የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
4 770
مشترکین
-23224 ساعت
-1 7917 روز
-3 26430 روز
آرشیو پست ها
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
ነሐሴ 20 ቀን 2014 ዓ.ም
አሸባሪው ህወሃት ጦርነት በከፈተበት ግንባር ናፍታ እና ቤንዚን ሊያቀብል የነበረ አይሱዙ ተሽከርካሪ በቁጥጥር ስር ዋለ።
መነሻውን ከሰመራ ያደረገ ኮድ 3 ታርጋ ቁጥር A47679 አይሱዙ ተሽከርካሪ መዳረሻውን ወደ አሸባሪው ህወሓት ቡድን በማድረግ 3000 /ሦስት ሺህ/ ሊትር ናፍጣ እና 2000 /ሁለት ሺህ/ ቤንዚል ካልዋን ላይ ሲደርስ በቁጥጥር ስር ውሏል።
በግዳጅ ቀጠናው የሚገኙት መቶ አለቃ መንግስተአብ አበራ እንደተናገሩት በአሁኑ ሰዓት አሸባሪው ህወሓት በሀገራችን ላይ ጦርነት ቢከፍትም በጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን አፀፋዊ ምላሽ እየተሠጠ ባለበት ወቅት በህገ ወጥ መንገድ ለጠላት ሊደርስ የነበረን ነዳጅ መቆጣጠር ችለናል ብለዋል።
መቶ አለቃ መንግስተአብ አበራ አክለውም በቀጣይም ለአሸባሪው የትህነግ ቡድን በህገወጥ መንገድ ሊደርስ የሚችል ማንኛውም ነገር ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በጋራ እንደሚሠሩ ተናግረዋል።
ምንላርግህ ሞሴ
ፎቶ ምንላርግህ ሞሴ
ለተጨማሪ መረጃዎች ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ።
ቴሌግራም 👇
https://t.me/+E_EOiTY9eq85ODI0
ፌስቡክ 👇
✍️ ቤተሰብ ይሁኑ!
👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/CommandoAndAirborneHeadQurter
#Germany
• ጀርመን ከWFP መጋዘን ህወሓት የፈፀመውን በኃይል የነዳጅ ክምችት የመውሰድ ድርጊት " አፀያፊ " ስትል አወገዘች።
የጀርመን መንግስት በሰሜን ኢትዮጵያ ለ5 ወራት የዘለቀው የተኩስ አቁም ስምምነት መጣሱና ጦርነቱ እንደገና መጀመሩ በእጅጉ እንዳሳዘነው ገልጿል።
በግጭቱ ውስጥ ያሉ ሁሉም አካላት አሁኑኑ መሳሪያቸውን አስቀምጠው ወደ ተኩስ አቁም በፍጥነት መመለስ አለባቸው ብሏል።
" ግጭቱ ሊፈታ የሚችለው በድርድር ጠረጴዛ ዙሪያ ብቻ ነው " ያለው የጀርመን መንግስት የአፍሪካ ህብረት የማሸማገል ጥረቶችን አሁንም መደገፉን እንደሚቀጥል እና ይህም ስራ አሁን መጠናከር እንዳለበት ገልጿል።
የትግራይ፣ የአማራ እና የአፋር ህዝብ በቂ ስቃይ ደርሶበታል ያለው የጀርመን መንግስት ሴቶች እና ህጻናትን ጨምሮ በጣም ብዙ ንፁሃን ዜጎች ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ለከባድ የሰብአዊ መብት ጥሰት ሰለባ ሆነዋል ብሏል።
ግጭቱ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ፣ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ቤታቸውን ለቀው እንዲወጡ ተገደዋል ፤ ሚሊዮኖችም በረሃብ እየተሰቃዩ ነው ሲል የጀመን መንግስት ገልጿል።
ከዚህም ዳራ አንፃር ህወሓት (TPLF) አስቸኳይ ህይወት አድን ሰብአዊ እርዳታን ለማከፋፈል የሚውልን ነዳጅ መውሰዱ " አስጸያፊ ነው " ስትል አውግዛለች።
በኢትዮጵያ 7 ትሪሊዮን ኪዪቢክ ጫማ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መኖሩ ተረጋገጠ
ዓለም አቀፍ ጥናቱ የኢትዮጵያን የመደራደር አቅም ያሳድገዋል ተብሏ
