fa
Feedback
የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️

رفتن به کانال در Telegram

Addis abeba Ethiopia

نمایش بیشتر
4 889
مشترکین
-25624 ساعت
-1 8217 روز
-3 02830 روز
آرشیو پست ها
የክልል ልዩ ኃይልን መልሰን እናደራጀው እንጂ  እንበትነው አላልንም - ጄነራል አበባው ታደሰ የክልል ልዩ ኃይልን መልሶ የማደራጀት ተግባር አሁን የተጀመረ ተግባር አይደለም ሲለ የጦር ሃይሎች ምክትል ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ ገለፁ፡፡ ጄነራል አበባው ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጡት ማብራሪያ፥  "የልዩ ኃይል አደረጃጀቶችን መልሶ የማደራጀት ተግባር አሁን የተጀመረ ተግባር አይደለም፤ ለረጅም ጊዜም ጥናት የተደረገበት ነው" ብለዋል፡፡ ጥናቱ የክልሎች ልዩ ሃይሎች ጥንካሬ ምንድነው ብሎ የተመለከተ ሲሆን፥ የክልሎች ልዩ ሃይሎች   ክልላቸውን መጠበቃቸው፣ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር ህይወታቸውን አሳልፈው መስጠታቸውና መሞታቸው፤ እንዲሁም መቁሰላቸውን በጥንካሬ ተመልክቷል ነው ያሉት። ነገር ግን የልዩ ኃይል አወቃቀሩ ጉድለት እንደነበረው እና ህጋዊም እንዳልነበረም አመልክተዋል። ከሀገሪቱ ህገመንግስት አንፃር ሲታይ አወቃቀራቸው ህጋዊ አይደለም፤ ህገመንግስቱም እውቅና አይሰጣቸውም ሲሉ ጄነራል አበባው አስረድተዋል። ይህ ልዩ ሃይል አገነባቡ ብሄር ተኮር መሆኑን በማንሳትም፥ ይህም የህዝቦችን አብሮ የመኖር እሴት የሚሸረሽር መሆኑ ጉድለቱ ነው ብለዋል። የሀገሪቱን የፖለቲካ መፍቻ መንገድ አበላሽቷል ያሉት ጄነራል አበባው፥ "በምን አበላሸ ለሚለው በእኛ ህገ መንግስት ፖለቲካ እና ጉልበት አብሮ አይሄድም፤ ለዚህም ፖለቲከኛው በሃሳብ ማሸነፍ ሲያቅተው ሌላ በትር አለው ማለት ነው፤ የታጠቀውን ልዩ ሃይል ያነሳል" ሲሉ ነው ያስረዱት። "ሌላው ልዩ ኃይል ያለበት እጥረት ለሀገር የሚሞተውን ሃይል መገዳደር መቻሉ ነው፤ ተገዳዳሪ ሃይል ተፈጠረ" በማለት ለዚህም እንደምሳሌ ለሁለት ዓመት የቆየውን የትግራይ ጦርነት አንስተዋል፡፡ በጥናቱ ይህ  የክልሎች ልዩ ሃይል ትክክል አይደለም ከተባለ አራት አመት እንደሆነው ነው ያመለከቱት። "በዚህም ይህንን ሃይል መልሰን እናደራጀው የሚል ውሳኔ ነው  እንጂ የተወሰነው ይበተን፤ ትጥቁን እናስፈታው አልተባለም" ብለዋል። የሚደራጅበትም መንገድ መከላከያ መግባት ያለበት ወደ መከላከያ፣ ፌደራል ፖሊስ የሚገባው ወደ ፌደራል እንዲገባ እና መደበኛ ፖሊስ መሆን የሚፈልገውም መደበኛ ፖሊስ እንዲሆን ነው የተቀመጠው ሲሉ አብራርተዋል። ይህም ክብሩን፣ ሞራሉን እና ጥቅሙን  በማይነካ መልኩ እንደሚፈፀም የተያዘው መርሃ ግብር ማስቀመጡን ጠቁመዋል። "ይህም ምንም ክፋት የለውም፤ ህግ የማስያዝ ነው፤ ጊዜ የሰጠነውም ሌላ ችግር ስለነበረ ነው" ብለዋል፡፡ ሁሉም ክልሎችን ባሳተፈ መልኩ ጥናቱ ላይ ለረጅም ጊዜ ምክክር ተደርጎ የተወሰነ መሆኑንም አንስተዋል፡፡ ይህንን ጥናት ሊያስፈፅም የሚችል ብሄራዊ ኮሚቴ መቋቋም አለበት ተብሎ መቋቋሙን በማከልም ይህም የተደረገው አፈፃፀም ላይ ጉድለት እንዳይኖር በማሰብ መሆኑን ገልፀዋል።

ጄነራሉ ምን አሉ ? የሀገር መከላከያ ሰራዊት ምክትል ጠ/ኢታማዦር ሹም ጄነራል አበባው ታደሰ ለብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣቢያ እና ለመከላከያ ሰራዊት ቴሌቪዥን ፕሮግራም ቃለመጠይቅ ሰጥተዋል። ይኸው ቃለመጠይቃቸው ዛሬ ለህዝብ ተሰራጭቷል። ጄነራሉ ምን አሉ ? በተለይም ስለ ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ጉዳይ ምን ሃሳቦችን አንስተው ተናገሩ ? ጄነራል አበባው ታደሰ ፦ - መላ የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲያውቅልን የምንፈልገው በሀገሪቱ የፀጥታ ኃይል እንዲገነባ ህገመንግስቱ የሚፈቅደው #መከላከያ_ሰራዊትና #ፌዴራል_ፖሊስን ነው። - በየክልሉ ያለው ልዩ ኃይል በሳይዙ ልክ አለው ፤ በሌላ አነጋገር ሀገር በሚመስል ደረጃ 14 እና 15 ሬንጀር አለው ይሄ ፈፅሞ አይቻልም። - አሁን ያለው የክልል ልዩ ኃይልን መልሶ የማደራጀት ስራ ዛሬ የተጀመረ / በሞራል የተገባበት ሳይሆን ከዚህ ቀደም ለረጅም ጊዜ ጥናት ተደርጎበት ነው። - የክልል ልዩ ኃይሎች ፦ የክልልን ፀጥታን ይጠብቁ ነበር ፣ ከእኛ (ከመከላከያ) ጋር ሆነው ይሞቱ ነበር ህይወታቸውን አሳልፈዋል ፣ ቆስለዋል ደምተዋል። ይሄ ኃይል ይሄን የመሰለ ትልቅ ኳሊቲ ነበረው። - ከህገመንግስት አንፃር ስናየው እነዚህ ኃይሎች ህጋዊ አይደሉም ህገመንግስቱ እውቅና አይሰጣቸውም። ለክልል ኃይል የሚሰጠው መደበኛ ፖሊስን ብቻ ነው። ህገመንግስቱ የታጠቀ ኃይል የሚያውቀው አንደኛ መከላከያ፣ ሁለተኛ ፌዴራል ፖሊስ፣ ሶስተኛ መደበኛ ፖሊስ ነው ከዚህ ውጭ ህገመንግስቱ አይልም። - የኃይል አገነባቡ (የልዩ ኃይል መዋቅር) ብሔር ተኮር ነው ፤ ለኦሮሞ ህዝብ እሞታለሁ ብሎ ቃል ይገባል አማራውስ ? ጉዳዩ አይደለም ማለት ነው በግልፅ አማርኛ ፤ አማራው ደግሞ ይመጣና ለአማራ ህዝብ እሞታለሁ ይላል ኦሮሞውስ ? ጉዳዩ አይደለም ። ብሄር ተኮር ስለሆነ ሀገር አቀፍ የሆነውን አብሮነት የመኖር ፤ የህዝቦችን አንድነት ይሸረሽረዋል። - የክልል ልዩ ኃይል መልሶ ማደራጀት ፕሮግራም ወደ መከላከያ ሰራዊት ማስገባት፣ ወደ ፌዴራል ፖሊስ ማስገባት፣ ወደ መደበኛ ፖሊስ ማስገባት ነው። በማን በራሱ ምርጫ፣ በምን ? ክብሩን ሞራሉን ፣ ጥቅሙን በማይነካ ሁኔታ። - አፈፃፀሙ በተመለከተ ሁሉንም እኩል እደራጀዋለን ፣ በጥንቃቄም ይሰራል። - አንደኛውን ክልል ኃይል እንዲኖረው ሌላውን ክልል ኃይል እንዳይኖረው አናድረግም። ይሄ ኢትዮጵያ ውስጥ አይታሰብም። - የታጠቁ ኃይሎች ትጥቅ መፍታት አለባቸው ለምሳሌ የትግራይ የትግራይ ክልል እንደማንኛውም ክልል መደበኛ ፖሊስ ብቻ ነው የሚኖረው ፣ የታጠቀ ልዩ ኃይል የሚባል በፍፁም አይኖረውም። - በአንዳንድ የአማራ ክልል አካባቢና ዩኒቶች ካልሆነ በስተቀር አማራ ልዩ ኃይል የሚባለው በአብዛኛው ተቀብሎታል ፤ ይሄ በኮሚኒኬሽን ያለ ችግር ነው ይሄን የኮሚኒኬሽን ችግር እየፈታን ነው ያለነው። አፈፃፀሙ ላይ የታየው ጉድለት ይሄ ነው እንዲህ አይነት ነገር ሊኖር እንደሚችል እንጠብቃለን አስበንም ነው የገባነው። ከዛ  ውጭ ባወጣነው ፕሮግራም መሰረት ይሄን ኃይል ወደምንለው ፕሮግራም እናስገባዋለን ሁሉንም እኩል አድርገን። ያንብቡ 👇 https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-04-07

በጉልበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣን እይዛለሁ ማለት የማይታሰብ ነው:: ፖለቲከኞች በስራችን አትግቡ፤ እኛም አንገባም:: ኢትዮጵያ አንድ የመከላከያ ሠራዊት ብቻ እንዲኖራት የምናደርገውን የሪፎርም ሥራ እ
በጉልበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣን እይዛለሁ ማለት የማይታሰብ ነው:: ፖለቲከኞች በስራችን አትግቡ፤ እኛም አንገባም:: ኢትዮጵያ አንድ የመከላከያ ሠራዊት ብቻ እንዲኖራት የምናደርገውን የሪፎርም ሥራ እንቀጥላለን:: ኢትዮጵያ ውስጥ ህዝብ የመረጠው ብቻ እንድ መንግሥት ይኖራል፤ ከዚህ ውጪ በጉልበት ኢትዮጵያ ውስጥ ሥልጣን እይዛለሁ ማለት የማይታሰብ ነው:: የጦር ኃይሎች ም/ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሰ (The Man)

በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት የተሰጠ መግለጫ፦ መንግሥት የሀገሪቱን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መጠበቅ የሚያስችል አንድ ጠንካራ የተማከለ ሠራዊት ለመገንባት አቅጣጫ አስቀምጧል። በዚህ መሠረት የየክልሉን ልዩ ኃይሎች ወደ ተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች እንዲገቡ የሚያስችላቸውን ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ ጀምሯል። በሁሉም ክልሎች የሚገኙ የልዩ ኃይል አባላት እንደ ምርጫቸውና እንደ ፍላጎታቸው በመከላከያ፣ በፌደራል ፖሊስ ወይም በክልል ፖሊስ አባልነት መካተት ይችላሉ። በዚህ ሐሳብ ላይም ከልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ጋር ከመግባባት ላይ ተደርሷል። ቀደም ብሎም በሁሉም ክልል አመራሮች ጥናት ተደርጎበት፣ በተገኘው ውጤትም ያለምንም ልዩነት ውሳኔው ስምምነት ተደርሶበታል ። ይህ ተግባር እንዲፈፀም መላ ህዝባችንም ሲጠይቅ ቆይቷል። ይሄንን ተከትሎም ተግባራዊ እንቅስቃሴ ተጀምሯል። የክልል ልዩ ኃይልን በተለያዩ የጸጥታ መዋቅሮች የማካተት ውሳኔና የተግባር እንቅስቃሴ በጥናት ላይ ተመሥርቶ የሚከናወን ነው። ይህ አካሄድ የኢኮኖሚ ዐቅማችንን በማሰባሰብ የሠራዊታችንን የሥልጠና፣ የትጥቅ እና የኑሮ ሁኔታ ለማሻሻል ከፍተኛ ፋይዳ አለው። ይሄንን በመረዳትም በሁሉም ክልሎች ሂደቱ በመግባባትና በውይይት እየተከናወነ ይገኛል። ሆኖም በአማራ ክልል በሚገኙ የተወሰኑ የልዩ ኃይል ክፍሎች ውስጥ፤ በአንድ በኩል የመልሶ ማደራጀት ሥራውንና ዓላማውን በአግባቡ ባለመረዳት፤ በሌላ በኩል የጥፋት አጀንዳ አራጋቢዎች ሆን ብለው በሚነዙት የሐሰት ወሬ በመጠለፍ ሂደቱን የሚያውኩ ተግባራት ታይተዋል። ከሚነዙት የሐሰት አጀንዳዎች መካከል፤ የመልሶ ማደራጀቱ መርሐ ግብር በአማራ ክልል ብቻ እየተካሄደ ነው፤ ሕወሐት ትጥቅ ሳይፈታ እንዴት የክልሉ ልዩ ኃይል ትጥቅ ይፈታል የሚሉትና ሌሎችም ይገኙበታል። እነዚህ አጀንዳዎች ሂደቱን ለማደናቀፍ በሚፈልጉ ኃይሎች እየተናፈሱ ይገኛሉ። የክልል ልዩ ኃይል አባላትን ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ፕሮግራም በመላ ሀገሪቱ የሚተገበር ነው። ሥራውም በሁሉም ክልሎች በተመሳሳይ ጊዜ እየተካሄደ የሚገኝ ነው። ሂደቱንም መንግሥት በጥናት፣ በዕቅድ እና በጥንቃቄ እየመራው ይገኛል። ወደ ሌሎች የጸጥታ መዋቅሮች የማስገባት ተግባር በሚፈጸምበት ጊዜ።፣ በክልሎች አስተማማኝ ሰላምና ጸጥታን ለማረጋገጥ የሀገር መከላከያ ሠራዊት በሁሉም ቦታዎች ሥምሪት ወስዷል። በሌላ በኩል ሕወሐት በፕሪቶሪያው ስምምነት መሠረት ሙሉ በሙሉ ትጥቅ እንዲፈታ እየተደረገ መሆኑ ሊታወቅ ይገባል። የሕወሐት ትጥቅ የመፍታት ሂደት በተፈረመው ስምምነት መሠረት ያለማወላወል የሚፈጸም እንጂ ከሌላ ሀገራዊ ዕቅድ ጋር የሚቀናጅም የሚጣረስም አይደለም። የሂደቱ ዋና ዓላማ የትኛውንም ልዩ ኃይል ትጥቅ ማስፈታት አይደለም። ልዩ ኃይሉ ትጥቁን ይዞ እና የተሻለ ዐቅም ተፈጥሮለት በምርጫው መሠረት የክልል ፖሊስን፣ የፌደራል ፖሊስን ወይም የሀገር መከላከያ ሠራዊትን እንዲቀላቀል ማድረግ ነው። በዚህ ሂደት መካተት የማይፈልግ ማንኛውም የልዩ ኃይል አባል ካለ መብቱ ተጠብቆ ወደ መደበኛ የሲቪል ሕይወት እንዲገባ መንግሥት አስፈላጊውን የማቋቋም ሥራዎች ይሠራል። እንዲቋቋምም ድጋፍ እንደሚያደርግ ያስታውቃል። የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና የማደራጀቱ ሥራ መንግሥት ለዘላቂ የሀገር ጥቅምና ደህንነት የወሰነው ውሳኔ በመሆኑ ኃላፊነቱንም በከፍተኛ ጥንቃቄ ይወጣዋል። ስለዚህ በተለያዩ የጥፋት አጀንዳ አራጋቢዎች ከሚሠራጩ አሳሳች መረጃዎች በመራቅ መላው ሕዝብ እንዲሁም የክልል ልዩ ኃይል አመራሮችና አባላት ለመርሐ ግብሩ ስኬት እንዲረባረቡ መንግሥት ያሳስባል። መጋቢት 28 2015 ዓ/ም አዲስ አበባ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት

