403
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
😘አብዛኛው ሰው ምሽት ላይ የሚወደውን ሰው ያስባል መንፈሱ ይረጋጋና ስለሆነ ነገር ማሰብ ይጀምራል። ስለዚህ ያንተ እንድትሆን ከምትመኛት ሴት ጋር ስልክ ለማውራት የፀሀይን መጥለቅ ተጠባበቅ። ስልክህን አንስተህ ደውል አንቺም አንሺለት። ረጋ ባለ መንፈስ ወሬህን ጀምር ልብሽን ከፍተሽ አዳምጭው ያኔ ሳቶዱ በግዳችሁ ወደፍቅር ስሜት ትጠልቃላችሁ። እና የኔ የምትላትን ሴት ለመረዳት እና የፍቅሯን ልክ ለማወቅ አሪፍ ሰአት ነው። ስለዚህ ምሽት ላይ በስልክ ማውራት የተቃራኒው ፆታ በናንተ ላይ ያለውን ፍላጎት ይጨምራል።#marsi
@Hayitiye 🦋🦋
🍁♥️🍁
"ፍቅር እውነተኛ ስሜት ነው። የሌሎችን ስሜት ሳይሆንየራስህን ስሜት የምታዳምጥበት ፤ ልብህን ከፍተህ የምታስቀምጥበት፤ በደስታው ደምቀህ በሀዘኑ መፍትሔ የምትሻበት ፤ ዛሬን ኑረህ ነገን የምታልምበት ፤ አዲስ ነገር የምታይበት ፤ ከራስህ አልፈህ ለሌሎች ምታስብበት ስብእናን ሚያጎናፅፍህ ፀጋ ነው፡፡
💞♥️
@Hayitiye 🦋
🌿🌹አንቺ የልቤ ንግስት🌹🌿
እንድታፈቅሪኝ እና እንድታስቢኝ ላስገድድሽ አልችልም.....
ግን አንድ ነገር የማስቸግርሽ
ላንቺ ያለኝ ስሜት ምን ያክል ጥልቅ እንደሆነ እንድታውቂልኝ ብቻ ነው...
┄┉┉✽»🌹✿🌹»✽┉┉┄
ይ🀄️ላ🀄️ሉን👉 @Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 8
✍ እድል
.
.
.
ዲና ስልኳን አንስታ አንተ እድሜክ እርዥም ነው አሁን በልቤ ሳነሳክ ነበር አለችው አዳምም አዎ እድሜዬማ በጣም እረጅም ነው ዛሬ እድሜዬ ጨምሯል እልልልል በይ ዲናዬ ሄዋኔ ነቅታለች እናትዬ ነቅታልኛለች ፍቅሬ ነቅታለችችችች አላት ዲና አፏን ከፍታ ቀርች አዳምም ዲና ኧር ምነው ዝም አለሽ ሄሎ ዲና ሲላት የምርህን ነው አለችው እጅግ ፈገግ እያለ የምሬን እኮ ነው ነቃች ታውቂያለሽ ለአያሌ ቀናት የተሰማኝን ስሜት እንዴት እንደተሰቃየው አሁን ግን ያ ሁሉ አልፎ ሄዋኔ ስትነቃ የተሰማኝ ደስታ በቃላት አይገለፅም አለ ዲናም ቀጠል አድርጋ ቆይ እሺሺ መጣው ላያት በጣም ነው የምፍልገው አሁን አንተ የት ነክ ውስጥ ከሷ ጋር ነህ እንዴ የማገገሚያ ክፍል አስገብተዋት እዛው በር ላይ ሆኔ ነው
የምደውልልሽ ግን አለ አዳም እረጅም የጭንቀት ትንፋሽ እያወጣ አሷ እኔን አታስታወሰኝም ለኔ በጣም ከባድ ነው ቢሆንም በመትረፏ ግን በጣም ደስስስ ብሎኛል ፈጣሪን አመሰግነዋለው አለ አዴም እና አሁን እንዴት ናት አለች ዲና ለመውጣት እየንጎዳጎደች አዘነ አሁን ጥሩ ስሜት ላይ አደለችም መስለኝ ፊቷ ላይ ብዙ ጥያቄዎች እንዳሏት ያሳብቃል እና ደሞ ዳክተሩ ማንነትህን ከጠየቀችክ ላለመንገር ጣር ስላለኝ ስለእሱ እቅድ
እንድናወጣ ነይ እባክሽ አላት ዲናም እሺሺ ስልኩን ዝጋው እየመጣው ነው አለችና ለባብሳ ወጣች የዲናና የአዳምን ቅርርብ ያየ ሰው ረዥም ጊዜያት በጓደኝነት የቆዩ ነው የሚመስሉት አዳም
ይህ ቅርርባቸው ያሰጋዋል ምክንያቱም ያ ሰይጣን ጊዲዮን ጓደኛ እንደሆኑ ካወቀ ይገላታል ስለዚህ ያስጋዋል።
ዲና ሀኪም ቤት ደረሰች ሄዌን ወደተኛችበት ሄዳ በሩ ላይ ቆመች ሄዋን በግሉኮስ ተኝታ አዳም ደሞ በፍቅር ወንበሩን ወደ አልጋው አስጠግቶ ተቀምጦ በሀሳብ ነጉዷል የደስታ የመከፋት የማዘን ስሜት ይንፀባረቅበታል ዲና በሩን እንደማንኳኳት ብላ ገባችና ራቅ ብሎ የተቀሙጠውን ወንበር አምጥታ ቁጭ አለች ክፍሉ በዝምታ ተዋጠ ዲናም አዳም አለችው ሄዌንን አተኩሮ ሲመለከታት
የነበረው አዳም ወደ ዲና ዞር አለ ሄዋን ንገረኛ ምንድነው ዶክተሩ ያለህ በዝምታ ላብድ እኮ ነው አለችው እሱም ወደ መውጫው በር ሄዶ በአይኑ ተነሽ የሚል ምልክት ለዲና ስጣት ዲናም ወጣች
ምንድነው አለችው ዲናዬ ሄዋን ምንም አታስታውስም እንዴት ልለምደው እችላለው አላት እጁን ጭንቅላቱ ላይ እያረገ ከምንም ቅድሚያ ያንተ መረጋጋት ይቀድማል ቢያንስ አንተ በብዙ ከሷ ትሻላለህ ቢያንስ ስላሳለፋችሁት ነገሮች ታውቃለህ ሁሉንም ታውቃለህ ጤነኛ ነህ
ስለዚህ ተረጋጋ አዳም አለችው በረጅሙ እየተነፈሰ ልክ ነሽ መረጋጋት አለብኝ አለ ግን ዲናዬ በፈጠርሽ መላ ዘይጂ ሄዋኔን ማን ብዬ ልተዋወቃት አላት ዲናም እንዴ ለካ እሱም አለ ለምን ታዲያ ፍቅርኛሽ ነኝ በላታ አለችው በተዝናኖት በሞላው አነጋገር አዳም ጭንቅላቱን በቀስታ እያወዛወዘ አይ አይሆንም ዶክተሩ ምንም ስላለፈው ህይወቷ እንዳትነግራት በሽታዋ ይብስባታል ነው ያለኝ ስለዚህ ምን እናድርግ አለች አዳምም ቀጠል አድርጎ እንቺና እሷ እህትማማች እንደሆናቹ እና እኔ ደሞ የሁለታችውም ጓደኛ እንደሆንኩ እና ደሞ ሶስታችን አንድ ቤት ስንኖር እንደነበር አንቺ ደሞ ቤት መቀመጥ ስለማትወጂ ውጪ እንደምታድሪ እና አንዳንድ ቀን ነው የምትመጪው እንደዛ ብለን በ ብንነግራትስ አለ።
ቀጠል አድጎ የሆነ ጊዜ ነው ከጓደኞቼ ለመዝናናት ወጣን ሹፊሩ ጠጥቶ ስለነበር መኪናውን በፍጥነት ነበር ሲያሽከርክር የነበረው መኪናው ፍጥነቱን ጨመረ ጨመረ በመጨረሻ መኪናው ተገለበጠ።
ይቀጥላል...
