cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

AA Airport Customs branch office /አ.አ ኤርፖርት ጉምሩክ

ራዕይ፡- "በ2022 በአገራችን ደረጃዉን የጠበቀ ዘመናዊ የጉምሩክ አስተዳደር ተገንብቶ ማየት"

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
3 293
مشترکین
+424 ساعت
+97 روز
+2930 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

የመንገደኞች የጉምሩክ ሥነ-ሥርአት አፈጻጸም  ለዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት በሕግ የተሰጠ መብት እንደተጠበቀ ሆኖ ማንኛውም ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ ወይም ከኢትዮጵያ የሚወጣ መንገደኛ በቀይ ወይም በአረንጓዴ ማለፊያ በመጠቀም ስለያዘው ማንኛውም ዕቃ ዲክሌር ማድረግ አለበት፡፡  ማንኛውም መንገደኛ የንግድ መጠን ያለው ዕቃ ወይም ገደብ የተደረገበት ዕቃ ወይም የተከለከለ ዕቃ ይዞ የአረንጓዴ ማለፊያ በመጠቀም ማለፍ የለበትም፡፡  በቀይ ማለፊያ ተጠቅሞ ዲክሌር ያደረገ መንገደኛ ሻንጣውን ለጉምሩክ ሹም በማቅረብ ማስፈተሽ ይኖርበታል፣  ከላይ የተቀመጠዉ እንደተጠበቀ ሆኖ ይህ ህግ ከትራንዚት ክልል በሚወጡ እና ወደ ትራንዚት ክልል በሚገቡ የትራንዚት መንገደኞች ላይም ተፈጻሚ ይሆናል፡፡  በአረንጓዴ ማለፊያ የተጠቀመ መንገደኛ የተከለከለ፣ ገደብ የተደረገበት ወይም ቀረጥና ታክስ የሚከፈልበት ዕቃ ይዟል ብሎ የጠረጠረ የጉምሩክ ሹም መንገደኛውን የመፈተሸ ስልጣን አለው፣ የደንበኞች ትምህርት ቡድን ሀምሌ 05/2016 ምንጭ፡ መመሪያ ቁጥር 923/2014
نمایش همه...
👍 2
መንገደኛው ወደ ውጭ አገር ሲጓዝ የሚፈቀድለት የውጭ ሀገር ገንዘብ ሀ. በኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ የሆነ ግለሰብ የውጭ ምንዛሬ ይዞ ከአገር መውጣት የሚችለው ከባንክ የገዛ ለመሆኑ 30 ቀናት ያላለፈው ማስረጃ ሲያቀርብ ብቻ መሆን አለበት፡፡ ለ. ትውልደ ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ አገር ዜጋ ከአስር ሺ ዶላር በላይ ወይም ተመጣጣኝ የውጭ አገር ገንዘብ ይዞ ወደ አገር የገባ ከሆነ የቪዛ ቆይታው ሳይጠናቀቅ አስመዝግቦ የገባበትን ዲክላራሲዮን በማቅረብ ከአገር መውጣት ይችላል፡፡ የደንበኞች ትምህርት ቡድን ሀምሌ 05/2016 ምንጭ፡ መመሪያ ቁጥር 87/2016
نمایش همه...
👍 1
ከጎረቤት አገር ወደ ኢትዮጵያን በየብስ የሚመጣ ሰው የሚፈቀድላቸው የዉጭ ምንዛሬ መጠን ከጎረቤት አገር የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጦ በየብስ የሚመጣ ሰዉ የያዘዉን ከ500.00 /አምስት መቶ/ የአሜሪካ ዶላር የሚበልጥ ወይም ተመጣጣኝ ሌላ በብሔረዊ ባንክ የማይመነዘር የዉጭ አገር ገንዘብ በኢትዮጵያ ድንበር በሚገኝ የጉምሩክ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት (ጣቢያ) አስመዝግቦ ወደ ኢትዮጵያ ይዞ መግባትና ገንዘቡንም ያስመዘገበበትን የጉምሩክ ሰነድ ካቀረበ ወደ ውጭ ይዞ መውጣት ይችላል፡፡ የደንበኞች ትምህርት ቡድን ሀምሌ 05/2016 ምንጭ፡ መመሪያ ቁጥር 87/2016
نمایش همه...
👍 2
