የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
5 400
مشترکین
-22624 ساعت
-2 2007 روز
-2 65830 روز
آرشیو پست ها
+4
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ አባላት የዕዙን ቢሮ ግንባታ ሂደት ጎበኙ።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 14 ቀን 2017 ዓ.ም
የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ ስታፍ አባላትና አመራሮች በኮዬ ፈጬ እየተገነባ የሚገኘውን የዕዙን ጠቅላይ መምሪያ ቢሮ የግንባታ ሂደት ተዘዋዉረዉ ጎብኝተዋል።
በጉብኝቱም የኮማንዶ እና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ዮሐንስ አያሌዉን ጨምሮ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች በጋራ በመሆን የግንባታ ሂደቱን ተመልክተዋል።
ለአመራሩና ለአባላቱ በፕሮጀክቱ መሀንዲሶች አማካኝነት ስለ ስራዉ ሂደትና አሁን ግንባታው የደረሰበት ደረጃ በማስመልከት ገለፃ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በዚህም መሰረት የግንባታ ሂደቱ ከተጀመረበት ከ2016 ጥር ወር ጀምሮ እስከ አሁን ድረስ በቀን እና በሌሊት እየተሰራ መሆኑን የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን የቤቶች ልማት ማዕከል ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ዘይነባ ዑመር ተናግረዋል።
በተጨማሪም አስራ አምስት ብሎኮች ያሉት መሆኑን እና 1.7ኪ.ሜትር የዉስጥ መንገድ ፣ ካፍቴሪያ ክሊኒክ እንዲሁም ሌሎች መሰረታዊ እና አስፈላጊ የሆኑ ነገሮች ሁሉ የተሟላለት መሆኑን አጠቃላይ የስራ ሂደቱም 65% እንደደረሰ እና በቀጣይ ጥቂት ወራቶችም ሙሉ ስራዉን በማጠናቀቅ እንደሚያስረክቡ ኢንጅነር ዘይነባ ዑመር ገልፀዋል።
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ሳይበር ኦፕሬሽን ዋና ዳይሬክቶሬት እና የጣሊያን የመከላከያ ሳይበር ክፍል በጋራ ለመስራት ተስማሙ።
የመከላከያ ሳይበር ኦፕሬሽን ዳይሬክተር ኮሎኔል ሀገር አስቻለ እንዳሉት ስምምነቱ በሳይበር ዘርፍ በትብብር ለመስራትና የሙያተኞችን አቅም ለማሳደግ ያለመ ነው፡፡
የተቋሙን የሳይበር ጥቃት ለመከላከልና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ብቁ የሆኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት ስምምነቱ ጠቃሚ ነው ማለታቸውን የመከላከያ ሠራዊት ማኅበራዊ ትስስር ገጽ መረጃ አመላክቷል፡፡
የኢትዮጵያ ተወካይ ከተመራጩ የሶማሊላንድ ፕሬዚዳንት ጋር ተወያዩ፡፡
በሶማሊላንድ የኢትዮጵያ ቆንጽላ ጽ/ቤት ኃላፊ ተሾመ ሹንዴ በቅርቡ ከተመረጡት የሶማሊላንድ አዲሱ ፕሬዚዳንት አብዱልራህማን ሞሓመድ አብዱላህ ጋር ተወያይተዋል፡፡
ተሾመ ሹንዴ ከኢትዮጵያ ወታደራዊ አታሼዎች እና ከቆንጽላ ጽ/ቤቱ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን በትላንትናው ዕለት ከኢትዮጵያ መንግስት የተላከ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አድርሰዋል።
ሀላፊው በዚህ ወቅት ከአዲሱ ተመራጩ የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዱልራህማን ሞሓመድ አብዱላህ ጋር፤ ቀጠናዊ ደህንነትን እና የንግድ ትብብርን ጨምሮ በኢትዮጵያ እና ሶማሊላንድ መካከል ግኑኝነትን በማጠናከር ዙሪያ መወያየታቸውን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።