••●◉Join us share
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 7
✍ እድል
.
.
የሆነች እጥፍጥፍ ያለች ወረቀት አገኘ ወርቀቱ እንዲህ ይላል
ሰላም ላንተ ይሁን ጠበቃ አዳም የጠበቃ እስማኤል ወዳጅ ነኝ
ወዳጅ ብቻ አይደለሁም መከታዬ ነው ወንድሜም ጓደኛዬም ሁሉም
ነገሬ ነው ለፍትህ ዘብ የቆመክ ለእውነት የምታድር ሰው
መሆንህን አውቃለው እስማኤል ፍትህ ለተራበ የሚያጠግብ
ለጎደለበት የሚሞላ ነው እስከኖረበት ጊዜ ለእውነት ኖሯል
በመጨረሻም ግን ለአንድ አውሬ ሰው ተበገረ ይህ አውሬ የወዳጄ
እስማኤልን ህይወት ቀጥፎብኛል አንተም እንደሱ ነህ ባንተ በኩል
ፍትህ ያገኙት ስላንተ አውርተው አይጠግቡም እጅግ የጠበቀን
ወዳጄን ህልም እንደምታስጨርስው እርግጠኛ ነኝ ትወጣዋለክ
እንደምትወጣው አምናለው አንብቦ እንደጨርሰ ያን በተለያዩ ልኮች የተፃፈውን እና አርንጎዴ ክር የተያዘውን ደብተር ከፍተው ውስጡ በሉኮቹ ላይ የሰፈሩትን
ተመለከተ ፅሁፎቹ እጅግ የተዋቡ ናቸው በሰማያዊ እና በጥቁር
እስኪብርቶ የተፃፈ ነው የታሪኩ ርእስ መንገደኛው ሎሌ ይሰኛል መንገደኛው ሎሌ መሄድ የለመደው አንድ ቀን ተነስቶ መጓዝ የጀመርው በሄደበት ሁሉ ብዙ ይታዘባል
ተመልካች ታዛቢ ሁሉንም ይሆናል ዛሬ ከቆመበት መንገዱን ጀምሮል
ብሎ አጠር ባለ መልኩ መንገደኛው ሎሌን ገልፇታል መንገደኛ
ስሙን ደሞ በሎሌ ቀይሮ የእዛን አውሬ ስራ አስፍሮታል።
አዳም መፅሀፍን ማንበብ ቀጠለ መፅሀፉም እንዲህ ይላል።
ይገርማችዋል ዛሬ መንገዱኛው ሎሌ እንደለመደው ጉዞውን
ቀጥሏል እየሄደ በመንገዱ ያጋጠሙት ደሀ እናት እና ልጅ ን አየ
እስከሚችለው ሊከተላቸው ወስኖ ሳይሆን እግር መንገዱን
እያያቸው መጓዝ ጀመር እናትና ልጅ በፀጥታ ከተጓዙ በኋላ
ልጅየው እናቷን ሽቅብ አንጋጣ እያየች እናቴ አለቻች እናት
የስማቻት አትመስልም የእኔ እናት እናትዬ እማ እያለች
ስትጎቶጉታት ሀሳቧን እና መንገዷን ገታ አድርጋ ወዬ የእኔ ልጅ
አለች በጣም በደከመና ትንፋሽ በተቀላቀለበት መለኩ እማ እስቲ
አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ እሽ እሺ ልጄ ጠይቂኝ ፍቅር እና መውደድ
ልዩነት አላቸው እንዴ እንዴ እናትም ልጄ በጣም እንጂ በጣም
ልዩነት አላቸው ልጅየው እንዴት አለቻት እናት ልጆ አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ ልጄ አለቻት ልጅም እሺ እማ አለቻት ጥንድ ጥንድ የሆኑ አካላቶችሽን ንገሪኝ ብላ እናት
ከመናገሯ ልጅት ጥንድ ጥንድ የሆኑት ለምሳሌ አይናችን ሁለት
ነው አለች እናት እሺ ሌላስ አለቻት ሌላ ደሞ እጃችን እግራችን
ሌላስ አለች እናት ልጅቱ ሌላ ጆሮአችን ሌላ ግን የለም አለቻት
እናት ፈገግ ብላ ተሳስተሻል የእኔ ውድ ልጅ አለቻት ልጅም እኔ
የምልሽ እማ ይህ አሁን ከጠየቅሽኝ ጥያቄ ጋር ምን አገናኘው
ያገናኘዋል እንጂ ልጄ እይውልሽ እንዳልሽው እጃችን እግራችን
አይናችን እና ጆሮችን ብቻ ሳይሆን ከልባችን በቀር ሁሉም አጋዥ
አለው ልጅየው ግራ ገባትና እንዴት እናቴ አለቻት ለምሳሌ ጣትሽ
ስንት ነው 10 እሺ ጨንጓራችንንስ እኔጃ እማ እሱም ትንሹ እና
ትልቁ አንጀት የሚባሉ አጋዦች አሉት ፀጉሯችንንም ብዙ አሉት
ከንፍራችን ደሞ ከላይና ከታች አለ ጥርሳችንን ተመልከች ብዙ
ናቸው ሊላም ብዙ ጥንድ ነገሮች አሉ ሁለም አጋዥ የላችውም
ልባችን ግን ብቸኛ ነው ይህ የሆነበት ምክንያት ደሞ ሊ ሌላኛው
ልባችን ጋር ሌላ ሰው ጋረ ስለሆነ ነው አለች እናት ልጅቱ እየተገረመች ማን ጋር? ብላ ጠየቀቻት እናትም የወደፊት የህይወትሽ አጋር ጋር እሱ ጋር ነው ለዛም ነው ፍቅር ሲይዘን ሁሉም ነገራችንን የሚቆጣጠርን ፍቅር ሲይዘን ሁሉም አካላታችን
ስራውን አቁሞ ልባችን የሚስራው ፍቅር ሲይዘን ልባችንን የሚስማን ፍቅር ሲይዝሽ በ ፍቅር ካፍቀሩት ጋር መኖር እድለኝነት ነው። አዳም ንባብን በእዚህ ገታ እና
ወርቀቱን ከደነው።
የማያልፍ ቀናት የለም አለፈ ዛሬ ሄዋን ከጥቄት ሰአታት በኋላ
ትነቃለች አዳም ውስጡ ደስ አለው ቀጥሎ የሚፈጠረው ነገር
መልካም እንደሚሆን አሰበ ስትነቃስ አለ በልቡ ስትነቃስ እንዴት
ነው የምቀርባት ሁሉንም ነገር እኮ እረስታለች ድጋሚ እንድትወደኝ
ላረግ ነው ስቀርባት ማነህ ብትለኝስ ልቡ ፈራ ውዴ እረሳሽኝ ወይ እስቲ መልሽለኝ
ምነው ቢሆን ለእኔ ሁሉን ባርገልኝ ብዬ ለመንኩትኝ ሀሳቤን ቢስማኝ
ብዬ በመጠበቅ ይህው ወራት ሞላኝ ለእሱ ብዙ ነገሩ ናት የሄዋን እጃች
በትንሹ መንቀሳቀስ ጀመሩ አላመነም ዶክተሩ ትነቃለች ቢለውም
የሚንቀሳቀስ እጇን ሲያስ አዳም ደስስስ አለው ዶክተሩን
ለመጣራት ከነፈ አጠገቡ ማንም አልነበርም ዲና በጠዋት ቤቷ
ፍቅድ ጠይቃ ሄዳለች ዲና በመንገድ ላይ እና ቤቷም ከገባች
በኋላ ሰለ አዳም ያለ ማቆርጥ ታስባለች ዲና ስልኳ ጠራ አዳም
ነበር ሄሎ አለችው በተርጋጋ ድምፅ.......
