደዌ ወደ ልጆቻችን እንዳይጋባ መከላከል፤ 5) በመከራው የፀናባቸውን እንደቤተሰባችን አድርገን መርዳት፤ 6) ለመከራችን ምክኒያት የሆነው ራሱን ከሰብእና፣ ከዜግነትና ሃይማኖት በላይ ያደረገውን የንዑስ ማንነት ፖለቲካ መቃወም፣ እና የመከራችን ምንጭ መሆኑን ሳይታክቱ ማጋላጥ፣ 7) ከመልካሞች ጋር በመደራጀት ክፉዎችን መከላከል፣ ማሸነፍና ሰው ማድረግ፤ 8) በየባህላችን፣ እምነቶቻችንና የማኅበረሰብ መዋቅሮቻችን ውስጥ ክፋትን የሚያገለግሉትን ለማስቆም የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ፤ 9) አገር ውስጥ ለሚገኙ የክፋት ቡድኖች ሁለገብ ድጋፍ የሚሰጡ የውጭ አካላትን ማወቅና መቃወም፤ ለተራ ወሬና ጊዜ ማጥፊያ ሳይሆን የሰውን ልጆች ለማዳን መጠቀም።

💯 4
ቀጥታ ከግንባር :- የአማራ ፋኖ በጎጃም ከመተከል እና ቤንሻንጉል ጉምዝ ነዋሪዎች ጋር የተደረገ ህዝባዊ ውይይት https://youtube.com/watch?v=3Lvb1hNAYB4&si=X97M-hN73_NuEXBg
نمایش همه...

یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.