" እኛ እንዲህ ዓይነት ዘረፋ ይኖራል ብለንም አስበን አናውቅም " - የዘረፋው መርማሪ ጠቅላላ ዘረፋውን ለመፈጸም የወሰደው 2 ሰዓት ከ13 ደቂቃ ነው። ዘረፋው በተመሳሳይ ሰዓት፣ በ28 አገራት ውስጥ ነው የተፈፀመው። ነገሩን በአጭሩ ለማስቀመጥ ተራ ግለሰቦች ወደ ባንክ ኤቲኤም ማሽን ሄደው ገንዘብ ያወጡበት ዘረፋ ነው። ይህ እንዴት ሆነ ? የሚለውን እንመልከት። በሕንድ የተወሰኑ ሰዎች ለአስተኔ ገጸባሕሪ (extra role) ፊልም ቀረጻ ተመለመሉ። ደስም አላቸው። የተሰጣቸው ሚና ከኤቲኤም ማሽን ብር ማውጣት ነው። ሕንድ ሀገር ማሃራሽትራ የሚገኙ ምልምል ተዋናዮች ድርጊቱን ሲፈጽሙ ለፊልም ቀረጻ መስሏቸዋል። የታላቁ የገንዘብ ርቆት አካል እንደተደረጉ በፍጹም አያውቁም። ይህ የሆነው በሐምሌ 2018 ሰንበት ነበር። ኮስሞስ ይባላል የተዘረፈው ባንክ። ጭር ባለው የሰንበት ዕለት ድንገት ዋናው የባንኩ መሥሪያ ቤት ያሉ ሠራተኞች መልዕክት ደረሳቸው። መልዕክቱ የሚመጣው ከአሜሪካ የቪዛ ካርድ ኩባንያ ነበር። ቪዛ ኩባንያ ለኮስሞስ ባንክ ሰዎች በቀጣይ ደቂቃዎች በርካታ የገንዘብ ጥያቄዎች ሊቀርቡላችሁ ይችላል ሲሉ አስጠነቀቁ።  ያልተለመዱ ነገሮች በኤቲኤም አካባቢ እየታዩ እንደሆነ አብራሩ። ግን የኮስሞስ ባንክ ሰዎች ምንድነው የምታወሩት በሚል ቸል አሉት ማስጠንቀቂያውን ነገሩ ሊገባቸው አልቻለም። ምክንያቱም እነርሱ ሲስተም ላይ የሚታይ ምንም የተለየ ነገር የለም። ከግማሽ ሰዓት በኋላ ቪዛ ኩባንያ በድጋሚ ወደ ኮስሞስ ደወለ። " እኔ ጋ የሚታዩ ምልክቶች ጤናማ አይመስሉም፤ ለማንኛውም ሁሉምን ኤቲኤም ማሽኖቻችሁን ለጊዜው ከጥቅም ውጭ አድርጉ " አላቸው። ይህ ለኮስሞስ ባንክ ብዙ ዋጋ የሚያስከፍል ውሳኔ ቢሆንም ምክሩን ተቀብለው ኤቲኤም ማሽኖቻቸውን ዘጉ። እንዲያም ሆኖ ዘግይተዋል። ኮስሞስ ባንክ በዚያች ሁለት ሰዓት ብቻ 14 ሚሊዮን ዶላር ተዘርፈው ነበር። ይህን ዘረፋ ማን አቀነባበረው ? ይህ ዘረፋ በ28 አገሮች ውስጥ በሚገኙ ኤቲኤም ማሽኖች ላይ በተመሳሳይ ሰዓት የተፈጸመ ነው። - ሩሲያ፣ - አሜሪካ፣ - ካናዳ፣ - ዩናይትድ ኪንግደም፣ - ዩናይትድ አረብ ኢምሬትስ ይገኙበታል። ሂደቱ በሰሜን ኮሪያ ጠላፊዎች መመራቱ እንደተደረሰበት ተነግሯል። የዝርፊያው አቀናባሪዎች ላይ ከመደረሱ በፊት የባንኩ ሰዎች ለምን በርካታ ሰዎች #በተመሳሳይ ሰዓት ወደ ኤቲኤም ማሽን ሄደው ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደሚወስዱ ግራ ገብቷቸው ነበር። የዘረፋው መርማሪ፣ “እኛ እንዲህ ዓይነት ዘረፋ ይኖራል ብለንም አስበን አናውቅም” ይላሉ። የደኅንነት ካሜራ (ሲሲቲቪ) ምስሎችን በመጠቀም የሕንድ መርማሪዎች ለጊዜው 18 ሰዎችን በቁጥጥር ሥር ማዋል ቻሉ። እነዚህ ሰዎች ተራ ሰዎች ናቸው። ሾፌሮች፣ የቡና ቤት አስተናጋጆች፣ ጫማ ጠራጊዎች ይገኙበታል። እነርሱ ለፊልም ቀረጻ መመልመላቸውን እንጂ ማን እየተጠቀመባቸውን እንደነሆ አያውቁም ነበር። በመጨረሻ ከዚህ ጥንቅቅ ካለ ዘረፋ ጀርባ ያለው ‘አልአዛር’ የተሰኘው የሰሜን ኮሪያ ጠላፊዎች ቡድን እንደሆነ ተደረሰበት። እንዴት ግን ቡድኑ በ28 አገራት ዘራፊ ሊያሰማራ ቻለ ? ዘራፊና አዘራፊን አገናኝ ደላላ ፦ " አልአዛር " በሚል የሚጠራው የዘራፊዎች ቡድን የሰሜን ኮሪያ የወታደራዊ ደኅንነት መሥሪያ ቤት የሚመራው ነው ይባላል። " አልአዛር " የሚለውን ስም ያገኘውም ከመጽሐፍ ቅዱስ ሞቶ ከተነሳው አልአዛር ነው። የእነርሱ የኮምፒውተር ቫይረሶች አንዴ ከገቡ ሁሉን ነገር ይገድላሉ። ኮምፒውተር ሲስተሙን መልሰው መቀስቀስ የሚችሉት እነርሱ ብቻ ናቸው። ከእዚሁ ተግባራቸው ጋር ተያይዞ ነው አልአዛር የሚለው ስያሜ የተሰጣቸው። ከዚህ ቀደም፦ - ሆሊውድን፣ - ሶኒ ፒክቸርስን እና ሌሎችንም ግዙፍ መሥሪያ ቤቶች መረጃ ዘርፈዋል። ከባንግላዴሽ ባንክ አንድ ቢሊዮን ዶላር ለመዝረፍ ሞክረዋል። ሰሜን ኮሪያ ይህ " አልአዛር " የተሰኘው ቡድን በአገሬ ስለመኖሩ አላውቅም ስትል ታስተባብላለች። ቡድኑ (አልአዛር) ኮስሞስ ባንክ ላይ ለፈጸመው ዘረፋ የተጠቀመው " ጃክፖት " የሚባለውን ስልት ነው። ይህ ስም የተሰጠው ልክ እንደ መቆመሪያ ማሽን ኤቲኤም ገንዘብ እንዲተፋ ስለሚያደርግ ነው። " አልአዛር " ቡድን ይህን ስልት በተግባር ከማዋሉ በፊት የተመሳሰለ ኢሜይል ወደ ባንኩ ሰዎች በመላክ እንዲከፍቱት ካደረገ በኋላ ወደ ባንኩ ሲስተም ሰርጎ መግባት ችሏል። ከዚያም የባንኩን የቁጥጥር ሥርዓትን ካሉበት ሆነው ማዘዘ ቻሉ። ይህ መቆጣጠሪያ ባንኩ የገንዘብ ወጪ ጥያቄ ሲቀርብለት ማሽኑ ገንዘብ እንዲተፋ የሚያዝ ሥርዓት ነው። ማለትም ከየትኛውም የዓለም ክፍል ከሚገኝ ኤቲኤም የገንዘብ ትዕዛዝ ቢመጣ ሰርሳሪዎቹ ማሽኑ ገንዘቡን እንዲለቀው ማድረግ ያስችላቸዋል። የማይችሉት አንድ ማሽን ምን ያህል ገንዘብ መልቀቅ እንዳለበት መወሰን ነበር። ብዙ ገንዘብ ለማውጣት ደግሞ የግድ ብዙ ካርድ ማተም ነበረባቸው። የሚቀራቸው ተመሳሳይ #የኤቲኤም_ካርድ_ህትመት ነው። ይህን የሚሠራ ሌላ ድርጅት ተገኘ። አስገራሚው እሱ አይደለም፤ ሰሜን ኮሪያዊያን እንዴት ከ28 አገር በተመሳሳይ ጊዜ ገንዘብ የሚያወጡላቸው ሰዎችን ማዘጋጀት ቻሉ ? ምክንያቱም ቪዛ ለማግኘት ራሱ ብዙ ችግር የሚያዩ ናቸው። ይህን ሥራ ለሌላ ለሚተባበራቸው ድርጅት ኃላፊነት መስጠት ነበረባቸው። በበይነ መረብ በተዘረጋው የጠላፊዎች ግንኙነት አንድ ሰው ይህን ሥራ እንደሚሠራ ገለጸ። ይህ ቢግቦስ በሚል ስም የሚጠራው መረጃ ቦርቧሪ ግለሰብ ኤቲኤም ካርዶችን ማምረት እና ሰዎችንም ማዘጋጀት እንደሚችል ገለጸ። በካናዳና አሜሪካ ተቀጣሪ ሊሆኑ የሚችሉ እንዲሁም ከኤቲኤም ማሽን ገንዘብ ማውጣት የሚቸሉ ግለሰቦችን እንደሚመለምል አስታወቀ። ይህ በትክክል አልአዛር ቡድን የሚፈልገው አገልግሎት ነበር። ቢግቦስ እና አልአዛር አብረው ጥምረት ፈጠሩ። ቢግቦስ ለ14 ዓመታት በስርቆት የተሰማራ ማንነቱ ሳይታወቅ የቆየ ግለሰብ ነበር። የሆነ ወቅት ላይ ማንነቱ ተደርሶበት አሜሪካ ውስጥ በመኖርያ ቤቱ ሳለ ተይዞ አሁን ዘብጥያ ወርዷል። የ35 ዓመት ካናዳዊ ነው። እርሱን መያዝ ቢቻልም የባንኩ 14 ሚሊዮን ዶላር ግን እስከወዲያኛው ቀልጦ ቀርቷል። እነዚህ የሰሜን ኮሪያ ሰርሳሪዎች በፍጹም ዝቀተኛ ገንዘብ ላይ ጊዜያቸውን አያጠፉም። እንዲያውም አሁን አሁን ላይ ትኩረታቸውን ወደ ክሪፕቶከረንሲ አዞረው ወደ 3.2 ቢሊዮን ዶላር ዘርፈዋል። የአሜሪካ ባለሥልጣናት አልአዛር የተባለውን የዓለም ግዙፍ የባንክ ዘራፊ ቡድን ብሎ ይጠራዋል ለዚያውም ያለ አንዳች የጦር መሣሪያ። Credit : BBC AMHARIC

