የኮማንዶና አየር ወለድ ዕዝ _ Commandos and Airborne Command ️
رفتن به کانال در Telegram
5 756
مشترکین
-27824 ساعت
-2 5467 روز
-1 99730 روز
آرشیو پست ها
+3
ሞሮኮ ቡርኪና ፋሶ የባህር በሯን እንድትጠቀም ፈቀደች !!
#Maleda: ሞሮኮ ቡርኪና ፋሶ የአትላንቲክ ውቅያኖስ የባህር በር እንድትጠቀም ፈቀደች ። በተመሳሳይ የባህር በር የሌላቸው ማሊ እና ኒጀር ያቀረቡት ጥያቄ ማፅደቃቸውን የሞሮኮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታወቀ።
የሦስቱ ወታደራዊ አገዛዝ የምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች በሞሮኮ ዋና ከተማ በራባት ከንጉስ መሀመድ ስድስተኛ ጋር ባደረጉት ውይይት የሀገራቸውን አቋም መጋራታቸውን የሚኒስቴሩ መግለጫ አመልክቷል።
ሀገራቱ ማሊ፣ቡርኪናፋሶ እና ኒጀር ኢኮዋስ ተብሎ የሚጠራውን የክልል ቡድን ለቀው መውጣታቸውን ባለፈው ዓመት አስታውቀዋል ።
ከዚያም የሳህል ግዛቶች ጥምረት በመባል የሚታወቀውን የራሳቸውን የፀጥታ አጋርነት ፈጠሩ፣ ከረጅም ጊዜ ጀምሮ ከምዕራባውያን አጋሮች እንደ አሜሪካ እና ፈረንሳይ ጋር ወታደራዊ ግንኙነታቸውን አቋርጠው ወታደራዊ ድጋፍ ለማግኘት ወደ ሩሲያ ፊታቸውን አዙረዋል ።
በምዕራብ አፍሪካ የፋይናንሺያል እና የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ባለሃብት የሆነችው ሞሮኮ፣ ኢኮዋስ በሦስቱ ሃገራት ላይ የንግድ ገደቦችን ከጣለ በኋላ፣ በህዳር 2023 የንግድ መዳረሻ ጅምርዋን እንደጀመረች ማስታወቋ ይታወሳል። መረጃው የአፍሪካ ሪፖርት ፋይል ነው ።
===================
የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመላው አለም ነው ስንል በኩራት ነው:: አየር መንገዳችን ዛሬ በፖይለት የበረራ መስተግዶና ቴክኒሻን ካስመረቃቸው ኢትዮጵያዊያን በተጨማሪ 38 ከቻይና፣ 34 ከዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ 19 ከሞዛምቢክ፣ 8 ከካሜሩን፣ 2 ከጋቦን፣ እና አንድ እያንዳንዳቸው ከዛምቢያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኡጋንዳ እና ሴራሊዮን ይገኙበታል።
+4
አዛዡ የ43ኛ ዙር ሰልጣኝ ከማንዶዎችን የመስክ ስልጠና ሂደት ተመለከቱ፡፡
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ስልጠናቸውን እያገባደዱ የሚገኙትን የ43ኛ ዙር ሰልጣኝ ኮማንዶዎችን የስልጠና ሂደት በመስክ ላይ ተንቀሳቅሰው ተመልክተዋል፡፡
አዛዡ ምልከታ ያደረጉት በወንዶ ገነት፣ ወንዶ ጢቃ፣ በሐዋሳ ሀይቅ እና በወንዶ ኮይሻ በፈታኝ የመሬት ገፅታና የውሃ አካላት ላይ የስልጠና መውጫና የኮማንዶነት ማረጋገጫ ስልጠናቸውን እያካሄዱ የሚገኙትን ሰልጣኞችን ነው፡፡