የኢትዮጵያ መንግስት የሶማሊላንድ ህዝብ ላካሄደው “ሰላማዊና ዴሞክራሲዊ ምርጫ” የእንኳን ደስ አላችሁ ሲል መልዕክት ማስተላለፉ ይታወሳል።
ሶማሊላንድ ሰሞኑን ባካሄደችው ምርጫ የዋዳኒ ፓርቲ መሪ የሆኑት አብዲራህማን ሞሀመድ አብዲላሂ (ሲሮ)፤ ከኢትዮጵያ ጋር የባህር በር ስምምነት የተፈራረሙትን የወቅቱን የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ሙሴ ቤሂ አብዲን በማሸነፍ ተመርጠዋል።
+2
በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ተሃድሶ ማዕከላት የማስገባት ስራ ተጀመረ
👉የቀድሞ ተዋጊዎችን መልሶ ለማቋቋም ዛሬ በይፋ በተጀመረው ስራ፣ በትግራይ ክልል የቀድሞ ተዋጊዎችን ወደ ተሃድሶ ማዕከላት ማስገባት መጀመሩን የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡
👉የቀድሞ ተዋጊዎች ወደ ተሀድሶ ማዕከላት ለመግባት በእጃቸው ያለውን ቀላል ትጥቅ ማስረከብ ይጠበቅባቸዋል።
👉በዚሁ መሰረት የመጀመሪያው ዙር የነፍስ ወከፍ እና የቡድን ጦር መሳሪያዎች ርክክብም የአፍሪካ ህብረት፣የመንግስታቱ ድርጅትና የአውሮፓ ህብረት ተወካዮች በተገኙበት ተከናውኗል።
👉በመቐሌ፣ እዳጋ ሀሙስ እና ዓድዋ የመጀመሪያ ዙር ተዋጊዎች ስልጠና የሚወስዱባቸው ማዕከላት መዘጋጀታቸውን የብሔራዊ ተሀድሶ ኮሚሽን ማስታወቁ ይታወሳል።
👉የቀድሞ ተዋጊዎች በተዘጋጁ ማዕከላት ስልጠናዎችን ከወሰዱ በኋላ የመቋቋሚያ ድጋፍ ተደርጎላቸው ወደ ማህበረሰቡ በመቀላቀል መደበኛ ሕይወታቸውን እንዲመሩ ይደረጋል ተብሏል።
Via :- FBC
#DDR
" ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረት ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " - የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር
የመጀመሪያ ዙር የትግራይ የቀድሞ ተዋጊዎችን ዲሞቢላይዝድ በማድረግ ወደ ተሃድሶ ስልጠና ማዕከላት የማስገባት ስራ በይፋዊ ስነስርዓት ተጀምሯል።
ዛሬ በተካሄደ ይፋዊ ስነስርዓት ላይ የተገኙት የኢፌዴሪ ሀገር መከላከያ ሰራዊት ከፍተኛ ወታደራዊ አመራር ብርጋዴር ጀነራል ደርቤ መኩሪያው ፤ " የዴሞብላይዜሽን አሰራር ሴት ተዋጊዎችን ፣ አካል ጉዳተኞችን እና በአደረጃጀት ውስጥ ያሉ አመራሮችን በማስቀደም ይፈፀማል " ብለዋል።
በዴሞብላይዜሽን አሰራር በየቀኑ 320 ታጣቂዎች ወደ ስልጠና ማእከላት የማስገባት ስራ እንደሚሰራ ጠቁመዋል።
በመጀመሪያ ዙር 75 ሺህ ታጣቂዎች እንደሚስተናገዱ አክለዋል።
" ማንኛውም ትጥቅ ከሀገር መከላከያ ሰራዊት ውጭ መያዝ የሀገሪቱ ህገ-መንግስት ይከለክላል ስለሆነም በትግራይ እየተፈፀመ ያለው የዴሞብላይዜሽን አፈፃፀም ህግና ስርዓት ተከትሎ የሚፈፀም ነው " ሱሉ ተናገረዋል።
ብ/ጄነራሉ ፤ " ትጥቅ መፍታት መሸነፍ ፣ መዋረድ ወይም ራስን ዝቅ ማድረግ ማለት አይደለም። ትጥቅ መፍታት ማለት የሀገር አንድነትና ሰላም በፅኑ መሰረይ ላይ ከማቆም አንፃር መታየት አለበት " ብለዋል።
" ትጥቅ ማስረከብ ማለት ያለችን እንዲት ሀገር ከሚጋረጡባት የውጭ ስጋቶች መታደግ መሆኑን መገንዘብ ያሻል " ያሉት ጀነራሉ " ትጥቅ የማስፈታት ተግባሩ የትግራይ እና በክልሉ ደንበር አከባቢ ያለው የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ተፈፃሚ ይሆናል " ሲሉ አሳውቀዋል።
የትግራይ የፀጥታ እና የሰላም ቢሮ ሃላፊ ጀነራል ፍስሃ በበኩላቸው ፤ " ትጥቅ የመፍታቱ ተግባር እርምጃ ለትግራይና ለሀገር ሰላም የተከፈለ ውድ እና ሁሌ በታሪክ ድምቆ የሚታወስ ፍፃሜ ነው " ብለዋል።