ማክሰኞ ምሽት! መጋቢት 26/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች 1፤ የጸጥታና ደኅንነት ግብረ ኃይል " በመንግሥት ባለስልጣናትና በከተሞች ላይ በጦር መሳሪያ የታገዘ ጥቃት ለመፈጸም ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ" ያላቸውን ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር አውያለሁ ማለቱን ፋና ብሮድካስት ዘግቧል። ምሁራን፣ የመገናኛ ብዙኀን ባለቤቶችና የማኅበረሰብ አንቂዎች የታቀፉባቸው ናቸው የተባሉት ኅቡዕ ቡድኖች፣ ጥቃቱን ሊፈጽሙ ያቀዱት በአዲስ አበባ፣ ባሕርዳር፣ አዳማ እና ድሬዳዋ እንደነበር ግብረ ኃይሉ መግለጡን ዘገባው ጠቅሷል። በቁጥጥር ስር ከዋሉት መካከል፣ ዶ/ር ወንደወሰን አሠፋ፣ ረዳት ፕሮፌሰር ሲሳይ አውግቸው፣ ፕሮፌሰር ማዕረጉ ቢያበይን እና ዶ/ር መሠረት ወርቁ የተባሉ ተጠርጣሪዎች እንደሚገኙበትና በአንዳንዶቸ ተጠርጣሪዎች እጅ ጦር መሳሪያዎች እንደተያዙ ዘገባው አመልክቷል። ተጠርጣሪዎቹ " የአማራ ሕዝብ በከፍተኛ ጭቆና ውስጥ ይገኛል"  በማለት፣ "ሕዝብን በሐይማኖት፣ በብሄርና በጽንፈኛ የፖለቲካ ዓላማ ዙሪያ ደጋፊ ለማሰባሰብ ሲሞክሩ ነበር" ተብሏል። 2፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ ከኦሮሚያ ክልል የተመረጡትን አባሉን ዶ/ር ጫላ ዋታን ያለመከሰስ መብት በአንድ ድምጸ ተዓቅቦ አንስቷል። ጫላ ያለመከሰስ መብታቸው የተነሳው፣ የሁሌ ቦራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት በነበሩበት ወቅት ከመንግሥት የግዥ ሥርዓት ውጭ ፈጽመውታል ተብለው በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል መኾኑን ለምክር ቤቱ የውሳኔ ሃሳቡን ያቀረበው የሕግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ አስረድቷል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ የወንጀል ተጠርጣሪው ጫላ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ስለመዋላቸው አልታወቀም። 3፤ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሌሊሴ ደሳለኝን የከፍተኛው ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት እና ዘሃራ ኡመርን የፍርድ ቤቱ ምክትል ፕሬዝዳንት ኾነው እንዲሾሙ የቀረበለትን የውሳኔ ሃሳብ በሁለት ድምጸ ተዓቅቦ አጽድቋል። ሌሊሴ የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤትን ጨምሮ በተለያዩ የክልሉና ፌደራል ፍርድ ቤቶች በዳኝነት እንዲሁም ባንድ ወቅት በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በምክትል ፕሬዝዳንትነት ማገልገላቸው የተገለጠ ሲሆን፣ ዘሃራ ደሞ በሱማሌ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በተለያዩ ኃላፊነቶች ማገልገላቸው ተጠቅሷል። ሌሊሴና ዘሃራ የተሾሙት፣ የፍርድ ቤቱ የቀድሞ ፕሬዝዳንት ብርሃን መስቀል ዋጋሪና ምክትል ፕሬዝዳንት ተናኘ ጥላሁን በፍቃዳቸው ከሃላፊነት በመልቀቃቸው እንደኾነ ተዘግቧል። 4፤ የአውሮፓ ኅብረት የውጭ ግንኙነት ኃላፊ ጆሴፕ ቦሬል ኅብረቱ ከኢትዮጵያ ጋር ያለውን ግንኙነት "በሂደትና ደረጃ በደረጃ" ከሰሜኑ ጦርነት በፊት ወደነበረበት እንደሚመልስ ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል። ቦሬል፣ አውሮፓ ኅብረት ከኢትዮጵያ ጋር ስለሚኖረው ግንኙነት ዛሬ መግለጫ የሰጡት፣ ብራስልስ ውስጥ ከአሜሪካው ውጭ ጉዳይ ሚንስትር አንቶኒ ብሊንከን ጋር ከተወያዩ በኋላ ነው። የሰሜን ኢትዮጵያው ጦርነት በመንግሥትና ሕወሃት መካከል በተፈረመ ሰላም ስምምነት መቋጨቱ አዎንታዊ ክስተት መኾኑን የጠቀሱት ቦሬል፣ የሰላም ስምምነቱ ዘላቂ እንዲኾን ኅብረቱ ከአሜሪካ መንግሥት ጋር በትብብር መስራት እንደሚቀጥል ተናግረዋል። ቦሬል፣ አውሮፓ ኅብረት የሰላም ስምምነቱን አፈጻጸም በቅርበት በመከታተል ላይ እንደኾነ የኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና የትግራይ ክልል አመራሮች እንዲረዱትም አሳስበዋል። 5፤ ኢትዮ ቴሌኮም የኢንተርኔት ግንኙነት ያለ "ቪፒኤን" ለማድረግ እንደተቸገረ ተደርጎ በማኅበራዊ ትስስር ገጾች የተሠራጨው መረጃ "የተሳሳተ ነው" ሲል ዛሬ በትዊተር ገጹ ባስተላለፈው መልዕክት አስታውቋል። ኢትዮ ቴሌኮም ያለ "ቪፒኤን" የኢንተርኔት ግንኙነት ለማድረግ "ተጨማሪ መዋዕለ ንዋይ ማፍሰስ እንዳስፈለገው" ተደርጎ የተሠራጨው መረጃም ሐሰት መኾኑን ጨምሮ ገልጧል። ኢትዮጵያ ውስጥ ምክንያቱ ባልተገለጠ ሁኔታ የፌስቡክ፣ ቴሌግራምና ዩትዩብ ማኅበራዊ መገናኛ አገልግሎቶች ከተገደቡ ሁለት ወር የተቆጠረ ሲሆን፣ ደንበኞች የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹን የሚጠቀሙት "በቪፒኤን" በመግባት ብቻ ነው። የማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎቹ ለምን እንደተገደቡ፣ ኩባንያው ያለው ነገር የለም። 6፤ በጅቡቲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ ከጅቡቲ የቀይ ባሕር ዳርቻ 142 ፍልሰተኞችን መታደግ እንደተቻለ ዛሬ በትዊተር ገጹ ባሰራጨው መረጃ አስታውቋል። ፍልሰተኞችን መታደግ የተቻለው፣ ፍልሰተኞቹ በሕገወጥ ሰው አዘዋዋሪዎች አማካኝነት በጀልባዎች ቀይ ባሕርን አቋርጠው ወደ የመን ለመሻገር ሲሞክሩ መኾኑን ኢምባሲው ገልጧል። ኢምባሲው፣ ፍልሰተኞቹን ሊያሻግሩ የነበሩ ሕገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎችም በቁጥጥር ስር እንደዋሉ የገለጠ ሲሆን፣ በቁጥጥር ስር የዋሉትን ሕገወጥ የሰው አዘዋዋሪዎች ብዛትና ዜግነታቸውን ግን አልጠቀሰም። 7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ9302 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 55 ብር ከ0088 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ6169 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ8892 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5844 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ7561 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏 👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇                             

