ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
رفتن به کانال در Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
نمایش بیشتر637
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1230 روز
آرشیو پست ها
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፮ (16) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ለጻድቁ_ንጉሥ #ለቅዱስ_ላሊበላ_ታላቅ_ወንድም ለሆነው #ለቅዱስ_ገብረ_ማርያም ለዕረፍቱ መታሰቢያ በዓል፣ ጌታችንን ልጅን በሞት እዲወስድለት የለመነው #ለጻድቁ_ንጉሥ_ለቅዱስ_ነዓኩቶ_ለአብ_ለልጁ ለዕረፍት በዓልና ለኢትዮጽያዊው ጻድቅ #ለአቡነ_መልከ_ጼዴቅ_ዘሚዳ ለልደታቸው መታሰቢያ በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ጻድቁ_ንጉሥ_አፄ_ገብረ_ማርያም፦ የላስታ ገሥታት የዘር ሐረጋቸው ከንጉሥ ሰሎሞን ዘር ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ ከ10ኛው እስከ 13ኛው መቶ ክፍለ ዘመን (920-1253 ዓ.ም ገደማ) በላስታ ቡግና ምድር የነገሡ የላስታ ቡግና ተወላጅ የሆኑ የኢትዮጵያ ቅዱሳን ነገሥታት የንግሥናቸው መጠሪያ "የዛጉዌ ሥርወ መንግሥት "ወይም" የላስታ መንግሥት" በመባል ይታወቃል፡፡ ከላስታ(ከዛጉዌ)ነገሥታት መካከል ቅዱስ ይምርሃነ ክርስቶስ፣ ቅዱስ ገብረ ማርያም፣ ቅዱስ ላሊበላና ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ እነዚህ አራቱ ነገሥታት እንደ መልከጼዴቅ(ዘፍ14፥18) ክህነትን ከንግሥና፣ ቅድስናን ከንጽሕና ጋር አንድ አድርገው በመያዝ እግዚአብሔርንም ሰውንም በቅድስናና፡ በንጽሕና አገልግለው አልፈዋል፡፡
❤ ጻድቁ ንጉሥ ቅዱስ ገብረማርያም በሌላኛው ስማቸው ሐርቤይ እየተባሉ የሚጠሩ ሲሆን የቅዱስ ላሊበላ ታላቅ ወንድም ናቸው፡፡ ታላቁን ጻድቅ ንጉሥ ቅዱስ ነዓኵቶ ለአብን ወልደዋል፡፡ አባታቸው ዣን ስዩም 40ዓመት ከነገሡ በኋላ በ76ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ ልጃቸው ገብረ ማርያም ንግሥናውን ተቀብለዋል፡፡ ከእርሳቸው ቀጥሎ ታናሽ ወንድማቸው ቅዱስ ላሊበላ ተወልዶ እንደሚነግስ በትንቢት ተነግሮ፡ ነበር፡፡ ይህን ጊዜ ከላሊበላ ጋር በአባት እንጂ በእናት ይለያዩ ነበርና የበጎ ነገር ጠላት የሆነ ክፉ ሰይጣን የእኅታቸው ክፉ ምክር ተጠቅሞ በወንድማቸው በላሊበላ ላይ በቅናት ክፉ እንዲያስቡ አድርጓቸዋል፡፡ስለ ንግሥናቸው ሲሉ ምንም እንኳን በወንድማቸው ላይ ክፉ አስበው የነበረና በእኅታቸውም ክፉ ምክር መርዝ የሰጡት ቢሆንም በኋላ በክፉ ሀሳባቸው እጅግ ተፀፅተው "አምላኬንም ወንድሜንም አሳዘንኩ" በማለት ወንድማቸውን ይቅርታ በመጠየቅ ላሊበላን አንግሠውት እርሳቸው መንኵሰው ገዳም ገብተዋል፡፡
❤ ቅዱስ ላሊበላ ካለበት አክሱም ድረስ ሄደው በዕንባና በልቅሶ ይቅርታ ጠይቀው ወደ አገራቸው ሮሐ ከተማ ይዘውት በመምጣት መንግሥታቸውን አስረክበውት ነው የመነኑት፡፡ በምንኵስናም ሆነው በታላቅ ተጋድሎ በጾም በጸሎት በመትጋት እግዚአብሔርን እያገለገሉ እያለ ጌታችን ተገልጦላቸው "ክብሩ እንደ መላእክት የሆነ ታላቅ ልጅ ትወልዳለህና ወደቤትህ ተመለስ" ብሎ ከነገራቸው በኋላ ወደቤታቸው ተመልሰው ቅዱስ ነአኵቶ ለአብን ወልደዋል፡፡
❤ ንጉሥ ቅዱስ ገብረ ማርያም በዘመናቸው ከነበሩት ከእስክንድሪያ ሊቀ ጳጳሳት ከአባ ዳንኤል ጋር መልእክት በመላላክ "ከሀገሬ ሊቃውንት መነኰሳት የሕዝቡን ቋንቋ የሚሰሙና የሚያስተምሩ ጳጳስ ይሹሙልን" በማለት ለእስክንድሪያ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ ምንም እንኳን የእስክንድሪያ ሲኖዶስ በወቅቱ ኢትዮጵያ፡ የራሷንልጆች እንድትሾም ስላልፈለጉና በወቅቱ ፈቃደ እግዚአብሔርም ስላልነበረ የቅዱስ ገብረ ማርያምን ጥያቄ ንግሥት ዘውዲቱና ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ድጋሚ በመጠየቅ ፍጻሜውን እንዲያገኝ ቢያደርጉትም መሠረቱን ግን የጣሉት ዐፄ ገብረ ማርያም ናቸው በዘመናቸው ብዙ አብያተ ክርስቲያናትንም ያሠሩ ሲሆን ጊዜ ዕረፍታቸው ሲደርስ ጌታችን ተገልጦላቸው "የእኔን መከራ እያሰብክ ከዓይንህ ዕንባ ሳያቋርጥ በጾም በጸሎት ተወስነህ ስላገለገልኸኝ በአንተ ስም ለተራበ ያበላውን፣ ለተጠማ ያጠጣውን፣ ለታረዘ ያለበሰውን ምሬልሃለሁ" በማለት ትልቅ ቃልኪዳን ሰጥቷቸው በካቲት 16 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፈዋል፡፡ ጻድቁን ንጉሥ ዐፄ ገብረ ማርያምን ሚያዝያ10 ቀን የሚነበበው ስንክሳር በሰፊው ይጠቅሳቸዋል፡፡ ከጻድቁ ከአቡነ ገብረ ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን! ።
✝ ✝ ✝
❤ #ጻድቁ_ንጉሥ_ነአኵቶ_ለአብም፦ እጅግ ጻድቅ ንጉሥ ሲሆን ያሳደገው ቅዱስ ላሊበላ ነው። ከላሊበላ ቀጥሎ በመንገሥ 40ዓመት በቅድስና አገልግሏል። "ነአኵቶ ለአብም" ብሎ ስሙን ያወጣለት መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ዕድሜው ከፍ ሲል ጌታችን ለላሊበላተገልጦለት ሚስት እንዲያጭለት ነግሮት ሚስት የታጨለት ቢሆንም እርሱ ግን እግዚአብሔርን በድንግልና ማገልገል ይፈልግ ነበር ሚስት ካገባም በኋላ ከሚስቱ ጋር ተማክሮ ሁለቱም ድንግልናቸውን ጠብቀው 25ዓመት ሙሉ በትዳር ውስጥ አብረው እየኖሩ ነገር ግን በድንግልና ሆነው ኖረዋል። እንዲህ አይነቱ ቅድስና በምን ዓይነት ቃል ይገለጻል በእውነት!?ከዚያም በኋላ መልአክ ተገልጦ ነአኵቶ ለአብን "በሕግ በንጽሕና የተጋባችሁት ልጅ ልትወልዱ ነው እንጂ ዝም ብላችሁ ልትኖሩ አይደለም" ብሏቸው እነርሱም ፈቃደ እግዚአብሔር ከሆነ ብለው አንድ ቀን ብቻ በግብር ተዋወቁና ልጅ ወለዱ። ልጁም እጅግ የሚያምርና የሚያሳሳ ቢሆንም፡ ንጉሡ ቅዱስ ነአኵቶ ለአብ ግን በእግዚአብሔር መንፈስ የወደፊቱን ያውቅ ነበርና ሱባኤ ገብቶ "በእኔ እግር ተተክቶ ሲነግሥ ፍርድ አጣሞ አንተንም ሰውንም ከሚበድል ይህን ልጄን ቅሰፍልኝና ሄሮድስ ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምርልኝ" በማለት፡ ወደ፡እግዚአብሔር ጸለየ፡፡ እንደ ጸሎቱም ጌታችን የካቲት 16 ቀን ልጁን በሰላም አሳርፎለት ሄሮድስ ካስፈጃቸው ሕፃናት ጋር ደምሮለታል፡፡ ከጻድቁ ንጉሥ ነአኵቶ ለአብ ልጅ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_መልከ_ጼድቅ_ዘሚዳ፦ አባቶቻችንና ወንድሞቻችን እነሆ እነግራችኋለን አባታችን መልከ ጼድቅ አገር ጐጃም ኤናይ በምትባል ቦታ በየካቲት ዐሥራ ስድስት ቀን ተወለደ። ይህ ቅዱስ አባት በተወለደ ጊዜም በአባትና እናቱ ቤት ታላቅ ደስታ ሆነ እግዚአብሔር ለብዙዎች አባት አድርጎ መርጦታልና። ይህም ጻድቅ ከከበሩና ነገሥታት ከሆኑት ወገን ተወለደ ልደቱም እንዲህ ነበር ንጉሥ ዓምደ ጽዮን፣ ምስርነዓዳን ወለደ ምስርነዓዳን በዝራምበሳን ወለደ፣ በዝራምበሳም ፍሬጽዮንን ወለደ፣ ቅዱስ ፍሬጽዮንም መልከጼድቅን ወለደ የእናቱም ስም ቅድስት ዓመተ ማርያም ነው። ከአቡነ መልከ ጼድቅ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። ምንጭ፦ገድለ አቡነ መልከ ጼድቅ የሰኞ።
❤ ከዚህም በኋላ ይቺ ቅድስት ኤልሳቤጥ መጥምቁ ዮሐንስን ፀንሳ ወለጀችው ከሰዎችም የሚደርስባት ሽሙጥ ተወግዶ እጅ ደስ አላት። ሕፃኑም በማሕፀኗ እያለ እመቤታችን ድንግል ማርያም ሰላምታ በሰጠቻት ጊዜ እንዲ ብላ ጮኸች "ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽም ፍሬ ቡሩክ ነው። የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጪ ዘንድ እኔ ምንድን ነኝ እነሆ እንዴት ነሽ ስትይኝ የሰላምታሽን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ልጁ በማሕፀኔ ውስጥ በደስታ ዘለለ (ሰገደ)"።
❤ ከዚህም በኋላ ጌታችንን አየችው በአምላክነቱም አመነች የሚያምኑበትም በመዳናቸው ደስ አላት ዕድሜዋንም በፈጸመች ጊዜ በበረሀ ውስጥ ሳለች የካቲት16 ቀን በሰላም ዐረፈች። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ኤልሳቤጥ ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 16 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ "ሰላም ለኪ መጽሐፈ ሕግ ወኪዳን። አምሳለ ጽሌ ዘዕብን። ለእለ ጸውዑ ስምኪ ውስተ ገጸ ኵሉ መካን። ርኅርኅተ ልብ ለኃጥአን ርኅርኅተ ልብ ለግፉዐዓን። ርኅርኅተ ልብ ለኵሉ ማርያም አማን"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የየካቲት 16።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ዘያነብራ ለመካን ውስተ ቤቱ። ወያስተፌሥሓ ለእመ ውሉድ። ዘያነብራ ለመካን ውስተ ቤቱ። መዝ 112፥9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ1፥5-18።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እስመ ትቤ ለዓለም አሐንጽ ምሕረተ። በሰማይ ፀንዐ ጽድቅከ። ኪዳነ ተካየድኩ ምስለ ኅሩያንየ"። መዝ 88፥2-3። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥1-12፣ 2ኛ ዮሐ 1-8 እና የሐዋ ሥራ 1፥13-15። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥39-57። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ቃል ኪዳን የተቀበለች (የኪዳነ ምሕረት) በዓል፣ የቅድስት ኤልሳቤጥ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፮ (16) ቀን።