ይቀጥላል..
••●◉Join us share
@Hayitiye
💔ግድ የለም ልቤ ይችላል ችላለሁ እኔን ቢያመኝም
ጨክኖ አንቺን ሚጠላ ኧረ እኔስ አንጀት የለኝም💔
[ያን ፍቅር ባወራ አንደበት ስምሽን ለሰው አወድሼ
ግድ የለም ህመሙን ችላለሁ ጠላዋት አልልም መልሼ]💔💔
@Hayitiye 🦋🦋
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 6
✍ እድል
.
.
.
አዳም ድካም እየተስማው ሲመጣ ሌላኛው አግዳሚ ወንበር ላይ
ሄዶ ጋደም አለ ግን ነገ ሄዋን ስለምትነቃ በጉጉት ሊሞት ነው
ሄዋን ከነቃች በኋላ ለሚፈጠርው ነገር እራሱን አእምሮውን አዘጋጀ
ሄዋን ነገ ከኮማ ስትነቃ ልክ እንደማታቀኝ ልታስመስል ነው ወይ
ብሎ እራሱን ከጠየቀ በኋላ መልሶ ለእራሱ አይ አይ ሄዋኔ ወዳ
አደለም የረሳችኝ እንደዚህ መሆኗስ ለእኔ ስትል አደል አለና
እራሱን አፅናና እንዲ ከራሱ ጋር በሀሳብ ሲሞገት ሳያስበው
እንቅልፍ አሽለበው።
የሆነ የሚያስፍራ ኮቴ ሰማ በቀስታ የሚጓዝ ማን እንደሆነ ለማየት
ቀና አለ ምንም አይነት ሰው አልታየውም መልሶ ተኛ አሁን
የሚንሾካሾክ ድምፅ ሰማ ቀና ሲል ከእሱ ትይዩ የተኛችው ዲና
የለችም የት እንደሄደች ግራ በመጋባት እና በፍርሀት ስሜት ወደ
ሄዋን ክፍል እያመራ ሳለ ዲና በ2 ትልልቅ አቅም ባላቸው ስዎች
ተይዛ በጥቁር ፕላስተር እጇ አፏ እና እግሯ ተይዟል በአስተማሚ
ወንበር ላይ ጥብቅ አድርገው አስርዋታል ። አዳምን ስታየው
በተቀመጠችበት ወንበር ላይ መወዛወዝ ጀመርች አዳም
ከታስረችው ዲና ትይዩ ኮማ ውስጥ ያለችውን ሄዋንን አንድ
ጭንብል ያርገ ሰው በህይወት እና በሞት መካከል እስትንፋሷ
የሆነውን ማሽን አዳምን ፍገግ ብሎ በ ሰራውልክ አይነት
አስተያየት እያየው ነቀለው አጭር ጩሀት ሰማ ዞር ሲል ዲናን
ድምፅ በሌለው መሳሪያ አናቷን በታተኑት አዳም
አይይይይይሆሆሆሆንንምምምምምምም ብሎ ጮከ ኧረ ድረሱልኝ
ሰው የለም እንዴ እያለ ቢጮክም ምንም አይነት ሰው ሊደርስለት
አልቻለም አዳምን የሆነ ባትሪ መሰል መብራት ነገር ስውነቱ ላይ
ጭንብል ከለበሱት ውስጥ አበራበት አዳም አቅም አጠርው
መንቀሳቀስም አልቻለም ከቆይታ በኋላ የአንድ ሰው ኮቴ ተሰማው
ይህንን ኮቴ ያውቀዋል ሁለት እግር አንድ ከዘራ ባለ ከዘራው እና
ባለ ብዙ ሀጢያቶች ባለቤት ይህ ሰው ሄዋን ለእዚህ ችግር
እንድትጋለጥ ያረገው ሰው ነው ፈገግ እያለ ወደ አዳም ቀረበው
አዳምም አይሆንምም ብሎ ከህልሙ ነቃ ዲና ደንግጣ በርግጋ
ተነሳች ምንነው ችግር አለ አዳም አለችው እሱም የለም ተኚ
ብሏት በጥድፊያ ሄዋን ጋር ሄዶ በመስታወቱ ያያት ጀመር።
እውነት ቢሆንስ ቆይ ህልሜ ካንቺ ተለይቼ እንዴት እኖራለው ብሎ
ተንስቀሰቀ።
ይህ ሰው ጌዲዬን ይባላል በወንጀል የታወቀ ነገር ግን መፍትሄ
ያልተገኘለት ሰው ለብዙ ህፃናት ደሀዎች እና ፍትህ ፍላጊዎች
እልቂት ተጠያቂ እጁ እስከ ከፍተኛ የወንጀልም ሆነ የቢዝነስ ነክ
ጉዳዎች ላይ የሚረዝም ከፈለገ ምንም ማድርግ የማያቅተው
ህይወት ያለው ሰው የሚታዘዘው ነው። ታዲያ ለእሱ አለታዘዝ ያለ
ስው በህይወቱ ፈርዶ ነው ባአስቃቂ እና በሚዘገንን መልኩ
ያስቃየዋል በቁሙ በህይወት እንዳለ ያለ በለዚያ ፈፅሞ አይርካም
አንድን ሰው ገደለ ማለት በጣም ጥሩ ስራ እንደስራ ነው
የሚስማው ሰውን በቁሙ ማስቃየት በአለም ላይ ለእሱ ትልቅ
ፌሽታ ነው ሁሉም ሰው የእዚህ ስው ስም ሲነሳ ይንቀጠቀጣል።
አዳም በጥብቅና ሙያው ማንም የማይስተካከለው እልልልል
የተባለለት ጠበቃ ነው ስራ የጀመርው ከአመት በፊት ቢሆንም
ባጭር ጊዜ ባጭር የፍርድ ቀጠሮ ብዙ አልበገር ባይ እና ወንጀል
ስርተው የሚሸሽጉ ስዎችን አጋፍጦ ለፍርድ ልኳል ወደ ሚገባቸው
አስናብቶቸዋል ።ጠበቃ አዳም ማለት ለወንጀለኖች ስይጣን ፍትህ
ለተነፈጉ ደሞ መላክ ነው።
ጌዲዮን የአዳምን የጥብቅና ችሎታ እና ዝናውን ሰምቶ በቢዝነስ
