fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 739
مشترکین
-124 ساعت
+17 روز
-730 روز
آرشیو پست ها
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ  "ብቃት" የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ሁለተኛ ዙር ትግበራ የመጀመሪያ ዙር የህይወት ክህሎት ስልጠና ያጠናቀቁ የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ላይ በድምቀት ተካሄደ፡፡ በዚህም የሰልጣኞች የምርቃት መርሃግብር ላይ የቢሮው አመራሮች የተገኙ ሲሆን የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ለሰልጣኞች የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን በስልጠናው ያገኙትን እውቀት በቀጣይ በስራ ላይ ለሚኖራቸው ስልጠና እንዲጠቀሙበት በማሳሰብ የሚመጡ እና የሚገጥሟቸን ፈተናዎች በጥንካሬ በማለፍ ለራሳቸውና ለሃገራቸው የሚጠቅሙ ዜጎች እንዲሆኑ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራ እና አንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት አቶ ሰኢድ አሊ  በበኩላቸው ባለፉት 10 ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና በኮሌጆቹ ውስጥ ሲሰጣቸው የቆየ ሲሆን ይህንንም ሲያጠናቅቁ በመረጡት የሙያ ዘርፍ በአስተዳደሩ በሚገኙ አምራችና አገልግሎት ሰጪ ኢንደስትሪዎች ላይ የኪስ ገንዘብ እየታሰበላቸው በተግባር እየሰሩ እውቀትና ክህሎታቸውን የሚያዳብሩ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡ በስልጠና ቆይታቸውም በኮሌጆቹ የህጻናት ማቆያ ቦታዎች ተዘጋጅቶላቸዋል በዚህም የልጅ እናት የሆኑ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች ስልጠናውን ሳይስተጓጎሉ እንዲወስዱ መቻሉን በማስታወስ ለዜጎች ሁሉን ተደራሽ የሚያደርግ የስራ ዕድል ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች በመሰራት ላይ ለመሆናቸው ይህ መርሃግብር ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 25/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ፕሮጀክት አመታዊ የአፈፃፀም ሪፖርት እና የኮሌጁ የ EASE ፕሮጀክት ማስጀመርያ ሰነድ ለኮሌጁ ቦርድ አቀረበ:: በዕለቱ በቅድሚያ በቀረበው ሪፖርት ስለ አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ)ፕሮጀክት አላማ እና እስካሁን የተሰሩ ስራዋችን እንዲሁም ዘርፉ ያጋጠመውን ችግሮች እና መፍትሄዋቻቸው በፕሮጀክቱ ሀላፊዎች ለቦርድ አባላት በዝርዝር ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል:: በመቀጠልም በአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) የተሰራውን የSolar Labor Market እና በድሬደዋ TVT Agency አማካኝነት የተሰራውን የSolar PV Street Light Value Chain Analysis in DD City ለቦርድ አባላት በማቅረብ የGreen Tvt Approach ትኩረት እንዲያገኝ የሚያስችል ሰፊ ገለፃና ማብራሪያ ተሰጥቶበት የቀጣይ አቅጣጫዎችንም ተቀምጠዋል:: በመጨረሻም በመድረኩ የቀረበው የኮሌጁ የEASE ፕሮጀክት Strategic Investment Plan(SIP) የቀጣይ አምስት አመት የፕሮጀክቱን ማስጀመርያ ስራዎች ሰነድ ለኮሌጁ ቦርድ አባላት ለማፀደቅ በኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ የቀረበ ሲሆን የቦርድ አባላቱም የቀረበውን ሰነድ በጥልቀት ከገመገሙ በኃላ ሰነዱን በሙሉ ድምፅ በማፅደቅ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 23 2016 ዓ.ም

በብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት ተጠቃሚ ለመሆን በአስተዳደሩ የወረዳ አንድ ማዕከላት የተመዘገባችሁ ሰልጣኞች ከመጋቢት 16/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ10 ተከታታይ ቀናት የህይወት ክህሎት ስልጠና የምትወስዱ ሲሆን ሰኞ ከጠዋቱ 2:00  የምትጀምሩ ይሆናል። በዚህም 👉 በወረዳ-1 አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-2 ዋናው አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-1  አንድ ማዕከል የተመዘገባችሁ ወጣቶች ስልጠናችሁ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ሲሆን፤ ---------------------------------------------------------- 👉 በወረዳ-2 ቅርንጫፍ-2  አንድ ማዕከል 👉 በወረዳ-4  አንድ ማዕከል የተመዘገባችሁ ደግሞ በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ተገኝታችሁ ስልጠናውን የምትወስዱ ይሆናል። ማሳሰቢያ፡- የታደሰ የነዋሪነት መታወቂያ  እና 2 ፎቶ ግራፍ ይዛችሁ እንድትገኙ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ

Repost from N/a
photo content
+8

Repost from N/a
የዛሬ ውሎ ተጨማሪ ምስሎች ፎቶ- ከንቲባ ቢሮ

በስራና ክህሎት ሚኒስቴር ሚኒስትር በክብርት ወ/ሮ ሙፈርሃት ካሚል የተመራው የፌደራል መንግስት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች የሱፐርቪዥን ቡድን በዛሬው ዕለት በኮሌጃችን የመስክ ምልከታ አካሂዷል። የሱፐቪዥኑ ቡድን በ ኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጁ አመራሮች ደማቅ አቀባበል የተደረገለት ሲሆን በነበራቸው ቆይታም በተቋሙ የተከናወኑና እየተሰሩ ያሉ የለውጥ ስራዎችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 13.2016 ዓ.ም