❤ እንኳን #አምላክን_ለወለደች_ለእናታችን_ለእመቤታች_ለቅድስት_ድንግል_ማርያም ከተወደደ ልጅዋ #ከጌታችና_ከመድኃኒታች_ከኢየሱስ_ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን ለተቀበለችበት (#ለኪዳነ_ምሕረት) ዓመታዊ በዓልና ለመጥምቀ መለኮት #ለቅዱስ_ዮሐንስ_እናት ለከበረች #ለቅድስት_ኤልሣቤጥ ለዕረፍቷ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ በዚች ዕለት የክርስቲያን ወገኖች ሁሉም #አምላክን_ለወለደች_ለእመቤታችን_ቅድስት_ድንግል_ማርያም በዓልን ያደርጋሉ። በዚች ዕለት መታቢያውን ለሚያደርግ ስሟን ለሚጣራ ለድኆችና ለችግረኞች እስከ ቀዝቃዛ ውኃ ለሚሰጥ የክብር ባለቤት ከሆነ ከተወደደ ልጅዋ ከጌታችና ከመድኃኒታች ኢየሱስ ክርስቶስ የምሕረት ቃል ኪዳንን ተቀብላለችና።
❤ ይህችም የከበረች እመቤታች ልጅዋ ንጹሕ ሥጋዋን ተዋሕዶ ከብቻዋ ኃጢአት በቀር የሰውነትን ሥራ ፈጽሞ ስለእኛ መዳን ወዶ ያደረገውን መከራ ተቀብሎ ሙቶ ተነሥቶ ከዐረገና በአባቱ ዕሪና ከተቀመጠ በኋላ እርሷን እናቱን ማርያምን በደቀ መዝሙሩ ዮሐንስ ዘንድ ትቷት ነበር እነሆ ልጅሽ እርሱንም እነሆዋት እናትህ ብሎ አደራ እንዳስጠበቀው። ከዚያንም ጊዜ ጀምራ እመቤታችን ማርያም ትጸልይ ዘንድ ያለ ማቋረጥ ወደ ልጅዋ መቃብር ሁል ጊዜ ስትሔድ ኖረች ይኸውም ጎልጎታ ነው። አይሁድም በአዩዋት ጊዜ ቊጣንና ቅናትን ተመልተው በደንጊያ ሊወግሩዋት ወደዱ እግዚአብሔርም ከዓይናቸው ሠወራት ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መጥታ በዚያ እንዳትጸልይ ተማክረው ከመቃብሩ ዘንድ ጠባቂዎችን አኖሩ እርሷ ግን በየዕለት መሔድን አላቋረጠችም ጠባቆችም አያይዋትም የልጅዋ የጌትነቱ መጋረጃ ሠውርዋታልና መላእክትም መጥተው ያገለግሏታል ጌታችንም ዘወትር፡ ይጐበኛታል የምትሻውንም፡ ይፈጽምላት ነበር።
❤ ከዚህም በኋላ መላእክት ወደ ሰማያት አሳረጓትና የጻድቃንን ማደሪያዎች አሳዩዋት አብርሃም፣ ይስሐቅና፣ ያዕቆብም ወዳሉበት አደረሱዋት ከአዳም ጀምሮ እስከዚያ ዕለት በአካለ ነፍስ ያሉ አባቶች ሁሉ "አንቺን ከሥጋችን ሥጋን ከዐፅማችን ዐፅምን ለፈጠረልን ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን የአምላክ ልጅ ከአንቺ ሰው በመሆኑ በአንቺ ድኅነትን አግኝተናልና ከጥፋትም የሕይወት ወደብ ሁነሽናልና" እያሉ ሰገዱላት። ከዚያም ወደ ተወደደ ልጅዋ የእሳት መጋረጃ ወደተተከለበት ወደ ጌትነቱ ዙፋን አደረሱዋት ጌታችንም እጅዋን ይዞ ወደ ውስጠኛው መጋረጃ አስገብቶ ከጌትነቱ ዙፋን ላይ አውጥቶ ከእርሱ ጋር አስቀመጣት ያዘጋጀላትንም ዐይን ያላየው ጆሮ ያልሰማውን በሰው ልቦና ያልታሰበው ተድላ ደስታን ሁሉ ነገራት። ከጌትነቱ ዙፋንም በታች የእስራኤል ንጉሥ አባቷ ዳዊትን የነቢያትና የመላእክት ማኅበር እንደግድግዳ ከበውት በመሰንቆ ሲያመሰግን አየችው እንዲህም ይላል "ልጄ ስሚ ጆሮሽም አድምጪ ወገንሽን የአባትሽንም ወገን ርሺ ንጉሥ ደም ግባትሽን ወዷልና እርሱም ጌታሽ ነውና።
❤ ዳግመኛም የሥቃይን ቦታ ያሳዩዋት ዘንድ መላእክት ከዚያ ወሰዱዋት ለሰይጣንና ለሠራዊቱ በእርሱ ጐዳና ለሚጓዙ ሁሉ ወደተዘጋጀ ወደጨለማው ዳርቻ አደረሷት። እመቤታችን ማርያምም "ወዮልኝ ወደዚህ እንዳይመጡ ለሰው ልጆች ማን በነገራቸው" አለች መልአኩም "እመቤቴ ቡርክት ማርያም ሆይ እግዚአብሔር ከአንቺ ጋር ይኖራልና ለአንቺም ከአንቺ በኋላም በቃል ኪዳንሽ ለሚታመኑ አትፍሪ" አላት ከዚህም በኋላ ወደ ቦታዋ መለሷት።
❤ ከዚያንም ጊዜ ጀምራ እመቤታችን ድንግል ማርያም ስለ ኃጥአን እጅግ እያዘነች ኖረች እንደ ዛሬዪቱም የካቲት ዐሥራ ስድስት ቀን በጎልጎታ ቦታ ቁማ ወደ ልጅዋ እንዲህ ብላ ለመነች። "ልጄ ሆይ በእግዚአብሔር አባትህ በክርስቶስ ስምህ፤ ከአንተ ጋርም ህልው በሆነ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ አማፅንሃለሁ፤ ዓለም ሁሉ ሊሸከምህ የማይችል ሲሆን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በተሸከመችህ ማኅፀኔ አማፅንሃለሁ፤ ልጄ ሆይ ያለ ሕማም ያለ ድካም ከእኔ በመውጣትህ በመወለድህ በአሳደጉህ ጡቶቼ ከአንተ ጋር በተመላለሱ እግቼ አማፅንሃለሁ። በውስጡ በተኛህበት በረት፤ በተጠቀለልክበት ጨርቅ አማፅንሃለሁ፤ የምወድህ ልጄ ሆይ በልቡናዬ ያለውን ሁሉ ትፈጽም ዘንድ የልመናዬን ቃል ሰምተህ ወደእኔ ትመጣ ዘንድ ወዳንተ ፈጽሜ እማልድሃለሁ"።
❤ የብርሃን እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምም እዲህ ብላ በጸለየች ጊዜ እንሆ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወረደ ከእርሱም ጋር አእላፋት መላእክት አሉ በዙሪያውም ሁነው ያመሰግኑታል። እርሱም "እናቴ ማርያም ሆይ ምን ላድርግልሽ" አላት እመቤታችንም ለተወዳጅ ልጅዋ እንዲህ ብላ መለሰችለት "ልጄ ወዳጄ ሆይ ጌታዬና ፈጣሪዬ አለኝታዬና መጠጊያዬ በእናቴ ማኅፀንም ሳለሁ በአንተ ጸናሁ አንተም ጠበቅኸኝ ሁልጊዜም ስም አጠራሬ አንተ ነህ። አሁንም ጸሎቴንና ልመናዬን ስማኝ ቃሌንም አድምጥ እኔ እናትህ እኔ አገልጋይህ የምለምንህ ይህ ነው መታሰቢያዬን ለሚያደርጉ በስሜ አብያተ ክርስቲያን ለሚሠሩ ወይም የተራቆተውን ለሚያለብሱ የተራበውን ለሚያጠግቡ የተጠማውን ለሚያጠጡ የታመመውን ለሚጐበኙ ያዘነውን ለሚያረጋጉ፣ የተከዘዌንም ደስ ለሚያሰኙ ወይም ምስጋናዬን ለሚጽፉ፣ ልጆቹንም በስሜ ለሚሰይም፣ በበዓሌም ቀን በማኅሌት ለሚያመሰግን አቤቱ ዐይን ያላየው ጆሮ ያልሰማውን በሰውም ልቡና ያልታሰበውን በጎ ዋጋ ስጣቸው በአማላጅነቴም የሚታመን፡ ሁሉ ከሲኦል ነጻ አድርገው ከአንተ ጋር የደረሰብኜን ረኃብና ጥማቱን መከራውን ሁሉ አስብ አለችው"። ጌታችንም ኢየሱስ ክርስቶስ "እንደልሽው ይሁንልሽ የሰጠሁሽም ቃል ኪዳን እንዳይታበል በራሴ ማልኩሌሽ" አላት።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእመቤታችን ድንግል ማርያም በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ይኑር ለዘላላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅድስት_ኤልሳቤጥ፦ ይህች ቅድስት ከኢየሩሳሌም የሆነች የእናቱዋ ስም ቅድስት ሶፍያ ነው። እርሷም ከሌዊ ነገድ ከአሮን ወገን ለሆነ ለማጣት ልጅ ናት በዝምድና አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የእናቷ እኅት ልጅ ናት። ማጣት ሦስት ልጆችን ወለዷልና የታላቂቱም ስም ማርያም ነው እርሷም ወደ ግብጽ በተሰደደች ጊዜ እመቤታችንን ያገለገለች ሰሎሜን ወለቻት፣ ሁለተኛዋም ሶፍያ ናት እርሷም የዚች ቅድስት ኤልሳቤጥ እናቷ ናት፣ የታናሺቱም ስም ሐና ነው። እርሷም የከበረች ድንግል እመቤታችንን ማርያምን ወለጀቻት። ሰሎሜ ኤልሳቤጥ እመቤታችን ማርያም የእኅትማማች ልጆች ናቸው።
❤ ይችንም ቅድስት ኤልሳቤጥ ካህኑ ዘካርያስ አገባት የከበረ ወንጌልም ስለርሳቸው፡ ተናግሯልና እነርሱ ሁለቱም ያለ ነውር ያለ ነቀፋ በእግዚአብሔር ሕግ ጸንተው የሚኖሩ ዕውነተኞች ደጎች ሆኑ። ኤልሳቤጥም መካን ስለሆነች ወደ እግዚአብሔር የሚለምኑና የሚሚማልዱ ሆኑ አርጅተውም የመውለጃቸው ዘመን በአለፈ ጊዜ እግዚአብሔር መልአኩን ቅዱስ ገብርኤልን ወደ ዘካርያስ ልኮ ጸሎታቸው ልመናቸው እንደ ተሰማ ስለ ዮሐንስ መወለድና ከእርሱ ስሚሆነው አስረዳው።
+5
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ ሊቀ ጳጳስ ዐቢይ ጾምን አገልግሎትን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ።
ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የአዲስ አበባና ሀዲያ ስልጤ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ዐቢይ ጾምን አስመልክተው ለገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች መመሪያ አስተላለፉ።
በትናትናው ዕለት በሀገረ ስብከቱ አዳራሽ በተከናወነው መርሐ ግብር ብፁዕነታቸው ጾሙ በረከት የምናገኝበት ታላቅ ሕይወት ጾም በመሆኑ የቤተ መቅደሱና የዐውደ ምሕረቱ አገልግሎት ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያንን በመጠበቅ በመልኩ በተጠናከረ ሁኔታ እንዲቀጥል አሳስበዋውል።
