ኤፌሶን ሚዲያ
رفتن به کانال در Telegram
1 277
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
در حال بارگیری داده...
کانالهای مشابه
ابر برچسبها
هیچ دادهای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
مارس '24
مارس '24
+3
در 0 کانالها
فوریه '24
+8
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '24
+2
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '23
+5
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '23
+4
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '23
+5
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '23
+8
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '23
+46
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '23
+8
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '23
+7
در 0 کانالها
Get PRO
مه '23
+6
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '23
+11
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '23
+8
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '23
+9
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '23
+65
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '22
+97
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '22
+211
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '22
+45
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '22
+79
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '22
+65
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '22
+89
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '22
+35
در 0 کانالها
Get PRO
مه '22
+27
در 0 کانالها
Get PRO
آوریل '22
+66
در 0 کانالها
Get PRO
مارس '22
+209
در 0 کانالها
Get PRO
فوریه '22
+5
در 0 کانالها
Get PRO
ژانویه '22
+19
در 0 کانالها
Get PRO
دسامبر '21
+14
در 0 کانالها
Get PRO
نوامبر '21
+94
در 0 کانالها
Get PRO
اکتبر '21
+113
در 0 کانالها
Get PRO
سپتامبر '21
+114
در 0 کانالها
Get PRO
اوت '21
+41
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئیه '21
