C/E/R/State Guraghe Zone Wolkite Poly-Technic College & Satellite Campus
رفتن به کانال در Telegram
Talking all about TVET Training, Technology Transfer & Industry Extention Services
نمایش بیشتر405
مشترکین
-124 ساعت
+167 روز
+4030 روز
آرشیو پست ها
+9
"#ብቃት_ለቴክኒክና_ሙያ_ልህቀት" #በሚል_መሪቃል_ለአሰልጣኞችና_ዲኖች_የሚሰጠው_ሥልጠና_ዛሬ_ተጀመረ።
=========================
ነሐሴ 22/2016፡ የፌዴራል የስራና ክህሎት ሚንስትር አዘጋጅነት "ብቃት ለቴክኒክና ሙያ ልህቀት" በሚል መሪቃል የተዘጋጀው ሀገር አቀፍ ስልጠና በማዕከላዊ ኢትዮዽያ ክልል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች አሰልጣኝ መምህራንና ዲኖች በዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ማዕከል ስልጠናቸውን ዛሬ ጀምረዋል።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ የተገኙት የዋቸሞ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉ ሲሆን በዋናነት ደግሞ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ቢሮ ምክትል ኃላፊ አቶ ሰለሞን ፈርሻ አፅንኦት ሰጥተው እንዳሳሰቡት ስልጠናው በከፍተኛ ትኩረት ከፌደራል ጀምሮ የሚሰጥ መሆኑን፤ በስልጠናው የሚሳተፍ አሰልጣኝም ሆነ ዲን በቀጥታ በተቋም ደረጃ አውርዶ የሚተገብረው መሆኑንና በልዩ ትኩረት መሰልጠን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
በስልጠናው ላይ ከኮሌጃችን የተውጣጡ 190 አሰልጣኝ መምህራንና ዲኖች እየተሳተፉ ሲሆን ሥልጠናው የሚያተኩረው በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ፖሊሲ ላይ መሠረት አድርጎ በ11ዱ የዘርፉ የለውጥ እሳቤዎችን በማስገንዘብ ወደ ተሟላ ተግባር ለመግባት ታሳቢ ተደርጎ የተዘጋጀ ሲሆን ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜን 3 ቀን 2016 ዓ.ም ለተከታታይ 12 ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።
=========================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+6
#ስልጠና_ላይ_ለሚሳተፉ_አሰልጣኝ_መምህራን_ኦረንቴሽን_ተሰጠ!!
=========================
ነሐሴ 20/2016 ዓ.ም፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፖስ #በቴክኒክና_ሙያ_የለውጥ_እሳቤዎች ላይ የፌደራል የስራና ክህሎት ሚኒስትር በሀገር አቀፍ ደረጃ ባዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና ለሚሳተፉ አሰልጣኝ መምህራን የቅድመ-ስልጠና ኦረንቴሽን ሰጥቷል።
በኦረንቴሽኑ ላይ ከፌደራል የወረደውን የማስፈፀሚያ እቅድ ሰነድ በኮሌጁ አቶ ኸይሩ አህመዲን የቀረበ ሲሆን በሰነዱም የስልጠናው አላማና አሰፈላጊነት፣ በስልጠናው የሚሰጡ ርዕሰ ጉዳዮች፣ አሰልጣኝ መምህራን በስልጠናው ቆይታቸው ምን እንደሚጠበቅባቸውና ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ስነ-ስርዓቶች፣ የስልጠና አሰጣጥ ሂደቱና የመሳሰሉት ጉዳዮች ላይ ገለፃ ተደርጓል።
በመጨረሻም በሰነዱ ገለፃ መነሻ በተሳታፊ አሰልጣኝ መምህራን ግልፀኝነት የሚፈልጉ ሀሳቦችና ጥያቄዎች ተነስተው በኮሌጁ ዲኖች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶ ተጠናቋል።
=========================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
#ለስልጠና_ለምትሄዱ_አሰልጣኝ_መምህራን_በሙሉ!!
