cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

እዚህ ቤት

አገር አገር ስልሽ—ደስ ይበልሽ በጣም ኢትዮጵያዊ ሆነን—የሚያግባባ አናጣም! ዕወቂው ዐለሜ...! ኢትዮጵያዊ መሆን—የውርስ እንቁጣጣ በአጥንት ክስካሽ—በደም ቅብ የመጣ! |ታመነ መንግሥቴ ውቤ—አባ ወራው| ግቡ፦ስለ አገር፣ፍቅር፣ሰላም፣ባሕል እና ጥበብ እናወጋለን! ጀበናዋ ተጥዳለች! ፍንጃሎቹ ሳይሞሉ፣የገባችሁ ሳትቋደሱ ረከቦት አይነሳም! ክሕሎት፣ጥበብ፣ መሻታችሁ በቤቱ ይስተናገዳሉ። ትውልድ❤

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
998
مشترکین
-324 ساعت
-57 روز
-1530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

نمایش همه...
TikTok · Afrihome

Check out Afrihome’s video.

نمایش همه...
TikTok · Afrihome

Check out Afrihome’s video.

1
በኢትዮጵያ ቀን የኢየሱስ ክርስቶስ የስቅለት በዓልና ጁምዓ ተገናኝተዋል። ኢየሱስ ለሰው ልጆች ሲል ራሱን ለሞት አሳልፎ የሰጠበትን ቀን እያከበርን የከፋው ጠባያችን ባመጣብን እዳ የተነሳ በየሜዳው፣ጫካው የተበተኑ፣በአውሬዎች የታረዱ ኢትዮጵያዊያንን እያሰብን እየተደጋገፍን እናስበው። የኢትዮጵያ ትንሳኤ እየደረሰ ቢሆንስ? ለሁሉም የመምህር ሃብታሙ አለማየሁን የክራር ግርፍ እየታደማችሁ ለዕለተ ስቅለት የሚሆኑ መልዕክቶችን፦ በጓዳ በኩል @GazetawBot ላይ ለእኔ ለአባወራው @Tamen1234 እያላችሁ ላኩልኝ። የቤታችንን በር @Gazetaw አንኳኩ፤ክፍት ናት!
نمایش همه...
1
የበረከት በላይነህ ሥንኞች፡- . . “ጎዳናው” . (በረከት በላይነህ ) . . ጎዳናው ይገርማል ይገርማል መንገዱ እግረኛው ይገርማል . ሸራ ጫማ ባ'ይነት በነጫጭ ካልሲ በሲኪኒ ሱሪ ከመምህሩ ጋራ አይስክሬም ሚልስ ያይስኩል ተማሪ ፀባይኛ ወጣት ጃንቦ ተከልሎ በምርቃና ሆኖ ሐሳብ የሚፈትል አንዲት ሙ...