በተለይም ቅዳሴ ሰዓት እንዲሁም የቅዱስ ወንጌል አገልግሎት በተመለከተ በትጋትና በጥንቃቄ እንዲከናወን አዳራ ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ መልአከ ምሕረት ቆሞስ አባ ገብረ መድኅን ንጉሤ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣ የሀገረ ስብከቱ ዋና ክፍል ሐላፊዎች፣ የክፍላተ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣ የገዳማትና የአድባራት አስተዳዳሪዎችና ሌሎች የአገልግሎት መሪዎች ተገኝተዋል።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለዐቢይ_ጾም_ሁለተኛ_ሳምንት_ለቅድስት እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዚህ_ሳምንት_የቅድስት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ ፭ "#ግነዩ_ለእግዚአብሔር_ወጸውዑ_ስሞ ወንግርዎሙ ለአሕዛብ ምግባሮ ሀቡ ስብሐተ ለስሙ #አክብሩ_ሰንበተ ተገበሩ ድድቀ ዝግቡ ለክሙ መዝገበ ዘበሰማያት ኀበ ፃፄ ኢያማስኖ ወኢይረክቦ ሰራቂ #ድልዋኒክሙ_ንበሩ ዘበላዕሉ ሀልዩ ኀበ ሀሎ #ክርስቶስ። ትርጉም፦ #ለእግዚአብሔር_ተገዙ ስሙንም ጥሩ ሥራውንም ለአሕዛብ ንገሯቸው፤ ለስሙም ምስጋናን ስጡ (አቅርቡ) #ሰንበትን_አክብሩ፤ እውነትንም አድርጉ፤ ብል የማያበላሸው ሌባም የማያገኘው በሰማያት ያለ መዝገብን ለእናንተ ሰብስቡ፤ #ተዘጋጅታችሁም_ተቀመጡ፤ #ክርስቶስ_ወዳለበት ወደ ላይ አስቡ። #ሊቁ_ቅዱስ_ያሬድ_በጾመ_ድጓ ላይ።
✝ ✝ ✝
❤ ቅድስት፦
❤ የዐቢይየዐቢይ ጾም ሁለተኛ ሣምንት ቅድስት ይባላል። የተቀደሰች፣ የተባረከች፣ ንጽሕት ማለት ነው።
❤ ለምን ቅድስት ተባለ?፦ "ጾምን ቀድሱ ጉባኤውን አውጁ ሽማግሌዎችንና በምድር የሚኖሩትን ሁሉ ወደ አምላካችሁ ወደ እግዚአብሔር ቤተ ሰብስቡ"፡፡ ት.ኢዩ 1፥14 ብሎ በነቢዩ ኢዮኤል አፍ የተናገረ ቅዱስ እግዚአብሔር የጾማት ጾም ስለሆነች (የጌታችን ጾም ከቅድስት ጀምሮ በመሆኑ) ቅድስት ትባላለች።
❤ እንዲሁም የዲያብሎስን ፈተና ድል ለመንሳት በቅድስት ከተማ በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ጫፍ የቆመባት ዕለት በመሆኗ ማቴ 4፥5 ዮሐ 10፥22-23 ሰው ሁሉ ጾምን ጾሞ እንደ ፈጣሪው ፈተናን ድል ነሥቶ ቅድስና እና ክብርን ያገኛልና ቅድስት ተብላለች።
❤ ቅድስት ዕለተ ሰንበት፦ "እግዚአብሔር ሰባተኛይቱን ቀን ባረካት ቀደሳት" ዘፍ 2÷3፣ ዘጸ 20፥8 ሰዎች ፍጥረት ያልተፈጠረባት ዕለት ብለው እንዳይንቋት እንዳያቃልሏት ዕረፍተ ሥጋ ዕረፈተ ነፍስ የተገኘባት ዕለት ስለሆነች ቀደሳት አለ፡፡ ቅዱስ ያሬድም "ሰንበትየ ቅድስትየ ዕንተ አዕረፍኩ እምኩሉ ግብርየ ይቤ እግዚኣብሔር " ብሉአል። በዚህ እሁድ (ሳምንት ) ቀደሳት፣ አከበራት፣ ከፍ ከፍ አደረጋት :- የተባለች ሰንበትን የምትታሰብበት የሰንበትንም ቅድስና የሚመለከቱ መዝሙሮች የሚቀርብበት ሳምንት በመሆኑ ቅድስት ተብሏል። ምንጭ፦ ከአምኃ ሥላሴ ፔጅ የተወሰደ።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔርሰ ሰማያተ ገብረ። አሚን ወሠናይት ቅድሜሁ። ቅድሳት ወዕበየ ስብሐት ውስተ መቅደሱ"። መዝ 95፥5-6። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛተሰሎ 4፥1-13፣ 1ኛ ጴጥ.1÷13-ፍም እና የሐዋ ሥራ 10፥17-30። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥16-25። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ኤጲፋንዮስ ቅዳሴ ነው። ዕለት ሰንበት (ቅድስት)ና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፭ (15) ቀን።
❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ደቂቀ_ነቢያት ለአንዱ ለታላቁ ለእውነተኛው ነቢይ #ለቅዱስ_ዘካርያስ ለዕረፍት በዓል፣ በገድል ተጠምዶ ለኖረ የገዳማውያን አባቶችን ገድል ለመጻፍ ብዙ ለደከመ (በበረሀ ውስጥ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ደርሶበታል ያለምግብ ሦስት ቀን ከቆየ በኋላ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ለሠሠው ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ለኖረ) ስለእነርሱም ብዙ ምሥጢራትን ላወቀ #ለአባ_በፍኑትዮስ ለዕረፍት በዓልና ስብስጥያ በምትባል አገር የሰማዕታት #አርባ_ሐራ_ሰማይ_ቤተ_ክርስቲያናቸው_ለከበረችበት እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ነቢዩ_ቅዱስ_ዘካርያስ፦ እርሱም ከሌዊ ነገድ ነው የአባቱም ስም በራክዩ ነው በገለዓድም ወለደው በባቢሎን ምርኮ ጊዜ ተማረከ ከዚያ ሳለም በላዩ የወረደለትን መለኮታዊ ትንቢትን ተናገረ መንፈስ ቅዱስም በእርሱ አንደበት ጠቃሚዎች የሆኑ ብዙ ቃሎችን ተናገረ። ለኢዮሴዴቅም እንዲህ ብሎ ትንቢትን ተናገረ "በኢየሩሳሌም እግዚአብሔር ን ካህን ሁኖ የሚያገለግል ልጅ ትወልዳለህ" ከሚጠትም በኋላ እንደቃሉ ሆነ። ለሰላትያልም ትንቢት ተናገረለት ባረከውም "ወንድ ልጅ ትወልዳለህ ስሙንም ዘሩባቤል ትለዋልህ እርሱም በኢየሩሳሌም መቅደስን ይሠራል" አለው ዳግመኛም ለፋርስ ንጉሥ ተናገረ የድል ምልክትንም ገለጠለት።
❤ ጌታችን በውርጫዪቱና በታላቂቱ አህያ ተቀምጦ ወደ ኢየሩሳሌም ስለ መምጣቱ ተናገረ። ይሁዳም መድኃኒታችንን ክርስቶስን አሳልፎ በመስጠቱ ስለ ተቀበለው ሠላሳ ብር ትንቢት ተናገረ። መድኃኒታችንም በሚሰቀልበት ዐርብ ሌሊት ስለ ሐዋርያት መበተን ተናገረ። በቀትር ጊዜም ስለ ፀሓይ መጨለም ተናገረ። ስለ እስራኤል ልጆች ኀዘንም እንዲህ አለ "ያን ጊዜ የወጉትን ያዩት ዘንድ አላቸው ወደ ኀዘንም ይመለሳሉ እንደ ሚወዱትም ያለቅሱለታል ሰው ለበኵር ልጁ እንደሚያዝን ጽኑ ኀዘንን ያዝናሉ"። የትንቢቱም ወራት በተፈጸመ ጊዜ የካቲት15 በሰላም ዐረፈ በነቢያት መቃብርም ተቀበረ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ በቅዱስ ዘካርያስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_በፍኑትዮስ፦ ይህም አባት ከታናሽነቱ መንኵሶ በጾምና በጸሎት በስግደትም እየተጋ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። ያማረ ምንኵስናውን ሥራ ፈጸመ ጊዜ መነኰሳት ከሚኖሩበት ገዳማት ርቆ ወደሚገኝ። በርሀ ውስጥ ይገባ ዘንድ የከበሩ ገዳማውያንንም ይጐበኛቸው ዘንድ ለሚያነቧት ጥቅም ትሆን ዘንድ ገድላቸውንም እንዲጽፍ ልዑል እግዚአብሔር አዘዘው። በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ትዕዛዝ ራሱን ዘንበል አድርጎ ወደ ውስጠኛው በርሀ ገባ በመንደር ውስጥ እንደ ሚዞር ሰው በዱር መካከል ዞረ። ከገዳማውያንም ብዙዎችን አገኛቸውና ዜናቸውን ተረድቶ ገድላቸውን ጻፈ ከውስጣቸውም የከበሩ ገዳምውያን ጢሞቴዎስና አቡናፍር አሉ።
❤ ይህንንም አባት በፍኑትዮስ ወደ ውስጠኛው በርሀ በመግባቱ ከርኃብ የተነሣ ሥቃይ ደርሶበታል ያለምግብ ሦስት ቀን አድሮአል። ከዚያም በኋላ ተርቦ ለሞት ተቃረበ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአክ ተገለጸለትና ሰውነቱን ሁሉ አፉንም ዳሠሠው ያለ ምግብም ዐሥራ ሰባት ቀን ኖረ።
❤ ዳግመኛም ከቶ ሰው ሳያዩ ስድሳና ሰባ ዓመት ከዚያም የሚበዛ የሚያስደንቅ የገዳማውያንን ኑሮአቸውን ተናገረ ወደ ውስጠኛው በረሀ በሚገቡ ጊዜ እርሱን ስለሚወጓቸው ከርኵሳን መናፍስትና ከሚያስፈሩ አራዊት ስለሚደርስባቸውም ፈተና ተናገረ ከዚህም በኋላ በትዕግሥታቸው የሚገዙላቸው ይሆናሉ አራዊትም እንደ ባሮች ያገለግሏቸዋል ቅዱስ ቊርባንንም እንዴት እንደሚቀበሉ ደግሞ ተናገረ በዕለተ ሰንበት የመድኃኒታችንን ክርስቶስን ሥጋና ደም መላእክት አምጥተው ያቀብሏቸዋልና ከገነትም ፍራፍሬዎችን ይሰጧቸዋል። ለዚህም አባት ስለ እሊህ ድንቆች ሥራዎች አይቶ ምስክር ሊሆን የተገባው ሆነ ከዚያም በኋላ የካቲት15 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በፍኑትዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ስብስጥያ_በምትባል_አገር_የሰማዕታት #አርባ_ሐራ_ሰማይ_ቤተ_ክርስቲያናቸው_ተከበረች፦ ይህች ቤተ ክርስቲያን በስማቸው አስቀድማ ተሠራች ታላቁ አባት ባስልዮስም አከበራት ስለርሳቸውም ድርሳናትን ደረሰ የካቲት15 በዚችም ዕለት በዓልን አደረገላቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የካቲት 15 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለዘካርያስ_ዘኮነ_ልዑለ_ቃል። በወራኀ ከሲል። ለቤተ ክርስቲያን ቅድስት ዘሐዋርያት መድብል። አምሳለ ተቅዋም ዘመኃቲዊሃ ጽዱል። ማዕከለ ክልኤ አዕፅቅ ርኢክዋ ይብል"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_15።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፬ (14) ቀን።