በኢትዮጵያ በኦጋዴን አካባቢ 7 ትሪሊዮን ኪዪቢክ ጫማ (200 ቢሊየን ሜትር ኪዩብ ደገማ) የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት መኖሩ የሚያረጋግጥ ጥናት ይፋ ተደረግ
የማዕድን ሚንስቴር ከአሜሪካው ኔዘርላንድ ስዌል ኤንድ አሶሲሼየትስ ኢንክ ኩባንያ (ኤልሲኤአይ) የጥናት ተቋም ጋር በመተባበር ያስጠናውን የነዳጅ ክምችት ጥናት ይፋ አድርጓል።
የአውሮፓ ህብረት የሩሲያ የተፈጥሮ ጋዝን ለመተካት አፍሪካን እያማተረ ነው
በዚህ መርሀ ግብር ላይ እንደተጠቀሰው ኢትዮጵያ በኦጋዴን ተፋሰስ 7 ትሪሊየን ጫማ ጥልቀት ያለው የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት እንዳላት በጥናቱ ተረጋግጧል ተብሏል።
የማዕድን ሚኒስትሩ ታከለ ኡማ ( ኢ/ር) በመድረኩ ላይ እንዳሉት ጥናቱ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ያላትን የመደራደር አቅም ያሳድገዋል ብለዋል።
“ከዚህ ቀደም የነበሩ ኩባንዎች ምን ያህል ክምችት እንዳለን አይነግሩንም ነበር” ያሉት ሚኒስትሩ አሁን የተጠናው ጥናት ግን ለክምችቱ መጠን ዓለም አቀፍ ማረጋገጫ መስጠቱን ገልጸዋል፡፡
ኢትዮጵያ በ2010 ሰኔ ወር ላይ በቀን እስከ 450 በርሜል ድፍድፍ ነዳጅ የማምረት ሙከራ ጀምራ አንደነበረ መገለጹ ይታወሳል።
ሆኖም ግን በህዳር ወር 2011 ዓ.ም ላይ በኦጋዴን አካባቢ በሙከራ ደረጃ ተጀምሮ የነበረው ድፍድፍ ነዳጅ የማውጣት ስራው መቆሙን የማዕድንና ነዳጅ ሚንስቴር ገልጾ ነበር።
ሱዳን ወታደራዊ ሹም ሽር አደረገች
የሀገሪቱ ጦር መሪ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄ/ል መሃመድ ዑስማን አልሁሴን ግን ከስልጣናቸው አልተነሱም
ሱዳን ወታደራዊ ሹም ሽር አደረገች፡፡
ከአሁን ቀደም አዲስ የአየር ኃይል ወታደራዊ አመራሮችን የሾሙት ቡርሃን የምድር ጦርን ጨምሮ በዘመቻ መምሪያ እና በወታደራዊ ሎጂስቲክ መምሪያዎች ሹም ሽር አድርገዋል፡፡
በሹም ሽሩ መሰረትም ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ለአስተዳደር ሌተናል ጄኔራል ሙናዋር ኦስማን ኑቁድ እና ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ለስልጠና ሌተናል ጄኔራል አብዱላህ አልበሽር አህመድ አል-ሳዲቅ የአንደኛ ሌተናል ጄኔራልነት ማዕረግን አግኝተው በጡረታ ከጦሩ እንዲሰናበቱ ተደርጓል፡፡
የምድር ጦር አዛዡ ሌተናል ጄኔራል ኢሳም መሃመድ ሐሰን ከራር እንዲሁም የሌተናል ጄኔራልነት ማዕረግን ያገኙት ሜጀር ጄነራል አህመድ ዑመር ሸናን በተመሳሳይ መልኩ ጡረታ ወጥተዋል፡፡ ሌሎች የሌተናል ጄኔራልነት የማዕረግ እድገቶችና ሹመቶችም ተሰጥተዋል፡፡
በዚህም ሜጀር ጄነራል አብዱል ሃሚድ ኢስማይል ሌተናል ጄኔራል ተብለው በምድር ጦር አዛዥነት ተሾመዋል እንደ ሃገሪቱ ዜና አገልግሎት ዘገባ፡፡
ሜ/ጄ አብዱል ማህሙድ ሃማድ ሁሴን አጃሚ፣ ሜ/ጄ ናስር አል-ዲን አብዱል ቀይዩም አህመድ አሊ እና ሜ/ጄ ሙባረክ ኮቲ ካጁር ክምቶር ደግሞ የጦር ኃይሎች ዋና ኢንስፔክተር ሆነው በቡርሃን ተሾመዋል።
የጦሩ ጠቅላይ አዛዥ ጦሩን በአዲስ መልኩ ለማደራጀት ያስችላሉ ያሏቸውን ሌሎች ሹም ሽሮችንም አድርገዋል፡፡ ሆኖም ቡርሃን የሃገሪቱን ጦር ኃይሎች መሪ ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄ/ል መሃመድ ዑስማን አልሁሴንን ከስልጣናቸው አላነሱም፡፡