ዓርብ ምሽት! መጋቢት 22/2015 ዓ.ም ዐበይት ዜናዎች 1፤ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ልዑካን ቡድን አዲስ አበባ ውስጥ ከፌደራል መንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተወያየ እንደኾነ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕስ መስተዳድር ጌታቸው ረዳ መናገራቸውን የክልሉ ቴሌቪዥን ዘግቧል። የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጌታቸው የመሩት የክልሉ ልዑካን ቡድንና የፌደራል መንግሥቱ ባለሥልጣናት እየተወያዩባቸው ከሚገኙባቸው አጀንዳዎች መካከል ዋነኛው፣ በትግራይ ክልል የመልሶ ማቋቋም እንቅስቃሴ ዙሪያ እንደኾነ ጣቢያው ገልጧል። 2፤ የብሄራዊ መልሶ ማቋቋሚያና ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ተሾመ ቶጋ በትግራይ ክልል የነፍስ ወከፍና የቡድን ጦር መሳሪያዎችን የማስፈታቱ ሂደት መዘግየቱን  መናገራቸውን ዴይቸቨለ ዘግቧል። ኮሚሽነር ተሾመ ዛሬ ባሕርዳር ላይ በጉዳዩ ዙሪያ በተካሄደ የምክክር መድረክ ላይ፣ ለሂደቱ መዘግየት ምክንያቶቹ፣ አዲሱ ኮሚሽን በቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠመዱና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ምስረታ መዘግየቱ መማኾናቸውን መጥቀሳቸውን ዘገባው አመልክቷል። ኾኖም ኮሚሽነር ተሾመ፣ ከአሁን ጀምሮ የነፍስ ወከፍና ቀላል የጦር መሳሪያዎችን ትጥቅ የማስፈታቱ ሥራ በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት ተግባራዊ መኾን ይጀምራል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። በምክክር መድረኩ ላይ የአማራ ክልል ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የመከላከያ ሠራዊት ከፍተኛ መኮንኖች ተገኝተዋል ተብሏል። 3፤ የመንግሥታዊው የኢትዮጵያ ባሕር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ አገልግሎትን በዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለስድስት ዓመታት የመሩት ሮባ መገርሳ ከሃላፊነታቸው መነሳታቸውን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል። በሮባ ምትክ፣ በሪሶ አመሎ የኩባንያው ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኾነው እንደተሾሙ ዘገባው አመልክቷል። ተሰናባቹ ሮባ የኩባንያውን ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ሃላፊነት ከመረከባቸው በፊት፣ በኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን በምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚነት ለዓመታት ያገለገሉና በዘርፉ የካበተ ልምድ ያላቸው እንደነበሩ ዘገባው ጠቅሷል። በተመሳሳይ፣ የኢትዮጵያ ማሪታይም ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር የኋላሸት ጀመረ ከሃላፊነት ተነስተው፣ በምትካቸው አብዱልበር ሸምሱ እንደተሾሙ ዜና ምንጩ ዘግቧል። 4፤ በደቡብ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የኛንጋቶም ወረዳ አስተዳደር የአንድ እምነት ተከታይ ኡጋንዳዊያን ወደ ወረዳው የገቡት "የምጽዓት ቀንን በመሸሽ ነው" መባሉን እንዳስተባበለ ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል። የወረዳው አስተዳደር፣ 277 ኡጋንዳዊያን ወደ ወረዳው ባለፈው ታኅሳስ መግባታቸውን አረጋግጦ፣ ኾኖም ግን ኡጋንዳዊያኑ "በኡጋንዳ ይጀምራል ብለው ያመኑትን የምጽዓት ቀን ሽሽተው የተሰደዱ ናቸው" ተብሎ የተነገረው "የተሳሳተ መረጃ ነው" ማለቱን ዘገባው ጠቅሷል። ኡጋንዳዊኑ ለኛንጋቶም ብሄረሰብ "የቤተክርስቲያን መልዕክት ለማድረስና አካባቢውን ለመጎብኘት" የገቡ የሐይማኖት ተጓዦች እንደኾኑ የጠቀሱት የወረዳው ባለሥልጣናት፣ ኛንጋቶም ብሄረሰብ ከኡጋንዳ የፈለሰ ነው የሚል አፈ ታሪክ መኖሩንም ተናግረዋል ተብሏል። ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር፣ ኡጋንዳዊያኑ "የምጽዓት ቀንን የሸሹ" መኾናቸውን ማረጋገጡን ትናንት ተናግሮ ነበር። 5፤ አሜሪካ የሱማሌላንድ ራስ ገዝ መንግሥት ወታደሮቹን የግጭት ቀጠና ከሆነችው ላስ አኖድ ከተማ እንዲያስወጣ ጠይቃለች። መንግሥትን የሚፋለሙ የላስ አኖድ የጎሳ ሚሊሻዎችም፣ በመንግሥት ኃይሎች ላይ ጥቃት ከማድረስ እንዲቆጠቡ አሜሪካ አሳስባለች። ሁለቱ ወገኖች ግጭቱን አብርደው ቀደም ሲል የተደረሰውን ተኩስ አቁም እንዲያከብሩ የጠየቀችው አሜሪካ፣ ሰብዓዊ ቀውሱ እንዳይባባስ ተፋላሚ ወገኖች በንግግር ግጭቱን መፍታት አለባቸው ብላለች። ባለፈው ኅዳር መካሄድ የነበረበት የሱማሌላንድ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ መዘግየቱ እንዳሳሰባትም አሜሪካ የገለጠች ሲሆን፣ የፕሬዝዳንት ሙሴ ቢሂ መንግሥት ምርጫው የሚካሄድበትን የጊዜ መርሃ ግብር እንዲያሳውቅ ጥሪ አድርጋለች። 6፤ የዓለማቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት መመስረቻ ስምምነት ፈራሚዋ ደቡብ አፍሪካ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቱን ለ"ብሪክስ" አገራት የመሪዎች ጉባኤ ሲሄዱ እንደምታስተናግዳቸው ዛሬ በውጭ ጉዳይ ሚንስትሯ ናለዲ ፓንዶር በኩል አስታውቃለች። የዓለማቀፉ ወንጀል ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ፑቲን በዩክሬን "የጦር ወንጀል ፈጽመዋል" በማለት የእስር ማዘዣ ማውጣቱን ተከትሎ፣ በቀጣዩ ነሐሴ የ"ብሪክስ" አገራት የመሪዎች ጉባኤ አዘጋጇ ደቡብ አፍሪካ አቋሟ ምን እንደሚኾን በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። ደቡብ አፍሪካና ሩሲያ በሌሎች አገራት ግፊት በድንገት ጠላት ሊኾኑ አይችሉም ያሉት ፓንዶር፣ ፑቲንን በጉባኤው እንዲገኙ እንደተጋበዙ ተናግረዋል። በዓለማቀፉ ፍርድ ቤት ስምምነት መሠረት፣ ደቡብ አፍሪካ ፑቲን ግዛቷን ከተረገጡ አስራ ለፍርድ ቤቱ የማስረከብ ግዴታ አለባት። "ብሪክስ" በፍጥነት በማደግ ላይ ያሉት ኃያላኑ፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ሕንድና ብራዚል የመሠረቱተ ቡድን ነው። 7፤ ንግድ ባንክ ዛሬ የአንድ ዶላር መግዣ ዋጋ 53 ብር ከ9017 ሳንቲም እና መሸጫ ዋጋው 54 ብር ከ9808 ሳንቲም ሆኖ እንደዋለ በድረገጹ ገልጧል። የአንድ የእንግሊዝ ፓውንድ መግዣ ዋጋ ደሞ 63 ብር ከ5330 ሳንቲም እና መሸጫው 64 ብር ከ8037 ሳንቲም ሆኗል። በተመሳሳይ አንድ ዩሮ በ58 ብር ከ5545 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ59 ብር ከ7256 ሳንቲም ሲሸጥ መዋሉን ባንኩ ገልጧል። አንድ የቻይና ዩዋን ደሞ በ7 ብር ከ0868 ሳንቲም ተገዝቶ፣ በ7 ብር ከ2285 ሳንቲም ተሽጧል ተብሏል። #ሼር በማድረግ ተባበሩኝ🙏 👉ወሳኝ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ቻናሉን ይቀላቀሉ👇👇👇  