+112
در 0 کانالها
Get PRO
ژوئن '21
+394
در 0 کانالها
Get PRO
مه '21
+338
در 0 کانالها
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 10 مارس | 0 | |||
| 09 مارس | 0 | |||
| 08 مارس | 0 | |||
| 07 مارس | 0 | |||
| 06 مارس | +1 | |||
| 05 مارس | +2 | |||
| 04 مارس | 0 | |||
| 03 مارس | 0 | |||
| 02 مارس | 0 | |||
| 01 مارس | 0 |
پستهای کانال
*[ታኅሣሥ 1 የተወለደው ነቢዩ ኤልያስ የነበረበት የቀርሜሎስ ዋሻ ይኽ ያለኹበት ነው።]*
*✍️በመጋቤ ሐዲስ ዶክተር ሮዳስ ታደሰ*
💥 የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደሚያስረዱት ነቢዩ ኤልያስ ትውልዱ ከነገደ ሌዊ ሲሆን የአባቱ ስም ኢያስንዩ የእናቱ ስም ቶና ይባላሉ፡፡
💥 ታኅሣሥ 1 በተወለደ ጊዜ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት እንደሚነግሩን “እስመ በዕለተ ተወልደ ርእየ አቡሁ አርባዕተ ዕደወ ብርሃናውያነ እንዘ ይሰግዱ ሎቱ ወጠብለልዎ በእሳት ህየንተ አጽርቅት ዘይጠበለሉ ቦቱ” ይላል በተወለደ ጊዜ ብርሃን የለበሱ 4 ሰዎች ሲሰግዱለትና ሕፃናት በሚጠቀልሉበት ጨርቅ ፈንታ በእሳት ሲጠቅልሉት አባቱ ተመልክቷል፡፡ ለዚህ ነው በትርጓሜ ወንጌል “ዘጥብሉል በአጽርቅተ እሳት” የሚለው፡፡
✍️ነቢዩ ኤልያስ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ወደ 100 ጊዜያት የሚደርስ ተጠቅሷል፡፡ ከሠራቸው ሥራዎች ውስጥ:-
💥 አክአብና ኤልዛቤል ጣዖት በማምለከታቸው ኤልያስ 3 ዓመት ከ6 ወር ዝናብን እንዳይዘንብ በጸሎቱ አቁሟል (1ኛ ነገ 17)
💥 የሰራጵታዋን መበለት የሞተ ልጇን አስነሥቷል (1ኛ ነገ 17:19)
💥 ያቀረበውን መሥዋዕት እሳት ከሰማይ ወርዶ በልቶለታል (1ኛ ነገ 18)
💥 ከ3 ዓመት ከ6 ወር በኋላ ቀርሜሎስ ወጥቶ በመጸለይ ዝናብ እንዲዘንብ አድርጓል (1ኛ ነገ 18)
💥 አካዝያስ የላካቸውን 50 አለቃዎች እሳት ከሰማይ አውርዶ አቃጥሏል (2ኛ ነገ 1)
💥 በመጐናጸፊያው የዮርዳኖስን ወንዝ ከፍሏል (2ኛ ነገ 2:14)
💥 በእሳት ሠረገላ በዐውሎ ነፋስ ወደ ሰማይ ወጥቷል (2ኛ ነገ 2:11)
💥 በደብረ ታቦር ጌታ ምስጢረ መንግሥቱን ሲገልጽ ከሙሴ ጋር ዐብሮ ተገኝቷል (ማቴ 17:4)
💥 ዳግመኛ በመምጣት በሐሳዌ መሲሕ ጊዜ መጥቶ ሰማዕትነትን ይቀበላል (ማቴ 17:11)
👉 ከኢትዮጵያ ሊቃውንት ውስጥ ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ በተአምኆ ቅዱሳን መጽሐፉ፦
“ሰላም ለኤልያስ ነቢይ ቴስብያዊ ኮሬባዊ ታቦራዊ
ሰማየ ዘለጐመ
ወከልአ ዝናመ፤
ቃለ ጸሎቱ ዘተሰምዐ ውስተ ዕዝኑ ለአዶናይ
ወአውረደ እሳተ እምሰማይ እስከ በልዖ ለማይ፤
ዘዐደወ ብሔረ ተድላ
ተጽኢኖ ዘእሳት ሠረገላ፡፡
(ቴስቢያዊ (የቴስቢያ ሰው)፤ ኮሬባዊ (ወደ ኮሬብ ተራራ የወጣ)፤ ታቦራዊ (በታቦር ተራራ የተገኘ)፤ ዝናብ እንዳይዘንብ ሰማይን የለጐመ ለኾነ፤ የጸሎቱ ቃልም በአዶናይ ዦሮ ውስጥ ለተሰማ፤ ውሃውን እስኪበላ ደርሶ እሳትን ከሰማይ ያወረደ ለኾነ፤ በእሳት ሠረገላ ተጭኖ ወደ ተድላ ደስታ ቦታ ለገባ ለነቢዩ ለኤልያስ ሰላምታ ይገባል)።