ሹም ሽሩ ቡርሃን በወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት የጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ መንግስትን አስወግደው ስልጣን ከያዙበት ካሳለፍነው ወርሃ ጥቅምት ወዲህ የተደረገ ወታደራዊ እርምጃ ነው፡፡ በወቅቱ የሃገሪቱን ጦር በአዲስ ማደራጀታቸውና የተለያዩ ሹመቶችን መስጠታቸው የሚታወስ ነው፡፡
ቡርሃን የሱዳንን ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት በፕሬዝዳንትነት እንደሚመሩ ይታወቃል፡፡
👉 (#ጥብቅ_ምስጢር‼) በጀግናው አየር ኃይላችን የተመታው "አንቶኖቨ" ወታደራዊ አውሮፕላን የማን ነው⁉️
♦ በውስጡ የያዘው "ጉዳይስ" ምን ነበር⁉️ ( ተነቦ ሼር የሚደረግ‼)
ከትናንት በስቲያ። ከምሽቱ አራት ሰዓት ላይ። አሸባሪው ወያኔ ጦርነቱን ለመክፈት ሰዓታት ቀርተውታል። ኢትዮጵያን ለመጠበቅ ለሰከንድ የማያንቀላፉት የንስር ዓይኖቻቸን፣ የሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ ሳተናዎች፣ የሀገሪቱን አየር ክልል በአራቱም ማዕዘኖች እያማተሩ ነው። በተጠቀሰው ሰዓት ድንገት አንድ ሰውና መሳሪያ የሚጭን ወታደራዊ የማመላለሻ አንቶኖቭ አውሮፕላን የአየር ክልላችንን ጥሶ በሑመራ ሰሜናዊ አቅጣጫ በከፍተኛ ፍጥነት እየበረረ ሲገባ ተመለከቱት። ከመነሻው ይታወቅ ነበር። ጉዳዩ የሀገር ሉዓላዊነት ነው። አውሮፕላኑ ወታደራዊ መሳሪያዎችንና ሰዎችን የሚያመላልስ ሲሆን፤ የእናት ኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የጣሰ ስለሆነ መመታት ነበረበት። በቅፅበት ተመታ። በውስጡ የነበሩት "ጉዳዮችም" እንዳልነበረ ሆኑ፤ ብትንትናቸው ወጣ‼
ግና አውሮፕላኑ የማን ነው⁉️--ምንም ጥያቄ አያሻውም። ከትናንት እስከዛሬ ድረስ የኢትዮጵያን ማደግና መበልፀግ የማትመኘው የታሪካዊ ጠላታችን የግብፅ ንብረት መሆኑን መረጃዎች ይጠቁማሉ። አይገርምም። አይደንቅም። የካይሮ መንግሥትና ሌሎች አካላት ትናንትም ከወያኔ ጋር በመሆን አሸባሪውን አልሸባብ በሶማሌ ክልል በኩል አስርገው አስገብተው ሊያውኩን ሞክረዋል። በአራቱም የሀገሪቱ ማዕዘናት ፀረ- ሠላም ኃይሎችን ቀጥረው ሠላማችንን ሊያውኩ ጥረዋል። ሆኖም አልሸባብም ሆነ ፀረ-ሠላም ኃይሎቹ በአንበሳው ጀግናው መከላከያ ሠራዊታችን፣ በልዩ ኃይሎችና በሠላም ወዳዱ
" ሲቪል ዜጎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው። የተዘረፈውን ነዳጅ መልሱ " - ሳማንታ ፓወር
የአሜሪካ ህዝብ ተራድኦ ድርጅት (USAID) አስተዳዳሪ ሳማንታ ፓወር ፤ ህወሓት (TPLF) የዓለም ምግብ ፕሮግራም ለስራ የሚጠቀምበትን 150,000 ጋሎን ነዳጅ መዝረፉን በመግለፅ ድርጊቱን አጥበቀው አውግዘዋል።
በተጨማሪም በእርዳታ ሰራተኞች ላይ እንግልት መድረሱን በመጠቆም ፤ ህወሓት (TPLF) በእርዳታ ሰራተኞች ላይ ያደረሰውን እንግልት ድርጅታቸው አጥብቆ እንደሚያወግዝ ገልፀዋል።
" ኢትዮጵያውያን ሲቪል ዜጎችን ለመመገብ የሚደረገውን ጥረት ማደናቀፍ እጅግ የጭካኔ ተግባር ነው " ያሉት ፓወር ህወሓት (TPLF) የዘረፈውን ነዳጅ እንዲመልስ በድርጅታቸው ስም ጥሪ አቅርበዋል።
ከነዳጅ ዝርፊያ ጋር በተያያዘ አሁንም ዓለም አቀፍ ተቋማት ድርጊቱን እያወገዙ ሲሆን ህወሓት (TPLF) በሰጠው ምላሽ " ከወራት በፊት ለዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) ያበደርኩትን ነዳጅ መልሼ ወስድኩ እንጂ ዘረፋ አልፈጸምኩም " ብሏል።