የኢትዮ- ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና የስራ ሂደት በስሩ የሚገኙ ዲፓርትመንቶችና የስራ ክፍሎችን በተከለሰው የውጤት ተኮር አሰራር ሰነድ መሠረት የ2016 ዓ.ም የአንደኛ ተርም አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ አካሄደ።   በመድረኩ የሁሉም ዲፓርትመንት ተጠሪዎች ሪፓርታቸውን ያቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ሪፓርቶች ላይም ከተከለሰው የውጤት ተኮር አሰራር ሰነድ አኳያ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን እና ክፍተት የተስተዋለባቸው ተግባሮች ላይ በመድረኩ ሀሳቦች ተነስተው ውይይት ተደርጎባቸዋል።     በዚህም በአፈፃፀም ወቅት የታዩ ጠንካራ ጎኖች በቀጣዩ ተርምም በተሻለ ጎልብተው እንዲቀጥሉ አፅዕኖት የተሰጠባቸው ሲሆን እንዲሁም በአፈፃፀም ወቅት የታዩ ክፍተቶች ላይ ትኩረት በመስጠትና ተቀናጅቶ በመስራት ትምህርትና ስልጠናውን በታለመለት አግባብ ለማስኬድም መግባባት ላይ ተደርሷል:: በተጨማሪም በዋና ስራ ሂደቱ በስሩ ለሚገኙ ክፍሎች ባለፉት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን የቴክኒካል ሱፐርቪዥን መርሃ-ግብር አጠናቆ ሪፖርት/ግብረመልስ የተሰጠበት ሲሆን በመጨረሻም እንደ ውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና የስራ ሂደት የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል። የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 12.2016 ዓ.ም

Repost from N/a
photo content

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
በድሬዳዋ አስተዳደር የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በኮሌጁ ጉብኝት አደረጉ። መጋቢት 10 2016 ዓ.ም       በድሬዳዋ አስተዳደር የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ቀደም ሲል ከተለያዩ አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጋር በተደረሰው የጋራ መገባባትና በተዘጋጀው የጋራ ዕቅድ መሰረት በዛሬው እለት የሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የቴክኖሎጂ ክበብ አባል ተማሪዎችን በሳይንስ፣ በቴክኖሎጂ፣ በምህንድስና እና በሂሳብ ማለትም(STEM) ግንዛቤ ለማስጨበጥ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንዲጎብኙ ተደጏል፡፡ በዚህም ተማሪዎቹ በኮሌጁ የተግባር ስልጠና የሚሰጥባችውን ዲፓርትመንቶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በሰልጠና ክፍሎች የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራንም ለጉብኝት ለመጡት ተማሪዎቹ የተግባር ስልጠና የሚስጥበትን ክፍሎች(workshops) በማስጎብኘት እንዲሁም በየዲፖርትመንቱ ስለሚሰጡ ሙያዎች በቂ ማብራሪያ እንዲያገኙ አስችለዋል:: በተጨማሪም ተማሪዎቹ በኮሌጁ ዲኖች ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተጨማሪ ግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ የተደረገላቸው ሲሆን ተማሪዎቹም በኮሌጁ የተፈጠረላቸውን ግንዛቤ እንደ ቴክኖሎጂ ክበብ በሚማሩበት ት/ቤት ለሚገኙ ሌሎች ተማሪዎችም ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ሃላፊነት ወስደው ጉብኝታቸውን አጠናቀዋል፡፡   ድሬዳዋ መጋቢት 10/2016 የኢትዮ ጣሊያን ኮምንኬሽን

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ሴት አመራሮችና ሰራተኞች ዘንድሮ በዓለም ለ133ኛ በሃገራችን ለ48 ጊዜ እየተከበረ የሚገኘው ዓለማቀፉ የሴቶች ቀንን "ሴቶችን እናብቃ፤ ልማትና ሰላምን እናረጋግጥ!" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ መርሃ-ግብሮች አከበሩ፡፡ በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን በዓሉን ስናከብር የሴቶችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ በመስራት ሊሆን ይገባል ብላዋል፡፡ የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው የሴቶችን ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነትና ተሳታፊነት ለማሳደግ በርካታ ስራዎች በመሰራት ላይ መሆኑን ጠቅሰው የሴቶችን ቀን በዓመት 1 ቀን ከማክበር ባሻገር የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን በማረጋገጥ መሆን እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ በበዓሉ አከባበር ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ፈቲህያ አደን፣ ም/አፈ ጉባኤ የተከበሩ ወ/ሮ ከሪማ አሊ እንዲሁም የአስተዳደሩ የፉይናስና ኢኮኖሚ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ የተገኙ ሲሆን ልምድና ተሞክሯቸውን በሰፊው ለታዳሚዎች አካፍለዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት የካቲት 28/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