Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
رفتن به کانال در Telegram
نمایش بیشتر
1 741
مشترکین
+224 ساعت
+37 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የISO 9001:2015 ትግበራን በኮሌጅ ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ ለሚሰሩ ስራዎችከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንቲትዩት በተመደቡ አሰልጣኞች ከኮሌጁ የስራ ሂደቶችና ክፍሎች ለተወጣጡ ሰራተኞች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
ኮሌጁ የ ISO 9001:2015 QMS ትግበራ ላይ እየሰራ የሚገኝ በመሆኑና ይህንን ትግበራ በተጠናከረ መልኩ በመስራት ኮሌጁ የ ISO 9001:2015 QMS CERTIFICATE ተሸላሚ/ certify እንዲሆን በትጋት እየሰራም ይገኛል።
ይህን የተጀመረውን ተግባር ስኬታማነቱን ለማረጋገጥ ከ INSTITUTE OF ETHIOPIAN STANDARD ጋር በተደረገ ስምምነት መሰረት ከኢንስቲትዩቱ ከተመደቡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን የISO 9001:2015 ትግበራ ስራ ነባራዊ ሁኔታውን በመገምገምና ተጨማሪ ስራዎችን በመስራት እንዲሁም የISO 9001:2015 QMS ትግበራን በኮሌጅ ደረጃ ኦዲት / INTERNAL AUDIT IES ለማከናወንና የሚያስችል ስልጠና AUDITING MANAGEMENT SYSTEM BASED ON ES ISO 19011:2018 ከኢትዮጵያ የደረጃዎች ኢንቲትዩት በተመደቡ ባለሙያዎች/EXPERTS ስልጠናው በመሰጠት ላይ ይገኛል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 24/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
#እንኳን_ደስ_አለን🥇🥈🥉
በሀገር አቀፍ ደረጃ በመዲናችን አዲስ አበባ ላይ በተካሄደው 3ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ላይ እንዲሁም የድሬዳዋ አስተዳደርን ወክለው በክህሎት፣ በቴክኖሎጂ እና በስራ ፈጠራ የተሳተፉ የኮሌጃች አሰልጣኝ መምህራንና ሰልጣኝ ተማሪዎቻች በውድድሩ 2 የወርቅ፣1 የብር እና 2 የነሀስ በድምሩ 5 ሜዳልያዎ በማሸነፍ ድሬዳዋን እንዲሁም ኮሌጃችንን ከፍ ባለ ደረጃ ስላስጠሩ እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን ።
"ክህሎት ለተወዳዳሪነት " በሚል መሪ ሀሳብ እየተካሄደ የሚገኘውን 3ኛው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር ላይ ኮሌጃችንን እና የድሬዳዋ አስተዳደርን ወክለው እየተሳተፉ የሚገኙ ተወዳዳሪዎች በምስል📸
🏓🏓🏆🏆🏆
በድሬዳዋ አስተዳደር ወጣቶችና ስፓርት ኮሚሽን አዘጋጅነት እየተካሄደ የሚገኘው የሰራተኞች ስፓርት ቭፌስቲቫል በዛሬው እለትም ቀጥሎ ሲካሄድ ኮሌጃችንን ወክለው በሴቶች ጠረቤዛ ቴኒስ የፍፃሜ ውድድር ያደረጉት ተወዳዳሪዎቻችን 1ኛ እና 2ኛ በመውጣት የወርቅና የብር ሜዳልያን ጨምሮ ለውድድሩ የዘጋጀውን ዋንጫ ወስደዋል።
በዚህም:-
🥇 አሰልጣኝ መምህር ሉሲ አብደላ 1ኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳልያና የዋንጫ ተሸላሚ…🥇🏆👏👏
🥈 ወ/ት እየሩስ ከበደ 2ኛ በመውጣት የብር ሜዳልያ ተሸላሚ ሆነዋል።👏👏
በተመዘገበው ውጤት እንኳን ደስ አላችሁ እንኳን ደስ አለን።👏👏👏👏
በድሬዳዋ አስተዳደር የሚካሄደው የሰራተኞች የስፓርት ፌስቲቫል በዛሬው እለት ጅማሬውን በማድረግ የመክፈቻ ውድድሮችን ያካሄደ ሲሆን
ኮሌጃችንን ወክለው በሴቶች ጠረቤዛ ቴኒስ የተወዳደሩት እንስቶቻችን ተጋጣሚዎቻቸውን በማሸነፍ ነገ ለሚደረገው የፍፃሜ ውድድር ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።👏👏👏👏👏
ኮሌጁ በቀጣይ ቀናት በተለያዩ የስፓርት ውድድሮች የሚወከልም ይሆናል።
#እንኳን_ደስ_አለን🏆
የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር የሆኑት አቤል ዘገየ በምርጥ የኢኖቬሽን ፕሮጀክት በሀገር አቀፍ ደረጃ ተወዳድረው አሸናፊና ተሸላሚ በመሆን የኮሌጁን ብሎም የአስተዳደሩን ስም በኩራት አስጠርተዋል።
አሰልጣኝ መምህሩ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ በተለይም በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት የሚያስችል "Initiating the resumption of industry extension service through stakeholder engagement" በሚል አርዕስት አቅርቦ በመወዳደር ነው አሸናፊ መሆን የቻለው።
ይህም በኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት አዘጋጅነት መልካም አጋጣሚን በመጠቀም ለዘርፉ እሴትን በመጨመርና የማህበረሰብን ችግሮች ለመፍታትና አዳዲስ ነገሮችን በመሞከር ተግባራዊ በማድረግ ለተመረጠ የተሻለ የኢኖቬሽን ፕሮጀክት እውቅናና ማበረታቻ ለመስጠት በማሰብ ከሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ተሰርተው ከቀረቡ አስራ ሁለት ፕሮጀክቶች በቀዳሚነት ተመርጦ እውቅናና ሽልማት ተበርክቶለታል፤
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ በተመዘገው ውጤት የኮሌጃችን አሰልጣኝ መምህር አቤል ዘገየ ምርጥ የተሻለ የኢኖቬሽን ፕሮጀክት በመባል በሀገር አቀፍ ደረጃ ተሸላሚ በመሆንህ እንኳን ደስ አለህ! እንኳን ደስ አላችሁ ይላል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 4/2015 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1444ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ ይላል።
የ1444ኛው ሂጅራ የረመዳን ወር ፆምን አስመልክቶ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራር እና ሰራተኞች በጋራ የአፍጥር ስነ ስርዓት አካሄዱ።
የረመዳን ፆም 29 ቀን በሆነው በትላንትናው ምሽት የኮሌጃችን አመራሮች እና ሰራተኞች የታደሙበት ደማቅ የአፍጥር መረሃ ግብር በማድረግ አብሮነታቸውን አሳይተዋል።
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን
ሚያዝያ 12/2015 ዓ.ም
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