💥ሊቁ አርከ ሥሉስም በአርኬ መጽሐፉ ላይ፦
"ሰላም ለከ ዐራጌ ሰማያት ለአዕርፎ
ሕይወተ ዓለም ምድራዊ በተናግፎ
በእንተ ምግባሩ ምንንት ለአክአብ እንተ ትዘልፎ
እንተ ነሠትከ ምሕራማተ ወቀጥቀጥከ ግልፎ
በስብሐቲከ ኤልያስ ተሰባሕከ እፎ”
(ምድራዊ የሆነ የዓም ሕይወትን አራግፈህ ለማረፍ ወደ ሰማያት ያረግህ ለሆንክ ለአንተ ለኤልያስ ሰላም እላለሁ፡፡ አክአብን ለተናቀ ሥራው እየዘለፍከው ጣዖታትን የቀጠቀጥክ ማምለኪያዎቹን ያፈረስክ በምስጋናህ ምንኛ ተመሰገንህ)።
✍️ “ምስለ ኤልያስ ሰማየ ዘለጐመ
ከመ ኢያዝንም ዝናመ
በሠረገላ በርህ ንዒ ከመ ትባርኪ ዓለመ
ማርያም ጸጋዊት ለምእመናንኪ ሰላመ
እለ ክህላ ከናፍርኪ አፈ ነደ እሳት ስዒመ
ይረስያ ማሕሌተነ ኀቤሆን ጥዑመ”
(ነዳዲ እሳትን መሳምን የቻሉ የቻሉ ከናፍሮችሽ በነርሱ ዘንድ ማሕሌችን የጣፈጡ ያደርጉ ዘንድ ለምእመናን ሰላምን የምትሰጪ ማርያም ዓለምን ትባርኪ ዘንድ ዝናብን እንዳይዘንብ ሰማይን ከለጐመው ከኤልያስ ጋር በብርሃን ሠረገላ ነዪ)።
💥 ከመልክኡ ውስጥም እንዲኽ ይላል፦
"ሰላም ለአዕዛኒከ እለ ሰምዐ ነገረ
እምእግዚአብሔር በኮሬብ ቀዳሚ ወበታቦር ካዕበ
ኤልያስ ነዓ ምስለ ማርያም ወትረ
ኀበ ንገብር በዓላ ወበዓለከ ኅቡረ
ከመ ተሀበኒ ተምኔትየ ኩሎ አሚረ"
(አስቀድሞ በኮሬብ ዳግመኛ በታቦር ከእግዚአብሔር ቃልን ለሰማ ዦሮኽ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ ምኞቴን ኹልጊዜ ትሰጠኝ ዘንድ በዓሏን ከበዓልኽ ጋር በምናደርግ ጊዜ ከማርያም ጋር ዘወትር ና)
[የነቢዩ ኤልያስ በረከት ይደርብን]
[በአስተያየት መስጫው ላይ ታኅሣሥ 1 ልደቱን የምናከብርለት ነቢየ እግዚአብሔር ኤልያስን ብቻ አመስግኑት፤ በጸሎቱ እንዲጠብቃችሁ በጎ መሻታችኹን ንገሩት]
| 2 | Photo from Solyana Shabel | 0 |
| 3 | *_<<የመነኩሴው_ፈሊጥ!>>_*
መጾም ያቃተውን ሰው ጹም፣ መመጽወት የተሳነውን መጽውት፣ መራመድ የማይችለውን ሩጥ የሚሉ መካሪዎች ብዙ ናቸው፡፡ መራመድ የማይችል እንዴት መሮጥ እንዳለበት ከማሳየት ይልቅ ቀንበር ማክበድ ጠባያችን ሆኗል፡፡ ይህ የሚያሳየው ቃሉ እንጂ ተግባሩ የተለየን መሆኑን ነው፡፡ በተግባር መግለጥ ብንችል ኖሮ፣ ማገዝ ቢያቅተን እናሯሩጠውና ሰውነቱ ሞቆ ተጋድሎ ሲጀምር እናፈገፍግ ነበር፡፡ እኛ ግን ልምድ የሌለውን ሁሉ ተሸከም ማለት ይቀለናል፡፡ ከባለ ግመሉ ከአባ ቆሪር ምክር ለመመጽወት የሄደ ክርስቲያን ግመሉ ከሚችለው በላይ ስለጫነው አንተ አቅም አጥተህ ምክር ለመቀበል መጥተህ ሳለ ግመሉን ካለ አቅሙ ለምን ጫንከው ተብሏል፡፡
ከዐቅማቸው በላይ ተሸክመው የከበዳቸውን ሰዎች በማገዝ ሸክሙ ሳይከብዳቸው፣ ከክርስቲያናዊ ተጋድሎ ሳያፈገፍጉ በእምነት እንዲኖሩ ማገዝ ከዘመናችን የሃይማኖት ሰዎች የሚጠበቅ መሆኑን ለማስታወስ የአባ ዳንኤልን ፈሊጥ በአብነት እጠቅሰዋለሁ፡፡ አንድ አባ ዳንኤል የሚባል መነኩሴ ነበር፡፡ የደከመ ባገኝ አግዛለሁ እያለ በጨረቃ ከበዓቱ ወጥቶ ገዳማውያን በሚገኙበት በረሓ ይዞር ነበር፡፡