በጉብኝታቸው ወቅትም ሰልጣኙን እና አሰልጣኙን ያበረታቱ ሲሆን የኮማንዶ ሠራዊት በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ በማለፍ ሀገሩን በጭንቅ ቀን የሚታደግና ሲታደግ የቆየ ሀይል ማሆኑን በማብራራት ሰልጣኙም የዚህ ትውልድ ታሪክ ባለቤት መሆኑን አውቆ ስልጠናውን በብቃት በመፈፀም ለላቀ ታሪክ ራሱን ማዘጋጀት እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡
43ኛ ዙር ሰልጣኝ ኮማንዶዎች ከዚህ በፊት ከነበረው የስልጠና ሂደት በላቀ ደረጃና ስልት መሰልጠናቸውን የተናገሩት አዛዡ ይህ ስልጠናም ሰልጣኙ ነገ የሚጠብቀውን ሀገራዊ ግዳጅ በፈታኝ ሁኔታ ውስጥ በቀላል መንግድ በመወጣት ሀገሩንና ህዝቡን በማኩራት የአያቶቹን አደራ እንዲያስቀጥል ታስቦ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ አሁናዊ የሀገሪቷ የሰላም ሁኔታ በመልካም መንገድ ላይ እንደሚገኝና አሸባሪው ሸኔ እና ፅንፈኛው ከባዕዳን ተልዕኮ ተቀብለው በሀገራችን ላይ ለመተግበር የሞከሩት የጥፋት እቅድ በመከላከያ ሠራዊት ክንድ መክሸፉን ገልፀዋል።
ሰልጣኙ ይህንን ውስብስብና ፈታኝ ስልጠና እየተወጣበት ያለው መንገድ ለሀገሩና ለሰንደቅ አላማው ያለውን ፍቅርና የአያት አባቶቹን አደራ ለማስቀጠል ፅናቱን ያረጋገጠበት በመሆኑ ያላቸውን አድናቆት በመግለፅ ለዚህ ውጤት መገኘት ያለዕረፍት እየተጉ ያሉትን አሰልጣኞች እና የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ ማሰልጠኛ ማዕከል አመራሮች አመስግነዋል፡፡ የዘገበው አብዱራህማን ሀሰን ነው።
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
+2
በሥልጠና ራሳችንን በማብቃት ተልዕኳችንን በውጤት መፈፀም ይገባናል።
ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ሚያዚያ 23 ቀን 2017 ዓ.ም
እንደ ልዩ ዘመቻዎች ራሳችንን በስልጠና እያበቃን የተጠለብንን ህዝባዊ አደራ በብቃት መወጣት አለብን ሲሉ የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ አዛዥ ሌተናል ጄነራል ሹማ አብደታ ተናግረዋል፡፡
አዛዡ በስልጠና ላይ ለሚገኙት የክፍሉ አመራሮች በሠራዊት ግንባታና የሽምቅ ውጊያ ሳይንሳዊ ጥበብ ላይ ለሁለት ቀን ስልጠና ሰጥተዋል፡፡
ሌተናል ጀነራል ሹማ አብደታ የአገር ትርጉሙ ያልገባቸዉ የፀረ-ሰላም ሃይሎች አገራቸዉን እና ህዝባቸዉን ክደዉ ከዉጭ ጠላቶች ጋር በመተባበር ኢትዮጵያን ለማዳከም እየሰሩ ነዉ ሆኖም ግን ለሀገሩ የታመነ ሠራዊት እያለ ይህ ቅዠታቸው አይሳካም ብለዋል።
በሰለጠነ ዘመን ነብሰ ጡር እናት በጤና ጣቢያ እንዳትወልድ እንዲሁም የነገ አገር ተረካቢ ህፃናት ትምህርት ቤት ገብተዉ እንዳይማሩ ትምህርት ቤቶችን እና የህዝብ መገልገያ ጤና ጣቢያዎችን በመዝጋት የፀረ-ሰላም ሃይሎች ህዝብን ለስቃይ እና ለእንግልት ዳርገዋል ነው ያሉት።
ቅዠታቸው እንዳይሳካ በየትኛውም መንገድ በሀገር ላይ የሚደቀነውን አደጋ ለመቀልበስና ጦርነትን ለማስቀራት ሁሌም በስልጠና አቅምን በመገንባት ለዛሬ ሳይሆን ለነገ ውጊያ መዘጋጀት አስፈላጊ ነው ያሉት ሌተናል ጄኔራል ሹማ አብደታ ማንኛዉም መሪ ለሚመራዉ ሠራዊት በቅድሚያ ራሱ አርአያ አድርጎ ህግና አሰራሩ በሚፈቅደዉ መሰረት መገንባት እንደሚያስፈልግም አስገንዝበዋል።