ይሁን በማንኛቸውም አይነት ጉዳዮችን አብሮት እንዲሆን በረብጣ
ገንዘብ ድርድር ያቀርብለታል ጊዲዮን በዙሪያው ሌሎች የእራሱ
ጠበቆች ቢኖሩትም የአዳምን ጥብቅና ግን አብዝቶ ፈልጎታል
አዳም ግን የጊዲዮን ድርድር ሆነ ገንዘብ አላማለለውም ጠበቃ
አዳም ለህሊናው የተገዛ ለፍትህ ጥብቅና የቆመ ለእውነት
የሚኖር ሰው ነው ።
ልክ እንደ አዳም በጊዲዮን አልመራ ያለ እና ጊዲዮን በቁሙ
አስቃይቶ የገደለው እስማኤል የተባለ እሳት የላስ ጠበቃ ነበር
እስማኤል የጊድዮንን ትእዛዝ አለመቀበል ብቻ ሳይሆን
ሊያስፈርድበት ሂደት ጀምሮ ነበር በጊዲዮን ሴራነት ሰውን ያለ
ምክንያት በሀሰት በመፍርድ ተብሎ ተከሶ ለእርዥም አመት ታስሮ
የታሰርበት እስር ቤት ውስጥ በጊዲዮን ትዛዝ መሰርት የታሳሪያን
ሻውር ቤት ውስጥ ሞቶ ነበር የተገኘው ይህንን ጠበቃ መጀመሪያ
የሚወዳቸውን ስዎች በመግደል ነበር አይምሮውን የገደለው
ጌዲዮን ይህ ነው ቁመቱ እጅግ የረዘመ የአይኑ ብሌንን ትኩር
ብሎ ለተመለከተው ልክ እንደ በርበሬ የቀላ መልኩም ወደ ጥቁር
ያደላ ሰው ነው።
ጋሞ ጎፋ እንደሆነና ይህንን ፀባዩን ከአባቱ እስከ ሰውነት አቆሙ
እንደወርሰው ይወራል ብዙ ሴቶችን አስርግዞ አረገዝኩ ብለው
ሲነግሩት የፀነሱትን ፇታ ካወቀ በኋላ ሴት ከሆነች ከእነ እናትየው
ይገላታል የተረገዘው ወንድ ከሆነ ግን እስኪወለድ ጠብቆ እሱን
ካልመስለ ይገለዋል ከመሰለ ግን አሳድጎ ገረዱ ያርገዋል
ይህንን ታሪኩን መንጉደኛው ሎሌ በሚል ርእስ ያ እሳት የላስ
ጠበቃው እስማኤል ፅፎታል እንዲፅፍ የረዳው ደሞ የጌዲዮን
አሽከር ነበር፡፡
አዳም ጠረፔዛው ላይ ፒያሳ አራዳ ጋር 9ስአት ጠብቀኝ የሚል
አጠር ያለ ፅሁፍ አገኘ አዳም የሰውየውን ማንነት ሳያውቅ
የተባለበት ቦታደረሰ ምናልባት ፍትህ የተነፈገ ሰው ስለሱ ሰምቶ
ሊያገኘው እንደፈለገ አልተጠራጠረም
ፒያሳ ጋር እንደደረሰ የሆነ ኩትት ያለ ልብስ የለበሰ ሰው ላዳ ይዞ
ና ግባ እኔ ነኝ የጠራውክ ብሎ ካስገባው በኋላ ጭር ያለ ቦታ
ወሰደው ሲደርሱ የተቀመጥከበትን ወንበር ግለጠው እና እየው
ብቻህን ሆነክ ክፈተው ተጠንቀቅ ማንም እንዳያይክ እዚህ ውስጥ
ስለከተትኩህ ይቅር በለኝ ግን እንደምታስተካክለው አውቃለው
አለውና ቤቱን ሳይነግርው ወደ ቤቱ አደርሰው አዳም ቤቴን እና
መስሪያ ቤቴን እንዴት አወቀ ብሎ ለእራሱ ጠይቆ ለስውየው
ሳይጠይቅ ወረደ ቤቱ በጥድፊያ እንደገባ ቦርሳውን ከፈተው ቦርሳ
ውስጥ በብዙ የተለያዩ ልሙጥ እና ባለ መስመር ሉክ ለሁለት
ታጥፈው በእስቴፕራል ሳይሆን በአርንጓዴ ክር የተሰፋ ደብተር አለ
ሳያነበው እየገላለለጠ ማየት ጀመር የብዙ ስው ፎቶዎች እና
ከፎቶዎች ስር ማብራሪያ ተፅፏል ደብተሩን ከደነው እና ቦርሳ
ውስጥ አንድ ተለቅ ያለ ስአት አገኘ በድጋሜ እጁን ሰደደው
የሆነች እጥፍጥፍ ያለች ወረቀት አገኘ ወረቀቱ እንዲህ ይላል....
ይቀጥላል..
••●◉Join us share
@Hayitiye
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 5
✍ እድል
.
.
.
ይኸውልሽ ከሳመችኝ በኋላ ምንም ያልኳት ነገር የለም ፈዝዤ ነበር
የሳመችውን ጉንጬን ይዤ የቀረውት እሷ ፊት ላይ ግን ስስመኝ
በመፍዘዜ ምክንያት ሳቅ ይታይባታል ደግማ ጠጋ ብላ "ምነው
ችግር አለ?" አለችኝ አይ ስላት እና "ፈዘካል እኮ
እሺ በቃ ቻው እንገናኛለን በቀጣይ ለእኔም ግጥም ገጥመክ ይዘክ
ና እሺ" ስትለኝ "እሺ መቼ አልኳት".... "ነገ ማታ 12 ስአት ላይ እዚህ
አለችኝና አትፍዘዝ ስስምክ ስትፈዝ እኮ ሳቄም መጥቶ ድንጋጤም
ያዘኝ" ብላ በድጋሚ ግንባሬን ግጥም አድርጋ ስማኝ ሄደች ከሄደች
በሆላ ድንጋጤዬ አለቀቀኝም ዲና በወሬው መሀል ገባችና እንዴት
ግን" አለች ምን እንዴት አለው ያኔ ጓደኛዬ የለከፋት ለት ገና ሳያት