በአንድ ወቅት የማትሠራው ኃጢአት ያልነበር፣ ከጽድቅ ተግባር የማትተዋወቅ ሴት አገኘ፡፡ አባ ዳንኤልም ሴቲቱን ወደ ሴቶች ገዳም ወስዶ ልብላ ካለች ትብላ፣ ልተኛ ካለች ትተኛ፣ የፈቀደችውን ሁሉ ታድርግ፣ የገዳሙ ሕግ አይፈቅድም በማለት ቀንበር አንዳታከብዱባት ብሎ ለእመምኔቷ አስረክቧት ሔደ፡፡ እመምኔቷም እንደታዘዘችው አደረገች፡፡ ሴቲቱ በፈለገች ጊዜ ትበላለች፣ ስትፈልግ ትተኛለች፡፡ ያሰኛትን ታደርጋለች፡፡ ግን ደስታ የላትም፤ አብረዋት የሚኖሩት መነኮሳት ቤተ ክርስቲያን አድረው፣ በሥራ ተጠምደው ሲኖሩ ተመለከተች፡፡ እሷ በልታ ይርባታል፡፡ እነሱ ሳይበሉ አይራቡም፣ እሷ ተኝታ ይደክማታል፣ እነሱ ቆመው ውለው፣ ቆመው አድረው ድካም አያውቁም፡፡ ቀስ በቀስ መገረም፣ ከዚያም በሕይወታቸው መቅናት ጀመረች፡፡
ምግብ ሲያቀርቡላት እስከ ሦስት ሰዓት ልቆይ ማለት ጸሎት አድርጋ መብላት ተለማመደች፡፡ ቆየችና እስከ ስድስት ልቆይ አለቻቸው ከዚያም እስከ ዘጠኝ፣ ከዚያም በ24 ሰዓት አንድ ጊዜ መመገብ ጀመረች፡፡ ከዚያም ከሳምንት አንድ ቀን ብቻ መቅመስ በመጨረሻም በዓቷን ዘግታ በሦስት ሳምንትም፣ በወርም በሕይወት ለመቆየት ያህል መቅመስ ደረሰች እንዲህ ድክመታችን ታግሠው ለክብር የሚያበቁን ባለ ፈሊጥ መምህራን ማግኘት ለዚህ ዘመን እንዛዝላ ተሸካሚ ከዕንቊ የበለጠ ስጦታ ነው እላለሁ፡፡
#ወስብሐት_ለእግዚአብሔር | 0 |
| 4 | Photo from Solyana Shabel | 0 |
| 5 | "ይህን ያኽል ትሕትና እንደምን ያለ ትሕትና ነው፣ ይህን ያህል ትዕግሥት እንደምን ያለ ትዕግሥት ነው፣ ይህን ያህል ቸርነት እነደምን ያለ ቸርነት ነው፣ ይህን ያህል ሰውን ማፍቀር እንደምን ያለ ፍቅር ነው፣ ፍቅር የአምላክን ልጅ ከዙፉኑ ሳበው እስከ ሞትም አደረሰው በደል የሌለበትን እንደ በደለኛ ሰቀሉት፣ አዳምን የፈጠሩ እጆች በመስቀል ቀኖት ተቸነከሩ..."
*ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ* | 0 |
| 6 | *[ አቤቱ ፥ ነፍሴን ከሲኦል አወጣሃት ! ]*
" ጌታዬና መድሃኒቴ ኢየሱስ ክርስቶስ የደረሰበትን ጉስቁልና ሊተካከል የሚችል ጉስቁልና እንደምን ያለ ነው? ቀላያት ፊቱን በተመለከቱ ጊዜ የሚንቀጠቀጡለት ፀሐይ ብርሃኗን የምትከለክልለት : ጨረቃ የምታለቅስለት : ከዋክብት የሚረግፉለት : ክፉዎች አይሁድ ተፉበት : እጃቸውን አክርረው መቱት : ከስድብ ሁሉ የከፋ ስድብ ሰደቡት::
ስድባቸው እንዲሁ የቃላት ብቻ አልነበረምና ምራቅና ቡጢም አለበት እንጂ : ይህ ብቻ አይደለም : - ክርስቶስ ሆይ በጥፊ የመታህ ማን ነው? ትንቢት ተናገርልን ¡ የሚል ስላቅም አለበትና:: ጌታዬና ንጉሴ መከራ ያልደረሰበት አካል አልነበረውም:: ጭንቅላቱ ላይ የእሾኽ አክሊል ደፉበት : ፊቱን በጥፊ መቱት ፡ ትከሻውን መስቀል አሸከሙት : እጁን በችንካር ቸነከሩት : እግሩን በምስማር ቸነከሩት : አፉን ኮምጣጤ አጠጡት : መላ አካልቱን በጅራፍ ገረፉት :: ወዮ ! እንዲህ ያለ መውደድ እንደምን ያለ ፍቅር ነው፡፡ "
"አቤቱ፥ ነፍሴን ከሲኦል አወጣሃት ፥ ወደ ጕድጓድም እንዳልወርድ አዳንኸኝ።" [መዝ.፴፥፫]
[ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ]
| 0 |
| 7 | https://youtu.be/DyIHJEzy5qE?si=xDwdR6bmRqrGZaX2
[ቻነሌን ሰብስክራይብና ሼር በማድረግ አገልግሎቴን ደግፉ፥ መልዕክቱ በስፋት አንዲዳረስ በማድረግ የድርሻችሁን ተወጡ። አመስግናለሁ።] | 0 |
| 8 | https://youtu.be/Uz-rX2Y3gTs?si=Wft-8nhFlweq_7ty | 0 |