የምንቆስልለት እና የምንሞትለት ህዝባችን ከእኛ ዉጭ ማንም የለዉም እና በአግባቡ በመንከባከብ ፅንፈኛዉ እና አሸባሪዉ ሸኔ ከሚያደርስበት ጥቃት እና ጥፋት መጠበቅ እንደሚያስፈልግና እነዚህን ሀይሎች በማጥፋት የላኪዎቻቸው የተዳከመች እትዮጽያን የመፍጠር ህልም ማኮላሸት የኢትዮጵያ ህዝቦች ህልውናን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ዘጋቢ ምህረት ስመኝ
ፎቶግራፍ በአብዱራህማን ሀሰን
የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ዩቲዩብ
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ሰበር — የተሳካ የድሮን ጥቃት ሰሜን ሸዋ ኮሳዬ ቀበሌ❗️
በዛሬው እለት ከቀኑ 8፡50 የሰማዩ ንግስት በላይነሽ አመዴ በሰሜን ሸዋ ዞን ሞረትና ጅሩ ወረዳ ስትቃኝ ጽንፈኛው ጃውሳ ኩሳዬ ቀበሌ ተሰባስቦ ተመለከተችው። ከፍ ዝቅ እያለች¹ በታጠቀችው Artificial Intelligence (AI) ገመገመችው።
360° ቅኝቱን እያካሄደች “በእኔ በኩል ጽንፈኛ ሃይል ለቀጣይ ጥፍት እየመከረ ስለመሆኑ እርግጠኛ ነኝ፤ ይሄው ማስረጃው በማለት የድምጽና የምስል መረጃውን አቅርባ ፍቀዱልኝና በእቅፌ ያለውን እንቁላል ላዘንብባቸው...” ስትል ፈቃድ ይሰጣት ዘንድ ለማዕከላዊ ዕዝ ጥያቄ አቀረበች...
[በማዕከል ተገመገመ - በላይነሽ አመዴ ትክክል ነች !!]
ተፈቀደላት!.. በላይነሽ አመዴ አነጣጥራ እንቁላሏን ጣለች 🔥
የተደመሰሰ ጃውሳ = 30 (ሊጨምር ይችላል)
ክፉኛ የቆሰለ ጃውሳ = 25
በኢትዮጵያ የሚመረተው Drone እጅግ የተራቀቀ ከመሆኑ ባሻገር ሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የታጠቀ ነው።
የሰላም መጥፎ የጦርነት ጥሩ የለውም ‼️
#ሠላም_ለሀገራችን!!
#ሠላም_ለህዝባችን!!
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይሏ ከጎረቤቶቿ ቀዳሚ ሆና ተቀምጣለች‼
📌 ከአፍሪካ በ5ኛ ደረጃ፣ ከዓለም በ52ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች
📌 ኤርትራ በ26ኛ፣ ሶማሊያ በ36ኛ ደረጃ ላይ ተቀምጠዋል
📌 በወታደራዊ ኃይል ግብጽ፣ አልጄሪያና ናይጄሪያ ይመራሉ
የዓለም አገራትን ወታደራዊ አቋም በመመዘን በየዓመቱ የጦር ሠራዊቶችን ደረጃ የሚያወጣው ግሎባል ፋየር ፓወር ኢንዴክስ፣ የ2025 የ145 አገራትን የወታደራዊ አቅም ደረጃ ይፋ ያደረገ ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ከአፍሪካ በ5ኛ ደረጃ፣ ከዓለም ደግሞ በ52ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧታል፡፡
ግሎባል ፋየር ፓወር ባወጣው የደረጃ ሰንጠረዥ መሠረት፤ ከአፍሪካ ግብፅ፣ አልጄሪያ፣ ናይጄሪያ፣ ደቡብ አፍሪካና ኢትዮጵያ በወታደራዊ ኃይላቸው የአህጉሪቱ 5 ቀዳሚ አገራት ሆነው ተመዝግበዋል። እነዚህ አገራት በሕዝብ ብዛትና በምጣኔ ሀብትም በአህጉሪቱ ውስጥ በከፍተኛው ቦታ ላይ የሚገኙ ናቸው ብሏል።