እኮ ነው ልቤን የስርቀችው ኡፍፍፍፍፍፍ በጣም ደስስስስ እሚል
ስሜት ነበር የተሰማኝ የምር ከሳመችኝ በኋላ ያለውን ጊዜ ዝም
ብዬ ስስቅ አሳለፍኩት ነገ በድጋሜ ተገናኝተን ግንባሬን እና
ጉንጭኤን በደንብ እንድትስመኝ ምርጥ ግጥም ልገጥምላት ወስኩኝ
ዲና አፉ ውስጥ ልትገባ ምንም አልቀራትም እሱም በጣም
በተመስጦ ነበር ሲነግራት የነበርው ጉሮሮውን ጠራርጎ ሊያወራ
ሲል "ንገረኛ" አለችው እሱም ልነግሽ እኮ ነው ከዛ ማታ ለእሷ
ግጥም ስፅፍ አመሸው ዲናም ፈጠን ብላ ምን የሚል እስቲ
በልልኝ ስትል ኧረ ተረጋጊ አላትና ወደወሬው ተመለሰ ማታ
ግጥም ገጥሜላት ግጥሙን12 ሰአት ደርሶ እስከማነብላት
ቸኮልኩኝ በጣምም ጓጓውኝ
ሰአተለ እንደምንም ደረሰልኝ እና 11:40 ላይ የግራሩ ዛፍ
ስር ቁጭ ብዬ
ጠበኳት 11:50 ሆነ ሰአቱ አልሄድ አለ በመከራ 12 ስአት ሞላልኝ
አልመጣችም ባትመጭም ቅጠሪኝ አለ ገጣሚው ባትመጣም ስለ
ቀጠርችኝ ደስስ
ብሎኝ ነበር ከባትመጭም ቅጠሪኝ ግጥም ውስጥ
የነፍስ ጥርን ሞት አይቶ እንደመሳቀቅ
በቆመ አውሎ ንፍስ ተመቶ እንደመውደቅ
የሚወዱትን ሰው ቀጥሮ እንደመጠበቅ
የሚያሳቅቅ ነበር እንደሌለ የገጠመው ግጥም ውል አለብኝ
ትዝዝም አለኝ 12:15ሲል ሄዋኔ ጥቁር የቱታ ሱሪ ሌዘር ጃኬት
አድርጋ እስኒከር ጫማ ተጫምታ ስትመጣ አየዋት ልቤ እሷ
በቀረበችኝ ቁጥር እርምጃዋን ባፈጠነችው ቁጥር የእኔም የልብ
ምት ይፈጥን ጀመር በስተመጨርሻ እኔ ካለሁበት ደረሰች እና
ጉንጬን ስማኝ ቀልጠፍ ብል ተቀመጠች እንደተቀመጠች እጇን
ወደፊቴ ዘርጋችው አፍጠጠች አፈጠጥኩባት እ ምን ታፈጥብኛለክ
ልትለኝ ነው እንዴ በል
ግጥሜን ስጠኝ እንደውም አንተ እራስክ አንብብልኝ አለችኝ ከዛ
እኔም ድምፄን ለሰለስ አርጌ ግጥሙን ማንበብ ጀመርኩ ግጥሙ
እንዲህ ይላል ዲና በጣምም ተመስጣ እሺ በልልኝ አለችው
ከግራሩ ዛፍ ስር
ከግራሩ ዛፍ ስር ልክ እንደለመድኩት
እያነበብኩ ሳለ ግጥም የገጠምኩት
በጩከት ውስጥ እና በመመስጥ ውስጥ
አንድ ድምፅ ተስማኝ የሚመስጥ
ድንገት ከየት መጣ ብዬ ደነገጥኩኝ
አንድ ልጅ ነበርች ግጥሜን ስቀኝ
ከተመጥኩበት ከግራሩ ዛፍስር
ከጀመርዬ ሆና ቃላቶችን ሳስር
ልጅት ብቃቴ እጅክ ተደምማ
ጉንጭና ግንባሬን በአድናቆት ስማ
ለኔም ግጠምኝ ብላ ብጠይቀኝ
12 ሰአት ላይ ልጅት ቀጠርችኝ
ትእዛዝንን አክብሬ ይህው ግጥም ገጠምኩኝ
የሚል ነበር እና ልክ ግጥሙን አንብቤ ሰጨርስ አመሰግናለው የኔ
ውድ ብላ ሁለቱን ጉንጮቼን እና ግንባሬን ሳመችኝ ዲናም ወሬውን
እኔ እምለው ሄዋን ግን እንደተርዳዋት በጣም ሰውን መሳም
ትወዳለች አለች አዳምም ቀጠል አድርጓ ሄዋኔ መሳም ትወዳለች
አዎ መሳም ትወዳለች አለ እና ዝም አለ ዲና እሺ ቀጥላ አለችው
አዳምም ወሬውን ቀጠለ ከዛ በነጋታው ጠዋት ክላስ ልገባ ሰል
ሄዋንን ከብዙ ወንዶች ጋር ቆማ ስትሳሳቅ አየዋት ቅናት ቢጤ
ጫር አረገኝ ቆሜ የሚሆነውን ማየት
ጀመርኩ ትንሽ ካወሩ በኋላ ሄዋኔ ሁሉንም እየዞረች ግንባራቸውን
ሰማቸው ሄደች እራቅ ካለች በኋላም እጆን እያውለበለበች
ተሰናብታቸው ወጣች ልከተላት ስለፈለኩኝ
መከተል ጀመርኩኝ። አዳም ዲናን እንደደከማት እያስተዋለ ውይ
በጣም ደከመሽ አይደል እንቅልፍሽ መጥቷል ታስታውቄያለሽ በቃ
ተኚ ነገ እነግርሻለው አላት አይ ንገርኝ አለችና ድርቅ አለች ግን
ደሞ እሱም ድርቅ ብሎ እንድትተኛ ነገራት እሺ ብላ ካመጣችው
አነስተኛ ኩኪስ ውሀ እና ጋቢ ሰጠችው እሱም ወደ ሄዋን ሄዶ
ሄዋንን በተመስጦ እና በፍቅር አይን ማየት ጀመር
ይቀጥላል...
••●◉Join us share
@Hayitiye
@Hayitiye
💁♂ዛሬም መጠጥ ቤት ነኝ።🍺🍻
በግራ እጄ
አረቄ ይዣለወ🥃
በቀኝእጄ ደሞ
ሲጋራ ይዣለው🚬🚬🚭
እኔ መስከርን አልጠላውም
👉 @Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
ክፍል 4
✍ እድል
.
.
.