| 9 | https://youtu.be/Uz-rX2Y3gTs | 0 |
| 10 | https://youtu.be/8th0O3CVdb0 | 0 |
| 11 | በብሔር ፖለቲካ የቡድን እሳቤ ተሸንፋችሁ እንወክለዋለን በምትሉት ጎሣ ስም በኦርቶዶክሳዊነት ላይ ተረከዛችሁን ላነሳችሁ የጥምቀት ልጆች ሁሉ ትድረስልኝ (በአራት ክፍል ተከፍሎ የተላከ ሲሆን በሚቀጥሉት ሶስት ቀናት በየቀኑ ከጠዋቱ 12፤ሰዓት ጀምሮ ይለቀቃል)፤ ያጋሩ — ግብረ መልስ ይላኩ፥ ይወያዩ፥ ይከራከሩ፥ ራሳችንን እንፈትሽበት
https://youtu.be/PkFtPLXeLUw?si=0p60_-v7KgRJmKCh | 0 |
| 12 | ደብተራ ፍጽምት ዘጳውሊ፤
ወማኅደሩ በጽድቅ ዘገብራ ከሃሊ፤
ፈለሰት እምዘይበሊ ኀበ ኢይበሊ፤
በመሰንቆሁ እንዘ የኃሊ፤
ዳዊት አቡሃ ዘወልዳ ወዓሊ።
«ለፈጠራት ለከሃሌ ኩሉ አምላክ በእውነት ማደሪያው የሆነች የጳውሎስ ፍጽምት ደብተራ የተባለች ድንግል እመቤታችን የልጇ ክርስቶስ ሎሌ/ባለሟል የሆነ ቅዱስ ዳዊት በበገናው እያመሰገናት/እየዘመረላት ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ (ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት) ተሻገረች።»
(ዚቅ ዘቅዱስ ያሬድ ነሐሴ ፲፮)
https://t.me/Epheson | 0 |
| 13 | بدون متن... | 0 |
| 14 | https://youtu.be/PkFtPLXeLUw | 0 |
| 15 | አባቴና እምነቱ - Copy.pdf | 0 |
| 16 | የጽድቅ በር (አለቃ አያሌው ታምሩ).pdf | 0 |
| 17 | የኢትዮጵያ ታክ በ3 ህግጋት.pdf | 0 |
| 18 | “....አባቴ በአዲስ አበባ መኖር ከጀመረበት ጀምሮ ከታዘባቸው ነገሮች ውሰጥ ዋነኛው ወጣቱ ትውልድ ለአገሩና ለራሱ ታሪክ የነበረው እላዋቂነትና ቸልተኛነት ነበረ፡፡ የኢትዮጵያንና የቤተ ክርስቲያንን ታሪክ አለማወቅ፤ አልፎ ተርፎም በውጪው ዓለም ባህል የመማረክና የራሰን ታሪክና ማንነት የማቃለል ዝንባሌ በውጣቱ ዘንድ አንደ ወረርሽኝ ተዛምቶ የራሰን ታሪከ እያናናቁ የሌሎችን የማዳነቅ ዝንባሌ ይታይ ነበር፡፡ እንደ አባቴ እምነት የዚያን ዘመኑ ወጣት ለዚያ ሁኔታ ያጋለጠው የኢትዮጵያ ጥንተ ጠላቶች በዘመናዊ ትምህርት ሰበብ ያስፋፉት ውስጠ መርዝ ትምህርት ነው፡፡
ምዕራባውያን ኃይሎች በቅኝ ግዛትና ጭቆና ሥር ወድቀው ለኖሩ የዓለም ሕዝቦች የነጻነት ተምሳሌት በሆነችው ኢትዮጵያ ላይ ልዩ ትኩረት በሰጡበት ዘመን፣ የረዥም ዘመን ነጻነቷን ሃይማኖቷንና እንድነቷን አጥፍተው በቁጥጥራቸው ሥር ለማዋል ዘመናዊ ትምህርትን እንደ መሣሪያ መጠቀማቸውን የሚመሰክረው በእነሱ የትምህርት ሥርዓት ውስጥ ያለፈው ትውልድና ይኼው ትውልድ በአገሪቱ ሁለንተናዊ ገጽታ ላይ ያሳረፈው አሻራ ነው፡፡
ጦርነትና ሚሲዮናዊ ተልዕኮዎች በኢትዮጵያ ላይ የነበራቸውን ሕልም ሊያሳኩላቸው እንዳልቻሉ የተረዱት ባዕዳን ኃይሎች በዘመናዊ ትምህርትንና በሥልጣኔ ሰበብ የኢትዮጵያን ወጣቶች አእምሮ ለመቆጣጠርና ሐሳባቸውን ለማሳካት ሠርተዋል፡፡
በዚህም የተነሣ የስንት ጀግኖች ሕይወት የተሠዋለትንና ብዙ ዋጋ የተከፈለለትን ኢትዮጵያዊነትን በዘርና በሃይማኖት ልዩነት ለመነቅነቅ ብዙ በቅተዋል፡፡ ዘርን ከዘር፣ ሃይማኖትን ከሃይማኖት ለማቃረን የጠቅማሉ ብለው ያመኑባቸውን የቂም ፍሞች በየተማሪው ልብ ውስጥ አዳፍነዋል፡፡...”