እንደ ቢቢሲ ዘገባ፤ ግጭትና ፖለቲካዊ ውጥረት በማይለየው የአፍሪካ ቀንድ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፤ ከአፍሪካ ቀዳሚ አምስት ወታደራዊ ኃያላን አገራት አንዷ ስትሆን፤በምጣኔ ሀብትና በፖለቲካም በቀጣናው ከፍተኛ ተጽእኖ ያላት አገር ናት።
ከአፍሪካ በሕዝብ ብዛቷ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ በአሁኑ ጊዜ 118 ሚሊዮን ሕዝብ እንዳላት የግሎባል ፋየር ፓወር መረጃ ያመለክታል። ውስጣዊና ውጫዊ የደኅንነት ስጋት ያለባት ኢትዮጵያ፤ የምድር፣ የአየርና የባሕር ኃይል ያላት ሲሆን፤ በወታደራዊ አቅሟ በዙሪያዋ ከሚገኙ ጎረቤት አገራት በቀዳሚ ደረጃ ላይ ትገኛለች፡፡
ከ160 ሺህ በላይ መደበኛ ሠራዊት ያላት ሲሆን፤ ከ2 ቢሊዮን 97 ሚሊዮን ዶላር በላይ ዓመታዊ በጀት በመመደብ በዙሪያዋ ካሉት አገራት ሁሉ ከፍተኛውን ገንዘብ ለሠራዊቷ እንደምታውል የግሎባል ፋየር መረጃ ያመለክታል፡፡
የኢትዮጵያ ሰሜናዊ ተዋሳኝ የሆነችው ኤርትራ በአንጻሩ፣ በወታደራዊ አቅም ከ145 አገራት 120ኛ ደረጃ ላይ ስትሆን፣ ከአፍሪካ ደግሞ 26ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። ከ6.3 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ ያላት ኤርትራ፤ 120 ሺህ መደበኛ ሠራዊትና 130 ሺህ ተጠባባቂ ኃይል እንዳላት መረጃው ይጠቁማል፡፡
በግሎባል ፋየር ፓወር የደረጃ ሠንጠረዥ ውስጥ ከተካተቱት 145 አገራት ውስጥ ሶማሊያ ለመቅደም የቻለችው ሦስቱን ብቻ ሲሆን፤በዚህም በወታደራዊ አቅሟ ከዓለም 142ኛ፣ ከአፍሪካ ደግሞ 36ኛ ደረጃ ላይ ትገኛለች። በሌላ በኩል፤ አንጎላ፣ ሞሮኮ፣ ዲሞክራቲክ ኮንጎ፣ ሱዳንና ሊቢያ ከ6ኛ እስከ 10ኛ ያለውን ደረጃ እንደ ቅደም ተከተላቸው ይዘዋል፡፡
በዓለም ላይ ኃያል ወታደራዊ አቅም ያላቸው በምጣኔ ሀብት የዳበሩቱ አሜሪካ፣ ሩሲያ፣ ቻይና፣ ሕንድና ደቡብ ኮሪያ ከአንድ አስከ አምስት ያለውን ደረጃ መያዛቸውን የግሎባል ፋየር መረጃ ያመለክታል፡፡
ቤተሰብ❤️ይህንን በቅንነት ሰብስክራይብ በማድረግ ተባበሩ
የሱዳኑ መሪ ጄኔራል አብደል ፈታህ አል ቡርሃን ከቱርክ አምባሳደር ጋር ተወያዩ
ጀነራሉ በቱርክ የልማት ፕሮጀክቶች፣ የሰብአዊ እርዳታ አሰጣጥ እና የአየር መንገድ አገልግሎትን እንደገና ማስጀመር ላይ ያተኮሩ ውይይቶች ከቱርኩ አምባሳደር ፋቲህ ይልዲዝ ጋር አካሂደዋል። በፖርት ሱዳን የተካሄደው ስብሰባ የሁለትዮሽ ግንኙነቱን በማጠናከር ላይ ያተኮረ ሲሆን ቡርሃን ከቱርክ ፕሬዝዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ጋር በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ያደረጉትን ውይይት መከታተላቸውን ባለስልጣናቱ ተናግረዋል።