አዳም ዶክተሩ ጋር ከመሄዱ በፊት ሄዋን ስትነቃ አበባ መስሎ እሷ
ፊት ለመቅርብ በማስብ እንዳልተጨፈጨፈ ደን የተጠቀጠቀውን
ፂሙን ሊስተካከለው ፀጉሩንም በወጉ ለማድርግ በማስብ ሄዋንን
አይቶ ባይጠግባትም ብዙ ደቂቃ አይቷት ወደ ፀጉር ቤት ከነፈ
በደስታ በሳቂታ ፊት እየተራመደ ከሆስፒታሉ ትንሽ እራቅ ብሎ
ወደሚገኘው ፀጉር ቤት ገባ እና ቁጭ አለ ወረፋው እስኪደርስ
የእሱን እና የሄዋንን
ፎቶዎች እያየ ውስጡ በሀሴት ሞላ ፀጉር ቤት የተከፈተው ሬዲዮ
ላይ አንድ ታዋቂ ዘፋኝ ቃለ ምልልስ እየተደርገለት ነው ስልኩን
በኪሱ ከቶ ቃለ ምልልሱን መስማት ጀመር ጠያቂው ለታዋቂው
ዘፋኝ የሚጠላው ነገርን ጠየቀው ያው ሁሉም የሚለው ግን
የሆነውን ውሽት እንደሚጠላ መለስለት በስተመጨሻ ማስተላለፍ
የምትፍልገው ነገር ካለክ እና አንድ ዘፈን ለአድማጮቻችን
ብታስማልን የማስተላልፈው ነገር እንኳን የለም ዘፈን ደሞ ከእኔ
ሳይሆን ከሌላ ሰው ዘፈን ላንጎራጉር
ታመሽ ታምሜያለው
ስደኝም እንደዛው
ስትሞች ግን አልሞትም
እኔ ምን በወጣኝ
ብሎ እንጉርጉሮውን ገታ። አዳም በጣምም ተናደደ ብሽቅ አለ በገነ... ምክንያቱ ግልፅ ነው የመጀመሪያው ሰው እንዴት
የሚያስተላልፈው መልክት አይኖርም በሚለው ሲሆን ሌላው እና
ዋነኛው ደሞ ለእሱ አይነት አፍቃሪ ልብ ለሚያፈቅራት ሴት
ላበደው ለአዳም
ታመሽ ታምሜያለው
ስድኝም እንደዛው
ስትሞች ግን አልሞትም
እኔ ምን በወጣኝ
የሚለውን ቃል መስማት ያማል አይምሮን አልፎ ውስጥ ድረስ
ልብ ድረስ ገብቶ ያደማል። ፕሮግራም አቅራቢዋም ለመስናበቻ
የሚሆን ዘፈን ብላ
አሜን አሜን አሜንንንን
ልበል እስቲ አሜንንን
የሚለውን የኑዋይ ደበበን ዘፈን የፕሮግራሙ መዝጊያ አረገችው
ቢያንስ ጋባዥዋ በጋበዘችው ዘፍን ንዴቱ ጠፋ ወደ ኋላ ከሄዋን ጋር
ወዳሳለፈው የፍቅር ጊዜ ማስብ ጀመር ከ አመት በፊት ዩንቨርሲቲ
እያሉ ልደቷን ስታከብር ይህንን ዘፈን በማራኪ ድምፁ በ ዩንቨርስቲ
የሙዚቃ ባንድ አጋዥነት በምርጥ እና ጊቢውን ባነጋገረ እና
ባስደመመ መልኩ ዘፍኖ ሰርፕራይዝ አርጓት ነበር
ከዛም ልደቷን ግቢ አክብረው ወጣ ብለው ሲዝናኑ በድንገት
ተንበርክኮ በደስታ የታገቢኛለሽ ጥያቄ አቅርቦላት እሷም ተንበርክካ ተያይዘው
ተላቅስው ጥያቄውን የተቀበለችበትን ጊዜ ከዛ ደሞ እሷም
በተራዋ
አንነጋገርም ጨዋታው ይቅርብኝ
ቁጭ በል ከጎኔ ያይን እራብ አለብኝ
የሚለውን የኩኩ ሰብስቤ ዘፈን ከዘፈኑ ጋር አብራ እየዘፈነች
በፍቅር አይን እንዴት ታየው እንደነበር አስታወስ እና ፍገግም ሳቅ
ሳቅ እያለ ከዋዠቀበት ሀሳብ ነቃ ያነቃው የፀጉር ቆራጩ ድምፅ
ነበር አዳም ደነገጠ ብዙ ጊዜ ጠርቶት እንዳልስማው ተርዳ
እንደማፈር ብሎ ቀና ሲል ና ወርፋክ ደርሷል ብሎ ፀጉር
መታጠቢያ መቀመጫው ላይ እንዲቁመጥ ጋበዘው አዳምም
ቀልጠፍ ብሎ ተቀመጠ ለ2 ወራት ውሀ ያልነካውን ፀጉሩን
አጠበው ለእሱ ፊት የሚሆን ቁርጥ አስመርጦ ተቆርጦ ለ ፁጉር
ቆራጩ ከምስጋና ጋር ክፍያውን እስከ ጉርሻው ሞላ አድርጎ ሰጠብ
ፀጉር ቆራጩም ጎንበስ ቀና ብሎ አመስግኖ አዳምም
በአቆራርጡ ቆራጩም በጉርሻው ተደስተው ተመሰጋግነው ተለያዩ
አዳም
በጣም ሽበላ ሆኖል ያው ከ አንገቱ በላይ ቢሆንም ። አንድ ነገር
እንደሚቀርው አሰበ ልብስ እና ጫማ ልግዛ ወይስ ሄዋኔ
የምትወዳቸውን ልብስ እና ጫማ ላድርግ ብሎ ከራሱ ጋር ትንሽ
ግብግብ ከፈጠር በኋላ በስተመጨርሻ ሄዋኑ የእሱ ውድ
የምትወዳቸውን ለማድርግ ወሰነ ይህን እያስበ ሆስቲታል ደርሰ
ዶክተሩ
ና ያሉበት ስአት ስለደርስ ወደ ዶክተሩ ቢሮ አመራ ሲደርስ አንኳኳ
ኳኳኳኳኳኳኳኳ
ዶክተር "ማነው? ይግብ" አለ "እኔ ነኝ" አለ አዳም ዳክተሩም "ኦኦኦኦኦኦ አዳም ና
ግባ እባክህ
ቁጭ በል አዳም በጣም አምሮብካል ደሞ ዛሬ አሉ አዳምም ያው
ለእሷ ብዬ ነው አለ አዳም ልብ እንደ ከበሮ ለጉድ መምታት ጀመር
አዳም ጉሮሮውን ጠራርጎ
ለምን ነበር የፈለጉኝ ዶክተሩ ርዥምምምም ትንፋሽ ተንፍሰው
ትንፍሻቸውን መልስው ከስበሰብ በኋላ ንግግራቸው እንዲ ሲሉ
ጀመሩ እየውልክ አዳም አሁን በምነግርክ
ነገር በጭራሽ እንዳታዝን እንደውም ጠንካራ ሁን የአዳም የልብ
ምት በጣምም ፍጠነ ልብ በአፉ ሊወጣ ደርሰ እሺ ዶክተር ቀጥሉ
እኛ ሄዋን ብለው አሁንም ረጅም
ትንፋሽ ወስዱ አዳም ሊያብድ ምንም አለቀርውም እና ምን ዶክተር
ንገሩኛ እእእእ
ዶክተር ወሬያቸውን ቀጠሉ ሄዋንንንን አዳም ሰፍ ብሎ ሄዋን ምን
ብሎ አፈጠጠባቸው ሄዋን በደርስባት የመኪና አደጋ ምክንያት
ብለው አሁንም ዝም አሉ
አዳም እራሱን መቆጣጠር አቃተው እኔ ላብድ ነው በሉ ይናገሩ
ምንድነው መሄድ አችልም ሊሉኝ ነው ወይስ ጭንቅላቷ ውስጥ
ደም ፈሷል ስለዚህ አተርፍም የምታያት ዛሬ ማታ ብቻ ነው ልትሉኝ
ነው አለ ዶክተር አይ እሱ አደለም እንደዛ አደለም ሄዋንንን
የምታያት ነገ ነው መዳኒቷን አስተካክዬላት ነገ እንድነቃ
አርጊዋለው ግን ሄዋን ጭንቅላቷ በሀይል ስለተመታ ብሎ ዶክተሩ
ወሬውን ሳይጨርሱ ይህው ብያለው በቃ ትሞታለች ልትለኝ ነው