❤ እንኳን #ለታላቁ_አባት ሃይማኖታቸው ለቀና ምዕመናን መምህራቸው ለሆነ ለአንጾክያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_ሳዊሮስ ለዕረፍቱ በዓል፣ ለእስክንድርያ ለኃምሳኛ ሊቀ ጳጳስ በጸሎቱ አንድ ሙት ላስነሳ ለከበረ አባት #ለአባ_ያዕቆብና ሰባ አምስተኛ ሊቀ ጳጳሳት ለከበረ አባት #ለአባ_ቄርሎስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_ከዳርዮስ፣ #ከጳውሎስ_ከአኩደራስና_ከሊድና ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ሳዊሮስ_ዘአንጾኪያ፦ የዚህ ቅዱስ ዘመዶቹ ከሮሜ አገር ናቸው አባቱም ስሙ ሳዊሮስ የሚባል ኤጲስቆጶስ ነው። እርሱም ስለ ንስጥሮስ በኤፌሶን ከተማ ጉባኤ በሆነ ጊዜ ከሁለት መቶ አባቶች ኤጲስቆጶሳት ጋር መጣ በዚያም እንዲህ የሚለውን ራእይ አየ "ከአንተ የሚወለድ ልጅህ ስሙም እንደ ስምህ ሳዊሮስ ተብሎ የሚጠራ እርሱ ለቀናች ሃይማኖትን" ያጸናታል።
❤ ይህም ኤጲስቆጶስ በዐረፈ ጊዜ ልጁን ሳዊሮስ ብለው ጠሩት ከቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆነውን ጥበብን ሁሉ ተማረ። ከመምህሩም ወጥቶ ወደ አንድ ቦታ ሲጓዝ በዋሻ ራሱን እሥረኛ አድርጎ የሚኖር ጻድቅ ሰው ተገናኘው በእርሱም ደስ ብሎት "የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ሃይማኖታቸው ለቀና ምዕመናን መምህራቸው የሆንክ ሳዊሮስ ሆይ መምጣትህ መልካም ነው" አለው። ሳዊሮስም ከቶ ሳያውቀው በስሙ በጠራው ጊዜ የሚደረግለትንም ከመሆኑ አስቀድሞ በመናገሩ አደነቀ።
❤ ከዚህም በኋላ ሳዊሮስ ትሩፋት በመሥራት አደገ መልካም ስም አጠራሩና ዜናው ተሰማ በአባ ሮማኖስ ገዳም መንኵሶ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ በትሩፋትም ሥራ እጅግ የተጠመደ ሆነ የከበረ ወንጌል "በተራራ ላይ የተሠራች መንደር መሠወር አትችልም" እንዳለ ዜናው በሁሉ ዘንድ ተሰማ። የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳትም በዐረፈ ጊዜ አዋቂዎች ኤጲስቆጶሳት ይህን የከበረ ሳዊሮስን ይሾሙት ዘንድ ተስማምተው ያለ ውዴታው ወስደው በአንጾኪያ አገር ላይ ጵጵስና ሾሙት በሹመቱም እስከ ዓለም ዳርቻ ያለች ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆነላት በአገሮች ሁሉ ወዳሉ መናፍቃን ከሀድያን ትምህርቱ በሚደርስ ጊዜ ሁለት አፍ እንዳለው ስለታም ሰይፍ ሥራቸውን ይበጥሳልና።
❤ ከጥቂት ቀኖችም በኋላ አማኒ ንጉሥ ሙቶ በርሱ ፈንታ ስሙ ዮስጥያኖስ የሚባል መናፍቅ ነገሠ ንግሥቲቱ ሚስት ግን ሃይማኖቷ የቀና ነው ስማ ቴዎድራ ይባላል። ንጉሡም የኬልቄዶን ወደ ሆነች ወደረከሰች ሃይማኖቱ ይህን የከበረ አባት ያስገባው ዘንድ ያስፈራራው ነበር እርሱ ግን ፈርቶ አይትዘዝለትም ቊጣውንም የሚፈራ መስሎት በእርሱ ላይ አብዝቶ ተቆጣ ቊጣውንም ባልፈራ ጊዜ በሥው፡ ሊያስገድለው መከረ ንግሥቲቱም አውቃ ከንጉሡ ፊት ይሸሽ ዘንድ ሊቀ ጳጳሱን መከረችው እርሱም በሥውር ወጥቶ ገለል አለ። እግዚአብሔር የዚህን አባት ሞት አልፈቀደምና ስለ ምእመናንም ጥቅም ጠበቀው። በአንድ ተራ መነኵሴ አምሳል ሁኖ፡ በቦታዎችና በገዳማት የሚዘዋወርና ምእመናንን የሚያጠናክራቸው ሆነ ስካ በሚባል አገር ስሙ ዶርታኦስ ከሚባል ደግ ምእመን ባለ ጸጋ ሰው ዘንድ ተምጦ ሳለ ጌታችን በእጆቹ ብዙ ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ ስካ በተባለ አገር እስከ ዐረፈ ድረስ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ ሁሉንም ያስተምራቸው ነበር ከዚህም በኋላ ወደ ዝጋግ ገዳም አፈለሱት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሳዊሮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ቄርሎስ፦ ይህም አባት ፍዩም ከምትባል አገር ነው። በእርሷም ቅስና ተሹሞ ኖረ ከዚህም በኋላ ከዚያ፡ ለቆ ከምስር ከተማ ውጭ ወደ ሆነች የኢትዮጵያውያን የጒድጓድ ውኃ ወዳለበት ወደ ቅዱስ ፊቅጦር ገዳም ደረሰ በውስጡም ታላቅ ተጋድሎን እነተጋደለ ብዙ ዘመናትን ኖረ።
❤ የዕውቀቱና የቅድስናው ዜና በተሰማ ጊዜ ያለ ውዴታው ይዘው በእስክድርያ አገር ሊቀ ጵጵስና ሾሙት መንጋውንም በበጎ አጠባበቅ ጠበቀ በቊርባንና በጸሎት ጊዜ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሊሠሩት የሚገባቸውን ለካህናት ሦርዓትን ሠራ። በሹመቱም ሰባት ዓመት ከዘጠኝ ወር ከሃያ ሰባት ቀን ኑሮ የካቲት14 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አባ_ያዕቆብ፦ ይህም አባት እልመቱዝ ለተባለ የግብጽ ንጉሥ በነገሠ በ17 ዓመት ተሾመ እርሱም ለመኰንኑ ለወልደ ኀሮን ረሽድ ወንድም የሆነ ነው፡ በዚህም አባት ዘመን የአስቄጥስ ገዳማት ታድሰው መነኰሳቱ ወደሳቸው ተመለሱ።
❤ አፎን በሚባል አገር ስሙ መቃርስ የሚባል ሰው ነበር ወደዚህ አባት ወደ ያዕቆብ መጥቶ ወደቤቱ በመሔድ ቤቱን ይባርክለት ዘንድ ለመነው እርሱም አብሮት ሔደ ታሞ የነበረ ልጁም ሞተ ወደ አባ ያዕቆብ አቅርቦ እንዲህ ብሎ ለመነው "ከርሱ በቀር ልጅ የለኝምና አባቴ ሆይ ራራልኝ እርሱም እነሆ ሞተ ስርሱ፡ ወደ እግዚአብሔር ትማልድ ዘንድ እለምንሃለው" አለው። አባ ያዕቆብም "እንደ እምነትህ ይሁንልህ አትፍራ" አለው። ሕፃኑንም ከአባቱ ተቀብሎ ታቀፈውና በላዩ ጸለየ በመስቀል ምልክትም አማተበበት ስለርሱም ወደ እግዚአብሔር ለመነ ጌታችንም ልመናውን ተቀበለው የሕፃኑ ነፍስ ተመልሳ ዐይኖቹን ገለጠ ከሞትም ድኖ ተነሣ አባቱንም "ልጅህን ውሰድ የሞተ አይደለም ያንቀላፋ ሁን ነው እንጂ" አለው። የሕፃኑም አባት ይህን ድንቅ ሥራ በአየ ጊዜ እጅግ ፈራ የገንዘቡንም እኩሌታ ለምጽዋት ብሎ ሰጠው እርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ልኮ ሃይማኖታቸው ለቀና ምእመናን ሁሉ ወደርሷ በመጡ ጊዜ መጠጊያ ይሆን ዘንድ ቤተ ክርስቲያንን ሠራበት።
❤ የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት ዲዮናስዮስም ወደ ምስር በመጣ ጊዜ ከአባ ያዕቆብ ጋር ተቀምጦ ወደ አገሩ ተመለሰ። ይህ አባት ያዕቆብ በሹመቱ ዐሥር ዓመት ከስምት ወር፡ ከሦስት ቀን ኑሮ የካቲት14 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ያዕቆብ በጸሎቱ ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት 14 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_ለያዕቆብ_ለእግዚአብሔር_ቅዱሱ። ዘአድባረ ገዳም ኵሉ በመዋዕሊሁ ተሐደሱ። እስከ አቡሁ ገነየ ለብዕለ ጸጋሁ ወዕበየ ሞገሱ። በግሠተ እዱ ወበጽላሎታ ለእርሱ። ውስተ በድነ ሕፃን ገብአት ዘወጽአት መንፈሱ። #ሊቁ_አርከ¶ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_14።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "አሕፃከ ስሑል ኃያል። አሕዛብ ይወድቁ ታሕቴከ። ውስተ ልቦሙ ለጸላዕተ ንጉሥ"። መዝ 44፥5። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 1፥7-12፣ 1ኛ ዮሐ 2፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥28-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 18፥15-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ቄርሎስ ቅዳሴ ነው። መልካም የአቡነ ሳዊሮስ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ እንዲህም ሆነ ከሕዝቡ ውስጥ አንድ ታናሽ ሕፃን እግዚአብሔር ዐይኖቹን ገልጦለት የቅዱሳን ሰማዕታትን ነፍሶቻቸውን መላእክት ወደ ሰማያት ሲያወጧቸው አይቶ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ይቅር በለኝ" እያለ በከፍተኛ ቃል ጮኸ እናትና አባቱም መኰንኑ ሰምቶ ስርሱ እንዳያጠፋቸው አፋን የሚዘጉ ሆኑ እርሱ ግን እንዲህ እያለ መጮኹን አልተወም በላዩ እስከ ተኙበትና ነፍሱን እስከ አሳለፈ ድረስ ከሰማዕታትም ጋር የምስክርነት አክሊልን ተቀበለ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት በጸሎቱ ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የየካቲት13 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የእስክንድርያ_አገር_ሊቀ_ጳጳሳት_አባ_ጢሞቴዎስ፦ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ሠላሳ ሁለተኛ ነው። ይህንንም አባት ስለ ቀናች ሃይማኖት ብዙ መከራና ችግር ደርሶበታል ። እንዲህም ሆነ በዚያ ወራት የአንጾኪያ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስ ወደ ግብጽ አገር መጣ እርሱም ከዚህ አባት ጢሞቴዎስ ጋር ምእመናንን እያጽናና ከሀገር ወደ ሀገር ከገዳም ወደ ገዳም ከቦታ ወደ ቦታ የሚዘዋወር ሆነ።
