cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ስውር ቁልፎች

ኢትዮጵያን መስራት የሚችሉት ኢትዮጵያውን ብቻ ናቸው። ኢትዮጵያውያን ያልሰሯት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትሆንም። ኢትዮጵያን ሰርተን እናኖራታለን፤ አሊያም ረስተን እናፈርሳታለን! @Siwur_Kulfoch

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 170
مشترکین
-124 ساعت
+17 روز
+2830 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

በማሕበራዊ ትስስር ድረ ገጾች ከምንታዘባቸውና ለትዝብት ከተጋለጥንባቸው ክስተቶች አንዱ በእነዚሁ መገናኛ መንገዶች የሚጋሩ ጽሑፎቻችን፣ አስተያየቶቻችን፣ ጥያቄዎቻችን፣ ትችቶቻችን፣ አገልግሎቶቻችን እና ክርስቲያናዊ ግብረ-ገባችን መስሎ ይታየኛል። የአንድ ነገር ልኩና መለኪያው ሲዛነፍና ልኬት በመመዘኛው ካልሆነ የሚያመጣው ውጤት የየግል እምነት፣ መርህ፣ አረዳድና ነገረ ትርጓሜ መሆኑ አይቀሬ ነው። የሁሉ ነገር መለኪያችን የሕያው የእግዚአብሔር ቃል ብቻ ሊሆን ይገባል። ይህንንም በጽኑ አምናለሁ። እንደ ባለአእምሮ ማሰብንም እቀበላለሁ። የግል ፍላጎቶች፣ ድብቅ ፍላጎቶች፣ የየራስ እውቀትና አረዳድ፣ እኛ የምንወደው፣ የእኛ... የሚሉ ሚዛኖች በቃለ እግዚአብሔር ቢፈተሹና ቢቃኙ መልካም ነው። ከቃለ እግዚአብሔርም በልጠውብን እንዳይሆን መመርመሩ ያድነናል። እግዚአብሔር የውስጠ ምክንያት አምላክ ነው። #ሁሉን እንደቃሉ! #ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር! #ሁሉን አካሉን ለማነጽ! #ሁሉን በፍቅር! #ሁሉን ለእግዚአብሔር መንግስት! #ሁሉን ወንድሞችን ለማቅናት! እንሁን! እናድርግ! እግዚአብሔር ልባችንን ይፈውስ! የልብ አንድነትንም ያድለን! ምንተስኖት መኩሪያ
نمایش همه...
👍 5
👍 18
Photo unavailableShow in Telegram
እጅግ የተወደድህ ወንድሜ ክብሩ ካሱ እና እህቴ ኤልሳቤት አሰፋ እንኳን ለከበረው ተቋም አምላክ አደረሳችሁ! እንኳን ደስ አላችሁ! 10 ዓመት በሙሉ ወንድሜ፣ ጓደኛዬ፣ በብዙ አጋዤ፣ የልብ ወዳጄ. . . ነህ፤ ክብርሽ። ትህትናህና ለእኔ የከፈልካቸው የቅንነት ዋጋዎችህ በእኔ ዘንድ ዋጋ አላቸው። ለሰው መልካም በመሆንህ አውቅሀለሁ። ብዙ የጓዳ ሀሳቦችን ተከፋፍለናል፤  ተመካክረናል። አንተ በእኔ ሕይወት ውስጥ በመኖርህ በብዙ አትርፌአለሁ። ሁሉን በዚህ መልኩ መመስከር አልፈልግምና ስለሁሉ በምስጋና ላብቃ። ኤልሲ በክብሩ ውስጥ አንቺን በብዙ አውቄሻለሁ። ታማኝና እውነተኛ እጮኛው መሆንሽን በድፍረት እመሰክራለሁ። ክበሪ እህቴ። ትዳራችሁን እግዚአብሔር ይባርክ! በኑሯችሁ እግዚአብሔር ይኑር! በእውነተኛ ተምሳሌታዊ ሕይወት ጌታ ዘመናችሁን ሁሉ ያለምልም! በፍቅር፣ በትዕግስት፣ በአብሮ ሰራተኝነት፣ ... ጌታ ቤታችሁን ይምራ!! መልካም ጋብቻ!! ወንድማችሁ ምንተስኖት መኩሪያ
نمایش همه...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
ባሳለፍነው ሳምንት  በታቦር ትምህርት ማዕከል(ኢቫን) ተገኝተን ከተማሪዎችና ከትምህርቱ ማሕበረሰብ ብር 6,075 መሰብሰባችን ይታወቃል። ዛሬ በተጨማሪ የሥነ መለኮት ተማሪዎች ብር 2,635 ሰብስበው ለዳጊ ህክምና አውለዋል። በጸሎትም ከጎናችን እንደሆኑ ገልፀውልናል።  ለዳግማዊ አሰፋ ስላሳዩት ፍቅር እናመሰግናለን።
نمایش همه...
መንፈሳዊ ውጊያ የተሰኘው የወንድማችን ኢያሱ መጽሐፍ ሊመረቅ እነሆ ቀናት ብቻ ቀሩት። የፊታችን እሁድ ሰኔ 02/2016 ዓ.ም በሀዋሳ አላሙራ ሕይወት ብርሃን ቤተ-ክርስቲያን ከቀኑ በ08:00 ይመረቃል! ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
نمایش همه...
👍 2
Photo unavailableShow in Telegram
የሀዋሳ ከተማን ጨምሮ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ አከባቢዎች እየተበራከተ ብቻም ሳይሆን እጅግ በሚያስፈራ ሁኔታ ዕድሜአቸው 14  ዓመት ከሆናቸው ታዳጊ ልጆች ጀምሮ በልደት ፕሮግራም የተጀመረ የአልኮል መጠጥ እና የጎጂ ሱሶች ልምምድ አስደንጋጭ ደረጃ ላይ ደርሷል። ምንም ገና ግራና ቀኛቸውን ለይተው ያላወቁ ታዳጊዎች እንደ መዝናኛ፣ እንደ ስልጣኔ፣ እንደ ማወቅ . . . ቆጥረው በዚህ ገዳይ ጎዳና እየነገዱ ለውድቀት መዳረጋቸው እንደ አንድ ሰው በብዙ የሚያሳዝነኝ ነው። ችግሩን እያወቅን እና እየታወቀ የሚሰጠው ትኩረት አናሳ መሆን፣ አባባሽ ምክንያቶችን በሕግ አለመከላከልና ምን አገባኝ? ባይነት ትውልድን እያመከነ ነውና ቸል አንበል! ምንተስኖት መኩሪያ
نمایش همه...
👍 1
እህቴ አትክልት አማረ እንኳን እግዚአብሔር ረዳሽ! እንኳን ደስ አላችሁ!! ቤታችሁን እግዚአብሔር ይስራ፤ ይባርክም። በኑሮአችሁ ሁሉ ክርስቶስ ይክበር። ትዳራችሁን በፍቅር ያጽና። መልካሙን ሁሉ እመኝላችኋለሁ! መልካም ጋብቻ! ምንተስኖት መኩሪያ
نمایش همه...
👍 4
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.