አደል አለ በለሆሳስ ዶክተርም አይ አይ ሄዋን አልዛይመር ወይም
የመርሳት በሽታ ይዞታል ሰለዚህ
አንተንም ሆነ በዙሪያዋ ያሉትን ነገሮች አታስታውስም አለው አዳም
ስቅስቅ ብሎ አለቀስ እናትዬ መከራሽ በዛ የኔ ህይወት አያለ
ተንስቀስቀ ዶክተሩ ከተቀመጠበት እየተነሳ አዳም ላንተ ከባድ
እንደሚሆን አውቃለው ግን ቆፍጠን ማለት አለብክ አለው አዳምም
እንዴት እንዴትትትት አለ በመከራ ዶክተሩ አዳምን አረጋጋው
ከረዳሃት ወደ ድሮ አቆሟ እንደምትመስል ነገረው እና ነገ ማታ
ስትነቃ ቁጥብነት እና ስርአት ባለው መልኩ እንዲያናግራት
አስጠነቀቀው አዳም ምድር የተደፍበት መሰለው ከዶክተሩ ቢሮ
ውልቅ ብሎ ወጣ
ቤተ ክርስቲያን ሄደ እና ሄዋንን ትውስታዋን እንዲመልስ
የሚያደርግ ትግስት እንዲስጠው እና እሷንም እንዲያኖርለት
ለመነው ተማፀነውም ፀሎቱን ሲጨርስ
ወደ ሄዋን ሄደ አያት ከዛም ኮሊደሩ ጥግ ባለ አግዳሚ ወንበር ላይ
ተኝቶ እንቅልፍ ጣለው የነቃው ዲና መጥታ ስትቀስቅስው ነው
ማታ 2 ስአት ላይ በርግጎ ሲነሳ ዲና ፈገግ ብላ አይዞን አለችው
ካጠገብ ተቀመጠች እና ዛሬ እዚህ ነው የማድርው ተረኛ ነሽ
እንዴ አይ አይ እያየከኝ በልብስ ነኝ እኮ እና አላት እናማ
በመጀመሪያ ዛሬ አምሮቦካል መቼም ለሄዋን ነው እንዲ መዋብክ
ሁለተኛ ደሞ በጣም አዝነካል ከቅድሙ ምን ሆነክ ነው ሶስተኛ
ደሞ ከሄዋን ጋር እንዴት እንደተዋወቃቹ ንገርኝ እሱም ቀጠለ
በመጀመሪያ አመስግናለው ሁለተኛ የከፋኝ ደሞ ብሎ እንባውን
አረገፍው ዲና ደነገጠች ምምምምም ምን ሆነክ ነው አለችው
ሁለተኛው ደሞ እናትዬ የኔ ህይወት ቢደርስባት አደጋ ምክንያት
ከአደጋው በኋላም ሆነ በፊት ያለውን ነገር አታስታውስም አለኝ
ዶክተሩ ሶስተኛው ጥያቄሽ ምን ነበር አዎ ትዝ አለኝ ከሄዋኔ ጋር
በደንብ የተዋወቅነው ዩንቨርስቲ ጊቢ ውስጥ ያሉ ልጆች ከጊቢ
ውጪ ድግስ ቢጤ አዘጋጅተው ነበር እና ጓደኛቼን እኔ
እንደማልሄድ ነግሬያቸው ጊቢ ቀረው ግጥም መፃፍ በጣም እወድ
ማጣት: መሸነፍ እና መውደቅ ብዙ እውነትነት የሌላቸው ስሜቶች ናቸው።
የተመኘነውን የማናገኘው ጊዜው ስላልደረሰ አልያም የተሻለ ነገር ስለታሰበልን ወይም ደግሞ ምኞታችን በመልካም መሰረት ላይ ስላልተመሰረተ ነው።
መሸነፍና መውደቅም እኛ የውሸት ማንነታችን ሲነካ የሚሰሙን ስሜቶች ናቸው።
የሚያጋጥሙን እንቅፋቶች መንገዳችንን አስተካክለን እንድንራመድ የሚያግዙን አጋጣሚዎች ናቸው።
እያንዳንዱ ስሕተት ከዚህ የተሻለ ማሰብ እንደምንችል የሚያስታውሰን ቅጣት ነው።
መልካም ምሽት!!
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°°
°°°°°°°\\\\°°°°°°°°°°°°\\\°°°
@Hayitiye
@Hayitiye
➭➭➭@Hayitiye
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
እውነተኛ አፍቃሪ መሆኔን ላስረዳ
ወረቀት ብዕሬን ይዤ ስሰናዳ
ሆሄያት ፊደሎች አቀረቀሩብኝ
ለፍቅርሽ የሚሆን ቃል የለኝም አሉኝ።
Join 👇👇👇
@Hayitiye
😘አለሜ ነሽ😘
🔥ክፍል 3
✍ እድል
.
.
.
ጩኸቱን ሲጨርስ ረዥም ሳቅ ሳቀ። በረዥሙ ተንፍሶ ወደ ቀልቡ ተመለሰ ። ዲና አሁን ላይ ይህቺ ሴት ማን እንደሆነች ልትጠይቀው ወሰነች ። ጉሮሮዋን
ከጠራረገች በኋላ" እእእእእ እስቲ ስለ ሄዋን ንገረኝ አዳም" አለችው
" ምን ልንገርሽ" አላት
"ማለቴ ያው እንዴት እንደተዋወቃችሁ... ፍቅር እንዴት
እንደጀመራችሁ እና እንዴት እንደዚህ ልታፈቅራት እንደቻልክ" ዲና ይህንን ብላ
ቁልቁል አዳምን አየችው ።
ፊቱ በፈገግታ በርቷል ። ልክ እንደ ነፀብራቅ ፈክቷል ።
ባለፈው ፈገግ ካለው ይልቅ ሲስቅ በጣም
እንደሚያምር አወቀች ።
" ኡፍፍፍፍ እሷን ያወቅኩበትን ቀን ላንዴም
አልዘነጋውም ። ከ5 አመት በፊት የካምፓስ ተማሪ ነበርኩ ። 6 ጓደኞች ነበሩኝ ። ከእኔ
ጋር 7 ማለት ነው ። የሁለተኛ አመት ተማሪ ነበርን ። ከእነሱ በጣም የተለየ ፀባይ ነበረኝ ። ማለቴ እነሱ ሴት ማተራመስ እና መላከፍ በጣም ይወዳሉ ። ወሬያቸው ሁሉ
ሰለ ሴት ነው ። እኔ ደግሞ ሀሳቤ ሁሉ መፅሀፎቼ ላይ ነው ። ፀጥ ያለ ቦታ ይመቸኛል ። ግን ጓደኞቼ አብሬያቸው እንድሆን ሲጠይቁኝ እንቢ ማለት አልችልም ። ሄዋኔን
ያየኋት የሁለተኛ አመት ትምህርት ለመጀመር ተማሪው ከቤቱ ወደግቢ
የሚጎርፍበት ሰአት ላይ ነበር ። ጓደኞቼ እንደለመዱት ለመላከፍ ወደሚመቻቸው
ቦታ ሄደው ተደላድለው ተቀምጠው ነበር ። ያኔ እኔም ነበርኩኝ ። አንድ መካከለኛ
ቁመት ያላት በጣም ቀይ እና ፀጉሯ በጀርባዋ የወርደ ግን በቅጡ ያልተያዘ ፀጉር ያላት...የወንድ የሚመስል አለባበስ ለብሳ በአጠገባችን ልታልፍ
ስትል አንዱ ጓደኛዬ "ኧረ ይቺ ልጅ ፍሬሽ ናት መስለኝ አይቼያት አላዉቅም ። እስቲ
ላስደስታት" አለና ድምፁን ሰልከክ አርጎ "እሙዬ ሻንጣውን ላግዝሽ " አላት
እሷም ፈገግ ብላ "አመሰግናለው ወንድሜ አጋዥ አያስፍልግም" አለችው ቀጠል አድርጎ "ወይም አንቺን ተሽክሜሽ ልግባ " አላት...