መንገደኞች ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ እና ሲወጡ የሚፈቀድላቸው የኢትዮጵያ ብር መጠን፡  ማንኛውም መንገደኛ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ እና ከኢትዮጵያ ሲወጣ እስከ 3,000.00 /ሶስት ሺህ/ የኢትዮጵያ ብር ይዞ መግባት ወይም መውጣት ይችላል፡፡  ሆኖም ወደ ጅቡቲ የሚጓዝ መንገደኛ ደግሞ እስከ 10,000 /አስር ሺህ / የኢትዮጵያ ብር ይፈቀዳል፡፡ መንገደኞች ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የሚፈቀድላቸው የዉጭ ምንዛሬ መጠን  ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ለሆነ መንገደኛ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ እስከ 4,000 (አራት ሺ) የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ የሌላ አገር ገንዘብ ይዞ መግባት የሚፈቀድለት ሲሆን ከዚያ በላይ ከያዘ ለኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በማሳወቅ ማስመዝገብ ይኖርበታል፡፡  ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ያልሆነ ወይም የዉጭ አገር ዜግነት ያለዉ ኢትዮጰያዊ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ እስከ 10,000.00 (አስር ሺህ) የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ የሌላ አገር ገንዘብ ይዞ መግባት የሚፈቀድለት ሲሆን ከዚያ በላይ ከያዘ ለኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በማሳወቅ ማስመዝገብ ይኖርበታል፡፡ የደንበኞች ትምህርት ቡድን ሀምሌ 05/2016 ምንጭ፡ መመሪያ ቁጥር 87/2016
نمایش همه...
👍 6👎 1
መንገደኞች ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ የሚፈቀድላቸው የዉጭ ምንዛሬ መጠን ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ለሆነ መንገደኛ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ እስከ 4,000 (አራት ሺ) የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ የሌላ አገር ገንዘብ ይዞ መግባት የሚፈቀድለት ሲሆን ከዚያ በላይ ከያዘ ለኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በማሳወቅ ማስመዝገብ ይኖርበታል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ነዋሪ ያልሆነ ወይም የዉጭ አገር ዜግነት ያለዉ ኢትዮጰያዊ ወደ ኢትዮጵያ ሲገባ እስከ 10,000.00 (አስር ሺህ) የአሜሪካን ዶላር ወይም ተመጣጣኝ የሌላ አገር ገንዘብ ይዞ መግባት የሚፈቀድለት ሲሆን ከዚያ በላይ ከያዘ ለኤርፖርት ጉምሩክ ቅ/ጽ/ቤት በማሳወቅ ማስመዝገብ ይኖርበታል፡፡
نمایش همه...
በገቢ፣ በወጪና ተላላፊ ዕቃዎች ላይ ስለሚደረግ የጉምሩክ ቁጥጥር 1. የሚከተሉት ዕቃዎች በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር ይሆናሉ፡- ➡️ለአገር ውስጥ ፍጆታ ወደ አገር ውስጥ የሚገቡ ዕቃዎች ጉምሩክ ወደብ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ የጉምሩክ ፎርማሊቲ ተከናውኖባቸው እስከሚለቀቁ፣ ➡️ወደ ቦንድድ ጉምሩክ መጋዘን የገቡ ዕቃዎች ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ ለተፈቀደላቸው ዓላማ እስከሚለቀቁ ➡️ወደ ውጭ አገር የሚላኩ ዕቃዎች ወደ ጉምሩክ ወደብ ከገቡበት ጊዜ ጀምሮ የጉምሩክ ፎርማሊቲ ተከናውኖባቸው እስከሚላኩ ➡️ተላላፊ ዕቃዎች እንዲንቀሳቀሱ ከተፈቀደበት ጊዜ ጀምሮ ወደተፈቀደው መድረሻ ቦታ እስከሚደርሱ ድረስ፣ ➡️ባለቤት የሌላቸው፣ የተተው፣ የተወረሱ ወይም በኮንትሮባንድ የተያዙ ዕቃዎች እስከሚወገዱ ድረስ፡፡ 2.ማንኛውም ሰው ከኮሚሽኑ ፈቃድ ሳያገኝ በተራ ቁጥር 1 በተገለፀው መሠረት በጉምሩክ ቁጥጥር ሥር ያሉ ዕቃዎች ወደ ተከማቹበት ሥፍራ መግባት፣ ዕቃዎችን መክፈት ወይም ማናቸውንም ተግባር በዕቃዎቹ ላይ መፈፀም አይችልም፡፡ ደንበኞች ትምህርት ቡድን ሰኔ 20/2016 ዓ.ም ምንጭ፡- የጉምሩክ አዋጅ 859/2006
نمایش همه...
👍 3
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.