+9
#ኮሌጃችን_በተለያዩ_ሙያዎች_መርሐግብሮች_ያሰለጠናቸው_ሰልጣኞች_አስመረቀ። (ነሐሴ18/2016ዓ.ም) =========================
የወልቂጤ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ በተለያዩ ሙያዎች በዲግሪ፣ በደረጃ ና በአጫጭር ጊዜ ያሰለጠናቸው 589 ሰልጣኞች አስመረቀ።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የክልሉ ቴ/ሙ/ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ደቼ የቴ/ሙያ ኮሌጆች ብቁና የሰለጠነ የሰዉ ሃይል በማፍራት እና የቴክኖሎጂ በማምረት እንዲሁም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ በመስጠት ለሀገራችን ብልጽግና ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ መሆኑን ገልፀው ለተመራቂዎች ባገኙት እውቀትና ክህሎት ስራ ፈጥረው ተጠቃሚ መሆን አለባችሁ ብለዋል።
የጉራጌ ዞን አስተዳዳሪና የኮሌጁ የቦርድ ሰብሳቢ ተወካይ አቶ ዳርጌ ተክሉ የብልጽግና ጉዟችንን ለማረጋገጥ የቴ/ሙያ ዘርፍ ዜጎችን በተገቢዉ በመቅረጽና ወደ ስራ እንዲሰማሩ በማድረግ ቁልፍ ድርሻውን እየተወጣ ነው ብለዋል።
የጉ/ዞ/ቴ/ሙ/መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ሰርገማ በበኩላቸው የሀገራችን ብልጽግና ለማረጋገጥ የቴ/ሙያ ኮሌጆች የበኩላቸውን ድርሻ እየተወጡ መሆኑንና የዕለቱን ተመራቂዎች በኮሌጅ ቆይታቸዉ ያገኙትን እውቀትና ክህሎት ተጠቅመው ራሳችሁን ልትለውጡ ይገባል ብለዋል።
የኮሌጁ ዲን አቶ ኸይሩ አህመዲን በበኩላቸው የሰለጠነና የበቃ የሰው ኃይል በማፍራት ለኢንዱስትሪው በማቅረብ፣ የወደፊት የኢንዱስትሪ መሠረት የሆኑትን ማህበራት በማብቃት አቅማቸውን የማሳደግ፣ ቴክኖሎጂን ቀድቶና አሻሽሎ በመስራትና ለተጠቃሚ ማድረስ ላይ በርካታ ውጤት መገኘቱን ገልፀዋል።
በተጨማሪ በጋርመንት ተማሪዎች የተዘጋጀ ፋሽን ሾው የቀረበ ሲሆን በተለያዩ ዘርፎች በማገዝ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ላደረገው አካላት፣ ኢንደስትሪዎች፣ አሰልጣኞችና ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ሰልጣኞች ሽልማት በመስጠት ፕሮግራሙ ተጠናቋል።
+2
#ለእለቱ_እንቁ_ተመራቂዎቻችንና_ቤተሰቦቻችሁ 💐💐💐
#እንኳን_ደስ_አላችሁ_ደስ_አለን !!??💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐
#ነገ_ነሀሴ_18_2016_ለምናደርገው_የምርቃት_ፕሮግራማችን !!💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐
#ሁሉም_ዝግጁ_ተደርጓል!!💐💐💐
+4
#ወደ_አረብ_ሀገራት_ለስራ_ስምሪት_ለሚሄዱ_ዜጎች_የክህሎት_ስልጠና_ሰጥቶ_የብቃት_ምዘና_የማስመዘኑ_ሂደት_ተጠናክሮ_ቀጥሏል!!!