የሱዳን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ምክትል ሴክሬታሪ ሁሴን አል-አሚን በጋዜጣዊ መግለጫው ላይ እንደተናገሩት ከሆነ ውይይቶቹ “የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ሂደት የሚያሻሽሉባቸው መንገዶች እና አንካራ በሱዳን በመጪው ጊዜ ውስጥ ልተገብራቸው ያቀደቻቸውን የልማት ፕሮጀክቶች” ያካተተ ነበር ተብሎለታል። ውይይቶቹ የሱዳን አየር መንገድ ከፖርት ሱዳን ወደ አንካራ በሰኔ ወር መጀመሪያ ላይ እንደገና ለመጀመር የታቀደውን በረራ ያካተቱ መሆኑ አል-አሚን አክለዋል።
ባለሥልጣናቱ ቱርክ በምትሰጠው ሰብዓዊ ዕርዳታ እና በተለዋጭ መንገዶች ወደ መካከለኛው እና ምዕራብ ሱዳን በቀጠለው ግጭት ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች ዕርዳታ ለማድረስ በተደረገው ዝግጅት ላይ ተወያይተዋል። የምዕራብ ዳርፉር ክልል ውስብስብ የሆነ ሰብአዊ ቀውስ የተጋረጠበት ሲሆን እንደ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ግምት ከሆነ 79 በመቶ የሚሆነው ህዝብ በጦርነት እና በቀደሙት ግጭቶች ምክንያት እርዳታ እና ጥበቃ ያስፈልገዋል ብሏል።
እንደ አል-አሚን ገለጻ ቡርሃን ቱርክ ለሱዳን ያላትን ድጋፍ በአህጉራዊ እና አለም አቀፍ መድረኮች አወድሷል። በቅርቡ በለንደን በተካሄደው የሱዳን የሚኒስትሮች ኮንፈረንስ ላይ አንካራ ስለተሳተፈችበት መግለጫ አምባሳደር ይልዲዝ አመስግነዋል። በእንግሊዝ፣ በፈረንሳይ፣ በጀርመን እና በአውሮፓ ህብረት በሚያዝያ 15 ያዘጋጀው ጉባኤ ከ800 ሚሊዮን ዩሮ (850 ሚሊዮን ዶላር) በላይ ለሰብአዊ ርዳታ የተሰበሰበ ቢሆንም ግጭቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስቆም የሚያስችል ፖለቲካዊ መግባባት ላይ ግን አልደረሰም።
አምባሳደር ይልዲዝ ስብሰባው በኤፕሪል 12 ቡርሃን ወደ ቱርክ ያደረጉትን የአንታሊያ ዲፕሎማሲ መድረክ ከፕሬዚዳንት ኤርዶጋን ጋር የተገናኘበትን ውጤት መገምገሙን አረጋግጠዋል። ይልዲዝ እንደተናገሩት እነዚያ የከፍተኛ ደረጃ ውይይቶች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን ወደ አዲስ ደረጃ ያሸጋግሩታል ተብሎ ይጠበቃል ብለዋል። የቱርክ አየር መንገድ ወደ ሱዳን ቀጥታ በረራ እንደሚጀምር እና የቱርክ ዚራአት ባንክ ቅርንጫፍ በፖርት ሱዳን እንደሚከፈት አስታውቋል። በካርቱም እና በአንካራ መካከል ያለው ግንኙነት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ እያደገ መጥቷል። ኤርዶጋን ከዚህ ቀደም በሱዳን እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች መካከል ያለውን አለመግባባት ለመፍታት ሀሳብ አቅርበው ነበር።
በቡርኪናፋሶ መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ላይ ያነጣጠር የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ ከሸፈ
የመፈንቅለ መንግሥት ሙከራው በርካታ ወታደራዊ አባላትን ያሳተፈ እንደነበር የሀገሪቱ የደህንነት ሚኒስትር ማሃማዱ ሳና አስታውቀዋል።
