የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
5 576
مشترکین
-40724 ساعت
-2 4147 روز
-2 42630 روز
آرشیو پست ها
የሰሜኑ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት "የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አይደለም ለተራ አሸባሪ የህወሓት ቡድን ቀርቶ ለአፍሪካ ቀንድ ሰላምዋ ማስጠበቅ የሚችል ብቁ ወታደር ነው፤ ኢትዮጵያን በማንም የሰፈር ሽፍታ ማሸነፍ አይቻልም" በማለት የተናገሩት የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላክያ ሰራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጀነራል #ሳሞራ_የኑስ ከረጅም ግዜያት በኃላ ወደ ሚዲያ ብቅ ብለው ዝምታቸውን ሰብረዋል።
ጀነራሉ "በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ለምን ወደ ውጊያው አልገቡም? የትግራይን ህዝብንስ ለምን አልደገፉም? የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው ለጥያቄው በአጭሩ መልስ ሲመልሱ “አልሄድም። ያልተዘጋጀሁበትን እና ያላመንኩበትን ውጊያ አልሳተፍም። እምነቴ የትግራይ ህዝብ መዋጋት የለበትም ወደ ውጊያ መግባት የለበትም የሚል ነው።” በማለት መልሰዋል።
ወዳጄ፤ ሰው ውግያን ጠንቅቆ ሲያቅ ልክ እንደዚህ ውግያን እና የእርስ በእርስ ጦርነትን አምርሮ ይጠላል። ነገርግን የደሀ ልጅን ደም እየገበሩ የስልጣን ጥማቸውን ለማርካትና ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ የሀገሪቱን ሀብት የመበዝበዝ ፍላጎት ያላቸው አንዳንድ የህወሓት አመራሮች ዛሬም ከትናቱ ጥፋታቸው ሳይማሩ ከፌደራል መንግስት ጋር ጨምሮ እዛው እርስ በእርስ ለመዋጋት ለስልጣን ሹኩቻ ሴራ ይጠነስሳሉ ጦርነት ይሰብካሉ።
በኢትዮጵያዊነታቸው ፈፅሞ የማይደራደሩት ጀነራል ሳሞራ የኑስ በሀገራችን ኢትዮጵያ ታሪክ የክብር ኒሻን ተሸልመው በሰላም ከስልጠን የወረዱ የመጀመሪያው ኢታማዡር ሹም ናቸው።
ጀነራሉን ቢያደምጡት ኑሮ በዚህ ስድስት ዓመታት ውስጥ በትግራይ ክልልም ሆነ በመላው ሀገሪቱ ላይ የደረሰው ሰብአዊና ቁሳዊ እልቂት ፈፅሞ አይደርስም ነበር።
+3
#NewsAlert
የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ለሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ላይ ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ ፃፉ።
እግዱ የተፃፈላቸው ከፍተኛ አመራሮች ፦
- ሜጀር ጀነራል ዮውሃንስ ወ/ጊዮርጊሰ
- ሜጀር ጀነራል ማሾ በየነ
- ብርጋዴር ጀነራል ምግበይ ሃይለ ናቸው።
ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ መጋቢት 1/2017 ዓ.ም የፃፉት ጊዚያዊ የእግድ ደብዳቤ ፦
" ከመንግስት ውሳኔ ውጪ መላ ህዝባችን ፣ ወጣቱን ወደ ግርግር ፤ የፀጥታ ሃይላችን ወደ እርስ በርስ ግጭት ብሎም ህዝባችን ወደ እማይወጣበት አዘቅት የሚያስገባ አደገኛ እንቅስቃሴ አልቆመም ስለሆነም እርስዎ ስርዓት ባለው አካሄድ መግባባት እስኪደረስ ድረስ ከመጋቢት 1/2017 ዓ.ም ጀምሮ ላልተወሰነ ጊዜ ከአዛዥነትዎ የታገዱ መሆንዎን አስታውቃለሁ " ይላል።
በትግራይ ክልል በአመራሮች መካከል የተፈጠረው ልዩነት እንዲፈታ ብዙ ጥረት ቢደረግም ምንም መፍትሄ ሳይገኝለት ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን ነዋሪዎችም ሁኔታው ስጋት ላይ ጥሏቸዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle
ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ✅
📢🔴https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
📢🔴ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
ትክክለኛውን የቴሌግራም ቻናላችንን አሁኑኑ ይቀላቀሉ✅
📢🔴https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
📢🔴https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://youtu.be/B5ZoVN-c6gI?feature=shared
ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://youtube.com/shorts/kD4K80lx3TY?si=CPbRFyXsiIrynkaM
ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://youtu.be/a1ImrJD44dk?si=-WR0ACyseSFR0V4e
ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://youtu.be/VtRnfLNH5H4?si=hgt2V60izE0MxWOl
ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
+9
#ኢትዮጵያ_ድሮን_ማምረት_ጀመረች 🇪🇹🇪🇹🇪🇹
ገና ያልታየ ተዓምር አብረን እናያለን:: ኢትዮጵያ በልጆቿ ትኩራ🇪🇹🇪🇹🇪🇹
በኢትዮጵያውያን እጆች የተሰሩ ሰው አልባ የሰማይ በራሪዎች ከጥቂት ደቂቃ በኋላ በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) አማካኝነት ይመረቃሉ።
የባንዳ ተለላኪ ባንዳዎች “ድሮን ምን ይሰራል?” የሚል ጽሁፍ እያዘጋጃችሁ ጠብቁን
በቅርቡ የኑክሌር ማብላያ ማሳካታችን እንደማይቀር ተስፋ አደርጋለው🇪🇹🇪🇹
Via: Natnael
ለተጨማሪ መረጃዎች ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ ⤵️
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ⤵️
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
😍 | ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች
🏴 በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ
09:30 | ኖቲንግሃም ከ ማንችስተር ሲቲ
12:00 | ብራይተን ከ ፉልሃም
12:00 | ክርስታል ፓላስ ከ ኢፕስዊች
12:00 | ሊቨርፑል ከ ሳውዝሃፕተን
02:30 | ብሬንትፎርድ ከ አስቶን ቪላ
05:00 | ወልቭስ ከ ኤቨርተን
🇪🇸በስፔን ላሊጋ
10:00 | ሴልታ ቪጎ ከ ሌጋኔስ
12:15 | አላቬስ ከ ቪያሪያል
02:30 | ቫሌንሲያ ከ ቫላዶሊድ
05:00 | ባርሴሎና ከ ኦሳሱና
🇮🇹በጣሊያን ሴሪያ
11:00 | ኮሞ ከ ቫሌንዚያ
11:00 | ፓርማ ከ ቶሪኖ
02:00 | ሊቼ ከ ኤሲ ሚላን
04:45 | ኢንተር ከ ሞንዛ
🇩🇪በጀርመን ቡንደስሊጋ
11:30 | ባየር ሌቨርኩሰን ከ ወርደር ብሬምን
11:30 | ባየር ሙኒክ ከ ቦኩም
11:30 | ዶርትሙንድ ከ ኦግስበርግ
11:30 | ሆልስታይን ኪል ከ ስቱትጋርት
11:30 | ወልቭስበርግ ከ ሴንት ፓውሊ
01:30 | ፍራይበርግ ከ RB ሌፕዚሽ
🇫🇷በፈረንሳይ ሊግ ኤ
01:15 | ሬምንስ ከ ፒኤስጂ
03:00 | ሊል ከ ሞንፔሌ
04:45 | ማርሴ ከ ሌንስ
ሩሲያ በባላስቲክ ሚሳዔልና ድሮን ጥቃት ዩክሬንን እጅ ወደላይ አስብላለች።
📌ዘለንስኪ የተኩስ አቁም እንዲታወጅ ጠይቀዋል።
ፕሬዚዳንት ዘለንስኪ ይህን ሀሳብ ያቀረቡት ሩሲያ የባላስቲክ ሚሳዔልና ድሮን ጥቃት መፈጸሟን ተከትሎ ነው።ጥቃቱ በዩክሬን የኃይል ምንጮች ላይ ጉዳት ማድረሱን ፕሬዚዳንቱ አስታውቀዋል።"ዩክሬን ለሰላም ዝግጁ ናት" ያሉት ዘለንስኪ "የሰላም ጥረታችን ሩሲያ ጦርነቱን እንድታቆም ያስገድዳታል" ሲሉ ተናግረዋል።
#ኢትዮጵያ በ #አልሸባብ ዒላማዎች ላይ አየር ጥቃት መፈጸሟን የ #ሶማሊያ ሚኒስትር አረጋገጡ
✓✓✓✓የኢትዮጵያ አየር ኃይል በሶማሊያ መካከለኛው ሸበሌ ክልል በአልሸባብ ታጣቂዎች ላይ ኢላማ ያደረገ የአየር ጥቃት ማካሄዱን የሶማሊያ የመከላከያ ሚኒስትር በዛሬው ዕለት አረጋገጡ።
የሀገሪቱ የመከላከያ ሚኒስትር አብዱልቃዲር መሀመድ ኑር እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ኃይል በአልሸባብ ምሽግ ላይ የሚሳኤል ጥቃት የተፈጸመው ከሶማሊያ ፌዴራል መንግስት ጋር በመተባበር ነው። "ያለ መንግስት እውቅና በሶማሊያ ምንም አይነት የአየር ጥቃት ሊፈፀም አይችልም" ብለዋል። ይሁን እንጂ በኦፕሬሽኑ ስለደረሰው ሞት ወይም ጉዳት ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል።
ሚኒስትሩ የአንካራው ስምምነት በአል-ሸባብ ላይ ለሚወሰዱ የጋራ ጥረቶች ማዕቀፍ መሆኑን በመጥቀስ የሶማሊያ እና የኢትዮጵያ የፀጥታ ትብብር እየጨመረ መምጣቱን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ የፈጸመችው የአየር ጥቃት፤ ሶማሊያ የኢትዮጵያ ኃይሎች በሶማሊያ የአፍሪካ ህብረት የድጋፍ ተልዕኮ (አውሶም) ውስጥ እንዲካተቱ መፍቀዷን ተከትሎ በቅርብ አመታት ውስጥ በክልሉ በይፋ ያደረገችው የመጀመሪያው የአየር ጥቃት ነው ተብሏል።
ይህ ዘመቻ የተካሄደው በውጭ አገር ወታደሮች ድጋፍ ባገኘው ሶማሊያ ኃይሎች እና በአልሸባብ ታጣቂዎች መካከል በዚህ በረመዳን ወር በመካከለኛው ሸበሌ እና ሂራን ጥቃት በተባባሰበት ወቅት ነው።
ይህ በእንዲህ እንዳለ #አሜሪካ ጥቃት ሊፈፀም እንደሚችል ማስጠንቀቋን ተከትሎ የ #ሞቃዲሾ ባለሥልጣናት በአደን አዴ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ የጦር መሳሪያዎች እና ወታደራዊ ተሽከርካሪዎች እንዳይገቡ በማገድ የፀጥታ ማስጠበቅ እርምጃዎችን አጠናክረዋል ሲል የጋሬዊው ኦንላይን ዘግቧል።
================
+7
የኢትዮጵያ ጦር የሶማሊያን ጦር በማሸነፍ ካራማራ ተራራ ላይ ደማቅ ታሪክ የፃፈበት 47ኛ ዓመት!