=========================
ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም፡ በወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ለስራ ስምሪት ወደ ተለያዩ የአረብ ሀገራት ለሚሄዱ ዜጎች የክህሎት ስልጠና ወስደው ዝግጁ ለሆኑ ዜጎች የብቃት ማረጋገጫ ምዘና እንዲመዘኑ ተደርጓል። በዛሬው የምዘና ፕሮግራም ላይ ከ130 በላይ የሚሆኑት ምዘናውን እንዲመዘኑና ብቁ እንዲሆኑ ተደርጓል።
በቀጣይም የዚህ ታላቅ እድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎቻችን ኮሌጃችን አስፈላጊውን ዝግጅት አድርጎ እየተጠባበቃችሁ ይገኛል።
#ከዚሁ_ጋር_በተያያዘ 😍😍😍
#በ2015 የስራ ዘመን ወደ አረብ ሀገራት ለስራ ስምሪት በኮሌጃችን #በቤት_አያያዝ፣ #በምግብ_ዝግጅትና #በቤተሰብ_እንክብካቤ ስልጠና ወስዳችሁ #የCOC ምዘና ተመዝናችሁ ብቁ ብትሆኑም በተለያዩ ምክንያቶች እድሉን ያልተጠቀማችሁ በሙሉ በአዲሱ አሰራር በOnline ተመዝግባችሁ የፓስፖርት ችግራችሁን ለመቅረፍና ተጠቃሚ እንድትሆኑ ለማድረግ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እየሰራን መሆኑን በደስታ እየገለፅን በማንኛውም የስራ ሰዓት በኮሌጁ የሰዉ ሀይል ልማት/ሬጅስትራር ቢሮ በመቅረብ ሪፖርት እንድታደርጉና ተጠቃሚ እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀባለን !!!🙏🙏🙏
#ለበለጠ_መረጃ
==========
0113301590
0113658672
0911318770
0923062919
በመደወል ተጨማሪ መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ👍
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅ!!!
#ማስታወቂያ !!
#በጋርመንትና_በውጭ_ሀገር_የስራ_ስምሪት_ላይ_የክህሎት_ስልጠና_ወስዳችሁ!!
#የብቃት_ምዘና_ለመውሰድ_ለተመዘገባችሁ_በሙሉ !!
ጤና ይስጥልን የቴክኒክና ሙያ ቤተሰቦች እንደምን ቆያችሁ?
በኢፌድሪ ስራና ክህሎት ሚንስቴር አዘጋጅነት የሚሰጠዉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማት አሰልጣኞች እና አመራሮች የማነቃቂያ ስልጠና ከነሃሴ 22 እስከ ጳጉሜ 03/2016 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑ ተገልጾልናል፡፡በመሆኑም ከወዲሁ የተቋም ስራዎች በጊዜ በመሸከፍ ወደ ስልጠና መግባት የሚያስፈልግ ሲሆን አንድ ሰልጣኝ ወደ ስልጠና ቦታ ሲሄድ ይዞ መሄድ ያለበት ግብዓቶች ቀጥሎ የተዘረዘሩት ናቸው፦
1. ብርድ ልብስ
2. ላብቶፕ/ስማርት ፎን
3. አንሶላ እና ትራስ ልብስ ይዞ መሄድ ይጠበቅበታል፡፡
እያንዳንዱ የስልጠና ተሳታፊ የት እንደተመደበ በቀጣይ ሲገለጽልን የምናሳዉቃችሁ ሲሆን በቢሮ ደረጃ የተመደቡ ባለሙያዎች የሚጠይቋችሁ መረጃ በአግባቡ በመስጠት ኃላፊነታችሁን እንድትወጡ እናሳስባለን፡፡
ሰለሞን ፈርሻ
15/12/2016 ዓ.ም
#በድጋሚ_የወጣ_አስደሳች_ማስታወቂያ 😍😍
=======================
#የውጪ_ሃገር_ሥራ_ስምሪት_ፍቃድን_በተመለከተ 👍👍
=======================