ነዳጁን ለድርጅቱ ያበደርኩት ከጥቂት ወራት በፊት በነዳጅ እጥረት ምክንያት የምግብ እርዳታ ማከፋፈል ባለመቻሉ ነው ያለው ህወሓት ድርጅቱ ነዳጅ መበደሩንና እንደሚመልስ ግንዛቤ ነበር ሲል ገልጿል፤ " ስምምነታችን በጽሁፍ ተሰንዶ ተቀምጧል " ሲል እየቀረበበት ላለው ክስ ምላሽ ሰጥቷል።
አሸባሪው ህወሓት ቡድን ወደ ትግራይ ክልል ሊያስገባ የነበረው አደገኛ ዕፅ ተያዘ
አሸባሪው ህወሓት ቡድን ወደ ትግራይ ክልል ሊያስገባ የነበረው አደገኛ ዕፅ መያዙን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ አስታወቀ።
አሸባሪው የህወሓት ቡድን ከአዲስ አበባ እስከ ሚሌ ኔትወርክ በመዘርጋት በአፋር ክልል በኩል ወደ ትግራይ ክልል ሊያስገባው የነበረ በርካታ ኩንታል አደገኛ ዕፅ በህብረተሰቡ ጥቆማ እና በፖሊስ ብርቱ ክትትል ነው መያዙ የተጠቀሰው፡፡
ሁለት ተጠርጣሪዎች በሰሌዳ ቁጥር አ.አ ኮድ 3-A40101AA ቶዮታ ዶልፊን ተሽከርካሪ ላይ አደገኛ ዕፁን ጭነው ሲያጓጉዙ በህብረተሰቡ በተሰጠው ጥቆማ መሰረት ከሌሎች የፀጥታና ደህንነት አካላት ጋር በመቀናጀት በቁጥጥር ስር ማዋሉን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጠቅሷል።
ከአደገኛ ዕፁ በተጨማሪ ለእኩይ ዓላማ ማስፈፀሚያ ሊውል የነበረ 2 ሚሊየን 370 ሺህ ብር መያዙንም ገልጿል።
በህወሓት የሽብር ቡድን አባልነት ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉት ሁለቱ ተጠርጣሪዎች በሚጠየቁበት ጊዜ አደገኛ ዕፁን የእርዳታ እህል የጫኑ ተሽከርካሪዎችን በመጠቀም ወደ ትግራይ ክልል ለማስገባት እንደሆነ ተናግረው ዕፁን ለመቀበል የተዘጋጀ ቡድን እንዳለም ጠቁመዋል።
ፖሊስም ይህንን ቡድን በቁጥጥር ስር ለማዋል በክትትል ላይ መሆኑን አስታውቋል።
ይህ የሽብር ቡድን ዕፁን ሊያስተላልፍ የነበረው እንደለመደው የትግራይ ወጣቶችን በዕፅ አደንዝዞ ወደ ጦርነት ለመማገድ እንደነበረ በቁጥጥር ስር የዋሉት ተጠርጣሪዎቹ መናገራቸውን ከፌዴራል ፖሊስ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
በየትኛውም ደረጃ የሚወጠኑ መሰል የወንጀል ተግባራትን ለመቆጣጠር ህብረተሰቡ ከፀጥታ አካላት ጋር ተገቢውን ቅንጅት በማድረግ የዜግነት ድርሻውን እንዲወጣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ባላት ግንኙነት ቱርክን አስጠነቀቀች
አሜሪካ ከሩሲያ ጋር ባላት ግንኙነት ቱርክን አስጠነቀቀች፡፡
አንካራ ከድርጊቷ የማትታቀብ ከሆነ ማዕቀብ ሊጠብቃት እንደሚችል ዋሽንግተን አሳስባለች፡፡
ከሩሲያ ጋር የንግድ ግንኙነቶችን ማድረግ የሚቀጥሉ ከሆነ ማዕቀብ ሊጠብቃቸው እንደሚችል የሚያሳስብ ደብዳቤ ከአሜሪካ ግምጃ ቤት እንደደረሳቸው የቱርክ የንግድና ዘርፍ ማህበራት አስታውቀዋል፡፡
አሜሪካ፤ ሩሲያ እና ቱጃሮች በቱርክ የንግድ ሸሪኮቻቸው በኩል ከተጣለባቸው ማዕቀብ ለመሸሽ እንቅስቃሴዎችን ሊያደርጉ ይችላሉ በሚል ሁኔታዎችን በንቃት እየተከታተለች ነው፡፡
የሩሲያ እና የቱርክ ፕሬዝዳንቶች ምጣኔ ሃብታዊ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ከወር በፊት በሪዞርት ከተማዋ ሶቺ መስማማታቸው ይታወሳል፡፡
ቱርክ ከሩሲያ ጋር ያላት የወጪ ንግድ መጠን ካሳለፍነው ግንቦት ወዲህ በእጥፍ እየጨመረ ነው፡፡ ከሩሲያ የምታስገባው የነዳጅ መጠንም ጨምሯል፡፡ ነዳጁን በሩብል ለመግዛትም በቅርቡ ተስማምታለች፡፡
ይህን ተከትሎ ባሳለፍነው ግንቦት ወደ አንካራ ጎራ ያሉት የአሜሪካ ግምጃቤት ምክትል ገዢ ስለ ሁኔታው አስጠንቅቀው ነበር፤ በማዕቀብ ስር ካሉ የሩሲያ ተቋማት ጋር ግንኙነት ማድረግ ለማዕቀqብ እንደሚዳርግ በማሳሰብ፡፡