ዛሬ ትጥቃቸው ያስረከቡ 320 የቀድሞ ተዋጊዎች ሲሆኑ ወደ ተዘጋጀላቸው የስልጠና ማእከላት ማምራታቸው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ስነ-ስርዓቱ ከተከናወነበት ቦታ በላከው መረጃ ገልጿል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
ባይደን ዩክሬን ከአሜሪካ በተላኩላት ሚሳኤሎች ሩሲያን እንድትመታ ፈቀዱ፡፡
- ቭላድሚር ፑቲን በበኩላቸው እጃችንን አጣጥፈን አንቀመጥም ብለዋል፡፡
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዩክሬን ከአሜሪካ በተላኩላት ሚሳኤሎች በሩሲያ ላይ ጥቃት እንድትፈጽም ፈቅደዋል።
ባይደን ኬቭ ለወራት ስታነሳው የነበረውን ከድንበሯ ውጭ (በሩሲያ መሬት ውስጥ) የአሜሪካን ሚሳኤሎች የመጠቀም ጥያቄ የተቀበሉት በጥር ወር ዋይትሃውስን ለቀው ከመውጣታቸው በፊት ነው።
የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮልድሚር ዜለንስኪ “እንዲህ አይነት ጉዳዮች በይፋ አይገለጹም፤ ሚሳኤሎቹ ራሳቸው ይናገራሉ” በማለት ከዋሽንግተን ፈቃድ ማግኘታቸውን በተዘዋዋሪ አረጋግጠዋል።
የባይደን አስተዳደር ከሞስኮ በሚነሱ ቅሬታዎች እና ማሳሰቢያዎች ምክንያት አሜሪካ ለዩክሬን የላከቻቸው ረጅም ርቀት ሚሳኤሎች በሩሲያ ግዛት ውስጥ ጥቃት ለማድረስ እንዳይውሉ ሳይፈቅድ ቆይቷል።
ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲንም ምዕራባውያን ሀገራት መሰል ውሳኔ ካሳለፉ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃልኪዳን ድርጅት(ኔቶ) በዩክሬኑ ጦርነት “በቀጥታ እንደተሳተፈ ይቆጠራል”፤ የኒዩክሌር ጦርነትም ሊያስነሳ ይችላል በሚል በተደጋጋሚ ማስጠንቀቃቸው የሚታወስ ነው።
የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ ማሪያ ዛካሮቫ፤ ፕሬዚዳንት ባይደን ዩክሬን በሚሳኤሎቹ የሩሲያን ግዛት እንድትመታ ፈቃድ መስጠታቸውን የሚገልጽ መረጃ መውጣቱን ተከትሎ ፕሬዚዳንት ፑቲን በጉዳዩ ላይ አስተያየት መስጠታቸውን ገልጸዋል።
ቃል አቀባይዋ ፕሬዚዳንቱ ሰጡት ባሉት ምላሽ፥ “ባይደን በሩሲያ ላይ ጥቃት እንዲፈጸም ፈቃድ ሲሰጡ እጃችንን አጣጥፈን አንቀመጥም” ማለታቸውን ተናግረዋል ፡፡
የተከሰከሰም ሆነ ችግር ያጋጠመው ሄሊኮፕተር የለም
የመከላከያ ሚኒስቴር
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 08 ቀን 2017 ዓ.ም
የኢፌዴሪ አየር ኃይል ካሉት "ቤዞች" አንደኛው ምድብ የሆነው ባህርዳር የሚገኘው የምዕራብ አየር ምድባችን ነው። በትላንትናው ዕለት በነበረው የአየር ኃይል የምድብ ልምምድ ምክንያት መደበኛ የአየር መንገድ በረራ ለጥቂት ጊዜያት ተቋርጦ የነበር መሆኑን የኢፌዴሪ መከላከያ ማኒስቴር አስታውቋል።
ይሁን እንጅ የአየር መንገድ ተሳፍሪዎች የተወሰነ መጉላላትን አጋጣሚ በመጥቀስ ሄሊኮፕተር ተበላሸ፣ ተከሰከሰ በሚል የማደናገሪያ ሃሳብ በአንዳንድ ማህበራዊ ሚዲያ እየተራገበ ይገኛል።
መደበኛ በረራ ለውስን ጊዜያት ተቋርጦ የነበረው በተገቢው መንገድ ስራ የጀመረ ሲሆን የምዕራብ አየር ምድብም ልምምዱን ስኬታማ በሆነ መንገድ አጠናቋል።
አሁን እያየን ያለነው ምናልባትም የጠላት ሁለንተናዊ አቅምና የፕሮፖጋንዳ መስክ መክሰርና መከስከስ ካልሆነ በስተቀር የተከሰከሰ ሄሊኮፕተር እንደሌለ ማሳወቅ እንወዳለን።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስቴር
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
https://youtu.be/qdVMWMXAKzg?feature=shared
የፅንፈኛው ፋኖ ገመና ሲገለጥ😭😭😭😭