#የሥራና_ክህሎት_ሚንስቴር በውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነታቸው ተረጋግጦ መስራት እንዲችሉ ሰፊ የሪፎርም ሥራ ሲሰራ መቆየቱ ይታወቃል።
በዚህም ከዚህ ቀደም የውጪ ሃገር ሥራ ስምሪቱ 6 ወራት ይወስድ የነበረውን ሂደት በ20 ደቂቃ መጨረስ የሚያስችል ስርዓት ተግባራዊ ተደርጓል፡፡
ከዚህ ባለፈ ዜጎች በተሰማሩባቸው ሃገራት ደህንነታቸውን መቆጣጠር እና ኮንትራታቸውን ጨርሰው ወደ ሃገራቸው በሚመለሱበት ወቅት የተሻለ ሥራ መስራት የሚችሉበትን ምቹ ሁኔታ ተመቻችቷል።
በዚህ ሰፊ ርብርብ እና ትልቅ ሥራ በተሰራበት የውጪ ሃገር የሥራ ሥምሪት ስርዓት 7 የመንግስት ተቋማት በቴክኖሎጂ የተሳሰሩ ሲሆን ከ100 በላይ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች፣ ከ28 በላይ የሙያ ብቃት ምዘና እና ከ400 በላይ የአንድ አገልግሎት መስጫ ማዕከላት (OSSC)፣ ከ1000 በላይ ኤጀንሲዎች እና ኤምባሲዎች በዚህ የቴክኖሎጂ ስርዓት ማጣመር ተችሏል።
በመሆኑም አሁንም የውጪ ሃገር የሥራ ስምሪቱ ላይ እያደረግን ባለው የማስፋት ሥራ ወደ ውጪ ሃገር የምናሰማራቸውን ዜጎች ከቤት ውስጥ ሥራ ባለፈ የሰለጠነ እና በከፊል የሰለጠነ የሰው ሀይል ለማሰማራት የሚቻል በመሆኑ ሰልጥነው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ እናቀርባለን፡፡
=======================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
#እንኳን_ደስ_አላችሁ !!💐💐💐
#Congratulations!! 💐💐💐
#አስደሳች_ዜና 💐👩🎓💐👨🎓💐
#ለተመራቂዎችና_የተመራቂ_ቤተሰቦች_በሙሉ 💐💐💐
#እንኳን_አደረሳችሁ_አደረሰን_Congratulation_እያልን 💐💐💐
#በማዕከላዊ_ኢትዮጵያ_ክልል_መንግስት_በጉራጌ_ዞን_የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ በ2016 ዓ.ም በተለያዩ የሙያዎች በዲግሪ፣ በደረጃ እና በአጫጭር ጊዜ በመደበኛ፣ በማታና በሳምንቱ መጨረሻ መርሐ-ግብሮች ያሰለጠናቸውን ሰልጣኞች የፊታችን ነሀሴ 18/2016 ዓ.ም በጉራጌ ባህል አዳራሽ በደማቅ ሁኔታ የሚያስመርቅ በመሆኑ ተገኝተው የደስታው ተካፋይ እንዲሆኑ ይጋብዛል!! 💐🙏💐🙏💐
+9
#በክረምት_ለ2ኛ_ደረጃ_ተማሪዎች_ሲሰጥ_የነበረው_የክህሎት_ስልጠና_ማጠቃለያ_መርሐግብር_ተካሄደ።
=======================
ነሀሴ 09/2016 ዓ.ም፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ ከወልቂጤ ከተማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት እና ት/ት ጽ/ቤት ጋራ በጋራ ሲሰለጥኑ የነበሩ ተማሪዎች የማጠቃለያና እውቅና መርሐግብር ተካሄደ።
ተማሪዎቹ በቆይታቸው በመሠረታዊ የኮምፒውተር አጠቃቀም፣ በሶፍትዌር ዲቨሎፕመንትና በልብስ ስፌት ላይ ስልጠና የወሰዱ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ በስልጠናው ሂደት የሰሩዋቸውና ያበለፀጓቸውን ሶፍትዌሮችና አልባሳት ለእይታ አቅርበዋል።
በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የወልቂጤ ከተማ የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አብድልበር ሰይድ እንዳሉት ሀገራችን ኢትዮጵያን በማበልፀግ ድህነትን ማሸነፍ የምንችለውና በሳይንሱ ዓለም ማደግ የምንችለው በሳይንስና ቴክኖሎጂ ራሳችንን ስንደገፍ ብቻ መሆኑን ገልፀዋል።
በሌላ በኩል የኮሌጁ ዲን አቶ ኸይሩ አህመዲን እንዳሉት በእኛ የልጅነት ጊዜ ቴክኖሎጂን በቀላሉ ማግኘት ስለማንችል ተጎጂ እንደነበሩ እና አሁን ያለው ትውልድ ግን በርካታ ምቹ ሁኔታዎች ያሉት በመሆኑ እድለኛ መሆኑን በዚህ ላይ ደግሞ ትንሽ ጥረት ካደረገ ተዓምር መስራት እንደሚችሉ በመሆኑ ኮሌጁ የሚያደርገውን ድጋፍ ይቀላል።
የሳይንስና ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሃምዱ ካሚል በበኩላቸው በተለያዩ ዘርፎች ሲሰጥ የበረው የሥልጠና በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁንና ኮሌጁ ላደረገው ነገር ምስጋና አቅርበዋል።
በስልጠናው የተሳተፉ ተማሪዎች በበኩላቸው እንዳሉት ስልጠናውን በማግኘታቸው ምስጋናቸውን አቅርበው የሙያና የክህሎት ሥልጠናዎች በበጋ ወቅትም እንዲቀጥል ጠይቀዋል።
በመጨረሻም ለስራው መሳካት ድጋፍ ላደረጉ ግለሰቦችና ተቋማት የምስጋና ምስክር ወረቀት በመስጠት መርሐ-ግብር ተጠናቋል።
+6
#ኮሌጃችን_የከይዘን_አሰራር_ስርዓትን_በሁሉም_ዘርፎች_የማስፋት_ስራ_አጠናክሮ_ቀጥሏል።
=========================
ነሀሴ 08/2016 ዓ.ም፡ የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፓስ በጉራጌ ዞን የወልቂጤ ከተማ አስተዳደር የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት በቀረበለት ጥያቄ መሠረት #የከይዘን_አሰራር_ስርዓትን በጽ/ቤቱ የመተግበር ስራው ዛሬ ጀምሯል።
ኮሌጃችንም የከይዘን ስርዓትን ተቀብለው እየተገበሩ ከሚገኙ ተቋማት መካከል አንዱ ሲሆን በትግበራው ሂደትም ባስመዘገባቸው ውጤቶች በተለያዩ ጊዜያት የእውቅና ሽልማቶችን ማግኘት ችሏል፤ ከዚህ በተጨማሪ የአሰራር ስርዓቱ ወደ ሌሎች ተቋማት የማስፋት ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ከነዚህም መካከል፦ በቋሚነት የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ አካል በማድረግ በጥ/አ/ኢንተርፕራይዞች ውስጥ እንዲተገበር በማድረግ ምርታማነታቸውንና የሀብት አጠቃቀማቸውን የመጨመርና የማሻሻል ስራ እንዲሁም በተለያዩ ጊዜያት በዞንና በከተማ አስተዳደር ስር በሚገኙ ሴክተር መ/ቤቶች ውስጥ እንዲተገበር በማድረግ የተሻለ አገልግሎት አሰጣጥና የተገልጋይ እርካታን ማሻሻል ተችሏል።
በዚህም መነሻነት የከተማ አስተዳደሩ የሳይንስና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጽ/ቤት የከይዘን አሰራር ስርዓቱ በጽ/ቤታቸው ደረጃ እንዲተገበር በጠየቁት መሠረት ስራው የተጀመረ ሲሆን በአጠቃላይ የትግበራ ሲጠናቀቅ የጽ/ቤቱን አደረጃጀት ለስራ ምቹና ማራኪ ከማድረግ ባለፈ የአገልግሎት አሰጣጡን ቀልጣፋ በማድረግ የተገልጋይ እርካታ በመጨመር ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
====================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+9
#የስራ_ፈጠራ_ክህሎት_ላይ_ለአሰልጣኝ_መምህራን_የአቅም_ግንባታ_ስልጠና_መሰጠት_ተጀመረ!!