ሆኖም፤ ምንም እንኳን የኔቶ አባል ብትሆንም ልክ እንደሌሎች ምዕራባውያን ሁሉ በሩሲያ ላይ ማዕቀብ ለመጣል ያልፈለገችው ቱርክ ከሩሲያም ሆነ ዩክሬን ጋር ገለልተኛ መስላ መታየትን መርጣለች፡፡
ይህም በሩሲያ ነዳጅ ላይ ካላት ጥገኝነት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ፕሬዝዳንት ረሲፕ ጣይብ ኤርዶሃን ተናግረዋል፡፡
"ህወሓት የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘንን መዝረፉ ተቀባይነት የሌለው አሳፋሪ ተግባር ነው"፦ በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር
በኢትዮጵያ የሩሲያ አምባሳደር ኤቭጌኒ ተረክህ፣ ህወሓት መቐለ ከሚገኘውን የዓለም ምግብ ፕሮግራም መጋዘን 12 የነዳጅ ታንከሮችን ከ570 ሺህ ሊትር ነዳጅ ጋር መዝረፉ ተቀባይነት የሌለው አሳፋሪ ተግባር ነው ሲሉ አወገዙ።
በህወሓት የተዘረፈው ነዳጅ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ለሚገኙ ዜጎች በእጅጉ አስፈላጊ እንደሆነ አምባሳደሩ ገልጸዋል።
የተፈጠረው ሁኔታ በተለያዩ ሰው ሠራሽ እና ተፈጥሮአዊ አደጋዎች ችግር ውስጥ የሚገኙ ንፁሃን የትግራይ ተወላጆችን የበለጠ አደጋ ላይ የሚጥል መሆኑን ነው አምባሳደር ኤቭጌኒ ተረክህ ለኢዜአ የገለጹት።
የበለጠ መጥፎው ነገር ደግሞ እነዚሁ ዘረፋውን የፈፀሙ ሰዎች በትግራይ ሕዝብ ላይ ችግር እና መከራ ተፈጠረ ብለው መጮኻቸው አይቀሬ መሆኑ ነው ብለዋል።
ነገር ግን ተወቃሽ የሚያደርጉት ማንን ይሆናል? ሲሉ ጠይቀዋል።
የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በጉዳዩ ላይ የሰጠው ግብረ-መልስን እንዴት እንደገመገሙ ተጠይቀው፣ ማንም ኅሊና ያለው ሰው ይህን መሰል እኩይ ተግባር ይደግፋል ብለው እንደማያምኑ ገልጸዋል።
በእርግጥ አንዳንዶች ድርጊቱን ከመኮንን እንደሚቆጠቡ እረዳለሁ ያሉት አምባሳደሩ፣ ነገር ግን ሁልጊዜ እውነት አሸናፊ እንደምትሆን እና ሁሉም ሰው የተፈጠረውን እና እየተፈጠረ ያለውን ጉዳይ እንደሚገነዘብ ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።
ሩሲያ የጦሯ ብዛት ከ2 ሚሊዮን በላይ እንዲሆን ወሰነች
የሩሲያ ጦር ብዛት 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን እንደነበር ተገልጿል
ሩሲያ የጦሯ ብዛት ከ2 ሚሊዮን በላይ እንዲሆን ወሰነች፡፡
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የብሄራዊ ጦር ብዛት ከ2 ሚሊዮን በላይ እንዲሆን መወሰናቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው ከሆነ ሩሲያ አሁን ላይ አንድ ነጥብ 9 ሚሊዮን ጦር ያላት ሲሆን አሁን ላይ የተለያዩ ስጋቶችን ታሳቢ በማድረግ የ137 ሺህ የጦር አባላትን እንዲጨምር ተወስኗል፡፡
የሩሲያ ጦር አባላት እንዲጨምር የተወሰነውን ውሳኔ ፕሬዝዳንት ፑቲን በፊርማቸው ማጽደቃቸውን ዘገባው ጠቁሟል፡፡
የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶ ከሁለት ወራት በፊት በስፔን መዲና ማድሪድ ባደረገው ጉባኤ ሩሲያ ዋነኛ የአውሮፓ ስጋት መሆኗን መወሰኑ ይታወሳል፡፡
ሩሲያ በበኩሏ ኔቶ ሞስኮን በስጋትነት መፈረጁ ስህተት መሆኑን ጠቅሳ ጉዳዩ አሜሪካ ሩሲያን ከአውሮፓ ለመነጠል የጠነሰሰችው ሴራ ነው ማለቷ ይታወሳል፡፡
