fa
Feedback
EECMY - School (online class)

EECMY - School (online class)

رفتن به کانال در Telegram

This channel is created with the thought of teaching students by supplying important files. Please pay attention.

نمایش بیشتر
487
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+17 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

ተማሪዎቻችን ግንቦት 30/2016 ዓ.ም በአንድነት ፓርክና በአድዋ መታሰቢያ ያደረጉት ትምህርታዊ ጉብኝት

photo content

ፈተና ከጀመርን በኋላ ማድረግ የሚገቡን ነገሮች (ፈተና ላይ እያለን)፤ # ወደ ፈተና ከመሄዳችን ቀደም ብለን ለፈተና የሚረዱንን መሳሪያዎች እና የመፈተኛ ቁሶችን ማዘጋጀት። # አብዝተን ፈተናን እና የምናመጣውን ነጥብ ስሌት አለመገመት ። # ፈተና ስንጨርስ የተሳሳትነውን ጥያቄ አብዝቶ ማሰብ እና ሌላ ተማሪ መጠየቅ ጭንቀት ውስጥ ስለሚከተን ከዚህ ይልቅ ቤት ሄደን እረፍት ማድረግ እና ለቀጣይ ፈተና መዘጋጀት ። # በፈተና ጊዜ ድንገተኛ ጭንቀት እና ድንጋጤ ከገጠመን ወዲያው የምንሰራውን ገታ አድርገን በጥልቀት አየር በአፍንጫችን ስበን ወደ ሳንባ እያስገባን መልሰን ማስወጣት ይህንንም እስክንረጋጋ መደጋገም ። ከዚህ በመቀጠል የማረጋጊያ ቃላትን ለራስዎ መንገር:: # ፈተና በምንሰራ ጊዜ ግራ ያጋባንን እና እርግጠኛ ያልሆንበትን ጥያቄ በይለፍ ማቆየት እና ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ይህም ጊዜያችንን በአግባቡ እንድንጠቀም ይረዳናል። ነገር ግን ምልክት አድርገን ማለፍ፤ # በተመሳሳይ እርግጠኛ ያልሆልንበትን መልስ ላይ ተደናግጠን መሰረዝ እና መደለዝን መቀነስ ይህም ስንደነግጥ እና ስንጨነቅ የምናውቀውን መልስ ትተን ወደ ሌላ መልስ እንድሰጥ ስለሚያረግ መሰረዝና መደለዝን መቀነስ ። # ፈተናውን ወደ ማገባደድ ስንደርስ በይለፍ ያስቀመጥናቸውን ግራ ያጋቡንን ጥያቄዎች ጥቂት አስበንበት መልስ መስጠት ፤ ካልሆነም ደግሞ ብልሀት ተጠቅመን የግመታ መልስ ሰጥተን ወደ ቀጣዩ ጥያቄ መሄድ ። #በተደጋጋሚ ሰአትን አለመመልከት ወይም ሰአት በቃን አልበቃን እያልን አለመጨነቅ። ለተፈታኞች መልካም  ፈተና

photo content

photo content

የሚኒስትሪ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡

የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በዛሬው እለት በአዲሥ ተሥፋ ትምሕርት ቤተት በሰአቱ ተገኝተው ነገ ሥለሚጀምረው ሚኒሥትሪ ፈተና ገለፃ ተደርጓላቸዋል፡፡ መልካም ውጤት ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን
የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን በዛሬው እለት በአዲሥ ተሥፋ ትምሕርት ቤተት በሰአቱ ተገኝተው ነገ ሥለሚጀምረው ሚኒሥትሪ ፈተና ገለፃ ተደርጓላቸዋል፡፡ መልካም ውጤት ለተፈታኝ ተማሪዎቻችን

ሠኞ ሠኔ 3/2016 ዓ. ም ጠዋት 1:30 ሠአት የምንገናኘው እንጦጦ ወንጌላዊት ትምሕርት ቤት ነው

ውድወላጆች /አሣዳጊዎች እንዲሑም የ8ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን ማክሠኞ ሠኔ4/2016 ዓ.ም ለሚጀመረው ከተማ አቀፍ ፈተና የመፈተኛ ቦታው አዲሥ ተሥፋ አንደኛና መካከለኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት ሢሆን ሠኞ ሠኔ3/2016 ዓ.ም በዚሑ ትምሕርት ቤት ኦረንቴሽን ሥለሚሠጥ ተማሪዎቻችን ሰኞ ጠዋት 1:300 ላይ ተገኝታችሑ ከመምህራን ጋራ ወደ ጣቢያው እንድትሔዴ መታወቂያና አድሚሽን ካርድ ያልተረከባችሑ ተማሪዎችም እንድትረከቡ እያሣሠብን ይሕ ሣይደረግ ቀርቶ ለሚፈጠረው ችግር ሐላፊነቱን በግል የምትወስዱ መሆኑን ትምሕርት ቤቱ ያሣሥባል :: በተጓዳኝም ያለባችሑን ማንኛውንም ክፍያ እንድታጠናቅቁ እናሣሥባለን::

ውድ ተማሪዎቻችን ፤ የተከበራችሁ ወላጆች/አሳዳጊዎች የክፍልም ሆነ የሚኒስትሪ ፈተና እየተቃረበ ስለሆነ በርትተን እናጥና፡፡ የሞዴል ፈተናዎችን ደጋግመን እንለማመድ፡፡ ወላጆች/አሳዳጊዎችም የተለመደውን ድጋፍና ክትትል ለልጆቻችን እናድርግ ፡፡ ከትምህርት ቤቱ የሚሰጡ ማሳሰቢያዎችን በየጊዜው እየተከታተልን ምላሽ እንስጥ፡፡ በተለይ ተማሪዎቻችን ማንኛውም አይነት ክፍያ እንደሌለባቸው እናረጋግጥ ፤ ይህም በቀጣይ ከሚፈጠር እንግልት ይታደገናል፡፡ መልካም ውጤት ለተማሪዎቻችን በሙሉ!! ት/ቤቱ