=========================
ነሀሴ 07/2016 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን ከኢትዮጵያ ኢንተርፕሪነርሺፕ ኢንስቲትዩት እና በማስተር ካርድ ፋውንዴሽን ባገኘው ድጋፍ መሠረት ከኮሌጃችን ሁሉም ት/ት ክፍሎች ለተውጣጡ አሰልጣኝ መምህራን የአሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ።
ስልጠናው ከኢንስቲዩቱ በመጡ በዘርፉ ከፍተኛ ልምድ ባላቸው አሰልጣኞች የሚሰጥ ሲሆን #በኢንተርፕሪነርሺፕ እና #በንግድ_አስተዳደር_ክህሎት ላይ አተኩሮ ለቀጣዮቹ ተከታታይ 8 ቀናት የሚሰጥ ይሆናል።
የስልጠናውም አላማ አሰልጣኞች በቀጣይ ሌሎች በኮሌጅና በክላስተር ደረጃ ሐሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን የሚያሰለጥኑ ሆኖ በዘላቂነት ደግሞ በየሚያሰለጥኑበት ሙያ የሚያበቋቸወን ሰልጣኞች ከሚሰለጥኑት ሙያ ጋር የስራ ፈጠራ ክህሎትና አስተሳሰብ ይዘው እንዲወጡ የበኩላቸውን እንዲወጡ ትልቅ ድርሻ እንዲያደርግ ታስቦ ነው።
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+9
#ዜጋ_ተኮር_የክረምት_በጎ_አድራጎት_ስራችንን_አጠናክረን_ቀጥለናል።
=========================
ነሀሴ 1/2016 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን የክረምቱ በጎ ፍቃድ አገልግሎት አካል የሆነ የአቅመ ደካማ አረጋዊ ቤት ግንባታ አጠናቆ አስረከበ።
በርክክብ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተለያዩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደር አመራሮች ተገኝተዋል። ከተገኙት መካከል የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ እንዳለ ስጦታው፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕግና አስተዳደራዊ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ክብርት ወ/ሮ መሠረት ወልደሰንበት፣ የጉራጌ ዞን ብልፅግና ፓርቲ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ ወ/ሮ አመተረዑፍ ሁሴን፣ የጉራጌ ዞን ቴ/ሙ/ት/ሥ/መምሪያ ኃላፊ አቶ መስፍን ስርገማ፣ የወልቂጤ ከተማ ምክትል የመንግስት ተጠሪ ወ/ሮ መንዚላ አህመድ፣ ከዞንና ከከተማ የተገኙ የሴቶች ሊግ አመራር አባላት፣ የኮሌጃችን ዲኖች እና የማኔጅመንት አባላት ይጠቀሳሉ።
በርክክቡ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት አመራሮች የተለያዩ መልዕክቶችን አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም የጉራጌ ዞን የሴቶች ሊግ አመራሮች የተለያዩ የቤት መገልገያ እቃዎች ድጋፍ አድርገዋል።
በመጨረሻ ድጋፍ የተደረገላቸው አረጋዊ ወ/ሮ ሽታዬ ኮሌጁ ያደረገላቸው ድጋፍ ከፍተኛ እንደሆነና ከቀዝቃዛውና ከሚያፈሰው ቤታቸው ወጥተው ወደ አዲሱ ቤታቸው በመግባታቸው ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል።
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+2
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ_የውስጥ_አቅማችንን_ለማሳደግ_በዋናው_ግቢያችን_ውስጥ_እያለማነው_የምንገኘው_3_ሄክታር_የበቆሎ_ማሳ_አሁናዊ _ገፅታ 😍😍
=========================
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+3
#ወደ_አረብ_ሀገራት_ለሚሄዱ_ዜጎች_የሚሰጠው_የክህሎት_ስልጠና_ተጠናክሮ_ቀጥሏል!!