እንኳን ለድሉ መታሰቢያ በዓል አደረሰን🇪🇹❤
ልክ የዛሬ 47 ዓመት ሀገር ጠርታው ተኝቶ የማያድረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዳር ዳር ተሰማማ። የተከበረች ሀገሩን የደፈረውን ጠላቱን ለመደምሰስ ተንቀሳሰ። ንቡ ተነሳ። አንበሳው አገሳ። ኢትዮጵያውያን ወደ ጦር ማሰልጠኛ ተመሙ። የእናት ሀገር ፍቅር ሰንቀው ሰለጠኑ።
ካራማራ ተራራ በኢትዮጵያውያን ጀግኖች ተመላች። በደስታ ዘለለች። ምስጢራዊት አረንጓዴ ቢጫ ቀይዋ ሠንደቅ በድል ተውለበለበች። የማይቀረው ድል ለእርሷ ብቻ የተሰጠ የሚመስለው አሸናፊነት ለኢትዮጵያ ኾነ። የኢትዮጵያ ሕዝብ በየካቲት 23 የዓድዋ ድልን አክብሮ በየካቲት 26 አዲስ ድል ተቀዳጀ። ሌላ የድል በዓል ለትውልድ አስቀመጠ።
ለአብሮነቶ ከልብ እናመሰግናለን🙏
+2
እስራኤል እጅግ አስደንጋጭ ነገር ከኒውክለር ጣቢያዋ አግኝታለች።
የእስራኤል ሰማይ ጠባቂ የሚባለው አይረን ዱምን ጨምሮ ሚስጥራዊ የኒውክለር ጦር መሳሪያ ማምረቻ ውስጥ የሚሰራ አንድ የኬሚካል ሳይንቲስት የኢራንን ተላላኪ ሆኖ መገኘቱ ተደርሶበት እስራኤል ተጨንቃለች።
የእስራኤልን ሚስጥራዊ የኒውክለር ጣቢያ መረጃዎች ያውቃል የተባለው ሰው የኢራን የስለላ መረብ ውስጥ ገብቶ መገኘቱን ያሳወቀው የእስራኤል ጦር ምናላባትም ለኢራን አደገኛ መረጃዎችን ሳያቀብል አልቀረም የሚል ጭንቅ ውስጥ መሆኑን የእስራኤል የዜና ገጽ አስነብቧል።
ለኢራን ሲሰልል ነበር በሚል የኢራን ሃገር ውስጥ የደህንነት ቢሮ በቁጥጥር ስር ያዋለው ዶሮን ቦኮብዛ የተባለ የ 29 ዓመት ወጣት ሳይንቲስት በደቡባዊ ሃይፋ የሚገኝ የእስራኤል ኒውክለር ጣቢያ ውስጥ በኬሜካል ኢንጂኒየርነት ለዓመታት ሲያገልግል የቆየ መሆኑ ተገልጿል።
እስራኤል የኢራንን ኒውክለር ጣቢያ ለመምታት በምትዘጋጅበት ሰዓት ይሄ ማጋጠሙ ምናላባትም ኢራን በአጸፋው የእስራኤልን ሚስጥራዊ ኒውክለር ጣቢያዎች የማጥቃት እድሉን ታገኛለች በሚል ስጋት እስራኤል ያቀደችው ጥቃት እንድትተው አሊያም እንድታዘገይ ሊያደርግ ይችላል ተብሏል።
በዚህ ልክ ኒውክለር ጣቢያ ድረስ የኢራን የስለላ እጅ መግባቱ ግን ለሞሳድ ትልቅ ውድቀት መሆኑን የእስራኤል ጋዜጦች እየገልጹ ይገኛሉ።