👉 ግብጽ አልተኛችም...ሴራዎቿ ግን ይከሽፋሉ‼️ ♦️ "የፋክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል" እንዳይሆን በንትርክ መባላትህን አቁመህ ሀገርህን ነቅተህ ጠብቅ‼️ ♦️ በኢትዮጵያ መንግስታዊ እና የልማት ተቋ
+1
👉 ግብጽ አልተኛችም...ሴራዎቿ ግን ይከሽፋሉ‼️ ♦️ "የፋክክር ቤት ሳይዘጋ ያድራል" እንዳይሆን በንትርክ መባላትህን አቁመህ ሀገርህን ነቅተህ ጠብቅ‼️ ♦️ በኢትዮጵያ መንግስታዊ እና የልማት ተቋማት ላይ የሳይበር ጥቃት ለማድረስ መዘጋጀቱን ከግብፅ የደህንነት ምንጮች ያፈተለኩ መረጃዎች ጠቁመዋል‼️ ♦ ይህን የኢጂአይኤስ እቅድ የግብፁ ፕሬዚደንት አልሲሲ አፅድቀውታል‼️ የግብፁ EGIS ከ60 ዓመታት በላይ ያስቆጠረ አጠቃላይ የደህንነት አገልግሎት ሲሆን፤ አፍሪካዊ እና ሌሎች ሀገራት እንዲሁም በግብፃዊ ዜጎችና ተቋማት ላይ የሳይበር ጥቃቶችን በማድረስ ስሙ የሚነሳ ተቋም ነው። በኢትዮጵያም በመንግስት ተቋማት ላይ ተደጋጋሚ የሳይበር ጥቃቶችን መፈጸሙና የመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደርም ጥቃቶቹን በጀግንነት ሲመክት መቆየቱ የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያን ሠላም ለመንሳት እና ለማበጣበጥ ተኝቶ የማያድረው የግብፅ መንግሥት፤ ከወትሮው በተለየ፣ በተጠና እና በከፍተኛ ደረጃ በአጠቃላይ መረጃ አገልግሎት (ኢጂአይኤስ) ከፍተኛ አመራሮች በተዘጋጀ እቅድ በኢትዮጵያ መንግስታዊ እና የልማት ተቋማት ላይ የሳይበር ጥቃት ለማድረስ መዘጋጀቱን ከግብፅ የደህንነት ምንጮች ያፈተለኩ መረጃዎች ጠቁመዋል። ይህን የኢጂአይኤስ እቅድ የግብፁ ፕሬዝደንት አልሲሲ እንዳፀደቁት ተነግሯል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ የመረጃ መረብ ደህንነት አስተዳደር እነዚህንና መሰል ጥቃቶች መከላከል የሚያስችል የሰው ኃይልና የቴክኖሎጂ አቅም እንዳለው ከዚህ ቀደም የተገለፀ ሲሆን፤ በተለይም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዘመኑ የሚጠይቀውን ክህሎት እና ቴክኖሎጂ የታጠቀ ደጀን ተቋም በመሆኑ፤ የሚደርሱ የሳይበር ጥቃቶችን በመከላከል የሀገር ደጀንነቱን ዳግም እንደሚያስመሰክር ቅንጣት ያህል ጥርጥር የለንም‼

ሩሲያ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቿን ቤላሩስ ውስጥ ልታጠምድ ነው ሩሲያ ስልታዊ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በአጋሯ እና በጎረቤቷ ቤላሩስ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንዲተኮሱ ለማድረግ እንደምታጠምድ ፕሬዝዳንት
ሩሲያ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቿን ቤላሩስ ውስጥ ልታጠምድ ነው ሩሲያ ስልታዊ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በአጋሯ እና በጎረቤቷ ቤላሩስ ውስጥ በማንኛው ጊዜ እንዲተኮሱ ለማድረግ እንደምታጠምድ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አስታወቁ። ፕሬዝዳንት ፑቲን አሜሪካ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቿን በአውሮፓ አገራት ውስጥ ማሰማራቷን በመጥቀስ፣ ይህ የሩሲያ ውሳኔ የኑክሌር ጦር መሳሪያን ለሌላ አገር ላለማስተላለፍ የተደረሰውን ስምምነት የሚጥስ አይደለም ማለታቸውን የሩሲያ የመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል። የአሜሪካ የመከላከያ መሥሪያ ቤት ባወጣው መግለጫ ላይ “ያሉንን ስልታዊ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎችን አቀማመጥ ለማስተካከል የሚያስገድደን ምንም ምክንያት አይታየንም” ብሏል። የጦር መሳሪያዎቹ የሚጠመዱባት የቤላሩስ መንግሥት ጠንካራ የሩሲያ ወዳጅ ሲሆን፣ በዩክሬን ላይ የፈጸመችውንም ወረራ ይደግፈዋል። ይህ የሩሲያ ውሳኔ የተለየ እንዳልሆነ የጠቀሱት ፑቲን “አሜሪካኖች ተመሳሳይ ነገር ለአስርት ዓመታት ሲያደርጉ ቆይተዋል። ስልታዊ የኑክሌር ጦር መሳሪያዎቻቸውን ከረጅም ጊዜ በፊት ነው በወዳጆቻቸው አገራት ግዛት ውስጥ ያሰማሩት” ብለዋል። በዚህ የሩሲያ እርምጃ ከ30 ዓመታት ወዲህ ሩሲያ ከግዛቷ ውጪ የኑክሌር የጦር መሳሪያ ማስወንጨፊያ ማዕከል ሲኖራት የመጀመሪያው ይሆናል ተብሏል። #ArifNeger #Ethiopia #Ethiopiannews  #ዜና #News ለፈጣን መረጃዎች አብራችሁን ስለሆናችሁ እናመሰግናለን!

ኢትዮጵያ በቁርጥ ቀን መኮንኖች ተጋድሎ ፈተናዎችን በድል አድራጊነት እየተሻገረች አሸናፊነቷን ታረጋግጣለች-የመከላከያ መኮንኖች ኢትዮጵያ በቁርጥ ቀን ልጆቿ ተጋድሎ ፈተናዎችን በድል አድራጊነት እየተሻ
+3
ኢትዮጵያ በቁርጥ ቀን መኮንኖች ተጋድሎ ፈተናዎችን በድል አድራጊነት እየተሻገረች አሸናፊነቷን ታረጋግጣለች-የመከላከያ መኮንኖች ኢትዮጵያ በቁርጥ ቀን ልጆቿ ተጋድሎ ፈተናዎችን በድል አድራጊነት እየተሻገረች አሸናፊነቷን ታረጋግጣለች ሲሉ የሀገር መከላከያ ሠራዊት መኮንኖች ገለጹ። በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚገጥማት የውጭም ይሁን የውስጥ ጠላት ያልተሸነፈችው ኢትዮጵያ እስካሁንም ነፃነቷን አስከብራ የዘለቀች ሀገር መሆኗ ይታወቃል። በአድዋና ማይጨው የባዕድ ወራሪን አሸንፎ በማስወጣት ለቅኝ ገዥዎች ያልተንበረከከች፤ የአፍሪካ ብሎም የዓለም ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ፈር-ቀዳጅ ስለመሆኗም ታሪክ የሰነደው እውነታ ነው። አሁንም ቢሆን የሚገጥሟትን ፈተናዎች እያለፈች፤ ጠላቶችን እያሸነፈች በድል አድራጊነት የምትሸጋገር መሆኑን የሚጠራጠር ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ የለም። በዚህ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የሀገር መከላከያ ሠራዊት መኮንኖች ለኢትዮጵያ ክብርና ሉዓላዊነት እንዲሁም ለሕዝቦች ሰላም ሲባል ሠራዊቱ  ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ቁርጠኛና ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል። ”መከላከያ ሰራዊት ማለት ሀገር ፍቅር ሰላም ማለት ነው ያሉት መኮንኖቹ ” ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምና ልማት መረጋገጥ ሰራዊቱ በአስተማማኝ ቁመና ላይ መሆኑንም ገልጸዋል። ”ለሀገሬ እስከ ህይወት መስዋእትነት ድረስ አገለግላለሁ” በማለትም በአጽንዖት ተናግረው በዚህም ከምንጊዜውም በላይ ዝግጁ ነን ሲሉ ገልጸዋል። ሁሉም በተሰማራበት የሥራ መስክ ኃላፊነቱን በመወጣት ለኢትዮጵያ የእድገት ስኬት ባለቤትነቱን በተግባር ማሳየት አለበትም ነው ያሉት። ”ሁሉም በየተሰማራበት ሙያ ሁሉ ስለ ሰላም እና ስለ ሀገር ፍቅር ፤ስለ አንድነት እና ስለመዋደድ እያስተማረ ሀገሩን የሚወድ ትውልድ ማፍራት መቻል አለበት ሲሉ አመልክተዋል።

✍️ ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የመንግስታቱ ድርጅት የውሃ ጉባዔ በኒውዮርክ እየተካሄደ ነው ~~~~~~~~~~~~~~~ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተባበሩት
✍️ ኢትዮጵያ የምትሳተፍበት የመንግስታቱ ድርጅት የውሃ ጉባዔ በኒውዮርክ እየተካሄደ ነው ~~~~~~~~~~~~~~~ የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስትር ሀብታሙ ኢተፋ በኒውዮርክ እየተካሄደ በሚገኘው የተባበሩት መንግስታት የውሃ ጉባዔ ላይ እየተሳተፉ እንደሚገኙ ተገለጸ። ጉባዔው በተባበሩት መንግስታት ድርጅት፣ በታጂክስታን እና ኔዘርላንድስ መንግስት ነው የተዘጋጀው። ድርቅና የአየር ንብረት ለውጥ ያስከተለውን ተጽዕኖ፣ የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር ፋይዳ፣ የግብርና ሥራዎችን እና የውሃ ሀብት ትብብርን በተመለከተ ሚኒስትሩ ንግግር  እንደሚያደርጉ ይጠበቃል። በመድረኩ በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ስለሺ በቀለ፣ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የኢትዮጵያ ቋሚ መልዕክተኛ አምባሳደር ዮሴፍ ካሳዬ፣ የኢትዮጵያ ሜትሪዮሎጂ ኢንቲትዩት ዳይሬክተር ጄነራል አቶ ፈጠነ ተሾመ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ አመራሮችና ባለሙያዎች እየተሳተፉ መሆኑን የውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር በማህበራዊ ትስስር ገጹ ያሰፈረው መረጃ ያመለክታል።