ደኛ እናት በ'ድሜ ከልጆቼ አንሳለሁ የምትል ፒዛውን የሚገምጥ ጭማቂ የሚመጥ አራዳ አባወራ በሚስቱ ትከሻ በልጆቹ ምላስ ቅምጥ የሚጣራ . አንድ ፍሬ ሴቶች . በተገዛ ቅንድብ በተገዛ ጸጉር በተገዛ ጥፍር በውሰት ወዘና የተብለጨለጩ ማኪያቶውን ከበው ለውስኪ ‘ሚንጫጩ ጅናም ጅንሳም ወንዶች በሴቶች ጫጫታ የሚቁለጨለጩ . ይገርማል ጎዳናው ይገርማል መንገዱ ድንቡሽቡሽ ሕፃናት በቶም ኤንድ ጄሪ ሱስ ቀልባቸው የከሳ በአይፎኑ አጮልቆ ያንጀሊናን ከንፈር የሚስም ጎረምሳ . ቀውጢ ዳያስፖራ... . የሎቲው የቁምጣው የቲሸርቱ ጥለት የተንዘረፈፈው አማርኛን ሲሸሽ "what's up" የጠለፈው . ነቄ ብላቴና... . ከዮፍታዬ ቀዬ ካ'ዲስ ዓለማየሁ ከመዝገቡ መንደር የአዲስ አ'ባ ጥሪ በቁምጣ ያበረረው ከቅኔ ተጣልቶ ከግዕዝ ተኳርፎ ሎተሪ 'ሚያዞረው . ጸዴ ብላቴና... . ከባላገር ዘመን ከጨለማ ዘመን ወደ ብርሃን ጥግ ተሸጋገርኩ ብሎ በሸንኮራ ምርኩዝ ከተማ ሚያካልል መቋሚያውን ጥሎ ነፍሱ እየሰለለች በከተሜነት ወግ ባ'ራዳነት ልምሻ ሲያዘግም የሚውል ሊስትሮውን ጭኖ በታቦት ትከሻ . ፎቆቹ.. . በመስታወት ቁመት በቆርቆሮ ገጾች ባ'ልሙኒየም ጥራዝ የተብረቀረቁ የጌቶቻቸውን ዕድሜ ‘ሚያሳብቁ ሁሉም... ሁሉም... ሁሉም ጥግ ናቸው ለወደቀ ወገን ይራራል ልባቸው . ሁሉም... ሁሉም ከዘለለት ጥድፊያ ከሰርክ ውጣ ውረድ በተረፈች አንጀት ለወደቀ ወገን ምርኩዝ ማበጃጀት ሁሉም... ሁሉም ይችላሉ ስለ'ግዚአር ላለ ይመፀውታሉ . . እኔ ግን... እኔ ግን... ‘ቆጥራለሁ የ'ድሜ ክቡር ጀንበር በጎዳና ፅልመት ሲዋጥ አስተውላለሁ ጡረታ መንገድ ዳር ሲከፈል ዐያለሁ ‘ቆጥራለሁ... ‘ቆጥራለሁ ‘ቆጥራለሁ አዛውንት በየአቀበቱ በየቁልቁለቱ ማረፊያ ፍለጋ የሚንከራተቱ ‘ቆጥራለሁ አዛውንት ከልጆቻቸው ፊት የልመና መዝገብ የገለጡ አሮጊት ‘ቆጥራለሁ በየመንገዱ ዳር እርጅና ሙሽራው ለምፅዋት ሲዳር ‘ቆጥራለሁ በየሸንተረሩ በየተፋሰሱ አቀርቅሮ ሲያዘግም እርጅና ሞገሱ . . ‘ቆጥራለሁ በ'ያደባባዩ የሽማግሌ ዐይኖች የልጅ ፊት እያዩ ‘ቆጥራለሁ በየሰርጣሰርጡ በልመና ጉልበት ከሞት ሲፋጠጡ የ'ርጅና መዳፎች እሾህ ሲጨብጡ . ቆጥሬ... ቆጥሬ... ቆጥሬ በለማኝ አዛውንት ብዛት ተሳክሬ የማሰንበቻ ሥንቅ ከኪሴ ቆንጥሬ ያጽድቆቴን ዋጋ በሳንቲም መንዝሬ ባ'ዛውንት ምርቃት ከሀገር ከቀዬው ትርፌን ሳመሳስል በጎዳናው ቀለም ጻድቅ መልኬን ስሥል ጎልቶ ሚታየኝ ግን የሚያሳፍር ምስል በቀላል ጥያቄ የነተበ ምስል . . ጥያቄ... . . የዲጄ ኳኳታ የደናሽ ጋጋታ የድራፍት እርካታ ያ'ረቄ ድንፋታ ባጣበበው መንገድ እንደምን ይቻካል ላ'ያት ሳንቲም ሰጥቶ በ'ርካታ መራመድ? ለወጣት ሹክሹክታ ለገደል ዝምታ ላስመሳይ ጫጫታ ላድርባይ እሪታ በተሰራ መንገድ እውነት ቀላል ነው ወይ ላ'ያት ሳንቲም ሰ’ቶ በ'ርካታ መራመድ? ለቡቲክ ሰልፈኛ ለካፌ 'ድምተኛ ለውስኪ ጭሰኛ ለበርገር ምርኮኛ በተሰራ መንገድ እንደምን ይቻላል ላ'ያት ሳንቲም ሰ’ቶ በ'ርካታ መራመድ? . . አያት....