❤ በዚህም አባት ጢሞቴዎስ ዘመን ከቊስጥንጥንያ የመጡ ክፉዎች ሰዎች በግብጽ አገር ተገለጡ እነርሱም የክርስቶስን ተዋሕዶ ምትሐት በሚያደርግ መከራውንና ትንሣኤውንም በሚክድ በረከሰ በአውጣኪ ትምህርት የሚያምኑ ናቸው ይህም አባት አውግዞ ከግብጽ አገር አሳደዳቸው።
❤ ዳግመኛም በዘመኑ ምእመን ንጉሥ አንስጣስዮስ አረፈና በርሱ ፈንታ ኬልቄዶናዊ መናፍቅ ዮስጣትያኖስ ነገሠ እርሱም በአባ ጢሞቴዎስ ፈንታ ሊናርዮስን ሊቀ ጵጵስና ሾመው ሃይማኖታቸው የቀና ምእመናንን ሁሉ በኬልቄዶን ግባኤ ወደተወሰነ ሃይማኖት ሊመልሳቸው ወዶ በቅስጥንጥኒያ ጉባኤ ሰብስቦ የአንጾኪያውን ሊቀ ጳጳሳት አባ ሳዊሮስን ከኤጲስቆጶሳቶቹ ጋር አስመጣው።
❤ በኬልቄዶን ጉባኤ በተወሰነች በተበላሸች ሃይማኖቱ ያምኑ ዘንድ አስገደዳቸው እነርሱ ግን አልተቀበሉትም ትእዛዙንም አልሰሙም ስለዚህም ሃይማኖታቸው በቀና ምእመናን ሁሉ ታላቅ መከራ አደረሰባቸው።
❤ ይህም አባት ጢሞቴዎስ በመንበረ ሢመቱ ዐሥራ ሰባት ዓመት ኑሮ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጢሞቴዎስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘለዓለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_እብል_ጢሞቴዎስሃ_ሰባኬ። ወሊቀ ጳጳሳት ዝኬ። ዘበመዋዕሊሁ ተውህበ ለመሃይምናን ቡራኬ። ወውዕዩ በነደ ቃሉ ከመ አገዳ ሐመል ወመሎኬ። እለ ተአመኑ በትምህርቱ ለዕልው አውጣኬ"። #ሊቁ_አርከ_ሥሉስ (አርኬ) #የየካቲት_13።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦"አይቴኑ አሐውር እመንፈስ። ወአይቴ እጐይይ እምቅድመ ገጽከ። እመኒ ዐረጉ ውስተ ሰማይ ህየኒ አንተ"። መዝ 138፥7-8። የሚነበቡት መልክታት 2ኛ ቆሮ 12፥1-11፣ 1ኛ ጴጥ 1፥6-10 እና የሐዋ ሥራ 15፥22-36። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 5፥27-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ፡ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት በሁላችንም ይሁንልን።
❤ በአንዲት ዕለት የሶርያው ንጉሥ ሚስት ቅዱስ አውሳብዮስን አይታው እጅግ ወደደችው፡፡ ከባሮቿም ውስጥ ሁለቱን ልካ ካስመጣችው በኋላ በወርቅ አጊጣ በሐር በተነጠፈ አልጋ ላይ ሆና ጠበቀችው፡፡ከእርሷም ጋር እንዲተኛ ስትጠይቀው "እኔስ ሚስቴንም እንኳን በግብር ያላወኩ ነኝና ተይኝ ንጉሡ ባልሽ በቤት ባይኖር ሰውም ባያየን እግዚአብሔር ግን ያየናልና እንዴት በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት እሠራለሁ? "በማለት ትቷት ሊወጣ ሲል ልብሱን ያዘችው፡፡ እርሱም ሮጦ በማምለጥ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ እርሷ ግን በመጮህ ባሮቿ ሲመጡላት" ክፉ ነገርን አድርጎብኝ ሄደ" ብላ በሐሰት ተናገረች፡፡ ጭፍሮቿም ቅዱስ አውሳብዮስን ከቤተ ክርስቲያን አውጥተው እየደበደቡ ወደ ንግሥቲቱ አመጡት፡፡ እጆቹንና እግሮቹንም አሥረው ከከተማ ውጭ በአራት ዕንጨቶች ላይ አሰቀለችው፡፡ ከባሮቿም ውስጥ አንዲቱ በንግሥቲቱ ተልካ ሄዳ አውሳብዮስን "ከተሰቀልክበት እንዲታወርድህ ለእመቤቴ ያለችህን እሺ በላት" አለችው፡፡ እርሱም "የአመንዝራን ቃል አልሰማም" አላት፡፡ ንግሥቲቱም እሺ እንዳላላት ስታውቅ አንገቱን በገመድ አሳንቃ 160 ፍላጻዎችን በሰውነቱ ውስጥ እንዲጭምሩበት አደረገች፡፡ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን ልኮለት ፍላጻዎቹን ከሰውነቱ ውስጥ አወጡለትና ፍጹም ጤነኛ ሆነ፡፡ ንጉሡም ከሄደበት ሲመለስ ንግሥት ሚስቱን አውሳብዮስን ለስቅላትና ለሞት ያበቃችው በምን ምክንያት እንደሆነ ሲጠይቃት አንተ በሌለህበት ወደ መኝታ ቤቴ ገብቶ ሊናገሩት የማይገባ ነገር ጠየቀኝ በከለከልኩትም ጊዜ በሥራዩ አሳመመኝ" አለችው፡፡ንጉሡም ተቆጥቶ ቅዱስ አውሳብዮስን ከተሰቀለበት አስወርዶ ካስመጣው በኋላ ለምን ይህን እንዳደረገ ጠየቀው፡፡ አውሳብዮስም እውነቱን በነገረው ጊዜ ጭፍሮቹን ምስክር ይሆኑ ዘንድ ሲጠይቃቸው ንግሥቲቱ ስትጮህ ወደ ውስጥ ሲገቡ ያጋጠማቸውን መሰከሩ፡፡ ንጉሡም የሚስቱን ነገር አምኖ በመቀበል በንዴት የቅዱስ አውሳብዮስን ሰውነቱን በሰይፍ አስቆርጦ ሥጋውን እንደ ላም ሥጋ ቆራርጦ በምንቸት አድርጎ በእሳት እንዲበስል አደረገው፡፡ ነገር ግን አሁንም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ከምቸቱ አውጥተው ከሞትም አድነው በማስነሣት ፍጹም ጤነኛ አደርገው አቆሙት፡፡
❤ ከሞት ከተነሣም በኋላ በአገሩ ውስጥ ሲሄድ ሰዎች አይተውት ለንጉሡ ስለነገሩት ንጉሡ ድጋሚ ካስመጣው በኋላ አራት ዛንጅሮች በአካላቶቹ ውስጥ በማስገባት እጅና እግሩን አሳስሮ በእሳት ውስጥ ጨመረው፡፡ የከበሩ ሁለቱ ቅዱሳን መላእክት አሁንም መጥተው ፈወሱት፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም ነጥቆ ወደ ሰማይ አሳርጎት በዚያው በሰማይ 14ዓመት ኖረ፡፡ ከዚያም ወደ ምድር ተመልሶ መጥቶ ወንጌልን እያስተማረ 40 ዓመት ኖረ፡፡ በእርሱም ትምህርት 85ሺህ አረማውያን አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስ በመጨረሻ ሰማዕትነቱንና ተጋድሎውን ፈጽሞ የካቲት13 ቀን በክብር ዐርፏል፡፡ጌታችንን፡ኢየሱስም ስሙ ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ እስከ ሰባት ትውልድ ሊምርለት ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውሳብዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሰርግዮስ፦ የዚህ ቅዱስ አባቱና እናቱ ደጎች ናቸው። የአባቱ ስም ቴዎድሮስ የእናቱም ስም ማርያም ነው። ዕድሜውም ሃያ ዓመት ሲሆነው በክብር ባለቤት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሞት ዘንድ አሰበ ወደ መኰንኑ ቆጵርያኖስም ቀርቦ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ መኰንኑም ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ያሥሩትም ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሰማይ አምጥቀው የቅዱሳን ሰማዕታትን መኖርያ ያሳዩዋት ዘንድ አዘዘ አይታም ተጽናናች ከሥቃይ ከሕማሙም ፈወሰው።
❤ ቀሲስ አባ መጹንና ሁለት ዲያቆናትም ተጋድሎውን ሰሙ ያን ጊዜም ተነሥተው ወደ አትሪብ አገር ገዥ ቀርበው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ የጸና ግርፈትም ይገርፋቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው። ሕዝቡም ሁሉ በዙርያቸው ሁነው ይመለከቷቸው ነበር ስለ ቄሱና ከእርሱ ጋር ስላሉትም አዘኑ ቄሱ ግን ፊቱን ወጀርሳቸው መልሶ ገሠጻቸው አስተማራቸውም "በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ በቀናች ሃይማኖት እንዲህ ጽኑ" አላቸው ከዚህም በኋላ በውኋ ላይ ጸልዮ በላያቸው ረጨ በዚያንም ጊዜ በላያቸው ወርዶአልና የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀበለው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ከዚያም በኋላ ቄሱን ከውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ እግዚአብሔርም ከእሳት አዳነው። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና እርሱ ስለ ክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ሦስት ጊዜ ምስክር እንደሚሆን አሰረዳው ከእሳት ማንደጃው ውስጥም አወጣው። መኰንኑም ወደ እስክድርያ አገር ላከው ተጋድሎውንና ምስክርነቱን በዚያ ፈጸመ የምስክርኘቱን አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ።
