fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 740
مشترکین
+124 ساعت
+37 روز
-530 روز
آرشیو پست ها
የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የፈጠራ ሃሳቦችን ወደ ተግባር በመቀየር በስፋት እየተከናወኑ ባሉ የልማት ስራዎች ላይ ጉልህ ሚና ሊጫወቱ እንደሚገባ ተገለ፡፡ በኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ የሚመራ የኮሌጁ የቦርድ አባላት በተቋሙ የተሰሩ የተለያዩ የፈጠራ ስራዎችና ፕሮጀክቶችን ተዘዋውረው ተመልክተዋል:: በቦርድ አባላቱ የተጎበኙት የፈጠራ ውጤቶችና ፕሮጀክቶች በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ከፍተኛ ጥረትና በኮሌጁ ያልተቋረጠ ድጋፍ የተሰሩ ሲሆን የማህበረሰቡን ችግር በከፍተኛ ደረጃ እንደሚፈቱ ታምኖባቸው የተሰሩ እንደሆነም ተገልፇል:: በኮሌጁ ችግር ፈቺ ተብለው ከተሰሩ የፈጠራ ስራዎችና ፕሮጀክቶች መካከልም...... 1.በአንድ በሬ ማረስ የሚያስችል የእርሻ ማረሻ ፈጠራ፣ 2. የዘር ብክነትን የሚያስቀር ዘር መዝርያ ማሽን፣ 3. በአንድ ጊዜ 500 እቁላሎችን ማስፈልፈል የሚችል ማሽን፣ 4. እፅዋትን ጨምሮ ከተለያዩ ግብአቶች የተመረተ የነዳጅ ዘይት፣ 5. ዘመናዊ የመንገድ ዳር ቁሻሻ ማጠራቀሚያ፣ 6. ለኮሪደር ልማቱ ተጨማሪ ውበት የሚያጎናፅፍ ዘመናዊ አገልግሎት መስጫ ሼድ፣ 7. የመንገደኞች ማረፊያ አግዳሚ ወንበር... የሚገኙበት ሲሆን በቀጣይ በስፋት ተመርተው ጥቅም ላይ እንዲውሉ እንደሚደረግም ተገልፇል:: ኮሌጁ የፈጠራ ሃሳብ ማበልጸጊያ ማዕከል እንዲሁም የኢንተርፕራይዞች መፍለቂያ ተቋም መሆኑን በተግባር እያሳየ እንደሆነ ተመልክተናል ያሉት የኮሌጁ ቦርድ ሰብሳቢ እንዲሁም የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ኃላፊና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ሀርቢ ቡህ አክለውም በቀጣይ የተጀመሩ ስራዎችን በፍጥነትና በጥራት በማከናወን የማህበረሰቡን ችግር በዘላቂነት ከመፍታት በተጨማሪ ተቋሙም የራሱን ገቢ ማሳደግ ያስችለዋልም ብለዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 19/2017 ዓ.ም

በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ለኮሌጁ የድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች ሲሰጥ የቆየው የ3ኛዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ጋር በጋራ ለመስራት በገባው ውል መሰረት ለ3ኛ ዙር ለኮሌጁ የፅዳትና ጥበቃ ሰራተኞች ለተከታታይ 3 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ግንባታ ስልጠና በዛሬው እለት ተጠናቋል:: ለ3 ተከታታይ ቀናት የተሰጠውን ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞች ምስጋና ያቀረቡት የድሬዳዋ ስራ አመራር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ አወቀ ለገሰ አክለውም ኮሌጁ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው ላይ የሚሰጡት አገልግሎት እንዲሻሻል በማቀድ ይህንና መሰል ስልጠናዎችን እንዲወስዱ ማመቻቸቱ የሚበረታታ ነውም ብለዋል:: በዚህ 3ኛ ዙር ስልጠና ላይ የተካፈሉ ሰልጣኞች የወሰዱትን ስልጠና በተግባር ላይ ማዋል የሚጠበቅባቸው መሆኑን የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም በቀጣይ በሚፈጠርላቸው መሰል የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ላይ በንቃት በመሳተፍ አቅማቸውን እንዲገነቡና በተመደቡበት የስራ ዘርፍ የተሻለ አገልግሎት በመስጠት ለተቋሙ ራዕይና ስኬት የድርሻቸውን እንዲወጡም ጠይቀዋል:: ሰልጣኞች ከዚህ ስልጠና በኃላ በስራ ገበታችሁ ላይ ያመጣውን ለውጥ በተግባር እንድታሳዩ ያስፈልጋል ያሉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ አክለውም በመሰል ስልጠናዎች የሚመዘገቡ ውጤቶችን በድጋፍና ክትትል እናረጋግጣለንም ብለዋል:: የ3ኛው ዙር ስልጠና ቀደም ብለው ከተሰጡት የ1ኛና 2ኛ ዙር ስልጠናዎች በተለያየ ምክንያት ዘግይቶ እንደተሰጠ ያስታወሱት የEASE ፕሮጀክት ዋና አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አክለውም ይህ ስልጠና ማስጀመርያ መሆኑንና ኮሌጁ ከኢንስቲትዩቱ ጋር በቅንጅት ለመስራት ባደረገው ስምምነት መሰረት አስፈላጊ የሆኑ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች በቀጣይ እንደሚዘጋጁም ገልፀዋል:: የማጠቃለያ መርሃ-ግብሩ ላይ ስልጠናውን በአግባቡ ተከታትለው ላጠናቀቁ ሰልጣኞችም ከእለቱ ክብር እንግዶች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት17/2017 ዓ.ም

"ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ቃል በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ 4ኛ ጊዜ የሚካሄደውን የክህሎት ውድድር መነሻ በማድረግ በክላስተር ደረጃ በኮሌጁ መካሄድ ጀመረ:: የክህሎት ውድድሩ ከዚህ ቀደም በተቋም ደረጃ መካሄዱ የሚታወስ ሲሆን በክላስተር ደረጃ የሚካሄደው ውድድርም በስራና ክህሎት ቢሮ አስተባባሪነት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ተካሂዷል:: በዛሬው እለት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የተካሄደው ውድድር በ7 ዲፓርትመንቶች በሚገኙ 7 የሙያ ዘርፎች ላይ ሰልጣኝ ተማሪዎችን ያሳተፈ እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን...... በAuto mechanics በBuilding Electrical Installation በIndustrial Electrical/Electronic control technology በStructural construction work በWood work technology.... በMechanics በHardware & Network Servicing በUllinary Art የሙያ ዘርፎች ላይ ውድድሮች ተደርገዋል:: ኮሌጁ ከተቋም ጀምሮ እስከ ሀገር አቀፍ ደረጃ በየጊዜው በሚካሄደው የክህሎት ውድድር መድመቅ የቻሉ እንዲሁም ሀገርን ወክለው በአለም አቀፍ ደረጃ የተወዳደሩ ውጤታማ ተወዳዳሪዎችን ያፈራ በመሆኑ ከስር ለሚመጡ ሰልጣኞች የበለጠ መነሳሳትን እንደሚፈጥር የገለፁት ደግሞ የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ ሂደት ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ናቸው:: ም/ዲኑ አክለውም ይህ ውድድር ወቅቱን ጠብቆ በየጊዜው መደረጉ ዘርፉ ትኩረት ሰጥቶ በክህሎት የበቁ ዜጎችን በማፍራት ኢንዱስትሪውን ለመመገብ በሚያደርገው ርብርብ ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ገልፀዋል:: በተቋሙ በክላስተር ደረጃ የተካሄደውን ውድድር የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላት ተዘዋውረው የተመለከቱ ሲሆን በእለቱ ተወዳዳሪ የነበሩ ሰልጣኝ ተማሪዎችንም አበረታተዋል:: ይህን ውድድር በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች በቀጣይ በአስተዳደር/በክልል ደረጃ በሚደረገው ውድድር ላይ ኮሌጁን ወክለው የሚሳተፉም ይሆናል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 16/2017 ዓ.ም

"ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሃሳብ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት የሚካሄደው የ2017 ዓ.ም የክህሎት ውድድር በክላስተር ደረጃ መካሄድ ጀመረ። በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በጋርመንት፣ ዉድ ወርክ፣ ኤሌክትሪክ፣ ሆቴል እና ቱሪዝም፣ ኮንስትራክሽን፣ አውቶሞቲቭ፣ ማኑፋክቸሪንግ እና በአይሲቲ ላይ ሰልጣኝ ተማሪዎች በአስተዳደር ደረጃ ለሚካሄደው ውድድር ኮሌጃቸውን ወክለው ለመሳተፍ ከየዘርፉ በተመረጡ ዳኞች ፊት ክህሎታቸውን በመጠቀም ስራዎቻቸውን በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። በዚህም በክላስተርና በአስተዳደር ያለውን ውድድር በበላይነት የሚያጠናቅቁ ተወዳዳሪዎች ኮሌጆቹን እንዲሁም አስተዳደሩን በመወከል በአገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄደው የክህሎት ውድድር የሚሳተፉ እንደሚሆን በዳይሬክቶሬቱ የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምጸሃይ ጌታቸው ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 16/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ዜና | ከኮሌጆች ጋር በጋራ መስራት እና ተመሳሳይ አቅም መገንባት የኢንዱስትሪውን የሰው ኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚ ያደረግ ተገለፀ :: የኢትዮ -ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከምዕራብ እና ምስራቅ አጎራባች ክልሎች ከተውጣጡ የኮሌጅ አመራሮች ጋር የልምድ ልውውጥ እና በጋራ ለመስራት የሚስችላቸውን የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል ። በወቅቱ የስራና ክህሎት ቢሮ ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሞያ ኤጀንሲ ዋና ዳሬክተር ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ኮሌጁ ከኢትዮጵያ የተሰማሚነት ድርጅት የጥራት ደረጃ እውቅና ( ISO) ያገኘና ትልቅ አቅም የሚፈጥር ኮሌጅ መሆኑን ጠቅሰው ይሄ አቅም ድሬዳዋ ላይ ብቻ ተወስኖ እንዳይቀር ከሌሎች አጎራባች ክልሎች የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ አመራሮች ጋር በጋራ በመስራት በቴክኒክም በክህሎትም ተመሳሳይ አቅም በመገንባት የኢንዲስትሪውን የሰው ኃይል ፍላጎት ከማሟላት ባሻገር የስራ እድል በመፍጠር በኩል ትልቅ አስተዋጽኦ እንደሚያደረግ ነው የገለፁት። ወ/ሮ ፈጡም አያይዘውም በየአካባቢያችን ያለውን ሀብት እንዴት መጠቀም እንዳለብን ጭምር የጋራ እውቀት አቅም እንዲኖረን የሚያደርግ የልምድ ልውውጥ ነዉ ብለዋል። ይህ የተሞክሮ ልውውጥ በዛሬ ብቻም አያበቃም ይቀጥላልም ነው ያሉት :: የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ በአለም ባንክ በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ኮሌጁ ( EASE)ኘሮጀክትን በመተግበር ላይ እንደሚገኝ ገልጸው ፕሮጀክቱ በተለዩ ስምንት (8) የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ይሰራል ብለዋል። ይህም የዛሬው የመጀመሪያው ዙር የድሬዳዋ አጎራባች ክልሎች የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ አመራሮች ጋር ያደረግነው የልምድ ለውውጥ እና በጋራ ለመስራት የተስማማንበት መድረክ አንዱ የፕሮጀክቱ ትግበራ አካል ነው ብለዋል :: አያይዘውም ፕሮጀክቱ በቴክኒክም በክህሎትም ጥራት ያለው መምህር በመፍጠር ገበያው የሚፈልገውን የሰው ኃይል በማቅረብ በኢንዱስትሪዎች ላይ የሚታየውን የሞያተኛ የብቃት ችግር ለመቅረፍ ብሎም የስራ አጥ ቁጥርን ለመቀነስ የሚረዳ ፕሮጀክት ነው ብለዋል፡ : ከአጎራባች ክልሎች የመጡት የቴክኒክ እና ሞያ ኮሌጅ ዲኖች በበኩላቸው የወሰድነው የልምድ ልውውጥ በየኮሌጃችን ለመተግበር የሚያስችል ተሞክሮ ቀስመናል ያሉ ሲሆን በተከታታይነትም ለመስራት የሚያስችለንን ስምምነት ላይ ደርሰናል ነው ያሉት :: ኮሌጁ በቀጣይ በጋራ ለመስራት በሚያስችላቸው ጉዳዮችላይ የስምምነት ሰነድ ተፈራርሟል :: በመጨረሻም ከአጎራባች ክልሎች የመጡት እንግዶች ኮሌጁን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል። #Dire tv አማርኛ መጋቢት 13/2047

ለድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሄደ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ ሀሙስ ቀን በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ በተከታታይ እያካሄደ የሚገኘውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በድሬዳዋ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሂዷል:: በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ቴክኒክና ሙያ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደ ዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በማስገንዘብ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል:: የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም አሰልጣኝ መምህራን ሲሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ ከወዲሁ በአስተሳሰብም ሆነ ለዘርፉ ባላቸው አረዳድ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርጋቸውን ምክረ ሀሳብና በኮሌጁ ያለውን ምቹ አጋጣሚ ለተማሪዎች በዝርዝር ያስረዱ ሲሆን የህይወት ልምዳቸውንም አካፍለዋል:: በቀጣይም ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳቸውን የቴክኒክና ሙያ (STEM) ክበብ በየትምህርት ቤቶቹ በመቋቋም ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ይህም የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ቀደም ብለው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩና በሲስተም ውስጥ እንዲያልፉ እድል እንደሚፈጥርላቸውም ተገልፇል:: በተጨማሪም በአንደኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች የሴት ተማሪዎች ቁጥር አብላጫውን እንደሚይዝና ነገር ግን የቴክኒክና ሙያ ዘርፉ ላይ የሴቶች ተሳትፎ ውስን በመሆኑ ሴቶች በዘርፉ በስፋት እንዲሳተፉ ማበረታታትና መደገፍም እንደሚገባ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 12/2017 ዓ.ም