https://youtu.be/qdVMWMXAKzg?feature=shared
የፅንፈኛው ፋኖ ገመና ሲገለጥ😭😭😭😭
ጁባላንድ፣ ከሞቃዲሾ ፌደራል መንግሥት ጋር ያላትን የሥራ ግንኙነት ማቋረጧን አስታውቃለች
ጁባላንድ ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ግንኙነቷን ያቋረጠችው፣ ፕሬዝዳንት ሐሰን ሞሐመድ በመላዋ ሱማሊያ የቀጥተኛ ምርጫ ሥርዓት ተፈጻሚ እንዲኾን ያወጡትን ሕግ ውድቅ በማድረግ ቀጥተኛ ያልኾነ ምርጫ ለማድረግ መወሰኗን ተከትሎ ነው።
የጁባላንድ አስተዳደር፣ የአገሪቱ ጦር አልሸባብን ከጁባላንድ እንዳያጸዳ ፌደራል መንግሥቱ እንቅፋት ፈጥሯል በማለትም ከሷል። ራስ ገዟ ፑንትላንድ ቀደም ሲል ከፌደራል መንግሥቱ ጋር ግንኙነቷን ማቋረጧ አይዘነጋም።
የክልሉ የግብርና ልማት የተረጋገጠው በሠራዊቱ ማስዋዕትነት ነው፡፡
ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ህዳር 02 ቀን 2017 ዓ.ም
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አረጋ ከበደ የክልሉ የግብርና ልማት የተረጋገጠው በሀገር መከላከያ ሠራዊት ማስዋዕትነት መሆኑን ገልፀዋል፡፡
ርዕሰ መስተዳደሩ ይህንን የገለፁት ከክልሉ እንዲሁም ከኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በመሆኑ በሰሜን ሸዋ ዞን በኩታ ገጠም የለማውን ከፍተኛ የስንዴ ምርት በጎበኙበት ዕለት ሲሆን በክልሉ ያለውን የግብርና ልማት የተመለከተ ሰው ሠራዊታችን በትክክል ተዋጊ ብቻ ሳይሆን ቁልፍ የልማት ሀይል መሆኑን ከመገንዘቡም በላይ የሀገር መከላከያ ሠራዊት ለሀገሩና ለህዝቡ የሚከፍለውን መስዋዕትነትና የላቀ ህዝባዊነቱን እያንዳንዱ የክልሉ አርሶ አደር በየመንደሩ በተግበር ያረጋገጠበት ነው ብለዋል፡፡
አቶ አረጋ ከበደ ሠራዊት ባይኖር ኖሮ የክልሉ ህዝብ በሰው ሰራሽ ድርቅ ተመትቶ ከመራብ አይድንም ነበር፤ በመሆኑም የግብርና ምርትን መስዋዕትነት ድረስ በመክፈል ለአርሶ አደሩ በማድረስ ይህንን አደጋ በመቀልበስ ግብርናውን ለውጤታማነት ያበቃው መከላከያ ሠራዊት ነውና አርሶ አደራችን ይህንን ውለታውን መቼም አይዘነጋውም ነው ያሉት፡፡ ብቻም ሳይሆን ጠላት እንደሚያወራው ሳይሆን ህዝባችን ለሠራዊቱ የላቀ ክብር አለው ብላዋል፡፡
በጉብኝቱ ላይ የተሳተፉት የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ ሃላፊ ዶክተር ኃይለማርያም ከፍያለው በበኩላቸው ክልሉ በ2016 /17 ዓ.ም የምርት ዘመን 5.2 ሚሊየን ሄክታር መሬት በሰብል በመሸፈን 169 ሚሊዮን ኩንታል የግብርና ምርት ለመሰብሰብ አቅዶ የሰራ ቢሆንም እቅዱ ያለ ሀገር መከላከያ ሠራዊት እንደማይሳካ ተናግረዋል።
ፅንፈኛው ሀይል የግብርና ግብዓት ለአርሶ አደሩ እንዳይደርስ በማድረግ ከህዝብ እየዘረፈና እየቀማ ሲበላ አርሶ አደሩ የግብርና ስራውን ሳይሰራ ቀርቶ ለችግር እንዳይጋለጥ መስዋዕትነት በመክፈል ይህንን ሁኔታ ቀልብሶ ዛሬ ለአጥጋቢ ውጤት ያበቃን የሀገር መከላከያ ሠራዊት ነው ብለዋል፡፡ እያየነው የለነው የስንዴ ጫካም የእሱ መስዋዕትነት ውጤት ነውና አርሶ አደራችንም ይህንን አይዘነጋም ሲሉ ተናግረዋል፡፡
https://youtu.be/NPfZYeC9Rvg?si=T2O0iYiz-j6-KX1_
አዲስ መረጃን ከቻናላችን ያግኙ👇
👇Telegram
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
👉YouTube 👇
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
#WhatsApp
https://whatsapp.com/channel/0029VaWOSZgLY6dED9IVqO36
Facebook 👇
https://www.facebook.com/Comando.and.airborne.forces