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 183ኛው ቀን ላይ የደረሰ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ሀገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን ተመድ ገልጿል፡፡
እንዲሁም ከዘጠኝ ሺህ በላይ የዩክሬን ወታደሮች መገደላቸውን እና 20 በመቶ የዩክሬን ግዛትም በሩሲያ ጦር ቁጥጥር ስራ መውደቁን የኬቭ ባለስልጣናት ከቀናት በፊት መናገራቸው አይዘነጋም፡፡
ፕሬዚዳንት ፑቲን አዲሱን አዋጅ በፊርማቸው አጽድቀዋል
የሩሲያ ጦር ብዛት 1 ነጥብ 9 ሚሊዮን እንደነበር ተገልጿል
ሩሲያ የጦሯ ብዛት ከ2 ሚሊዮን በላይ እንዲሆን ወሰነች፡፡
የሩሲያ ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲን የብሄራዊ ጦር ብዛት ከ2 ሚሊዮን በላይ እንዲሆን መወሰናቸውን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡
እንደዘገባው ከሆነ ሩሲያ አሁን ላይ አንድ ነጥብ 9 ሚሊዮን ጦር ያላት ሲሆን አሁን ላይ የተለያዩ ስጋቶችን ታሳቢ በማድረግ የ137 ሺህ የጦር አባላትን እንዲጨምር ተወስኗል፡፡
የሰሜን አትላንቲክ ቃል ኪዳን ጦር ወይም ኔቶ ከሁለት ወራት በፊት በስፔን መዲና ማድሪድ ባደረገው ጉባኤ ሩሲያ ዋነኛ የአውሮፓ ስጋት መሆኗን መወሰኑ ይታወሳል፡፡
የቃል ኪዳን ጥምር ጦሩ ከዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው የኔቶ አባል እሆናለሁ ማለቷን ተከትሎ በሩሲያ ጦር መደብደቧን ተከትሎ ነው፡፡
ሩሲያ በበኩሏ ኔቶ ሞስኮን በስጋትነት መፈረጁ ስህተት መሆኑን ጠቅሳ ጉዳዩ አሜሪካ ሩሲያን ከአውሮፓ ለመነጠል የጠነሰሰችው ሴራ ነው ማለቷ ይታወሳል፡፡
የሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ከተጀመረ 183ኛው ቀን ላይ የደረሰ ሲሆን ከ10 ሚሊዮን በላይ ዩክሬናዊያን ሀገራቸውን ጥለው መሰደዳቸውን ተመድ ገልጿል፡፡
ዩክሬን ከሩሲያ ጦር እየደረሰባተር ያለውን ወታደራዊ ጥቃት ለመመከት አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት የጦር መሳሪያዎችን በመለገስ ላይ ናቸው፡፡
ህወሃት በትግራይ ህዝብ ስም የገባን የሰብአዊ ድጋፍ ለወታደራዊ አላማ ማዋሉን ቀጥሏል በመቀሌ የህወሃት የሽብር ቡድን የአለም የምግብ ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማከማቻ መጋዘን ውስጥ በነበረ 12 የነዳጅ ታንከርና ውስጡ የነበረውን 570 ሺህ ሊትር ነዳጅ ላይ የፈጸመውን ዝርፊያ መንግስት በፅኑ ያወግዛል። ዘረፋው የተፈጸመው የሽብር ቡድኑ ለዳግም ጥቃት እየተዘጋጀ ባለበት ወቅት ነው።
ለትግራይ ህዝብ እጅግ አንገብጋቢ የሆኑትን የምግብና የግብርና ግብአቶች ለማከፋፈል ወደ ክልሉ በገባው ነዳጅ ላይ ዝርፊያ የፈጸመው የሽብር ቡድኑ፤ ህወሃት በትግራይ ህዝብ የሚነግድ ኢሰብአዊ ቡድን መሆኑን በተጨባጭ የሚያረጋግጥ ብቻ ሳይሆን ግልጽ የጦር ወንጀልና አለምአቀፍ የሰብአዊነት ህግጋቶችንም የጣሰ ድርጊት ነው።
ትናንት በሽብር ቡድኑ የተፈጸመው የሰብአዊ እርዳታ ዝርፊያ በአለም የምግብ ፕሮግራምና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብአዊ እርዳታ ማስተባበሪያ ጉዳዩች ቢሮም ተረጋግጧል። ለትግራይ ህዝብ የገባ የሰብአዊ የነዳጅና የምግብ እርዳታ ላይ ህወሃት ትናንት የፈጸመው ዝርፊያ ዳግም በቆቦና አካባቢው ላይ ለከፈተው ጥቃት ማስፈጸሚያ ሊጠቀምበት እንደሆነም ታውቋል። አለም አቀፎቹ ተቋማት እንዳረጋገጡት የህወሃት የሽብር ቡድን በመቀሌ ከፈጸመው ዝርፊያ ባሻገር ድርጊቱን ለማስቆም የሞከሩ የሰብአዊ እርዳታ ባለሙያዎችንም አስሯል።