=========================
ሐምሌ 29/2016 ዓ.ም፡ ወደ አረብ ሀገራት ለስራ ስምሪት ለሚሄዱ ዜጎች የሚሰጠው የክህሎት ስልጠና ተጠናክሮ ቀጥሏል።
ስልጠናው ዜጎች ለስራ የሚሰማሩባቸውን ሀገራት ባህልና ልምድ አውቀው ስራቸውን በአግባቡና በጥራት እንዲሰሩና ተወዳዳሪነታቸውንና ተጠቃሚነታቸውን የሚያሳድጉ ከፍተኛ ጥቅም ያለው ነው።
ስልጠናው በአጭር ጊዜ ውስጥ በንድፈ-ሀሳብና በተግባር የሚሰጥ ሲሆን ስልጠናው እንደተጠናቀቀ የብቃት ምዘናው (COC) እንዲወስዱ በማድረግ ወደ ፈለጓቸው ሀገራት የስራ ስምሪት እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታ የምንፈጥር ይሆናል።
የስልጠናውና የሰራ እድሉ ተጠቃሚ መሆን የምትፈልጉ አካላት በኮሌጁ ተገኝታችሁ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንጋብዛለን።
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
+5
#2ኛ_ዙር_የሶላር_አጫጭር_ጊዜ_ስልጠና_ተጀመረ።
=========================
ሐምሌ 29/2016 ዓ.ም፡ ኮሌጃችን ADRA Ethiopia በሚያደርግለት ድጋፍ እየተሰጠ የሚገኘው #የSolar_PV አጫጭር ጊዜ ስልጠና 2ኛው ዙር ዛሬ ተጀምሯል።
በስልጠናው ማስጀመሪያ ላይ የኮሌጁ ዲኖች፣ የADRA Ethiopia የኮሌጁ አስተባባሪ እንዲሁም የት/ት ክፍሉ ተጠሪዎች ተገኝተው የተለያዩ መልዕክቶችን ያስተላለፉ ሲሆን ስልጠናውንም በይፋ አስጀምረዋል።
ስልጠናው በአጫጭር ጊዜ በነፃ የሚሰጥ ሲሆን ሰልጣኞቹ በስልጠና ቆይታቸው በSolar_PV ሙያ ላይ አስፈላጊውን እውቀትና ክህሎት እንዲጨብጡ በማብቃት የራሳቸውን የስራ እድል እንዲፈጥሩ በሚያስችላቸው ደረጃ እንዲበቁ የሚደረግ ይሆናል።
በዚሁ አጋጣሚ የዚህ ሙያ ባለቤት በመሆን ተጠቃሚ ለመሆን የምትፈልጉ ዜጎች ከነገ ጀምሮ በኮሌጁ በመገኘት በመመዝገብ ስልጠናውን በነፃ መቀጠል የምትችሉ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን።
#ለአረንጓዴ_የኢንደስትሪ_አብዮት_እንተጋለን 🌳🌲🌴
#We_Stand_for_Green_Industrial_Revolution ☘️🌿🌴
#የወልቂጤ_ፖሊ_ቴክኒክ_ኮሌጅና_ሳተላይት_ካምፓስ 🌴🌿☘️
#አስደሳች_ዜና 😍😍
#ዓለም_አቀፍ_ሰርተፍኬት_የሚያስገኝ_ስልጠናን_በነፃ_መሠልጠን_ለምትፈልጉ_በሙሉ 👍👍
=========================
የወልቂጤ ፖሊ-ቴክኒክ ኮሌጅና ሳተላይት ካምፖስ ሀገራችን ኢትዮጵያ ከአረብ ኤምሬትስ መንግስት ባገኘችው #የ5_ሚሊየን_ኮደርስ አለም አቀፍ የነፃ የስልጠና የእድል ተጠቃሚ ይሁኑ እያለ ለመመዝገብ ከዚህ በታች ያለውን ሊንክ በመጠቀም ባሉበት ቦታ በቀላሉ መመዝገብ የምትችሉ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪ በኮሌጃችን ሬጅስትራር ጽ/ቤት በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን በደስታ እናስታውቃለን !!👍👍
https://forms.gle/xzsaujgyB4ihgAEt7