(አባቴና እምነቱ-ገጽ-53-ከሥምረት አያሌው)
አለቃ አያሌው ታምሩ ነሐሴ 14 1999 ዓ.ም አረፉ። | 0 |
| 19 | بدون متن... | 0 |
| 20 | በዓለ ደብረ ታቦር እና ቡሄ
ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን ለገለጠበት ለበዓለ ደብረ ታቦር እንኳን በሰላም አደረሰን!
ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ታቦር ብርሃነ መለኮቱን፣ ክብረ መንግሥቱን መግለጡን በማሰብ በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን በዓሉ በድምቀት ይከበራል፡፡ ይህ በዓል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ዘንድ ‹ቡሄ› በመባል ይታወቃል፡፡ ቡሄ ማለት ‹መላጣ፣ ገላጣ› ማለት ነው፡፡ በአገራችን ክረምቱ፣ ጭጋጉ፣ ደመናው ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታይበት በዚሁ በዓል አካባቢ ስለ ኾነ በዓሉ ‹ቡሄ› ተብሎ ይጠራል፡፡ በዓለ ደብረ ታቦር ጌታችን ምሥጢረ መለኮቱን የገለጠበት፤ ብርሃን የታየበትና ድምፀ መለኮቱ የተሰማበ ዕለት ስለ ኾነ ‹የብርሃን› ወይም ‹የቡሄ› በዓል ይባላል፡፡
ቡሄ ሲመጣ የክረምቱ ጨለማነት አልፎ ወደ ብርሃን፣ ወደ ጥቢ የሚያመራበት፤ ወደ መፀው የሚገባበት፤ ወገግታ የሚታይበት፤ ሰማይ ከጭጋጋማነት ወደ ብሩህነት የሚሸጋገርበት ወቅት በመኾኑ ከቡሄ በኋላ የጠነከረ ክረምት አይኖርም፡፡ ‹‹ቡሄ ከዋለ የለም ክረምት፤ ዶሮ ከጮኸ የለም ሌሊት›› እንዲሉ፡፡ በአንዳንድ የአገራችን አካባቢዎች የቡሄ ዕለት ማታ ምእመናን ችቦ ያበራሉ፡፡ ይህም በደብረ ታቦር ለታየው ብርሃነ መለኮት ምሳሌ ነው፡፡ ሕፃናቱ ይህ በዓል ከመድረሱ በፊት ቀደም ብለው ጅራፍ ሲገምዱና ሲያጮኹ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ፡፡ እናቶችም ለዚህ በዓል የሚኾን ዳቦ ለመጋገር ስንዴያቸውን ሲያጥቡ፣ ሲፈትጉ ይሰነብታሉ፡፡ በበዓሉ ዋዜማ (ነሐሴ ፲፪ ቀን) ሕፃናት በየቤቱ እየዞሩ ‹‹ቡሄ ና በሉ፤ ቡሄ በሉ፡፡ ቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ፤ ቅቤ ቀቡት እንዳይነጣ …›› እያሉ ይጫወታሉ፡፡ በዚህ ጊዜ እናቶች ካዘጋጁት ዳቦ እያነሡ ይሰጧቸዋል፡፡ ሕፃናቱ ‹ቡሄ› የሚሉትም ዳቦውን ነው፡፡
ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት እረኞች ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጥተዋል፡፡ ‹ቡሄ› ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና በበዓሉ ችቦ የሚበራውም ከዚህ ታሪክ በመነሣት ነው፡፡ ለክርስትና ልጅ፣ ለአማች፣ ለምራት፣ ለዘመድ አዝማድ ዅሉ የቡሄ ዳቦ ይሰጣል፡፡ ልጆችም ዳቧቸውን እየገመጡ ጅራፍ ሲገርፉ ይውላሉ፡፡ የጅራፉ መጮኽ የድምፀ መለኮት ምሳሌ ሲኾን፣ ጅራፉ ሲጮኽ ማስደንገጡም ነቢያትና ሐዋርያት በድምፀ መለኮት መደንገጣቸውንና መውደቃቸውን ያስታውሳል፡፡