እንደሚታወቀው መንግስት ወደ ትግራይ ክልል አስፈላጊው ሰብአዊ ድጋፍ በአግባቡ እንዲደርስ ለማድረግ የተናጠል ተኩስ አቁም ከማድረግ ባሻገር ያልተቋረጠ የሰብአዊ ድጋፍ በየብስም በአየርም እንዲቀርብ ሲያደርግ ቆይቷል።
በተጨማሪም መንግስት ባለፉት ወራት ለግጭቱ ሰላማዊ መፍትሄን ለመስጠት እንዲሁም መተማመንን ለመፍጠር እንዲቻል የሰብአዊ ድጋፍና መሰረታዊ አገልገሎትን ለማስጀመር
የሚያስችሉ ዝግጅቶችን ሲያደርግ መቆየቱ ይታወቃል። ሆኖም መንግስት ለሰላም የወሰዳቸው እርምጃዎች በሙሉ በህወሃት የሽብር ቡድን በኩል ተቀባይነትን አላገኙም።
ከዚህም አልፎ ከቀናት በፊት የህወሃት የሽብር ቡድን አባልና ደጋፊው የአለም የጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር፤ አለም አቀፉ ተቋም ለሁሉም ዜጋ በእኩል ማገልገል አለበት የሚለውን መሰረታዊ መርሁን ወደ ጎን በማለት ትግራይ ውስጥ ሰብአዊ እርዳታን ለማከፋፈል የሚውል ነዳጅ እጥረት አለ በማለት ሃሰተኛ ውንጀላ ሲያቀርብ እንደነበር ይታወቃል።
የትናንትናው የህወሃት የሽብር ቡድን ዝርፊያ ግን ቡድኑ ለሰብአዊ እርዳታ የሚገባን ነዳጅና የምግብ ድጋፍ ለጦርነት አላማ ሲዘርፍና ሲጠቀም የመቆየቱን ሃቅ ለመላው አለም በግልጽ ያሳየ ነው። ከጦርነቱ ጅማሮ አንስቶ ይህንኑ የህወሃት የሽብር ቡድን እርዳታን ለወታደራዊ አላማ የመጠቀም ወንጀል መንግስት ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ በተደጋጋሚ ሲያሳስብና ሲያስጠነቅቅ ቆይቷል። መንግስት ሲገልጽ የቆየውንና የህወሃትን ሰብአዊ እርዳታን ለጦርነት የማዋል ወንጀል ገለልተኛ አለም አቀፍ ምርመራዎችም በተጨባጭ ያረጋገጡት ሃቅ ነው። ሆኖም መላው ኢትዮጵያውያንን ባሳዘነ መልኩ ይህ የመንግስት ማሳሰቢያ በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ሰሚ ሳያገኝ፤ ተገቢ የሆነ የተጠያቂነት እርምጃም በሽብር ቡድኑ ላይ ሳይወሰድ ቆይቷል።
ትናንት በሽብር ቡድኑ የተፈጸመው ለትግራይ ህዝብ የገባ የሰብአዊ እርዳታ ዝርፊያ ለመላው አለም ግልፅ በሆነ መልኩ የቡድኑን ማንነት ያሳየ ይሁን እንጂ ከሽብር ቡድኑ ታሪክ መረዳት እንደሚቻለው ህወሃት ከ1970ዎቹ ጊዜ ጀምሮ ለትግራይ ህዝብ ተብሎ የሚገባን ሰብአዊ እርዳታን መዝረፍ የለመደ ከሰብአዊነት ያፈነገጠ ወንጀለኛ ቡድን ነው።
ስለዚህ መንግስት
1) የተዘረፈው ነዳጅ እንዲመለስ
2) የሰብአዊ እርዳታ አቅራቢ ድርጅቶች የቀረበላቸውን ማስረጃ ከግምት በማስገባት
በሽብር ቡድኑ ላይ ግልጽ የሆነ ተጠያቂነትን እንዲያሰፍኑ
3) አለምአቀፉ ማህበረሰብ የህወሃት የሽብር ቡድን በፈጸማቸው ወንጀሎች ተጠያቂ
እንዲያደርግ እንዲሁም ወደ ትግራይ የሚገባው ሰብአዊ እርዳታ ለታለመለት አላማ መዋሉንና ለትግራይ ህዝብ እየደረሰ መሆኑን ማስተማመኛ እንዲሰጥ ይጠይቃል።
በኢፌዴሪ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
መንግስት አሁንም ለሰላማዊ አማራጭ በሩ ክፍት መሆኑንና የህወሃት የሽብር ቡድንም ዳግም እየፈጸመ የሚገኘውን ጥቃት አቁሞ ወደ ሰላማዊ ምክክር እንዲመጣ ያሳስባል። ሆኖም ህወሃት ይህንን የመንግስትን የሰላም ጥሪ የማይቀበል ከሆነ መንግስት ሃገራዊ ሉአላዊነትንና የዜጎችን ደህንነት ለማረጋገጥ አሰፈላጊውን እርምጃ ሁሉ ይወስዳል። ሽብርተኝነት በምእራቡም ሆነ በተቀረው አለም ተቀባይነት እንደሌለው ሁሉ በኢትዮጵያም ፍጹም ቦታ የለውም!