❤ ከዚያም በኋላ መኰንኑ ቆጵርያኖስ የከበረ ሰርግዮስን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ ታላቅ ሥቃይንም አሠቃየው የነሐስ መንኰራኵሮችንም አምጥተው ከውስጣቸው አስገብተው አበራዩት ሕዋሳቱም አራት ክፍል ሁኖ ሥጋው ሁሉ ተቆራረጠ ጌታችንም አድኖ ያለ ጉዳት በጤና አስነሣው። ዳግመኛም እንዲሰግድለት ጣዖትን አመጡ ቅዱሱ ግን ሲረግጠው ወድቆ ተቀጥቅጦ ደቀቀ መኰንን ቆጵርያኖስም አይቶ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነ "አምላክ ቢሆን ራሱን ማዳን በቻለ ነበር" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ የጭፍራ አለቃ ስሙ አውህዮስ የሚባል የከበረ ሰርግዮስን ፈልጎ ያዘው ቆዳውንም ገፈው በተቀላቀለ ኮምጣጤና ጨው ቊስሉን ያሹት ዘንድ አዘዘ ጌታችን ግን በሥቃዮች ላይ ያጸናውና ያበረታው፡ ነበር። እናቱና እኅቱም ሰምተው ወደርሱ መጡ በአዩትም ጊዜ በላዩ አለቀሱ ከኀዘንም ብዛት እኅቱ ነፍሷን አሳለፈች የከበረ ሰርግዮስም ስለ እኅቱ ወደ ጌታችን ጸለየ ከሞትም ድና በሕይወት ተነሣች። ያን ጊዜ የሰማዕታትን ገድል የሚጽፍ የአቅፋስ፡አገር ሰው የከበረ ዮልዮስ መጣ ገድሉንም ሁሉ ከእርሱ ተረዳ ለሥጋውም እንደሚያስብ ቃል ገባለት።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ የከበረ ሰርግዮስን በመንኰራኵር ውስጥ ያሠቃዮት ዘንድ በጆሮዎቹ የእሳት መብራቶችን እንዲጨምሩ የእጆቹንና የእግሮቹን ጥፍሮች እንዲነቅሉ በአንገቱም ከባድ ደንጊያ አንጠልጥለው ከብረት ዐልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አውህዮስ አዘዘ እንዳዘዘውም አደረጉበት ጌታችን ኢየሱስ ያጸናውና ያለ ጥፋት በጤና ያስነሣው ነበር። የሠራዊት አለቃ አውህዮስም ማሠቃየቱን በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ፡አዘዘ የከበረ ሰርግዮስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ወደ አባቱና ወደ እናቱ ወደ ወንድሞቹም ላከ ዘመዶቹ ሁሉም የእርሱ የሆኑ ሰዎችም መጡ በአፋም ልጓም ለጒመው ቸብቸቦውን ወደሚቆርጡበት ሲስቡት አገኙትና መኰንኑን የረከሱ ጣዖታቱንም ረገሙ መኰንኑም ከከበረ ሰርግዮስ ጋር ሁሉንም ቸብቸቧቸውን እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ።
❤ በአንዲት ዕለት የሶርያው ንጉሥ ሚስት ቅዱስ አውሳብዮስን አይታው እጅግ ወደደችው፡፡ ከባሮቿም ውስጥ ሁለቱን ልካ ካስመጣችው በኋላ በወርቅ አጊጣ በሐር በተነጠፈ አልጋ ላይ ሆና ጠበቀችው፡፡ከእርሷም ጋር እንዲተኛ ስትጠይቀው "እኔስ ሚስቴንም እንኳን በግብር ያላወኩ ነኝና ተይኝ ንጉሡ ባልሽ በቤት ባይኖር ሰውም ባያየን እግዚአብሔር ግን ያየናልና እንዴት በእግዚአብሔር ፊት ኃጢአት እሠራለሁ? "በማለት ትቷት ሊወጣ ሲል ልብሱን ያዘችው፡፡ እርሱም ሮጦ በማምለጥ ቤተ ክርስቲያን ሲገባ እርሷ ግን በመጮህ ባሮቿ ሲመጡላት" ክፉ ነገርን አድርጎብኝ ሄደ" ብላ በሐሰት ተናገረች፡፡ ጭፍሮቿም ቅዱስ አውሳብዮስን ከቤተ ክርስቲያን አውጥተው እየደበደቡ ወደ ንግሥቲቱ አመጡት፡፡ እጆቹንና እግሮቹንም አሥረው ከከተማ ውጭ በአራት ዕንጨቶች ላይ አሰቀለችው፡፡ ከባሮቿም ውስጥ አንዲቱ በንግሥቲቱ ተልካ ሄዳ አውሳብዮስን "ከተሰቀልክበት እንዲታወርድህ ለእመቤቴ ያለችህን እሺ በላት" አለችው፡፡ እርሱም "የአመንዝራን ቃል አልሰማም" አላት፡፡ ንግሥቲቱም እሺ እንዳላላት ስታውቅ አንገቱን በገመድ አሳንቃ 160 ፍላጻዎችን በሰውነቱ ውስጥ እንዲጭምሩበት አደረገች፡፡ጌታችንም ቅዱስ ሚካኤልንና ቅዱስ ገብርኤልን ልኮለት ፍላጻዎቹን ከሰውነቱ ውስጥ አወጡለትና ፍጹም ጤነኛ ሆነ፡፡ ንጉሡም ከሄደበት ሲመለስ ንግሥት ሚስቱን አውሳብዮስን ለስቅላትና ለሞት ያበቃችው በምን ምክንያት እንደሆነ ሲጠይቃት አንተ በሌለህበት ወደ መኝታ ቤቴ ገብቶ ሊናገሩት የማይገባ ነገር ጠየቀኝ በከለከልኩትም ጊዜ በሥራዩ አሳመመኝ" አለችው፡፡ንጉሡም ተቆጥቶ ቅዱስ አውሳብዮስን ከተሰቀለበት አስወርዶ ካስመጣው በኋላ ለምን ይህን እንዳደረገ ጠየቀው፡፡ አውሳብዮስም እውነቱን በነገረው ጊዜ ጭፍሮቹን ምስክር ይሆኑ ዘንድ ሲጠይቃቸው ንግሥቲቱ ስትጮህ ወደ ውስጥ ሲገቡ ያጋጠማቸውን መሰከሩ፡፡ ንጉሡም የሚስቱን ነገር አምኖ በመቀበል በንዴት የቅዱስ አውሳብዮስን ሰውነቱን በሰይፍ አስቆርጦ ሥጋውን እንደ ላም ሥጋ ቆራርጦ በምንቸት አድርጎ በእሳት እንዲበስል አደረገው፡፡ ነገር ግን አሁንም ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል ከምቸቱ አውጥተው ከሞትም አድነው በማስነሣት ፍጹም ጤነኛ አደርገው አቆሙት፡፡
❤ ከሞት ከተነሣም በኋላ በአገሩ ውስጥ ሲሄድ ሰዎች አይተውት ለንጉሡ ስለነገሩት ንጉሡ ድጋሚ ካስመጣው በኋላ አራት ዛንጅሮች በአካላቶቹ ውስጥ በማስገባት እጅና እግሩን አሳስሮ በእሳት ውስጥ ጨመረው፡፡ የከበሩ ሁለቱ ቅዱሳን መላእክት አሁንም መጥተው ፈወሱት፡፡ መልአኩ ቅዱስ ዑራኤልም ነጥቆ ወደ ሰማይ አሳርጎት በዚያው በሰማይ 14ዓመት ኖረ፡፡ ከዚያም ወደ ምድር ተመልሶ መጥቶ ወንጌልን እያስተማረ 40 ዓመት ኖረ፡፡ በእርሱም ትምህርት 85ሺህ አረማውያን አምነው ተጠምቀዋል፡፡ ቅዱስ አውሳብዮስ በመጨረሻ ሰማዕትነቱንና ተጋድሎውን ፈጽሞ የካቲት13 ቀን በክብር ዐርፏል፡፡ጌታችንን፡ኢየሱስም ስሙ ለሚጠራ መታሰቢያውንም ለሚያደርግ እስከ ሰባት ትውልድ ሊምርለት ቃል ኪዳን ሰጠው፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አውሳብዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ሰርግዮስ፦ የዚህ ቅዱስ አባቱና እናቱ ደጎች ናቸው። የአባቱ ስም ቴዎድሮስ የእናቱም ስም ማርያም ነው። ዕድሜውም ሃያ ዓመት ሲሆነው በክብር ባለቤት በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ይሞት ዘንድ አሰበ ወደ መኰንኑ ቆጵርያኖስም ቀርቦ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ታመነ መኰንኑም ጽኑ ሥቃይን ያሠቃዩት ዘንድ ያሥሩትም ዘንድ አዘዘ ጌታችንም ነፍሱን ወደ ሰማይ አምጥቀው የቅዱሳን ሰማዕታትን መኖርያ ያሳዩዋት ዘንድ አዘዘ አይታም ተጽናናች ከሥቃይ ከሕማሙም ፈወሰው።
❤ ቀሲስ አባ መጹንና ሁለት ዲያቆናትም ተጋድሎውን ሰሙ ያን ጊዜም ተነሥተው ወደ አትሪብ አገር ገዥ ቀርበው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ የጸና ግርፈትም ይገርፋቸው ዘንድ አዘዘ እንዲሁም አደረጉባቸው። ሕዝቡም ሁሉ በዙርያቸው ሁነው ይመለከቷቸው ነበር ስለ ቄሱና ከእርሱ ጋር ስላሉትም አዘኑ ቄሱ ግን ፊቱን ወጀርሳቸው መልሶ ገሠጻቸው አስተማራቸውም "በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ፡፡ በቀናች ሃይማኖት እንዲህ ጽኑ" አላቸው ከዚህም በኋላ በውኋ ላይ ጸልዮ በላያቸው ረጨ በዚያንም ጊዜ በላያቸው ወርዶአልና የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ ተቀበለው በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመኑ ራሶቻቸውንም በሰይፍ ቆረጧቸው የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ። ከዚያም በኋላ ቄሱን ከውሽባ ቤት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኰንኑ አዘዘ እግዚአብሔርም ከእሳት አዳነው። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ተገለጠለትና እርሱ ስለ ክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም ሦስት ጊዜ ምስክር እንደሚሆን አሰረዳው ከእሳት ማንደጃው ውስጥም አወጣው። መኰንኑም ወደ እስክድርያ አገር ላከው ተጋድሎውንና ምስክርነቱን በዚያ ፈጸመ የምስክርኘቱን አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበሉ።
❤ ከዚያም በኋላ መኰንኑ ቆጵርያኖስ የከበረ ሰርግዮስን ያቀርቡት ዘንድ አዘዘ ታላቅ ሥቃይንም አሠቃየው የነሐስ መንኰራኵሮችንም አምጥተው ከውስጣቸው አስገብተው አበራዩት ሕዋሳቱም አራት ክፍል ሁኖ ሥጋው ሁሉ ተቆራረጠ ጌታችንም አድኖ ያለ ጉዳት በጤና አስነሣው። ዳግመኛም እንዲሰግድለት ጣዖትን አመጡ ቅዱሱ ግን ሲረግጠው ወድቆ ተቀጥቅጦ ደቀቀ መኰንን ቆጵርያኖስም አይቶ በክብር ባለቤት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመነ "አምላክ ቢሆን ራሱን ማዳን በቻለ ነበር" አለ።
❤ ከዚህም በኋላ የጭፍራ አለቃ ስሙ አውህዮስ የሚባል የከበረ ሰርግዮስን ፈልጎ ያዘው ቆዳውንም ገፈው በተቀላቀለ ኮምጣጤና ጨው ቊስሉን ያሹት ዘንድ አዘዘ ጌታችን ግን በሥቃዮች ላይ ያጸናውና ያበረታው፡ ነበር። እናቱና እኅቱም ሰምተው ወደርሱ መጡ በአዩትም ጊዜ በላዩ አለቀሱ ከኀዘንም ብዛት እኅቱ ነፍሷን አሳለፈች የከበረ ሰርግዮስም ስለ እኅቱ ወደ ጌታችን ጸለየ ከሞትም ድና በሕይወት ተነሣች። ያን ጊዜ የሰማዕታትን ገድል የሚጽፍ የአቅፋስ፡አገር ሰው የከበረ ዮልዮስ መጣ ገድሉንም ሁሉ ከእርሱ ተረዳ ለሥጋውም እንደሚያስብ ቃል ገባለት።
❤ ከዚህም በኋላ ደግሞ የከበረ ሰርግዮስን በመንኰራኵር ውስጥ ያሠቃዮት ዘንድ በጆሮዎቹ የእሳት መብራቶችን እንዲጨምሩ የእጆቹንና የእግሮቹን ጥፍሮች እንዲነቅሉ በአንገቱም ከባድ ደንጊያ አንጠልጥለው ከብረት ዐልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን እንዲያነዱ አውህዮስ አዘዘ እንዳዘዘውም አደረጉበት ጌታችን ኢየሱስ ያጸናውና ያለ ጥፋት በጤና ያስነሣው ነበር። የሠራዊት አለቃ አውህዮስም ማሠቃየቱን በደከመ ጊዜ ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ፡አዘዘ የከበረ ሰርግዮስ ሰምቶ እጅግ ደስ አለው ወደ አባቱና ወደ እናቱ ወደ ወንድሞቹም ላከ ዘመዶቹ ሁሉም የእርሱ የሆኑ ሰዎችም መጡ በአፋም ልጓም ለጒመው ቸብቸቦውን ወደሚቆርጡበት ሲስቡት አገኙትና መኰንኑን የረከሱ ጣዖታቱንም ረገሙ መኰንኑም ከከበረ ሰርግዮስ ጋር ሁሉንም ቸብቸቧቸውን እንዲቆርጡ አዘዘ በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፫ (13) ቀን።