አያት...አያትነት ማለት በደማቅ አሻራ የሸመኑት ጥለት ለተራኪ ዕድሜ የተሰጠ አንደበት ባ'ባት በ'ናት ጽናት የማይደክም ጉልበት በልጅ ልጅ መነጽር የማያረጅ ውበት በልጅ ልጆች ጥበብ የሚታደስ ዕውቀት የሚታደስ እውነት አያት ሆኑ ማለት ድርብ አባትነት ድርብ እናትነት . . በተለይ እዚህማ... በዚህች ዓይነት ሀገር ጎጆዋን ላቆመች በተጋድሎ ካስማ ባርበኝነት ማገር በዚህች ዓይነት ሀገር ጥያቄና መልሷን ባ'ዘን በቅዳሴ በምትሠራ መንደር በዱአ በጸሎት በምናኔ ምርኩዝ በከረመች ሰፈር የአያትነት ዋጋው በልኩ ቢሰፈር ለሳንቲም ምርቃት ባልተሻማን ነበር! ታሪክ በመዳፉ ስላደላደለው ሁሉም ኢትዮጵያዊ ንጉሥ አያት አለው የልጅ ልጆች ስባት ባያመነምነው ያያቶቻችን መልክ ሁሌም አንድ ዓይነት ነው . እላለሁ... እላለሁ.... የልጆች ምፅዋት ያ'ያቶች ልመና ያ'ባቶች ግርግር በሞላው ጎዳና መንገዱ አይልቅም ጎዳናው አያልቅም ይሰፋል ይረዝማል ይሄዳል ይጓዛል እግረኛው ሞኝ ነው ሳንቲሙን ዘርዝሮ ከወደቁ አዛውንት ምርቃት ይገዛል መንገዱ ያስፈራል መንገዱ ይጨንቃል ልጆች ሣቅ ሲያንቃቸው አያት እንባ ይጨምቃል መንገዱ ያሠጋል መንገዱ ያረጃል ከዘናጭ ልጆች ጎን እርዛት ያዘለ አያት ይወለዳል ሰጪ ካለቀሰ ተበዳሪ ሥቆ ጌታ ከለመነ አማኙ 'ግር ወድቆ ልዑል ከዘመረ ንጉሡ ተዋርዶ ገጹ ተመሳቅሎ ሽፋኑ ካማረ ወለሉ ተንቆ ምንጣፍ ከከበረ ባ'ገርኛ ስሌት ማነው ያልከሰረ? . እላለሁ... እላለሁ . ከየጎዳናው ገጽ ጥያቄ አነሣለሁ ጥያቄ እጥላለሁ እርጅና ለማምሻው ጎዳናን ካመነ አያት ከልጅ ልጁ ሳንቲም ከለመነ ባገርኛ ስሌት ማነው ያልመከነ? በ'ግዚኦታ ዘመን በምሕላ ዘመን እመንገድ ዳር ወድቆ ትራፊ መለመን በጥሞና ዘመን የሚያስቡት ማጣት በማውረሻ ዕድሜ የሚሰጡት ማጣት በማልበሻ ዘመን በ'ርዛት መቀጣት በለጋሽነት ወቅት በማጉረሻ ዘመን በጥማት መገረፍ በረኃብ መመንመን ከሆነ ዕጣችን ይጠየቅ ትርጉሙ የልጅነታችን ይፈተሽ መንገዱ የልጅ ልጆቻችን . ግድ የለም እንመን እንመን . በሰውኛ ስሌት ውጤቱ ሲሠራ ትውልድ ያደኸያል ያያቶች ኪሣራ በልጅ ልጆች ዓለም እንደጉድ ቢደለቅ ቢዘመር ቢዘፈን አባት ይወራጫል ባ'ያቶች መታፈን . አባት ሆይ... . ለልጆችህ ርዕዮት ትላንቱን የረሳ ተስፋ ሲደራረት ሕልሜ ነው ይልሃል ያ'ያቶቹ ቅዠት ከልጅህ አንደበት ቋንቋ እንደዶፍ ቢዘንብ ትርጉም ቢንፎለፎል ሺ ቃላት ቢጎርፍም የልጅ ልጅ አግባቢ ግማሽ ገጽ አይጽፍም ከልጆችህ ባሕር ዓሣ የሚያጠግቡ ለዓሣ 'ሚስማሙ ዕፅዋት ተክሎች እንደጉድ ቢራቡ እንደጉድ ቢያብቡ ገበታ አይሞላም ተቀዷል መረቡ . ግድ የለም እንመን... እንመን . የስኬት ክብደቱ የምቾት አይነቱ የነገ ውበቱ ባሻው ቋት ቢለካ በምንም ቢሰፈር ባሻው ቃል ቢነገር ጀግና ልጅ አትወልድም አያቶቿን ገድላ የምትሸልል ሀገር . ከፎቆቹ ጥላ... . ከያስፓልቱ ገላ ሲታተም ድምቀቴ በመስታወት አጀብ ሲጠገን ጉልበቴ ይኸው አነበብኩት አያቶቼ ፊት ላይ ተጽፏል ሽንፈቴ በመኪና ብዛት በመስታወት አይነት ሲለካ ፍጥነቴ በግንብ አጥር መአት በፎቆች ጋጋተ ሲሰላ ስኬቴ ይኸው ይታየኛል አያቴ ገጽ ላይ ተስሏል ውድቀቴ ተስሏል ሽንፈት።
نمایش همه...
4👍 1
ትኩሳት ፣ሥብሃት ገብረእግዚአብሔር ቃሉ የባሕራን ነው! ✍️ባሕራን በፈረንሳይ አገር ይማር የነበረ ኢራናዊ ወጣት ነው።ይችን ቁም ነገር ለጋሽ ስብሃት የነገረው በፈረንሳይኛው ደካማነት ሰበብ ከትምህርት በመውደቁ የተነሳ ነበር። ✍️የጋሽ ስብሃት አገር ኢትዮጵያ(አክሱም) እና የባሕራን አገር ኢራን(ፋርስ) የዛሬ 2ሺህ ዓመት ገደማ ከዓለማችን አራት ኃያላን አገራት መካከል ሁለቱ እንደነበሩ ማኒ ጽፏል።
نمایش همه...
4
አያልነህ ሙላት/ሙላቱ 📝ሰውየውን የማውቃቸው ገጠር ሳለሁ በአማራ ራዲዮ ነው።ማራኪ ተናጋሪ ናቸው።ልጅነታቸው ይጣፍጣል። 📝የ ብንያም አቡራ «ወደ ፍቅር ጉዞ»መጽሐፍ የተመረቀ 'ለት ከወመዘክር ወጣ እንዳልነ አንዱ ገጣሚ ፣ጋዜጠኛ እና አሁንም ሥነ-ጽሑፍ የሚማር ጓደኛየ እንደዋዛ «ጋሽ አያልነህ የእርስዎን ግጥሞች እኮ መምህሮቻችን 'አብዮታዊ ግጥሞች'እያሉ ነው የሚያስተምሩን፤»ብሎ አበሸቃቸው። ጨሱ።ጸያፍ ሥድብ አመለጣቸው።ልጁ ሲነግረኝ ረጅሙን የግጥም መጽሐፋቸው አንብቧል።እውነትም ሥንኞቻቸው ከኪናዊ ለዛ ይልቅ አቢዮታዊ ቃና እንደሚነበብባቸው አወጋኝ። ሳላነብ አመንኩት።ግጥም ማንበብ ላይ ሰነፍ ነኝ።