ነሃሴ 19 ቀን 2014 አዲስ አበባ የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
ነሐሴ 19 ቀን 2014 ዓ.ም
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ በየትኛውም የማህበራዊ ሚዲያ ፕላት ፎርም አካውንት የሌላቸው መሆኑን እንገልፃለን።
በስማቸውና የፕሮፋይል ፎቷቸውን በመጠቀም የተከፈቱ የማህበራዊ ሚዲያ ገፆች ፊልድ ማርሻሉን የማይወክል መሆኑን እየገለፅን በስማቸውና ፎቶግራፋቸውን በመጠቀም የፌስቡክ እና ሌሎች የማህበራዊ ሚዲያ አካውንት ከፍታችሁ የምትጠቀሙ አካላት ከድርጊታችሁ እንድትቆጠቡ እናሳስባለን።
ኢትዮጵያ ኢንተርኔትን በዝቅተኛ ዋጋ በማቅረብ ከሰሃራ በታች ካሉ የአፍሪካ ሀገራት 10ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጣለች
በብሪታኒያው “Cable.co.uk” የተሰራ ጥናት 233 ሀገራት ያለውን 5,292 የሞባይል ዳታ ጥቅል ዋጋ መረጃ በመተንተን በፈረንጆቹ በ2022 በጣም ርካሹን እና በጣም ውድ የሆነውን የሞባይል ዳታ የሚያቀርቡ ሀገራት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
ሪፖርቱ በሁሉም ሀገራት የ1 ጊጋ ባይት (1GB) የሞባይል ዳታ ዋጋን ተመልክቷል። ከሪፖርቱ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በአጠቃላይ ለሞባይል ዳታ ዋጋ በውድነቱ ከአለም ሁለተኛ ደረጃ ላይ ይገኛሉ።
ሆኖም 5 ከሰሃራ በታች ያሉ ሀገራት ኢንተርኔትን በርካሽ ዋጋ ከሚያቅርቡ 50 የዓለም ሀገራ ውስጥ መካተት መቻላቸው ጥናቱ ይጠቁማል።
የኢንትርኔት ዳታን በርካሽ ዋጋ የሚያቀርቡ 5 ከሰሃራ በታች ያሉ ሀገራት በቅደም ተከተል፦
🇬🇭 ጋና 1 ጊጋ ባይት በ0.61 ዶላር
🇸🇴 ሶማሊያ 1 ጊጋ ባይት በ0.63 ዶላር
🇳🇬 ናይጄሪያ 1 ጊጋ ባይት በ0.71 ዶላር
🇹🇿 ታንዛኒያ 1 ጊጋ ባይት በ0.71 ዶላር
🇸🇩 ሱዳን 1 ጊጋ ባይት በ0.75 ዶላር
.
.
.
🇪🇹 ኢትዮጵያ በዝርዝሩ ውስጥ የተካተተች ሲሆን፤ ደረጃዋም ከሰሃራ በታች ካሉ ሀገራት መካከል ኢንተርኔትን በዝቅተኛ ዋጋ በማቅረብ 10ኛ ከዓለም ደግሞ 73ኛ ላይ ተቀምጣለች።
በጥናቱ መሰረት በኢትዮጵያ የ 1 ጊጋ ባይት የኢትነርኔት ዳታ ዋጋ 1 የአሜሪካ ዶላር ወይም 52 ብር ገደማ እንደሆነ ተመላክቷል።
እስራኤል 1 ጊጋ ባይት ኢንትርኔት በ0.04 ዶላር በማቅረብ በርካሽ ዋጋ ቀዳሚ ስትሆን በደቡብ አትላንቲክ ባር ላይ የምትገኘው ሴንት ሄሊና ደሴት ደግሞ 1 ጊጋ ባይት ኢንተርኔት በ 41.06 ዶላር በማስከፈል ውዷ ሀገር ሆናለች። (AlAin)