ጥቂት ሄድ ካለች በኋላ ፊቷን
ፍክት አድርጋ ፈገግ እያለች "አንዴ እስኪ ና " አለችው...
ደስ እያለዉ ወደ እሷ
ቀረበ ። ሌላኛው ጓደኛችን "ኧረ ንቀት እራስሽ አትመጪም እንዴ..ምንሼ ነው" አላት...
እሷም ዝም ብላ ያኛውን ጎደኛችንን በአይኖቾ አታላ አጠገቧ አመጣችው ። ከዛም
በጥፊ ጭንቅላቱን አዞረችበት ። ሁሉም ደነገጡ ። እኔ እራሴም ደነገጥኩ ። 'ትስማኛለህ '
አለች እየጮኸች...
" አንተ ከንቱ.. የማትርባ አፍክህ በከፈትክ ቁጥር ባዶነትህን
ነው የሚያሳየው ። ዳግም እንዲህ ብታደርግ አንላቀቅም ።" ብላው ሄደች... ስታወራ...ጩከቷ አለም ላይ ያለ ሰዉ ድምፅ አዋጥቶ ለእሷ የተሰጣት ይመስላል ።
በጣም በጩከት ነው የምታወራው ። ልጅቷ ከሄደች በኋላ ጓደኛችን በድንጋጤ
ደርቆ ጉንጩን እየሸፈነ መጣ ።
ምን ብለሃት ነው ስንለው...' ለምንድነው
ወንድሜ የምትይኝ ..ይልቅ ማታ አልጋ ይዘን ለምን አናወራም ' ነበር ያልኳት አለ ።
ሁላችንም በጣም ሳቅንበት ። ይቺ ሴት ሄዋን ነበረች ። ሁሉም ሴት
ሲለከፉ እያፈሩ እና እየተሽኮርመሙ ሲሄዱ እራስዋን ያላስበገርችው ሄዋን ናት ።
ሄዋን ልጁን መታው ከመሄዷ በፊት አንድ ቃል ተናግራለች ። "እኔ ሄዋን ነኝ እሺ
የምሽኮርመምልህ ወይም የምፈራህ እንዳይመስልህ ። በጭራሽ እንዳትሳሳት.. ቀና ብለህ እንዳታየኝ ። ተግባባን !! ብላ አስጠንቅቃዉ ነበር ።
በጣም ገርመችኝ... ወኔዋ በእራስ
መተማመኗ እና ሁሉ ነገሯ አስገረመኝ ። ለፍቅር ያጨኋት ማለቴ
በአይነ ህሊናዬ የሳልኳት አይነት ሰው ሳትሆን ግን ልቤን እና ሁሉ ነገሬን በአንድ
ጊዜ ተቆጣጠረችው ።" አለ አዳም ። ፈገግ እያለ ነበር የሚያወራው ።
" በቃ የቀረውን ደግሞ
ሌላ ጊዜ" አላት የእጅ ሰአቱን እየተመለከተ ።
" ኧር አለስማህም... ልቤን
እንደዚህ አንጠልጥለኸዉ ወልፈት የለም ። በቃ እንደውም ዛሬ ሆስፒታል ነው የማድርው።" አለችው ።
አዳም በአግራሞት እያያት "ዛሬ እረፍት አደለሽ እንዴ " አላት
"አዎ ነኝ ግን የእረፍት ጊዜዬን ጣፋጭ የፍቅር ታሪክ በመስማት ላሳልፍው
ወስኛለሁ" አለችው ።
የመድሀኒት መደብሩ ጋር ደርሱና መድሀኒቱን ገዙ ። መድሀኒቱ በጣም ውድ ነው ። ቢሆንም ግን የገንዘብ ችግር የለበትም ። ገዛና ወደ ሀኪም ቤቱ ተመለሱ ።
ከመድሀኒት ቤቱ እስከ ሆስፒታሉ ምንም ነገር አላወሩም ነበር ። ሆስፒታሉ በር
ላይ ሲደርሱ
ዲና "በቃ አሁን ቤቴ ሄጄ እርፍት ላድርግ..አመሻሹ ላይ መጥቼ
የጀመርክልኝን ትጨርስዋለህ። እንገናኛለን" ብላዉ ተሰናበተችዉ ። ባይኑ ሽኛትና ሄዋን ወደተኛችበት ክፍል አመራ ። ሄዋን አሁንም ኮማ ውስጥ ናት ። ግን ደግሞ
ልትነቃ ትንሽ ለሊት ማታ እና ቀን ወይም ሰአት ነው የቀረው ።
"ሄዋኔ " አለ በለሆሳስ
ደምፅ ...
"አንቺን አለማፍቀር ይቻላል...? እእ አንቺን አለመውደድስ ...? አይ በጭራሽ
አይቻልም ። አዎ አይቻልም.. የኔ አስተዋይ .. የእኔ ጩኸታም.. የኔ አኩራፊ ንቂ ...ንቂልኝ ።
ሄዋኔ ሄዋኔ አንቺ ነሽ ሰላሜ
እናቴ ልበልሽ በቃ ነሽ አለሜ
የፍቅርሽ ወላፈን ከአድማስ ባሻገር
ልቤን አሳመመሙ ለኔ ሳይናገር ።
ኮማ ውስጥ ያለሽው ፍቅሬ ተይ ንቂልኝ
ጨርቄን ጥዬ ሳላብድ ባክሽ ድርሽልኝ ።
እያለ አጠር ያለችውን የግሉን ግጥም በውስጡ አዥጎረጎርው ።
በተመስጦ
እሷን በማየት ግጥሙን ቀጠለዉ...
ትነቂያለሽ ብዬ በተስፋ ልጠብቅ
አትነቂም ብሎ ውስጤ እንዳይጨነቅ።
እያለ በሀዘን ፊት ያያት ጀመር ።
"ትነቂያለሽ ውዴ" አለ በለሆሳስ....
እዚህ ሀስብ ውስጥ ሆኖ ጠና ያለው ዶክተር ትካሻውን ለመጣራት እና
ለማፅናናት ያክል መታ አደረገው።
"ከአንድ ሰአት በኋላ ቢሮ ና" ብለውት ሄዱ...
"ምን ሊሉኝ ነው...? አትተርፍም ትሞታለች ሊሉኝ ነው...? ለምን እንዲህ አዘኑ..? እእእ "
ይቀጥላል....
━━━━━━━✦✿✦━━━━━━━
••●◉Join us share
🌹 @Hayitiye 🦋
🌹 @Hayitiye 🦋
Amlak degu laysanew konjinash 🙏
Tnish kenes argot wubetish
Mognnete ygermegna tselyalew
Sew balayat ylal lbe emegnalew
@Hayitiye ✨✨✨
በቆጅና በለህ ውበት ዝና አሸነፍከኝ አንተ የልቤ ጀግና❤️ንብረት የለኝ የራሴ የምለውእንካ ልቤን ያለኝ እሱ ነው ትንሽ ቤቴ🛖🏡 የምናርባት ባዶም ብቶን ግን ፍቅርማ አላት🥰🥰😍
@Hayitiye ✨✨✨✨