❤ እንኳን #መልካም_ስም_አጠራርና ጣፋጭ ዜና ላለው ለሶርያ መስፍን ልጁ ለሆነ በሰማዕትነት ካረፈ በኋላ #ቅዱስ_ሚካኤልና_ቅዱስ_ገብርኤል ከሞት አስነሥተውት፤ #ቅዱስ_ዑራኤልም ነጥቆ ወደ ሰማይ አሳርጎት በዚያው በሰማይ 14 ዓመት ለኖረ፤ ተመልሶ ወደ ምድር መጥቶ 40 ዓመት ለኖረ በተአምራቱና በትምህርቱ 85ሺህ አረማውያንን አሳምኖ ላጠመቀ #ለተመሰገነ_ለሁለተኛው_ለቅዱስ_አውሳብዮስ ለምስክርነቱና ለዕረፍቱ በዓል፣ ለከበረ #ለቅዱስ_ሰርግዮስ ከአባቱና እናቱ ከወድሞቹም ከሌሎችም ብዙ ሰዎች ጋር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓልና ለኅርማኖስ ልጅ ለታላቁ ሰማዕት #ለቅዱስ_ፊቅጦር ለልደቱ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረ አባት ከእስክድርያ አገር ሠላሳ ሁለተኛ ሊቀ ጳጳስ #ከአባ_ጢሞቴዎስ ዕረፍት፣ #ከቅዱስ_ፋሲለደስ ልጅ #ከቅዱስ_ቴዎድሮስ ከምስክርነቱ መታሰቢያ፣ #ከአባ_ክፍላና_ከአባ_ኅብስት ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_ፊቅጦር፦ ለዚህ ቅዱስ የአባቱ ስም ኅርማኖስ ነው እርሱም ለዲዮቅልጥያኖስ የአማካሪዎቹና የሠራዊቱ አለቃ ነው ስለ አምልኮ ጣዖት ሥራ ምክሩና ንግግሩ ሁሉ ከእርሱ ጋራ ነበር የእናቱም ስም ማርታ ይባላል በክርስትናዋ የጸናች ብፅዕት ናት።
❤ ቅዱስ ፊቅጦርም በአደገ ጊዜ አባቱ ወደ ንጉሥ አቀረበው ንጉሡም በመንግሥቱ ውስጥ ሦስተኛ ማዕርግ አድርጎ ሾመው በዚያን ጊዜ ዕድሜው ሃያ ዓመት ነበረ። እርሱም የዚህን ዓለም ክብር ናቀ ሥጋ አይባላም ወይን አይጠጣም ዘወትርም ይጾማል ጸሎትንም ባለማቋረጥ በቀንና በሌሊት ይጸልያል። በክብር ባለቤት ክርስቶስ ስም የታሠሩትን ይጐበኛቸዋል ለድኆችና ለምስኪኖችም ይመጸውታል።
❤ የቅዱስ ቆዝሞስና ድምያኖስ እናት ቅድስት ቴዎዳዳን በገደሉዋት ጊዜ ንጉሡም ስለ መፍራት ሊቀብራት ማንም አልደፈረም። ይህ ቅዱስ ፊቅጦርም መጥቶ ሥጋዋን ወሰደ ከንጉሥ ስለሚመጣው ቅጣት ሳይፈራ ቀበራት። ጣዖት ስለ ማምለኩ አባቱን ዘወትር የሚገሥጸውና ብዙ ጊዜም የሚመክረው ሆነ አባቱም ወደ ንጉሥ ከሰሰው እንጂ አልሰማውም። ተከሶም ወደ ንጉሥ በአቀረቡት ጊዜ "አማልክት ያልሆኑ ርኲሳን ጣዖታትን ለሚያመልክ ሰነፍ ዝንጉ ልብ የለሽ ለሆነ ንጉሥ አላገለግልም። ከዛሬ ጀምሮ ለሕያው ንጉሥ ክርስቶስ እገዛለሁ የሰጠኸኝንም ገንዘብህን ንሣ" ብሎ በፊቱ ትጥቁን ፈትቶ ጣለለት።
❤ አባቱ ኅርማኖስም ወደ እስክንድርያ እንዲልከውና በኄርሜኔዎስ መኰንን ዘንድ በዚያ ፊቅጦር እንዲቀጣ ንጉሡን መከረው። በዚያን ጊዜም ከአደባባይ አወጡት እናቱም በብዙ ልቅሶ ልትሸኘው መጣች። እርሱም ሲመግባቸው ስለ ነበረ የታሠሩ ምዕመናን ስለ ድኆችና ምስኪኖች ስለ ሙት ልጆችና ስለ ባልቴቶች የሚሹትን በመስጠት እንድትጐበኛቸው አዘዛት ከዚያም አፉን ለጉመው ወሰዱት።
❤ በእስክንድርያ አገር ወደ መኰንኑ ኄርሜኔዎስ ዘንድ በደረሰ ጊዜ ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት የእግዚአብሔርም መልአክ ወደ ሰማያት አውጥቶ ስለ ክብራቸው ለመናገር የሚያስጨንቁ የብርሃን ማደሪያዎችን አሳይቶ ወደ መኖሪያው መለሰው። መኰንኑም በእሳት በአፈሉት በዝፍት፣ በዲን ደግሞ አሠቃየው ከዚያም በብረት አልጋ ላይ አስተኝተው ከበታቹ እሳትን አነደዱ። ደግመው ከውሽባ ማንደጃ ውስጥ ጨመሩት በየአይነቱ በሆነ ሥቃይም አሠቃዩት የክብር ባለቤት ጌታችንም ያጸናውና ከሥቃዩ ያስታግሠው መልአኩንም ልኮ ከቊስሉ ይፈውሰው ነበር።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ እንዴናው ከተማ ላከው በዚያም ታላቅ ሥቃይን አሠቃዩት ምላሱን ቆረጡ። በእሳት ያጋሉዋቸውን ችንካሮች በጐኖቹ ውስጥ ጨመሩ እግዚአብሔር ግን አጽንቶ አስታግሦ ያለ ጉዳት በደኅና ያነሣዋል። ከዚህም በኋላ በዚያ በረኃብ እንዲሞት ከዱር ባለ ግምብ ውስጥ አሠሩት። እርሱ ግን መጥረብ የሚያውቅ ስለሆነ ላይዳዎችን በመጥረብና በመሸጥ በየጥቂቱ እየተመገበ የቀረውን ለድኆች እየሰጠ ኖረ። አንድ መኰንንም መጥቶ በዚያ ግምብ አቅራቢያ አደረ ስለ ቅዱስ ፊቅጦርም እርሱ የንጉሥ የሠራዊት አለቃ የሆነ የኅርማኖስ ልጅ እንደሆነ ነገሩት። መኰንኑም ወደርሱ አቅርቦ ብዙ ሸነገለው ባልሰማውም ጊዜ ያሠቃዩት ዘንድ አዘዘ ጅማቶቹን መዘዙ አፋን መቱት ቊልቊል ሰቀሉት በእጆቹ ላይ ከባድ ደንጊያ አንጠልጠሉ። ከዚያም ከሚነድ እሳት ውስጥ ጨመሩት ሙጫ፣ አደሮ፣ ማርና ዘይትን አፍልተው በላዩ ደፉበት በማበራያም አበራዩት አፉንም በአሞትና በእሬት አመረሩት ዐይኖቹንም አወለቁት ደግመውም ዘቅዝቀው ሰቀሉት። የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾለት አጸናው አረጋጋው። ሥሮቹንም ሕዋሳቶቹን በቦታቸው መለሰለትና አዳነው።
❤ አንዲት ዓሥራ አምስት ዓመት የሆናት ብላቴና ነበረች ቅዱስ ፊቅጦርን ሲአሠቃዩት በቤቷ መስኮት ታየው ነበር። መላእክትም በእጆቻቸው አክሊሎችን ይዘው እነርሱም በቅዱስ ፊቅጦር ራስ ላይ ሲያኖሩአቸው አይታ እንዴት እንዳየች ለአሕዛብ ነገረቻቸው እጅግም አደነቁ ከእርሳቸውም ብዙዎች በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምነው በሰማዕትነት ዐረፉ። ያቺም ብላቴና በጌታችን አመነች መኰንኑም ራሷን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ። የሕይወት አክሊልንም ተቀበለች ሁለተኛም የአመኑትን ሁሉ ራሳቸውን እንዲቆርጡአቸው አዘዘ የሕይወትንም አክሊል ተቀበሉ።
❤ ከዚህም በኋላ የከበረች የቅዱስ ፊቅጦርን ራስ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘ ተጋድሎውንም ሚያዝያ 27 ፈጽሞ የሕይወትና የድል አክሊል ተቀበለ። ምዕመናን ሰዎችም ሥጋውን ወስደው በከበሩ ልብሶች በድርብ በፍታ ገነዙት። እናቱ ማርታም ከአንጾኪያ እስክትመጣ በንጹሕ ቦታ አኖሩት በመጣችም ጊዜ ከዚያ ወሰደችው። ውብ ቤተ ክርስቲያንም ሠርታ ሥጋውን በውስጥዋ አኖረች ከእርሱም ታላላቅ ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የቅዱስ ፊቅጦር በረከቱም ከእኛ ጋራ ለዘላለም ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የሚያዝያ 27 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #ሰማዕቱ_ቅዱስ_አውሳብዮስ_ዘሀገረ_ሶርያ፦ ይኽም ቅዱስ የሶርያው መስፍን ልጅ ነው፡፡ ለርሱም መንፈስ ቅዱስን የተመላች ስሟ አውሎፊያ የምትባ እኅት አለችው ይህንንም በተግሣጽና በጥበብ በማስተማር ካሳደጉት በኋላ የሮሜውን ንጉሥ ልጅ በታላቅ ክብር አጋቡት፡፡ በሠርጉም ዕለት ወደ ቅድስት ወደሆነችው ወደ እኅቱ ዘንድ ገብቶ "እስቲ ምከሪኝ ልቤ ይህን ጋብቻ አይሻውም ዓለምን ንቆ መተውን እንጂ" አላት፡፡እኅቱም "የዚህ የኃላፊው ዓለም ጣዕም ምን ይጠቅምሃል?እንደ ሊቀጳጳሳት ድሜጥሮስ በድንግልና መኖር ይሻልሃል" አለችው፡፡ ምሽትም በሆነ ወደ ሙሽራይቱ ጫጉላ ቤት ገብቶ የእነርሱ ውበትና ደምግባት እንደሚጠፋ ከዚህም ይበልጥ የሚጠቅማቸውን የጽድቅ ሥራ በመሥራት ድንግልናቸውን መጠበቅ እንዳለባቸው ሙሽራይቱን አዋያት፡፡ ሙሽራይቱም በሀሳቡ ተስማምታ ድንግልናቸውን በመጠበቅ በጾም በጸሎት እየዋሉ ሌሊትም ከባሕር ውስጥ፡ገብተው፡ቆመው ሲጸልዩ ያድሩ ጀመር፡፡ አትራ ወደምትባል ቤተ ክርስቲያን ሄደው አራት እልፍ ይሰግዳሉ፡፡
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፪ (12) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮያዊው_ጻድቅ አጽፋቸውን አንጥፈው ዓባይ ወንዝ ለተሻገሩት፣ የንጉሡ ልጅ ሞቶ ሊቀበር ሲሂድ ጥላቸው ሲያርፍበት ከሞት ላስነሱት ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ ለዕረፍታቸው በዓል፣ ለኢትዮጵያኑ ሰማዕታት (#በ1929ዓ.ም #የካቲት_12_ቀን_ከ30,000 በላይ ኢትዮጵያውያን አባቶች፣ እናቶች፣ ወጣቶችና ሕፃናት በሮማዊው የፋሽስት ጦር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት) በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አቡነ_ሠርጸ_ጴጥሮስ፦ የትውልድ አገራቸው ሸዋ ደብረ ጽላልሽ ሲሆን በሕፃንነታቸው ወደ ወሎ ሄደው ሐይቅ እስጢፋኖስ ገብተው ብዙ ተጋድለዋል፡፡ከተጋድሎአቸውም በኋላ በአቡነ ኢየሱስ ሞዐ እጅ መነኰሱ፡፡ በገዳሙ ብዙ ካገለገሉ በኋላ በመልአክ ትእዛዝ ወደ ጎጃም ሲሄዱ ዓባይን የተሻገሩት አጽፋቸውን አንጥፈው እርሱን እንደ ጀልባ ተጠቅመው ነው፡፡ ጻድቁ ታላቋን ተድባበ ማርያምን ለ41ዓመት አጥነዋል፡፡