የሀገሪቱ የደህንነት አገልግሎት ተቋማት የሴራው አካል በሆኑ የቡርኪናቢ ወታደሮች እና የታጣቂ ቡድን መሪዎች መካከል የነበረውን ግንኙነት በመጥለፍ የሚገኙበትን ቦታ እና የወታደራዊ እንቅስቃሴዎችን ዝርዝር ሁኔታ እንዳገኙ ሚኒስትሩ ጨምረው ገልጸዋል፡፡
በቡርኪናፋሶ ፕሬዝዳንት ላይ የተሴረው መፈንቅለ መንግሥት በመጀመሪያ ሚያዝያ 8 ቀን ለማካሄድ ታቅዶ እንደነበር ሚኒስትሩ ተናግረዋል።
በእንግሊዘኛ ያንብቡ
@sputnik_ethiopia
📲 መተግበሪያ | 👉 X ላይ ይከተሉን
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
“ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቷል።
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለትንሳኤ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን በዓሉ የሰላም እና የደስታ ይሁንልን።
መልካም በአል🙏
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
ሐገርህን የምትወድ ከሆነ መከላከያ ሰራዊትህን አክብር። ልጅህ በሰላም ወጥታ እንድትገባ፣ ቤተሰብህ ደህንነቱ እንዲጠበቅ፣ ዳር ድንበርህ በጠላት እንዳይደፈር ከፈለግክ ሰርተህ መግባት አርሰህ መብላት፣ ዘርተህ ማጨድ ከፈለግክ፣ ከመከላከያ ሰራዊትህ ጎን ቁም!
ይሄ ሰራዊት መሬት ላይ ታላላቅ ጀብዱ ቢፈፅምም የሚዲያ አርበኞች ስሙን አጥፍተውታል። ተገድሎ ገዳይ፣ ተደፍሮ ደፋሪ ተብሏል። ህዝቡን ሊያድን ቢሰዋ “ደመሰስነው” ተብሎ ተቀልዶበታል። ደጀን ይሆነኛል ባለው ተከድቶ ልብሱ ተገፍፏል። መለዮው ረክሷል። ቦኔቱን የማንም ኩታራ አጥልቆታል። ይህ ሁሉ ተፈፅሞበትም እንደገና እራሱኑ ይከስሱታል። የተቀባበለ ጥይት ይዞ ህዝቤን አልገድልም ባለ ተገድሎ ይፎከርበታል።
እመነኝ ከዚህ በኋላ መከላከያ ሰራዊትን መንካት ዘር ማንዘርህ ከፍሎ የማይጨርሰው ሃጢአት ይሆናል። እኛ በፋብሪካ የምናመርተው ሰራዊት የለንም። ለቤተሰቡና ለሐገሩ ውድ የሆነ ፣የከበረ ነፍስ ያለውና ሐገሪቱ መዋእለ ንዋይዋን ያፈሰሰችበት ክቡር ሰራዊት ነው ያለን። አይደለም ቃታ መሳብ ይቅርና ሰራዊቱን የሚያጣጥልና የሚያንቋሽሽ ንግግር መናገር ራሱ ትልቅ ዋጋ የሚያስከፍልበት ዘመን እየመጣ ነው። እመነኝ። ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያን ወታደር የልብሱን ጫፍ እንኳን ከነካህ መሬቱ ረመጥ ይሆንብሀል። እናት ሐገሩን ሊጠብቅ ወላጅ እናቱን ጥሎ የወጣ ወታደር ላይ ሰይፍ ያነሱ ሁሉ በሰይፍ ይጠፋሉ።
ክብር ለታላቁና ለጀግናው መከላከያ ሰራዊታችን!
©ናትናኤል መኮንን
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
#Ethiopia
#BREAKING
📹📹 https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
https://www.youtube.com/@Ethio_Commandos
የቴሌግራም ቻናሉን Join በማድረግ ቤተሰብ ይሁኑ📥
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
https://t.me/Commando_And_Airborne_Command