👉 ወጣቶች‼~ወርቃማው ዕድል እንዳያመልጣችሁ‼️ ♦ የስመ ገናናው የጀግናው የኢፌዴሪ አየር ኃይል አባል መሆን ያኮራል‼️ ዘመንና ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሠራ የኢትዮጵያን የአየር ክልል ነቅቶ ሲጠብቅ
+3
👉 ወጣቶች‼~ወርቃማው ዕድል እንዳያመልጣችሁ‼️ ♦ የስመ ገናናው የጀግናው የኢፌዴሪ አየር ኃይል አባል መሆን ያኮራል‼️ ዘመንና ትውልድ ተሻጋሪ ታሪክ የሠራ የኢትዮጵያን የአየር ክልል ነቅቶ ሲጠብቅ የኖረ ፣ የአየር ላይ ንሥር ተዋጊዎችን የፈጠረ፣ አሁንም ከተተኪው  ትውልድ ውስጥ  እየፈጠረ ያለ የሀገር አለኝታና መኩሪያ መመኪያ ተቋም ነው‼ወጣቶቻችን ፍጠኑ‼ጀግናውን የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ተቀላቀሉ‼️ ጀግናው አየር ኃይላችን የአውሮፕላን ቴክኒሻኖችን መልምሎ ለማሰልጠን የቅጥር ማስታወቂያ አውጥቷል‼መስፈርቱን የምታሟሉ ወጣቶች ይህ ወርቃማ ዕድል እንዳያመልጣችሁ‼የጀግኖቻችን አባል ሆኖ ሀገርን ማገልገል ታላቅ ክብርና  ኩራት ነው‼️የቅጥር መስፈርቶቹ ከታች ተያይዘዋል‼👇👇👇 #የኢትዮጵያ_ክንድ ለተጨማሪ መረጃዎች👇👇👇

አንድ ጊዜ ታዋቂው ሳይንቲስተት አልበርት አይንስታይን በክፍል ውስጥ ባለው ሰሌዳ ላይ የሚከተሉትን ስሌቶች እየጻፈ ለተማሪዎቹ እያሳየ ነበር ፡- (9 X 1 = 9) . . . (9 X 2 = 18) . .
አንድ ጊዜ ታዋቂው ሳይንቲስተት አልበርት አይንስታይን በክፍል ውስጥ ባለው ሰሌዳ ላይ የሚከተሉትን ስሌቶች እየጻፈ ለተማሪዎቹ እያሳየ ነበር ፡- (9 X 1 = 9) . . . (9 X 2 = 18) . . . (9 X 3 = 27) . . . (9 X 4 = 36) . . . (9 X 5 = 45) . . . (9 X 6 = 54) . . . (9 X 7 = 63) . . . (9 X 8 = 72) . . . (9 X 9 = 81) . . . (9 X 10 = 91) ከእነዚህ የሂሳብ የድምር ስሌቶች ሁሉም ትክክል ሆነው ሳለ ለመጨረሻው የሰጠው መልስ 90 መሆን ሲገባው 91 በመሆኑ እንደተሳሳተ የተመለከቱ ተማሪዎቹ በጣም ሳቁበት ፡፡ “ይህንን የመሰለ ሊቅ እንዴት ይሳሳታል” ነበር የሳቁ መነሻ ፡፡ እሱም ሳቃቸውን እስከሚጨርሱ ጠበቀና ፣ “የመጀመሪያዎቹን ዘጠኙን ጥያቄዎች በትክክል መመለሴን በማንሳት ማንም ተማሪ አላደነቀኝም ፡፡ ነገር ግን አንዷን ስለተሳሳትኩኝ ብቻ ሁላችሁም ሳቃችሁብኝ ፡፡ ይህ ማለት ምንም እንኳ በአብዛሃኛው ነገር ስኬታማ ብትሆኑም ሕብረተሰቡ አንዷንና ትንሿን ስህተት የማጉላት ዝንባሌ አለው ፡፡ ስለዚህ ምን እንደበረዶ ብትነጣ ከሰዎች ትችትና ነቀፌታ አታመልጥምና ለሰዎች ብለህ ትልቁን ሕልምህን ከማሳካት ወደኋላ አትበል ።

✍️የዓለማችን አስፈሪው ሊግ! እግርኳስ ደጋፊነት በዚያ ህይወትን ቀብድ አሲይዞ ለሞት እንደመደራደር ይቆጠራል። ህዝቡ ከእግርኳሱ ጋር ያለው ቁርኝት ቢለካ የሮሚዮ እና ጁሊዬትን ፍቅር የሚያስንቅ ይሆና
✍️የዓለማችን አስፈሪው ሊግ! እግርኳስ ደጋፊነት በዚያ ህይወትን ቀብድ አሲይዞ ለሞት እንደመደራደር ይቆጠራል። ህዝቡ ከእግርኳሱ ጋር ያለው ቁርኝት ቢለካ የሮሚዮ እና ጁሊዬትን ፍቅር የሚያስንቅ ይሆናል። እግርኳስ አመፅ ሞት…በዚያ የህይወት አንድ አካል ከሆኑ ሰንብተዋል። እንደ ሪያል ማድሪድ እና ባርሴሎና አይነት ክለቦች አሊያም እንደ ክርስትያኖ ሮናልዶ እና ሊዮኔል ሜሲ አይነት ኮኮቦች በዚያ የሉም። በአመፃቸው ልክ ለልኬት ቢቀርቡ ሆሊጋኒዝም ብርቃቸው ካልሆነባቸው ጣሊያናዊያን እና የምስራቅ አውሮፓ ሀገራት እጥፉን ቢበልጡ እንጂ ሊያንሱ አይችሉም። የምናወራው በአውሮፓ ውስጥ ስላለች አሊያም በእግርኳሱ ስለበለፀገች ሀገር አይደለም ስለ ኢንዶኔዢያ እንጂ። በአህጉረ ኤዢያ የምትገኘው ሀገሪቱ ከ 260 ሚሊየን በላይ ህዝብ የሚኖርባት ፣ 700 የሚደርሱ ቋንቋዎች የሚነግሩባት ፣ በ 17ሺ ደሴቶች የተከበበች ፣ የእስልምና ሀይማኖት ተከታዮች በብዛት የሚገኙባት ነገር ግን ከክርስትና እስከ ሒንዱይዝም ያሉ ሀይማኖቶችን በውስጧ ያቀፈች ሀገር ናት። እግርኳስ በኢንዶዎች ዘንድ አለሁኝ ያለው በ 20ኛው ክፍለ ዘመን እንደሆነ ይነግራል…ከደጋፊው ጋር ለመዋሃድ ግን ጊዜም አልፈጀበት። ህዝቡ ግን ኳስን የሚመለከተው ጎሳ ለይቶ ነው። በራሳቸው ቋንቋ "Sampai Mati" ይላሉ በአማርኛው እስከ ሞት ድረስ እንደማለት ነው። የአክራሪነት መነሻው ቱሪን ላይ ቢሆን እድገቱም ምስራቅ አውሮፓ ላይ ቢታይ የትርጉሙን ምንነት ግን ከነሱ በላይ አስረጂ የለም ወደሌላ ፅንፍ ወስደውታል። ይቀጥላል

በሀገራዊ ተልዕኮና ተሳትፎ የሴት ሠራዊት አባላት ሚና ከፍተኛ ነው ሌ/ጄኔራል ሹማ አብደታ በኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ጠቅላይ መምሪያ የሴት የሠራዊት አባላት ሀገራዊ ተልዕኮ እና ተሳትፎ ሚና ከፍተኛ መሆኑን የዕዙ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል፡፡ ዕዙ ከሴት የሠራዊት አባላት ጋር በተልዕኮ አፈፃፀም እና በማህበራዊ ጉዳይ ዙሪያ ውይይት አድርጓል፡፡ በፕሮግራሙ ላይ በክብር እንግድነት በመገኘት  ማብራሪያ የሰጡት የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ናችው፡፡   ዋና አዛዡ ያለ ሴቶች ተሳትፎ ግቡን የሚመታ ስራና ተልዕኮ አይኖርም፤ ሴቶች ለሀገራቸው ሉአለዊነት፣ አንድነትና ሰለም ከትላንት እስከ ዛሬ ከፍተኛ መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ በአድዋ ጦርነት ከወንዶች እኩል ግንባር ድረስ በመዝመት ስንቅ አቀብለዋል፤ ቁስለኛ ተንከባክበዋል፤ ዘመን ተሸጋሪ ታሪክ ሰርተዋል ብለዋል፡፡ ሌተናል ጄኔራል ሹማ በሀገር ደረጃም በፖለቲካ አመራር የሴቶች ተሳትፎ እያደገ መምጣቱን በማስታወስ፤ የዛሬ ሴት የሠራዊት አባላትም የሀገራችንን ጀግና እና ተምሳሌት ሴቶች በመሆን ተሞክሮአቸውን በማስተላለፍ የታሪክ አሻራ እያሳረፉ መምጣታቸውን ገልፀዋል፡፡ የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ ሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ ኮሎኔል አለምነሽ ታረቀኝ በባኩላቸው፤ የኢትዮጵያ ሴቶች ትላንት ለሰንደቅ አላማቸው ክብርና ለሀገራቸው ሠላም ከፍተኛ ተጋድሎ ማድረጋቸውንና የአሁኑ ትውልድ ሴቶችም ይህንን በቆራጥነት በማስቀጠል ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ ሌተናል ኮሎኔል ወርቅውሃ ከበደ እና አስር አለቃ አስቴር በየነ በሰጡት ተመሳሳይ አስተያየት፤ ሴቶች አቅማቸውን እየገነቡ ወደ ላቀ ደረጃ እንዲመጡ ተቋሙ አስፈላጊውን እገዛ ሁሉ እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል። ሴቶች በሀገር ግንባታ፣ በሀገር ሉአላዊነትና አንድነት ውስጥ ከፍተኛ ሚና ያላቸው በመሆኑ፤ ከወንዶች እኩል ተወዳዳሪ ለመሆን ራሳቸውን በሁለገብ እውቀት መገንባት እና ማብቃት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡

የኢፌዴሪ መከላከያ መጋቢት 04 ቀን 2015 ዓ.ም ብላቴ የጀግኖች መፍለቂያ፦ በብላቴ የኮማንዶና አየር ወለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ብቁ  የኮማንዶ ሰልጣኞችን ለማብቃት ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡ በውጊያ ማርሽ ቀያሪ አሃድ መፍለቂያ ማህፀን ብላቴ ማሰልጠኛ ማዕከል ስልጠናቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ የምድር ድሮኖች የዞብል ኮርስ መሰረታዊ ኮማንዶ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን በእልህ በቁርጠኝነት በከፍተኛ ሞራል እና ተነሳሽነት እየተከታተሉ መሆናቸውን የኮማንዶ አየር ወለድ ማሠልጠኛ ምክትል አዛዥ ለኦፕሬሽናል ሌተናል ኮሎኔል አበባው ሞላ ገልፀዋል፡፡ የተመረቁ የኮማንዶ፣አየር ወለድ ፣የልይ ኃይል ተመራቂዎች በአውደ ውጊያ ያስመዘገቡት ድል በሚገርም ሁኔታ ሀገርን እንደ ሀገር ካስቀጠሉ የመከላከያ ክፍሎች አንዱ ነው፡፡ እነኝህ የሠራዊት አባላትም በኮማንዶና አየር ውለድ ማሰልጠኛ ማዕከል ሰልጥነው የተመረቁ ናቸው ፡፡ ተመራቂዎች በማንኛውም የአየር ንብረትና ፀባይ፣የመሬት አቀማመጥ፣  የውጊያውን ሁኔታ በመቀየር በገቡበት የውጊያ ቀጠና ሁሉ አኩሪ ገድል በማስመዝገባቸው በሃገርና በተቋም ደረጃ በተዘጋጀው ጀግኖችን የማመስገን መርሃ ግብ ታሪኩ በታላቅ መዝገብ አርፏል፡፡ በዚህም በማንኛው ውጊያም በትክክል መሰዋዕትነት በመክፈል የሀገር ሉዓላዊነት የሚያሥቀጥል ኮማንዶ፣አየር ወለድ ልዩ ኃይል እና ፀረ-ሽብር የማሠልጠን ተግባር እየተከናወነ መሆኑን  ገልፀዋል፡፡ ስልጠናውን በተመለከተ ከዚህ በፊት የነበሩ ጠናካራና ደካማ ጎኖችን በማንጠር ዘመናዊ  ስልጠና  ለመስጠት በማሰብ የነበረውን ሥርዓተ ትምህርት  በማሻሻል  ሠፋፊ ስራዎች እየተሠሩ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡ የአሁኑ ዙር ስልጣኞችም ከዚህ በፊት ከነበሩ ዙሮች አንፃራዊ በሆነ መልኩ ከሁሉም የኮማንዶ ዙሮች በተለየ መልኩ ግዜ ተሰጥቷቸው ብቁ ኮማንዶና በገባበት የውጊያ አውደ ውሎ በየብስ፣በአየር እና በውሃ  ግዳጅ መፈፀም የሚያስችላቸው ስልጠና እየተሰጣቸው መሆኑንም ምክትል አዛዡ ገልፀዋል፡፡ ሰልጣኞች በኮማንዶ መመረቂያ መስፈርት መሰረት በእወቀት፣ በችሎታ፣ አስተሳሰብና በባህሪ የሚፈለገውን እቅም እዲጨብጡ ሁሉም አመራርና አሰልጣኝ የበኩሉን ሚና እየተጫወተ ይገኛል፡፡ የሥርዓተ ትምህርቱን እቅድ ለማሳካት አመራሮች፣ አሰልጣኞች እና የስልጠናው ድጋፍ ሰጪ ተረባርበውና ተደጋግፈው የሚፈለገውን ግብ ለማስመዝገብ በየፊናቸው ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ነው፡፡ ሰልጣኞች በአካል ብቃት ትምህርት የተለያዩ የእጅ ለእጅ ውጊያ ትምህርት የውጊያ አካል ብቃት ትምህርቶችን እየወሰዱ የሚገኙ ሲሆኑ በዚህም በማንኛውም የአየር ፀባይና ወቅት ተፈጥሯዊና ሰው ሰራሽ መሰናክሎችን ማለፍ የሚያስችል አካላዊ ጥንካሬ ተጣጣፊነትና የማድረግ አቅም ለመፍጠር የሚያስችል ስልጠና እየወሰዱ ነው፡፡ በስልት ትምህርት ደግሞ ሰልጣኞች የተለያዩ የመሬት ገፆች በወታደራዊ እንቅስቃሴ የሚኖራቸውን ጠቀሜታ እንዲረዱ የነብስ ወከፍ እንቅስቃሴዎችን በተገቢ የመሬት አይነት መጠቀም እንዲቸሉ እና በተለያዩ ሁኔታዎች እና ግዳጆች በላቀ ውጤት ማጠናቀቅ የሚያስችላቸውን ስልታዊ አስተሳሰብና የማድረግ ብቃት የመፈጠር ስራ እየተሰራ መገኘቱንም ሌተናል ኮሎኔል አበባው ሞላ ገልፀዋል፡፡ በተኩስ ትምህርት ደግሞ በታጠቋቸውን የተለያዩ መሳሪያዎች ያላቸውን ፀባይ፣መጠንና ችሎታ እንዲሁም እውክታን የማስወገጃ ዘዴዎችንና የጥንቃቄ ደንቦችን በሚገባ በመረዳት በተለያዩ ስፍራ አያያዝ እና የውጤት ርቀት ፈጣንና ገዳይ ተኩስ በመተኮስ የሚሰጣቸውን ተቋማዊ ተልዕኮ መወጣት የሚያስቸላቸው ብቃት ፈጥረዋል፡፡ ሰልጣኞች በስልጠና እየጨበጡት ያለውን አቅም ስልጠናቸውን በሚገባ አጠናቀው የውጊያ ማርሽ ቀያሪ  አሃድ ሲቀላቀሉ የዕዙ የጀግንነት ታሪክ በመድገም የኢትዮጵያን አንድነት እና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ በሞራልና በስነልቦና ዝግጁ መሆን እንዳለባቸውም ምክትል አዛዡ ገልፀዋል፡፡ የዞብል ኮርስ ኮማንዶ ሰልጣኞች ስልት ዲፓርትመንት ኃላፊ መ/አ አግማስ  ባዬ እና  የኮማንዶ ሴት የተኩስ አሰልጣኝ ፲/አ  አስረሳሽ አስፈው በበኩላቸው  ሰልጣኞች ስልጠናው ላይ ያላቸው ቁርጠኝነት እና የማወቅ ጉጉት ጥሩ በመሆኑ የሚፈለገውን ሁለንተናዊ ብቃት እየፈጠሩ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡  አሰልጣኞች ሰልጣኞችን የተሻለ የኮማንዶ ሁለንተናዊ ብቃት ለመፍጠር እርስ በእርስ ተደጋግፈው እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀው ከሰልጣኞች ጋር ባለን ግንኙነትም ወጥ የሆነ መመሪያና  አሰራርን ተከትለን በመስራታችን ጥሩ የሆነ የአሰልጣኝና ሰልጣኝ ግንኙነት ለመፍጠር ተችሏል ብለዋል፡፡ የኮማንዶ ሰልጣኞች በሰጡት አስተያየትም ስልጠናቸውን በከፍተኛ ሞራልና ስነ-ልቦናዊ ዝግጁነት እና በከፍተኛ የሃገር ፍቅር ስሜት እየተከታተሉ እንደሚገኙ ገልፀው ስልጠናቸውን ከጨረሱ በኋላ ወደ ነባሩ ሠራዊት በመቀላቀል በማንኛውም ግዳጅ አኩሪ ገደል ለማስመዝገብና በዚህም ለሃገራቸው ማንኛውንም ዋጋ ለመክፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