መምህረ ሐዋርያት ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን ተማሪዎቹን ጴጥሮስን፣ ያዕቆብንና ዮሐንስን ይዞ በደብረ ታቦር ምሥጢር መግለጡን በማስታዎስ የአብነት ተማሪዎች ከመምህራቸው ጋር በመኾን በዓለ ደብረ ታቦርን (ቡሄን) ያከብራሉ፤ ስሙን ይጠራሉ፡፡ የአብነት ተማሪዎች ‹‹ስለ ደብረ ታቦር›› እያሉ እኽል ከምእመናን በመለመንና ገንዘብ በማዋጣት ጠላውን ጠምቀው፣ ዳቦውን ጋግረው፣ ቆሎውን ቆልተው ለደብረ ታቦር ዕለት ሊያስቀድሱ የመጡትን ምእመናን በመጋበዝና እርስበርስ በመገባበዝ፣ እንደዚሁም ቅኔ በማበርከት በዓለ ደብረ ታቦርን በታላቅ ድምቀት ያከብራሉ፡፡ ይህም እስከ አሁን ድረስ በአብነት ትምህርት ቤቶች የሚሠራበት ነባር ትውፊት ነው፡፡
ነገር ግን በአንድ አካባቢዎች በተለይ በከተማ ዙሪያ በዓለ ደብረ ታቦር (ቡሄ) ሃይማኖታዊ ትውፊቱን የለቀቀ ይመስላል፡፡ ለዚህም ልጆች የሚጫወቱበት መዝሙር ግጥሙና ዜማው ዓለማዊ መልእክት የሚበዛበት መኾኑ፤ በወቅቱ ችቦ ከማብራት ይልቅ ርችት መተኮሱና በየመጠጥ ቤቱ እየሰከሩ መጮኹ፤ ወዘተ. የበዓሉን መንፈሳዊ ትውፊት ከሚያደበዝዙ ተግባራት መካከል የሚጠቀሱ ናቸው፡፡ ከዚሁ ዅሉ ጋርም በዚህ በዓል ገንዘብ ለመሰብሰብ ብቻ የሚሽቀዳደሙ ነገር ግን የበዓሉን ታሪካዊ አመጣጥ የማያዉቁ ልጆችም ጥቂቶች አይደሉም፡፡
ስለዚህ ወላጆች ለልጆቻቸው የበዓለ ደብረ ታቦርን መንፈሳዊነት፣ የመዝሙሮቹን ያሬዳዊነትና አከባበሩን ከቤተ ክርስቲያን መምህራን በመጠየቅ ማስተማር፤ ልጆችም ከወላጆች ወይም ከመምህራን በመጠየቅ የበዓሉን አከባበር መረዳትና የዚህን በዓል መንፈሳዊ ትውፊት ሳይበረዝ ለትውልድ ማስተላለፍ ይገባቸዋል፡፡ ‹‹ድምፅህን ሰማና በብሩህ ደመና፤ የቡሄው ብርሃን ለእኛ በራልን …›› የሚለውንና ይህን የሚመስሉ መንፈሳውያን መዝሙራትን እየዘመሩ በየቤቱ በመዘዋወር የሚያገኙትን ዳቦና ገንዘብ ለነዳያንና ለቤተ ክርስቲያን የሚሰጡ ልጆችንም ማበረታታትና አርአያነታቸውን መከተል ይኖርብናል፡፡
መልካም በዓል ይኹንልን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር፡፡
ምንጭ፡- መጽሐፈ ታሪክ ወግስ፣ መ/ር አፈወርቅ ተክሌ፤ ፳፻፭ ዓ.ም፣ ገጽ ፫፻፲፭-፫፻፲፯፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ፣ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ፤ ፳፻፯ ዓ.ም፣ ገጽ ፻፲፩፡፡ | 0 |