ከእናቴ የሚበልጥ ገጣሚ ስላላገኘሁ ይሆናል። ለሁሉም ጋሽ አያልነህን እንዲህ ያስታወስኳቸው በጴጥሮስ ቶጃ(ርዕሰ ምሁር ናቸው፤) ግለ-ታሪክ የጀርባ ሽፋን ላይ የሚከተለውን ሥንኝ እና አሳዛኝ ሥሜቱን አጋርተው አግኝቻቸው ነው። ኑ በአባቶቻችን አብረን እንዘን፤እንፈርም፣ወይም ከተገኘ እንኩራ፦ «በ1965 ዓ.ም አውሮፓ እያለሁ አንድ አጭር ግጥም ቋጥሬ ነበር። እሳት ነደደ አሉ በአገራችን ጓዳ ጓዶች ብርድ አይምታን ገብተን እንጣዳ። እንለግስ ጭራሮ አንሁን ማገዶ እሳቱ እንዳይጠፋ ጢሶ ጢሶ ነዶ። (ጥገት ላም) ይህ ግጥም ለእኔ ማዕበል ጠሪ ወፍ🦃 ነው።እጅግ በርካታ ጓዶችን ከውጭ አገር ዩኒቨርስቲዎች ቤተ-መጽሐፍት እያበረታታ ለአብዮት የሰደድ እሳት «ጭድ»^ያደረጋቸው መስሎ ስለሚታየኝ ለግጥሙ ያለኝ ፍቅር እጅግም ነው።» 🦃አዲሱ የዓለማየሁ ገላጋይ መጽሐፍ ርዕሱ «ማዕበል ጠሪ ወፍ»ይላል።የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ነበርኩ። ^የጴጥሮስ ቶጃ ግለ ታሪክ ርዕሱ «የጭድ እሳት» ነው። ሰላም ይስጥልነ!
نمایش همه...
👍 2👏 1
نمایش همه...
👍 1👏 1
ኦሮማይ መጽናኛየ ነው።ተማሪ ሳለሁ አራት ጊዜ አነበብኩት።መመረቂያ ጽሑፌም ደራሲው በኦሮማይ ጋዜጠኝነትን እንዴት እንደተመለከተው ያትታል። ትረካውን በጣም እወደዋለሁ።ፍቃዱ ተክለማርያም ፊያሜታን ሲያስመላት በቃ ሙትት እላለሁ። ለመጀመሪያ ጊዜ እንዲህ ያለ መጽሐፍ መኖሩን የጠቆመኝ እና PDF የላከልኝ ፊያሜታ ላይላ ነው። ሌላኛው የእኔ ምርጥ መጽሐፍ የ«ሐበሻ ጀብዱ» ይሰኛል።በንባብ ሁለት ጊዜ አጥንቸዋለሁ።ተርጓሚውን ተጫነ ጆብሬ መኮንን'ን አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ መጥተው ጠይቄያቸው አውቃለሁ።ምርጥ ሰው ናቸው። መጽሐፉ በአማርኛ ተተርኳል።ትረካውን እንደ ሙዚቃ አደምጠዋለሁ። ሶስተኛው ለልቤ የቀረበ መጽሐፍ «ሌላ ሰው»ነው። ኮቪድ ሊገባ ሳምንታት ሲቀሩት የአብርሐም አፈወርቂን እና ፀሐይቱ ባራኪን ዘፈን ማጀቢያ አድርጌ ያነበብኩት ውብ ሥራ ነው። ዘፈኖቹን በሰማሁ ቁጥር መጽሐፉ ትዝ ይለኛል። ዛሬ ዛሬ ሳነብ ለቅንጦት አይደለም።በቀጥታ ለሥራዬ ሊጠቅመኝ ይገባል። ሳድግ አንድ የሐዲስ ዓለማየሁን ፍቅር እስከ መቃብር የሚልቅ ልብወለድ የመጻፍ አሳብ አለኝ።ታዲያ ከዚያ በፊት ኑሮየ ሊደላኝ ይገባል። ገጠመኞቸ'ን የያዘው «የትውልዴ ገድል»በቅርብ ዓመታት ውስጥ መነበቡ አይቀርም። ግን አልቸኩልም።
نمایش همه...
🙏 4 2👍 1