❤ የንጉሡ ልጅ ሞቶ ሊቀብሩት ሲወስዱት የአቡነ ሠርጸ፡ጴጥሮስ ጥላቸው ቢያርፍበት ከሞት አፈፍ ብሎ ተነሥቶ ድኖ "አምላከ አቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ" ብሎ ፈጣሪውን አመስግኗል፡፡ ጻድቁ ሲያርፉም መቋሚያቸው አፍ አውጥታ ተናግራለች፤ ርዕደተ መቃብራቸው ሲፈጸምም እንባ አፍስሳ አልቅሳላቸዋልች፡፡ ይህቺ ተአምረኛ መቋሚያቸው ዛሬም ጎጃም ውስጥ መካነ መቃብራቸው ባለበት በደብረ ወርቅ ገዳም ትገኛለች፡፡ ጻድቁ ደብረ ወርቅ ገዳምን እንደ መሶብ አንሥተው አስባርከዋታል፡፡ አቡነ ሠርፀ ጴጥሮስ የካቲት12 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸውም በታላቋ ደብረ ወርቅ ይገኛል፡፡ ከሰማይ የወረደላቸው የወርቅ መስቀላቸውም በዚያው ይገኛል፡፡ጸበላቸው እጅግ ፈዋሽና ኃይለኛ ከመሆኑም በላይ በሰውነት ውስጥ የሚገኝ በሽታንና አጋንንትን የሚያስወጣበት መንገድ ለየት ያለው፡፡
ከአቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #የካቲት ፲፪ (12) ቀን።
❤ እንኳን #ለመላእክት_አለቃ ለከበረ #ለቅዱስ_ሚካኤል ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ተልኮ ኃይልን ሰጥቶት ጠላቶቹን ድል እንዲያደርግ ለረዳበት ወራዊ መታሰቢያ በዓል፣ ተጋዳይ ፍጹም የዋሕና ትሑት ለሆነው ለከበረ አባት #ለአባ_ገላስዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከዶርቃስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #የከበረ_ቅዱስ_ሚካኤልን በዚች ዕለት እግዚአብሔር ወደ ረዓይታዊ ወደ ሶምሶን ላከው የፍልስዔም ሰዎች ሊገድሉት በጠላትነት በተነሡበት ጊዜ ድል እስከ አደረጋቸውና እስከ ገደላቸው ድረስ ረዳው ኃይልንም ሰጥቶ በአህያ መንጋጋ ከእርሳቸው አንድ ሺህ ሰዎችን ገደለ። ተጠምቶም ለሞት በተቃረበ ጊዜ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ተገለጠለትና አጸናው እግዚአብሔር ከአህያ መንጋጋ አጥንት ውኃን አፈለቀለትና ጠጥቶ ዳነ።
❤ ዳግመኛም ከሚስቱ ጋር ተስማምተው ዐይኖቹን አሳውሩ የራሱንም ጠጒር ላጩ አሠሩትም ከዚያም በኋላ ለጣዖቶቻቸው በዓልን በአዘጋጁ ጊዜ ሶምሶንን ወደ ጣዖቶቻቸው ቤት ወሰዱት በዚያም ሦስት ሽህ ያህል ሰዎች ተሰብስበው ነበር የከበረ ቅዱስ ሚካኤልም ተገለጠለትና ኃይልን መላው የዚያንም ቤት ምሰሶዎች ነቀላቸው ቤቱም በላያቸው ወድቆ ከእርሱ ጋር ሁሉንም ገደላቸው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሚካኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ገላስዮስ፦ የዚህ ቅዱስ ወላጆቹ እግዚአብሔርን የሚፈሩ ምዕመናን ናቸው በጥበብንና የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተማሩትና ዲቁና ተሾመ። ከታናሽነቱም ጀምሮ ይህን ዓለም ንቆ ተወ የክብር ባለቤት የሆነ የክርስቶስንም ቀንበር በመሸከም በምንኵስና ሁኖ በትጋት እየጾመ እየጸለየና እየሰገደ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ እግዚአብሔር መርጦት በአስቄጥስ ገዳም ባሉ መነኰሳት ላይ ቅስና ተሾመ። ተጋድሎውንና አገልግሎቱን እየፈጸመ ሳለ ለአባ ጳኵሚስ እንደ ተገለጠ የእግዚአብሔር መልአክ ተገለጠለትና መነኰሳትን ሰብስቦ ፈሪሀ እግዚአብሔርን የምንኵስናንም ሕግ ያስተምራቸው ዘንድ አዘዘው በዚያንም ጊዜ ብዙዎች መነኰሳትን ሰበሰበ መንፈሳዊ የሆ የአድነት ማኅበርራዊ ኑሮንም ሠራላቸው እርሱ በመካከላቸው እንደ መምህር አልሆነም ከእርሳቸው እንደሚያንስ አገልጋይ እንጂ።
❤ ይህ አባት የዚህ ዓለም ጥሪት ሁሉ ንቆ የተወ ሆነ እጅግም የዋህና ቸር ሆነ ከብሉይና ከሐዲስ መጻሕፍቶችም የተሰበሰበ አንድ ታላቅ መጽሐፍን አጻፈ ለማጻፊያውም ዋጋ ዐሥራ ስምንት የወርቅ ዲናር አወጣ ከርሱ ሊጠቀሙ በሚፈልጉ ጊዜ መነኰሳቱ እንዲያነቡት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአትሮንስ ላይ አኖረው። አንድ መጻተኛ ሰውም አረጋዊ አባ ገላስዮስን ሊጎበኝ በገባ ጊዜ ያንን መጽሐፍ አየውና አማረው በጭልታም ከዚያ ሰርቆ ወጣ ወደ ከተማ ውስጥም በገባ ጊዜ ሊሸጠው ወደደ አንድ ሰውም ዋጋው "ምን ያህል ነው" አለው እርሱም "ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር ስጠኝ" አለው። ያ የሚገዛውም ሰው "ያልከውን እሰጥሃለሁ ነገር ግን ለወዳጄ እስካሳየው ታገሰኝ" አለው ያሳየውም ዘንድ ወደ አባ ገላስዮስ ወሰደውና "ተመልከትልኝ መልካም ከሆነ እገዛዋለሁ" አለው አባ ላስዮስም "ያመጣውን ሰው ከአንተ ምን ያህል ፈለገ" አለው "ዐሥራ ሰባት የወርቅ ዲናር" አለው ቅዱስ ገላስዮስም "መጽሐፉ መልካም ነው ዋጋውም ቀላል ነው ግዛው" ብሎ መለሰለት። ወደ ሌባውም በተመለሰ ጊዜ አባ ገላስዮስ የነገረውን ሠውሮ "ለአባ ገላስዮስ አሳየሁት እርሱም ዋጋው በዝቷል አለኝ" አለው፡ሌባውም "ያ ሽማግሌ ሌላ የተናገረህ ነገር የለምን" አለው "አዎን የለም" አለው። ሌባውም "እንግዲህ እኔ አልሸጠውም" ብሎ ወደ አባ ገላስዮስ ሒዶ ከእግሩ በታች ወድቆ ለመነው "ሰይጣን አስቶኛልና ይቅር በለኝ መጽሐፍህንም ውሰድ" አለው የከበረ ገላስዮስም "እኔ መጽሐፉን መውሰድ አልሻም" አለው። ሌባውም በፊቱ እያለቀሰና እየሰገደ ብዙ ለመነው በብዙ ድካምም መጽሐፉን ተቀበለው ማንም ያወቀ የለም። እግዚአብሔር ትንቢት የመናገርን ሀብት ሰጥቶት ድንቆች ተአምራቶችን አደረገ።
❤ በአንዲትም ዕለት ለገዳሙ መነኰሳት ዓሣ አመጡ ባለ ወጡ ዓሣን አብስሎ በቤት ውስጥ አኑሮ አንዱን ብላቴና ጠባቂ አድርጎ ወደ ሥራው ሔደ ብላቴናውም ከዚያ ዓሣ በላ። ባለ ወጡ በመጣ ጊዜ ተበልቶ አገኘውና በብላቴናው ላይ ተቆጥቶ "አረጋዊ አባቶች፡ ሳይባርኩት እንዴት ደፍረህ በላህ" አለው የቊጣ መንፈስም በልቡ አደረና ብላቴናውን ረገጠው ወዲያውኑ ሞተ እንደሞተም አይቶ ደነገጠ ታላቅ ፍርሀትንም ፈራ ሒዶ ለአባ ገላስዮስ የሆነው ሁሉ ነገረው እርሱም "ወስደህ ከቤተ መቅደሱ ፊት አስተኛው" አለው ሰውየውም እንዳዘዘው አደረገ ወደ ማታ ጊዜም አረጋውያን መነኰሳት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰብስበው የማታውን ጸሎት አድርሰው ወጡ አረጋዊ አባ ገላስዮስም በወጣ ጊዜ የሞተው ብላቴና ተነሥቶ በኋላው ተከተለው ከመነኰሳትም ማንም አላወቀም እርሱም የገደለውን ባለ ወጥ ለማንም እንዳይናገር አዘዘው።
❤ የተመሰገነ አባ ገላስዮስም ያማረ ትሩፋቱንና ተጋድሎውን ፈጽሞ አድርሶ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ይህንንም በጎ መታሰቢያን ትቶ ከዚህ ከኃላፊው ዓለም የሚለይበት ሲደርስ የካቲት12 በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ገላስዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦የየካቲት12 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤#የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ። ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ። ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር"። መዝ 33፥7-8። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 25፥31-ፍ.ም።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ወበኀቤየሰ ፈድፋደ ክቡራን አዕርክቲከ እግዝኦ። ወፈድፋደ ፀንዑ እምቀደምቶሙ። እምኌቆሙ እምኆፃ ይበዝኁ"። መዝ 138፥17-18። የሚበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 5፥6-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥9-19 እና የሐዋ ሥራ 28፥30-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 20፥24-29። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ሚካኤል በዓል፣ የአቡነ ሠርጸ ጴጥሮስ የዕረፍት በዓልና የጾም ወራት ለሁላችንም ይሁንልን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ ዚአየ ውእቱ ኵሉ አራዊተ ዘገዳም። እንስሳ ገዳምኒ ወአልሕምት። ወአአምር ኵሎ አዕዋፈ ሰማይ"። መዝ 49፥10-11። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 4፥14-19፣ ያዕ 3፥5-11 እና የሐዋ ሥራ 14፥19-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ማር 1፥12-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ባስልዮስ ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የጾም ወራት ለሁላችን ይሁንልን።
